uk
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Відкрити в Telegram

EEP Communication

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 15 695 підписників, посідаючи 8 016 місце в категорії Технології та додатки та 2 154 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 15 695 підписників.

За останніми даними від 30 серпня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 145, а за останні 24 години на 2, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 31.28%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 16.96% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 4 909 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 2 661 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 10.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
EEP Communication

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 31 серпня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Технології та додатки.

15 695
Підписники
+224 години
+187 днів
+14530 день
Архів дописів
የኃይል መሰረተ ልማቱን መጠበቅ የብሔራዌ ደህንነት አጀንዳ ነው ……..///……... የኤሌክትሪክ ኃይል ግሪድ የሳይበር ጥቃት ተጋላጭ እንዳይሆን የተለያዩ የደህንነት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን በኢት
+1
የኃይል መሰረተ ልማቱን መጠበቅ የብሔራዌ ደህንነት አጀንዳ ነው ……..///……... የኤሌክትሪክ ኃይል ግሪድ የሳይበር ጥቃት ተጋላጭ እንዳይሆን የተለያዩ የደህንነት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሳይበር ደህንነት መምሪያ ዳይሬክተር ገለፁ፡፡ ዳይሬክተሩ አቶ ጌትነት አድማሱ እንደተናገሩት የኤሌክትሪክ ኃይል ለሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት የሚኖረውን አስተዋጽኦ ከግምት ውስጥ በማስገባት የኦፕሬሽናል ቴክኖሎጂውን... ሙሉ ለማንበብ 👉 https://www.eep.com.et/?amh-news=የኃይል-መሰረተ-ልማቱን-መጠበቅ-የብሔራዌ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 26 ቀን 2018 ዓ.ም

#vacancy የፈተና ውጤት ማስታወቂያ ......///........ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሾፌር-1ኛ የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ጥቅምት 03 ቀን 2018 ዓ.ም የውጭ ማስታወቂ
+2
#vacancy የፈተና ውጤት ማስታወቂያ ......///........ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሾፌር-1ኛ የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ጥቅምት 03 ቀን 2018 ዓ.ም የውጭ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወቃል፡፡ በዚሁ መሰረት ህዳር 17 ቀን 2018 ዓ.ም የጽሁፍ ፈተና ተፈትናችሁ በአሽከርካሪ እና ተሽከርካሪ ፍቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን ደንብና መመሪያ መሰረት 74 እና ከዚያ በላይ ውጤት ያመጣችሁ ለተግባር ፈተና ያለፋችሁ ሲሆን ፤ ከተራ ቁጥር 1 እስከ 16 ስማችሁ የተገለጸው አመልካቾች ታህሳስ 02 ቀን 2018 ዓ.ም እና 17 እስከ 32 ስማችሁ የተገለጸው ታህሳስ 03 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ በሚገኘው ዋናው መ/ቤት ተሽከርካሪ ጥገና አስተዳደር ቢሮ የተግባር ፈተና የሚሰጥ በመሆኑ ለፈተና እንድትገኙ እናሳውቃለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 26 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+4

ሙስና ሀገራዊ ዕድገትን የሚገታ ካንሰር ነው ......///....... ሙስና ሀገራዊ ዕድገትን የሚገታ ካንሰር በመሆኑ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞች በጋራ ሊታገሉት እንደሚገባ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ አሳሰቡ፡፡ 22ኛው ዓለም አቀፍ የፀረ- ሙስና ቀን "ትውልድን በሥነ ምግባር፣ ተቋምን በአሰራር" በሚል መሪቃል በተቋሙ ሲከበር እንደተናገሩት የካንሰር በሽታ የሰውነት ህዋሶችን ቀስ በቀስ እያጠፋ ለሞት እንደሚዳርግ ሁሉ ሙስናም ቀስ በቀስ እየተስፋፋ እና ስር እየሰደደ ሀገርን አደጋ ላይ ይጥላል። ተቋሙ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ የሚፈስበት እንደመሆኑ መጠን ተቋሙ ያስቀመጣቸው የአሰራር ስርዓቶች ሳይሸራረፉ እየተተገበሩ መሆኑን በየጊዜው ማረጋገጥ ይገባል ብለዋል፡፡ ተቋሙ በሚያከናውናቸው ግዥዎች፣ በፕሮጀክት አፈፃፀም፣በንብረት ማስወገድ ላይ ጥንቃቄ በተሞላበት መንገድ ማከናወን እንደሚገባም ነው ያሳሰቡት፡፡ ሙስናን የመከላከል ተግባር ለሥነምግባር መከታተያና ፀረ ሙስና መምሪያ ብቻ የሚተው አለመሆኑን የጠቆሙት ኢንጂነር አሸብር ሁሉም የተቋሙ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። ዋና ሥራ አስፈፃሚው አክለውም ከተቋም ባሻገር በሥነ ምግባር የታነፁ ሀገር ወዳድ ዜጎችን ለማፍራት ቀን ከሌት መስራት ይገባል ብለዋል። ከሙስና መከላከያ ስልቶች መካከል የዲጂታል የአሰራር ስርዓት አንዱና ዋነኛው በመሆኑ ይህን አሰራር እውን ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም አረጋግጠዋል። ሙስናንና ብልሹ አሠራርን የሚጠያፉ አርአያ የሆኑ አመራሮች እና ባለሙያዎች ለመፍጠር መስራት ይገባልም ብለዋል። የተቋሙ የኮርፖሬት ገቨርናንስ እና ኮምፐሊያንስ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ድጉማ ነዳ በበኩላቸው ሙስና የሀገርን ህልውና የሚፈታተን አደገኛ ወንጀል ስለሆነ በጋራ እና በተቀናጀ መንገድ መከላከል እንደሚገባ አስታውቀዋል፡፡ ሙስና ከአስተሳሰብ ይጀምራል ያሉት ሥራ አስፈፃሚው ስነ ምግባር የተላበሰና ህጋዊ የአሠራር ስርዓት የሚከተል የስራ መሪ እና ሠራተኛ መፍጠር እንደሚያስፈልግም ተናግረዋል፡፡ ሙስና በባህሪው ውስብስብ ከመሆኑ አንፃር ሳይከሰት ቀድሞ መከላከል ተመራጭ እና አዋጭው ስልት መሆኑንም ነው የገለፁት። በመርሃግብሩ መገባደጃ ላይ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚን ጨምሮ የተቋሙ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች የሀብት ማስመዝገቢያ ሰነድ በመሙላት ለተቋሙ የስነ ምግባር እና የፀረ-ሙስና መከታተያ መምሪያ በማስረከብ የአርአያነት ተግባር አከናውነዋል፡፡ በመጨረሻም ሁሉም የተቋሙ አመራሮች እና ሠራተኞች ሙስናን ለመከላከል በተቋሙ የስነ ምግባር እና የፀረ-ሙስና መከታተያ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ደረጀ አጥናፌ አማካኝነት ቃለ መሃላ ፈፅመዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 25 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+9

ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን በተቋም ደረጃ እየተከበረ ነው ......///...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች በተገኙበት ዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀንን በዋ
+6
ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን በተቋም ደረጃ እየተከበረ ነው ......///...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች በተገኙበት ዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀንን በዋና መስሪያ ቤት የስብሰባ አዳራሽ እያከበረ ይገኛል። መርሃ ግብሩን በይፋ ያስጀመሩት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደገለፁት ሁሉም የሥራ መሪና ሠራተኞች የዕለት ከዕለት ስራዎችን ሲያከናውኑ ሥነ ምግባርን በመላበስ እና ህጋዊ የአሰራር ሥርዓት በተከተለ መንገድ መሆን ይኖርበታል። የዘንድሮው የፀረ- ሙስና ቀን "ትውልድን በሥነ ምግባር፣ ተቋምን በአሰራር" በሚል መሪ ቃል በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ እየተከበረ መሆኑንም ነው ዋና ሥራ አስፈፃሚው የገለፁት። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 25 ቀን 2018 ዓ.ም

የአካል ጉዳተኞች ቀን በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተከበረ ይገኛል ........///................ የ2018 ዓ.ም የአካል ጉዳተኞች ቀን “አካል ጉዳተኝነትን የሚያካትት ማህበረሰብ መገንባት ለተሻለ ማህበራዊ ዕድገት!” Fostering disability inclusive societies for advancing social progress! በሚል መሪ ቃል በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተከበረ ይገኛል፡፡ የተቋማችን የሴቶች እና ማኅበራዊ ጉዳዮች መምሪያ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኢዳኤ ዕለቱን አስመልክቶ ለኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ባስተላለፉት መልዕክት በተቋማችን ውስጥ ለሚገኙ የአካል ጉዳተኛ ሠራተኞች በማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች ውስጥ የዕኩል እድል ተሳታፊና ተጠቃሚ ማድረግ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ ዳይሬክተሯ በመልዕክታቸውም አካታች ማህበረሰብ የመፍጠር አንዱ እና ዋነኛው መገለጫ የአካል ጉዳተኞችን የእንቅስቃሴ ችግሮች መቅረፍ በመሆኑ በተቋማችን ለሚገኙ የአካል ጉዳተኞች ሁለንተናዊ ድጋፍ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ያሉት የስራ ቦታዎች ለአካል ጉዳተኞች ምቹ መሆናቸውን የማረጋገጥ ስራና፤አካል ጉዳተኞች እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ እኩል ተጠቃሚ እንዲሆኑ የክትትልና ድጋፍ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውንም ነው የገለፁት፡፡ ተቋሙ በሚያከናውናቸው ፕሮግራሞች ፣ ፕሮጀክቶችና በሚያወጣቸው የተለያዩ ፖሊሲዎችና የአሰራር መመሪያዎች የአካል ጉዳታኞችን ታሳቢ እንዲያደርግ እየተሰራ ነውም ብለዋል፡፡ አካል ጉዳተኝነት ማለት ከውልደት ጀምሮ ወይም ከውልደት በኋላ በአደጋ ወይም በህመም የሚያጋጥሙ የአካል ወይም የአዕምሮ ጉዳቶች ናቸው፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 23 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+1

በትራንስፎርመር ብልሽት ሳቢያ በከፊል ተቋርጦ የቆየው ኃይል ዳግም ተመልሷል .....///..... በኮምቦልቻ አንድ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፊያ ጣቢያ ካሉት ሁለት ትራንስፎርመሮች መካከል በአንደኛው ላይ ባጋጠመ ችግር ምክንያት በከፊል ተቋርጦ የቆየው ኃይል ዳግም መመለሱን የሰሜን ምስራቅ 1 ሪጅን አስታወቀ።   ‎በሪጅኑ የኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ ዳይሬክተር አቶ በድሩ አህመድ እንደገለፁት 40 ሜጋ ቮልት አምፒር ኃይል የመጫን አቅም ባለው ትራንስፎርመር ላይ ባጋጠመ የእሳት አደጋ ምክንያት ለአንድ ወር ያህል  በአካባቢው በከፊል ኤሌክትሪክ ተቋርጦ ቆይቷል፡፡ በዚህም በትራንስፎርመሩ ታፕ ቼንጀር ላይ በደረሰው ጉዳት ምክንያት በደሴ እና ኮምቦልቻ ከተሞች እና በአካባቢያቸው  በከፊል የኃይል ተቋርጦ መቆየቱን ተናግረዋል፡፡ ጉዳት የደረሰበትን ባለ 132/66/15 ኪሎ ቮልት ትራንስፎርመር ጠግኖ  ዳግም  አገልግሎት ለማስጀመር ከሪጅኑ እና ከማዕከል የተውጣጡ የጥገና ባለሙያዎች ርብርብ ሲያደርጉ መቆየታቸውንም ነው የገለፁት። በአካባቢው በከፊል ተቋርጦ የቆየውን የኤሌክትሪክ ኃይል በዛሬው ዕለት ሙሉ በሙሉ መመለስ ተችሏል ያሉት አቶ በድሩ በጥገና ሥራው ላይ ርብርብ ሲያደርጉ ለነበሩ የጥገና ባለሙያዎች በሙሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 23 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+4

በተቋሙ  ተግባራዊ የሚደረጉ የቴክኖሎጂ አሰራሮችን ደህንነት ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው …….///…….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚገኙ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ (IT) መሰረተ ልማቶች ለሳይበር ጥቃት እንዳይጋለጡ  በትኩረት እየተሰራ መሆኑን በተቋሙ የሳይበር ደህንነት መምሪያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ጌትነት አድማሱ እንዳስታወቁት የኢንተርኔት እና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሲስተም አጠቃቀም ማደጉን ተከትሎ የሳይበር ደህንነት ስጋት ተጋላጭነት በዓለም አቀፍ ብሎም በሀገር ደረጃ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል፡፡ ይህን ተከትሎም በተቋሙ የሚከናወኑ የአሰራር ሥርዓቶች በተቀላጠፈ ሁኔታ እንዲከናወኑ የሚያግዙ  እና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መሰረተ ልማቶች ላይ የሳይበር ጥቃት እንዳያጋጥም  ከቴክኖሎጂ አጠቃቀም ጀምሮ መተግበሪያዎች፣ ኮምፒውተሮች፣ ሰርቨሮች እንዲሁም የኔትዎርክ ዕቃዎችን የሳይበር ደህንነት ለማስጠበቅ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ የዲጂታላይዜሽን አሰራሮች ለሳይበር ጥቃት ተጋላጭ እንዳይሆኑ በሶፍትዌሮች እና ሀርድዌሮች ግዥ ላይ የሳይበር ደህንነት መስፈርቶች እንዲሟሉ ከማድረግ ጀምሮ የተለያዩ የአሰራር ሥርዓቶች መዘርጋታቸውን ተናግረዋል፡፡ ሳፕና ኢአርፒን የመሳሰሉ አሰራር ማዘመኛዎችን ጨምሮ በተቋሙና በውጭ እየለሙ የሚገኙ ሶፍትዌሮች ወደ ሥራ ከመግባታቸው በፊት የሳይበር ደህንነት መመዘኛዎችን ማሟላታቸውንና ለጥቃት ተጋላጭ መሆንና አለመሆናቸውን ፍተሻና ክትትል እንደሚደረግባቸው ዳይሬክተሩ አስረድተዋል፡፡ ወደ ሥራ ከገቡ በኋላም በእያንዳንዱ ሲስተም ላይ የተለያዩ የሳይበር ደህንነት መከታተያ የአስራር ሥርዓቶችን በመተግበር እና ሶፍትዌሮችን በመጠቀም ደህንነታቸውን የማስጠበቅና የመቆጣጠር ሥራ እየተከናወነ ስለመሆኑ አመልክተዋል፡፡ በተጨማሪም በተቋሙ ኔትወርክ ላይ ማንኛውም ሰው ከተቋሙ ዕውቅና ውጭ ኢንተርኔትም ሆነ የተቋሙን ሲስተም መጠቀም እንዳይቻል የሚያደርጉ የደህንነት ማስጠበቂያ አሰራሮች መዘርጋታቸውን አቶ ጌትነት አስረድተዋል፡፡ እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ የሳይበር ደህንነትን ለማስጠበቅ በእያንዳንዱ ሲስተም ላይ ያሉ የጥቃት አጋላጭ ዓይነነቶችን አስቀድሞ በመለየት የመከላከል ሥራ እየተከናወነ ይገኛል፡፡ የመረጃ መንታፊዎች ቴክኖሎጂዎችን ሰብሮ ከመግባት ይልቅ በሰው አማካኝነት በቀላሉ የሳይበር ጥቃት የማድረስ አቅም እንዳላቸው የጠቆሙት አቶ ጌትነት ይህን በመገንዘብም በተቋሙ በሳይበር ደህንነት ምህዳር ላይ ንቃተ ሕሊና ያለው ሠራተኛ መፍጠር ይገባል ብለዋል፡፡ የተቋሙን የሳይበር ደህንነት ለማረጋገጥ ክፍሉ ብቻ ሳይሆን ሁሉም የተቋሙ የሥራ መሪ እና ሠራተኛ ኃላፊነት እንዳለበት ተገንዝቦ በትኩረት መስራት እንደሚጠበቅበት አሳስበዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 22 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+3

ለተቋሙ የሥራ ኃላፊዎችና  ሠራተኞች  የግዥ አፈጻጸም ሥልጠና  እየተሰጠ ነው ----///--- በኢትዮጵያ  ኤሌክትሪክ ኃይል ከሁሉም የሥራ ክፍሎች ለተውጣጡ የሥራ ኃላፊዎች እና  ባለሙያዎች አዲስ በወጣው የመንግስት የልማት ድርጅቶች የግዢ አዋጅና መመሪያ አፈፃፀም ዙሪያ ሥልጠና በመሰጠት ላይ ነው። የተቋሙ የግዥና ሎጀስቲክስ ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ጽዮን ብርሃኑ እንደገለፁት የግዢ አፈፃፀም ሂደትን ማወቅ የግዥ ፈጻሚው ክፍል ብቻ ሳይሆን ግዥ እንዲፈጸምለት ጥያቄ ያቀረበው የሥራ ክፍል ሥራ መሆን ስላለበት ሥልጠናው ከተቋሙ የግዢ ባለሙያዎች በተጨማሪ ሌሎች የሥራ ክፍሎችን ጭምር ማካተቱን ገልፀዋል፡፡ ስለሆነም ስልጠናው የሚቀርቡ የግዢ ጥያቄዎች በጊዜና በጥራት ህግን ተከትለው ተፈጻሚ እንዲሆኑ እንደሚያግዝ ገልፀዋል፡፡ በስልጠናው  ላይ ተሳታፊ የሆኑት በተቋሙ የጤና ክፍል የጤናና ሴፍቲ ሥራ አሰኪያጅ አቶ ሆርሳ ቴሬሳ በበኩላቸው ሥልጠናው በግዢ ሂደት ላይ የሚያጋጥሙ ችግሮችን በመቅረፍ ግዢዎችን በአግባቡ ለመፈፀም የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጇ ገለጻ እየተሰጠ የሚገኘው ሥልጠና በተቋሙ ግዢና ሎጀስቲክስ  መምሪያ እንዲሁም በመንግስት ሀብት አስተዳደር እና በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ በጋራ መዘጋጀቱ ውጤቱን የላቀና ከፍተቶችን የሚሞላ ሥልጠና ያደርገዋል ብለዋል፡፡ በተቋሙ የሚፈጸሙ የግዢ ሂደቶች ወጥነት ያለው እና ሃገራዊ የግዢ ስርዓትን በመከተል ተፈጻሚ እንዲሆኑ የሚያስችል እውቀት ከስልጠናው እያገኙ መሆኑን የገለጹት ደግሞ ከልማትና ስልጠና ማዕከል ተሳታፊ የሆኑት ወ/ሮ የምስራች መኮንን ናቸው፡፡ የሠራተኛ ማኅበር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኃይሉ ወልዴ በበኩላቸው ሥልጠናው በግዢ አፈፃፀም ሂደት ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን አሟልቶ የተሻለና ህግን የተከተለ አሰራር ለመዘርጋት እንደሚያግዝ ተናግረዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 19 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+4

#ዲጂታልመጽሔት እነሆ ነፀብራቅ ዲጂታል መጽሔት ለንባብ በቅታለች፡፡ መፅሔቷ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባለፉት ወራት የተከናወኑ አበይት ጉዳዮችን ትዳስሳለች ከስር የተቀመጡትን ሊንኮች በመጫን መፅሔ
+2
#ዲጂታልመጽሔት እነሆ ነፀብራቅ ዲጂታል መጽሔት ለንባብ በቅታለች፡፡ መፅሔቷ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባለፉት ወራት የተከናወኑ አበይት ጉዳዮችን ትዳስሳለች ከስር የተቀመጡትን ሊንኮች በመጫን መፅሔቱን እና ሌሎች ተቋሙን የተመለከቱ መረጃዎች በቀላሉ ያግኙ! 👉 https://www.eep.com.et/?page_id=17536#flipbook-df_22343/2/ 👉 https://www.eep.com.et/?page_id=17536 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 19 ቀን 2018 ዓ.ም

የተቀናጀ ተቋማዊ ፖሊሲ ቀረጻ እና ማሻሻያ ስራዎች ማስጀመሪያ ዎርክሾፕ መካሄድ ጀመረ ……//…. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በበጀት ዓመቱ ሊያሻሽላቸው እና በአዲስ መልክ ለመቅረጽ በዕቅድ የያዛቸውን ፖሊሲዎች ዝግጅት ለማስጀመር የሚያስችል የቴክኒክ ቡድን አቋቋሞ ወደ ሥራ የሚያስገባውን የ 2 ቀናት ዎርክሾፕ ማካሄድ ጀምሯል፡፡ የዋና ስራ አስፈጻሚ ተወካይና የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሕይወት እሽቱ በወርክሾፑ መክፈቻ ላይ እንደተናገሩት በበጀት ዓመቱ መጀመሪያ ጸድቆ ተግባራዊ በተደረገው የሪፎርም ዕቅድ መሰረት ትኩረት ከተሰጣቸው ጉዳዮች አንዱ የፖሊሲ ቀረጻና ማሻሻያ ስራ ነው፡፡ በመሆኑም ይህ ተግባር የድርጊት መርሀ ግብር ወጥቶለት ተግባራዊ መደረጉ ተቋሙ የአሰራር ስርዓት ለማሻሻል የጀመረውን እርምጃ የሚያሳይ ነው። እንደ ሥራ አስፈፃሚው ገለጻ 12 የሚሆኑ ተቋማዊ ፖሊሲዎች በተያዘው ሩብ  ዓመት ተዘጋጅተው እና ተሻሽለው እንዲተገበሩ ለማስቻል የፖሊሲ ዝግጅት ቡድን ተቋቋሞ ወደ ሥራ ተገብቷል፡፡ ለአንድ ተቋም የአሰራር ወጥነትና ቀጣይነት ያለው መሻሻል እንዲኖር አስቻይ የሚሆኑና የውሳኔ አሰጣጥ መርህን እንዲሁም ተቋማዊ ፍላጎትን የሚያንጸባርቁ ፖሊሲዎች፥ አሰራር ሂደቶችና መመሪያዎች መኖር መሰረታዊ መሆናቸውን የተናገሩት ሥራ አስፈፃሚው  እነዚህ ሳይኖሩ ወይም ያሉትን ሳያሻሽሉ መቅረት ተቋማዊ ሥራን ለማሳለጥ አስቸጋሪ እንደሚያደርገው አስረድተዋል። የሥራ ቡድኑ የተሰጠው ኃላፊነት ወሳኝ መሆኑን ሥራው ከሌሎች መደበኛ ሥራዎች እኩል ተይዞ በከፍተኛ ትኩረት መከናወን የሚገባው መሆኑን ገልጸው ሁሉም የቡድኑ አባላት ለስራው በቂ ጊዜ መድበውና የተቀመጠውን አሰራር ተከትለው እንዲሰሩ አሳስበዋል፡፡ የሰው ሀብት ሥራ አስፈጻሚ አቶ አታላይ አበበ በበኩላቸው  ፖሊሲ በከፍተኛ ደረጃ የሚዘጋጅና የሚተገበር፥ እንዲሁም ወሰኝ የሆኑ ጥቂት ጉዳዮችን ይዞ የተቋሙን ዋና ዋና ፍላጎቶችን የሚያመላክት ሰነድ በመሆኑ አዘጋጆች ከተቋሙ ስትራቴጂ ጋር አገናዝበውና አዋህደው  እንዲሰሩ አሳስበዋል፡፡ የሚዘጋጀው ፖሊሲ ሂደትን መሰረት ያደረገ እንዲሆን ዝግጅት መደረጉን የገለፁት በዋና ስራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት የፕሮሰስ ፓሊሲና የለውጥ ስራ አመራር ዳይሬክተርና አቶ አንዱዓለም ኪዳኔ ፖሊሲዎቹን በ 40 ቀናት ውስጥ አዘጋጅቶ ለማቅረብ ይሰራል ብለዋል፡፡ ሂደቱን በከፍተኛ ጥራት በተቀመጠው ጊዜ ለማከናወን እንዲቻል ይህ የማስጀመሪያ ዎርክሾፕ የፖሊሲ ዝግጅት 12 ቡድኖችን በሁለት በመክፈል ለሁለት ቀናት የሚከናወን መሆኑን ጠቅሰው ሂደቱን የሰፖርት ፕሮሰስና ፖሊሲ ማኔጅመንት ስራ ክፍሎች በበላይነት እንደሚያስተባብሩት ገልጸዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 19 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+7

ተቋሙ የያዘውን ርዕይ ለማሳካት የባለሙያውን አቅም ማሳደግ እንደሚገባ ተገለፀ -----------///------------------- በኢንጂነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዘርፍ በሚከናወኑ የኤሌክትሮ ሜካኒካል እና የሲቪል ግንባታ ሥራዎች ላይ እየተሳተፉ የሚገኙ ሠራተኞችን አቅም ለማሳደግ  ለአንድ ወር ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቀቀ። በሥልጠናው ማጠናቀቂያ ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰው ሀብት ሥራ አስፈፃሚ አቶ አታላይ አበበ  እንደተናገሩት የተቋሙ የራስ ኃይል በሀገር ውስጥና በውጭ ለማከናወን የያዘውን ርዕይ ለማሳካት የባለሙያውን አቅም በማሳደግ የሰርተፊኬት ባለቤት እንዲሆን ማድረግ ይጠይቃል። ተቋሙ በትምህርት ያልተደገፉ ልምድ ያላቸው ባለሙያዎችን የሰርተፊኬት ባለቤት ለማድረግ የስልጠና ስርዓት ቀርፆ  ስልጠናዎችን በራስ አቅም መስጠት መጀመሩን ተናግረው በቀጣይ መሠል ስልጠናዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል። ከመረጃ አያያዝ ጀምሮ የፕሮጀክቶቹን አፈፃፀም ለማሻሻል ሠራተኞች ከስልጠናው ያገኙትን እውቀት ወደ ተግባር መለወጥ እንደሚጠበቅባቸውም አሳስበዋል። በተቋሙ የኢትዮ ፓወር አካዳሚ ዳይሬክተር ወንድወሰን ካሳ (ዶ/ር) በበኩላቸው ስልጠናው የራስ ኃይልን አሁን ካለበት ደረጃ ለማሳደግ ከፋተኛ ሚና ይኖረዋል ብለዋል። አካዳሚው በሠራተኞች ላይ የሚስተዋሉ የክህሎትና የዕውቀት ክፍተቶችን በመለየት በራስ አቅም ስልጠናዎችን ለመስጠት እየሰራ መሆኑን ጠቁመው በቀጣይ ከተቋሙ ተልዕኮ ጋር በተያያዘ ብቃት ያለው ባለሙያ ለማፍራት እስከ ደረጃ 5 ባለሙያዎችን ለማሰልጠን አቅዶ እየሰራ  መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ በኢንጅነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዘርፍ የምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚው ተወካይ አቶ ግርማ ዘለቀ እንደተናገሩት ስልጠናው ሠራተኞች በልምድ ያገኙትን እውቀት ከንድፈ ሃሳብ ጋር በማቀናጀት ሥራቸውን ሳይንሳዊ በሆነ መልኩ እንዲያከናውኑ ለማድረግ፣ ሥራውን ጥንቃቄ በተሞላበት መልኩ ለማከናወን፣ ከሥራ ጋር በተያያዘ የሚያጋጥሙ ክፍተቶችን እና  አለመግባባቶችን ለመቅረፍ ያግዛል። በዘርፉ የሀብት አስተዳደር መምሪያ ዳይሬክተር ወ/ሮ መንበረ ክፍሌ በበኩላቸው ሠራተኞች እየሰሩበት ያለው የሥራ ፀባይ ራሳቸውን በትምህርት እንዳያሳድጉና የሚፈልጉት ደረጃ ላይ እንዳይደርሱ ማድረጉን አንስተዋል፡፡ ችግሩን ለመቅረፍ የኢትዮ ፓወር አካዳሚ ስልጠናውን በማመቻቸቱ አመስግነው ሠልጣኖች ስልጠናው መነሻ እንጅ መዳረሻ አለመሆኑን ተገንዝበው በቀጣይ ራሳቸውን በተለያዩ መንገዶች ማብቃት እንደሚጠበቅባቸውም አስገንዝበዋል፡፡ በራስ አቅም በሚከናወኑ ፕሮጀክቶች ላይ እየሰሩ የሚገኙ ሠራተኞችን አቅም ለማሳደግ የተሠጠው ስልጠና ከዚህ በፊት በሠራተኞች ሲነሱ የነበሩ ጥያቄዎችን ለመመለስ እየተሰራ መሆኑን አንዱ ማሳያ ነው ያሉት ደግሞ የተቋሙ መሠረታዊ የሠራተኞች ማህበር ጸሐፊ አቶ ሀይሉ ወልዴ ናቸው፡፡ የሥልጠናው ተሳታፊዎች በበኩላቸው ከስልጠናው ዘመኑን የዋጀ ሥራ ለማከናወን የሚያስችል ዕውቀትና ክህሎት ማግኘታቸውን ተናግረዋል፡፡ በዕለቱም ለአንደ ወር በቆየው ስልጠና ላይ የተሳተፉ 41 የሲቪል እና 12 የኤሌክትሮ መካኒካል ግንባታ ባለሙያዎች የምስክር ወረቀት ተሰጥቷቸዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 18 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+9

በኢነርጂ ዘርፍ ተፅዕኖ ፈጣሪ የሆኑ እንስት ባለሙያዎች ዕውቅና ተሰጠ …....///…... የኢትዮጵያ ሴቶች ኢነርጂ ማህበር (EWiEN) በኢነርጂ ዘርፍ ላይ በፈጠራና በአስተዳደር እንዲሁም በልዩ ልዩ ደረጃዎች ተፅዕኖ ለፈጠሩ ሴቶች ዕውቅና ሰጠ፡፡ የዕውቅና መርሃግብሩ ሴት ባለሙያዎች በኢነርጂ ዘርፍ ላይ የሚያደርጉትን አስተዋጽዖ ለማስተዋወቅ፣ ለማበረታታት እና ክብር ለመስጠት እንዲሁም ወጣት ሴቶች በዘርፉ እንዲሰማሩ ለማድረግ ያለመ መሆኑ ተገልጿል፡፡ በመርሃግብሩ ላይ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የትራንስሚሽን እና ሰብስቴሽን ፕሮግራም መምሪያ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሃይማኖት ተፈራን ጨምሮ በኢነርጂ ዘርፍ ላይ ተፅዕኖ ፈጣሪ ለሆኑ ተጨማሪ ሁለት ሴቶች ዕውቅና እና ሽልማት ተበርክቷል፡፡ ወ/ሮ ሃይማኖት ተፈራ በዕውቅና ሥነስርዓቱ ላይ በሀገሪቱ በ160 ቦታዎች ላይ የስማርት ሜትር ፕሮጀክትን በማስተግበር ተቋሙ የገቢ አቅሙን እንዲያጠናክር እና የኃይል ብክነትን በመቀነስ ረገድ ለተጫወቱት የአመራርነት ሚና ዕውቅናው ስለተሰጣቸው ማህበሩን አመስግነዋል፡፡ የቮልቴጅ ቁጥጥር ሥርዓትን በመዘርጋት በሰመራ፣ አዲጋላ እና ባህርዳር በተደጋጋሚ ሲያጋጥም የነበረውን የቮልቴጅ መዋዠቅ በማረጋጋት እና የኃይል መቆራረጥን በመቀነስ ረገድ የነበራቸው ሚና ለሽልማት እንዳበቃቸውም ተናግረዋል፡፡ እንደ ወ/ሮ ሃይማኖት ገለፃ በኢነርጂ ዘርፉ ላይ መሰል የዕውቅና እና ሽልማት ፕሮግራሞች መዘጋጀታቸው ለሌሎች ሴት ባለሙያዎች መነሳሳትን የሚፈጥር በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት፡፡ ዕውቅናው በቀጣይ በኃይል ልማት ዘርፉ ላይ በሚያከናወኑ በርካታ ፕሮጀክቶች ላይ በትጋት ኃላፊነታቸውን ለመወጣት ትልቅ የሞራል ስንቅ እንደሆናቸውም ነው ያብራሩት፡፡ በዛሬው ዕለት በተካሄደው መርሃግብር ከቀረቡት ስድስት ዕጩዎች መካከል ወ/ሮ ሰላማዊት ስለሺ በኢንጂነሪንግ ዘርፍ እንዲሁም ወ/ሮ ነፃነት በኃይሉ በኤሌክትሪክ አቅርቦት ዘርፍ የዓመቱ የኢነርጂ ዘርፍ ተፅዕኖ ፈጣሪ ሴቶች በመባል ተመርጠዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 18 ቀን 2018 ዓ.ም