uk
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Відкрити в Telegram

EEP Communication

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 15 525 підписників, посідаючи 8 336 місце в категорії Технології та додатки та 2 179 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 15 525 підписників.

За останніми даними від 07 липня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 5, а за останні 24 години на -2, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 28.59%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 16.03% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 4 440 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 2 489 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 10.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
EEP Communication

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 08 липня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Технології та додатки.

15 525
Підписники
-224 години
-57 днів
+530 день
Архів дописів
ዋና ሥራ አስፈፃሚው የደገሀቡር ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያን ጎበኙ .........//......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ ባለፈው ዓመት አገልግሎት መስጠት የጀ
+3
ዋና ሥራ አስፈፃሚው የደገሀቡር ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያን ጎበኙ .........//......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ ባለፈው ዓመት አገልግሎት መስጠት የጀመረውን የደገሀቡር ባለ 132/33 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ትናንት ማምሻውን በመጎብኘት ከጣቢያው የኦፕሬሽን ሠራተኞች ጋር ተወያይተዋል። የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል በተሰሩ ስራዎችና ለጣቢያው መሟላት ባለባቸው የስራ ግብዐቶች ዙሪያም ተነጋግረዋል። የጣቢያው ኃላፊ አቶ ከድር ዑስማን ስለጣቢያው የኃይል አቅርቦት፣ ከአካባቢው የመስተዳድር አካላት ጋር ስላላቸው ግንኙነትና የጣቢያው ሰራተኞች በራስ ተነሳሽነት የሰሯቸው ስራዎችን በተመለከተ ለዋና ስራ አስፈፃሚው ገለፃ አድርገውላቸዋል። ዋና ስ ራ አስፈፃሚው በበኩላቸው ቀሪ ስራዎችን በመለየት ከሚመለከታቸው ክፍሎች ጋር በመሆን የማሟላት ስራ እንደሚሰራ ጠቁመዋል። ጣቢያውን ኃይል ከማቅረብ በተጓዳኝ ለስራና ለዕይታ ምቹ በማድረግ በኩልም ትኩረት ሰጥተው እንዲሰሩ አሳስበዋል። በስፍራው የተገኙት የክልለሉ መንግስት የስራ ኃላፊዎችም የደገሀቡር እና አካባቢው ኃይል ማግኘት የአካባቢውን ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ እንዳነቃቃው በመግለፅ ተቋሙ ለሚያከናውነው ስራ አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል። የደገሀቡር ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ካሉት 5 ወጪ መስመሮች መካከል በአሁኑ ሰዓት አገልግሎት እየሰጡ ያሉት ሁለቱ ብቻ ሲሆኑ አሁን ካለው ከእጥፍ የሚበልጥ የኃይል ፍላጎት ቢመጣ እንኳ የማስተናገድ አቅም አለው። ሚያዝያ 04 ቀን 20122 ዓ/ም

በጣቢያው የበጎ ፍቃድ ተግባራት በመከናወን ላይ ናቸው ……..///……. የጊቤ 2 የኃይል ማመንጫ ጣቢያ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል በጣቢያው ውስጥ ባቋቋመው ግብረ ሃይል አማካኝነት የተለያዩ
+1
በጣቢያው የበጎ ፍቃድ ተግባራት በመከናወን ላይ ናቸው ……..///……. የጊቤ 2 የኃይል ማመንጫ ጣቢያ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል በጣቢያው ውስጥ ባቋቋመው ግብረ ሃይል አማካኝነት የተለያዩ ሥራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ የጣቢያው ኃላፊ አቶ ሃብታሙ ገረመው እንደተናገሩት የቆሴ እና ፉፋ ኬላዎችን ጨምሮ በኃይል ማመንጫ ቤት እንዲሁም በመኖሪያ ቤቶች አካባቢ 10 የእጅ መታጠቢያ ቦታዎችን በማዘጋጀት ሠራተኛው የእጅ ንፅህናውን እንዲጠብቅ እየተደረገ ነው። ሃገሪቱ አሁን ካለችበት አስቸጋሪ ሁኔታ እንድትወጣ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ወሳኝነት እንዳለው የተናገሩት ኃላፊው በኃይል ማመንጫ እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ለሚሰሩ ሠራተኞች መንግሥት እና ተቋሙ ልዩ ትኩረት እንዲያደርግ ጠይቀዋል። ለጣቢያው ሠራተኞች 210 ሊትር የእጅ ማፅጃ ሳኒታይዘር እና ማስኮች እንዲሁም 500 የሜዲካል ግላቮች ከተቋሙ የጤና እና ሴፍቲ የሥራ ክፍል እንደተሰጣቸው አቶ ሃብታሙ የጠቆሙ ሲሆን ከወረዳው ጋር በመነጋገርም ተጨማሪ 50 ጥንድ ጓንት እና ማስክ ከሆጃ ጤና ጣቢያ እንደተበረከተላቸው ተናግረዋል፡፡ በሃገሪቱ ውስጥ የወረርሽኙ የመስፋፋት ሥጋትን በማየት ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በህብረት ይሰራ የነበረውን የጥበቃ ሥራ ለጊዜው በማቋረጥ የተወሰኑ ሰዎችን ብቻ በመምረጥ የጥበቃውን ሥራ በማከናወን ላይ እንደሚገኙ አስታውቀዋል፡፡ ከመኖሪያ ቤት ወደ ኃይል ማመንጫ ይደረግ የነበረውን የሠራተኞች የሰርቪስ አጠቃቀም በማሻሻልም የንክኪ መጠኑን መቀነስ መቻሉን ነው ኃላፊው የጠቆሙት፡፡ የጣቢያው የጥገና ክፍል ኃላፊ አቶ ገበየሁ በላይ በበኩላቸው እንደገለፁት 210 የሚሆኑ የጣቢያውን ሠራተኞች እንደ ሥራ ባህሪያቸው በመክፈል ለ9 ጊዜ ያህል የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን ማከናወን ተችሏል።

የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የሚያስችሉ ተግባራትን በማከናወን ላይ ይገኛሉ ……………….//…………… የኮሮና ወረርሽኝ በአሁኑ ሰዓት ዓለምን እያስጨነቀ፣ በየሃገራቱ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ እና ማህበራዊ ቀውስን እየፈጠረና የብዙ ንፁሃን ዜጎችን ህይወት እየቀጠፈ የሚገኝ ተላላፊ ቫይረስ ነው፡፡ ይህ ወረርሽኝ በህክምናው ዘርፍ ከፍተኛ ደረጃ ደርሰዋል ለምንላቸውን ኃያላን ሀገራት ራስ ምታት ሆኖ ሲፈታተናቸው እያስተዋልን እንገኛለን፡፡ ለዚህ ደግሞ የቫይረሱ የመተላለፊያ መንገዶች ቀላል መሆን እና የሥርጭት ፍጥነቱ እንደ ዋነኛ ምክንያት ይጠቀሳል፡፡ ኢትዮጵያ እንደሌሎች የዓለም ሃገራት ሁሉ የቫይረሱን የሥርጭት መጠን ለመከላከል በአሁኑ ሰዓት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅን ከማወጅ ጀምሮ ሌሎች በርካታ ወሳኝ እርምጃዎችን እየወሰደች ብትገኝም የቫይረሱ ስርጭት መጠን ግን ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ በመሄድ ላይ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እንደ ተቋም የቫይረሱን ሥርጭት ከመከላከል አንፃር መጠነ ሰፊ ሥራዎች በዋናው መስሪያ ቤት፣ በኃይል ማመንጫ እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች እንዲሁም ፕሮጀክቶች ላይ እያከናወነ ይገኛል፡፡ ከዚህም ጋር ተያይዞ የጊቤ 1፣ 2 እና 3 የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ቫይረሱን ከመከላከል አኳያ ምን እየሰሩ እንደሆነ ዞረን ለመመልከት ሞክረናል፡፡ የጊቤ 3 የኃይል ማመንጫ ጣቢያ 1870 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም ያለውና በኢትዮጵያ ትልቁ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሲሆን ወረርሽኙን ለመቆጣጠር በጣቢያው ውስጥ የኮሮና ቫይረስ መከላከል ግብረ-ኃይል ተቋቁሞ የተለያዩ ሥራዎች በመሰራት ላይ መሆኑን የጣቢያው ኃላፊ አቶ ሃብታሙ ሰሙ ተናግረዋል፡፡ እንደ አቶ ሃብታሙ ገለፃ የጣቢያውን ሠራተኞች ሙሉ በሙሉ ወሸባ ከቅጥር ግቢው እንዳይወጡና ሌሎች ሰዎችም ወደ ጣቢያው እንዳይገቡ ተደርጓል፡፡ የተቋቋመው ግብረ ኃይል ቀደም ሲል ይደረግ የነበረውን የተናጠል የመሠረታዊ ፍጆታ ሸቀጦች ግዥ በማስቀረት ለሠራተኛው የሚበቃ የጅምላ ግዥ በመፈፀም ላይ ቢሆንም ሂደቱ ግን አስቸጋሪ እንደሆነ አቶ ሃብታሙ ተናግረዋል፡፡ ለጣቢያው ሠራተኞች 300 ሊትር የእጅ ማፅጃ ሳኒታይዘር፣ 51 ማስኮች እና በርካታ የእጅ ጓንቶች ከተቋሙ የጤና እና ሴፍቲ የሥራ ክፍል እንደተሰጣቸው አቶ ሃብታሙ በመጥቀስ የተላኩት የመከላከያ ግብዓቶች ግን ካለው የሠራተኛ ቁጥር አንፃር በቂ እንዳልሆኑ ተናግረዋል፡፡ ይሄንን እጥረት ለመቅረፍም ጣብያውን ከገነባው ከቻይናው ዶንግፋንግ ኢንተርናሽናል ኩባንያ 80 ማስኮች ድጋፍ እንደተደረገላቸው አቶ ሃብታሙ ጨምረው አብራርተዋል፡፡ ከጣቢያው ለሥራም ሆነ ለሌላ ተግባራት የሚወጡ ሠራተኞች ወደ ጣቢያው ሲመለሱ ለ14 ቀናት ራሳቸውን አግልለው እንዲቆዩ እየተደረገ እንደሆነም ነው አቶ ሃብታሙ የጠቆሙት፡፡ በጣቢያው ውስጥ የፅዳት እና የአትክልት ሥራዎችን ይሰሩ የነበሩ 6 ሠራተኞች በግቢው ውስጥ ጊዜያዊ ቤት እንዲሰጣቸው በማድረግ ውጪ ካለው ማህበረሰብ ጋር የነበራቸውን ንክኪ ለመቀነስ ተችሏል ነው ያሉት። እንደ ጣቢያ ኃላፊው ገለፃ በጣቢያው ውስጥ የተቀመጠውን ህግ እና ደንብ አክብረው በማይንቀሳቀሱ ሠራተኞች ላይ የቅጣት እርምጃዎችን መውሰድ ተጀምሯል፡፡ https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=513893655952139&id=320447995296707

“ግድቡ ከመቼውም ጌዜ በላይ የኢትዮጵያ ህዝብ ትኩረት እየሆነ መጥቷል” የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሠራተኞችን ከኮሮና ቫይረስ ለመከላከል የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የፕሮጀክቱ ምክትል ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር በላቸው ካሳ ገለፁ ። ምክትል ስራ አስኪያጁ ለኢዜአ እንደገለፁት የህዳሴው ግድብ ፕሮጀክት በሁለት ፈረቃዎች ተከፍሎ ሥራው 24 ሰዓታት እየተከናወነ ነው፡፡.https://www.facebook.com/Ethioelectric/posts/512788792729292

የኮቪድ-19 ሥርጭትን ለመከላከል፣ ለመቆጣጠር እና የሚያስከትለውን ጉዳት ለመቀነስ የወጣ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በተመለከተ ከኢፌዲሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የተሰጠ ማብራሪያ *******************
የኮቪድ-19 ሥርጭትን ለመከላከል፣ ለመቆጣጠር እና የሚያስከትለውን ጉዳት ለመቀነስ የወጣ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በተመለከተ ከኢፌዲሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የተሰጠ ማብራሪያ ************************************************** መጋቢት 30 ቀን 2012 ዓ.ም 1) የአዋጁ አስፈላጊነት እና አላማ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ሕገ-መንግሥት ለሃገር እና ለህዝብ አደጋ የሆኑ ሁኔታዎች ሲያጋጥሙ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በማወጅ የሚተዳደርበትን ሥርዓት በአንቀጽ 93 ላይ አስቀምጧል። በአንቀጽ 93 (1) (ሀ) መሰረት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲታወጅ መነሻ ከሚሆኑ ሁኔታዎች አንዱ “የሕዝብን ጤንነት አደጋ ላይ የሚጥል በሽታ ሲከሰት” የሚል ነው።የኮቪድ-19 የሕዝብን ጤንነት በከፍተኛ ደረጃ አደጋ ላይ የሚጥል በሽታ እንደሆነ ዕሙን ነው። ይህን ወረርሽኝ ለመከላከል፣ ለመቆጣጠር እና የሚያስከትለውን ጉዳት ለመቀነስ የሚወሰዱ እርምጃዎችን ለማሳለጥ እና ውጤታማ ለማድረግ ደግሞ ከተለመደው አሠራር እና ሕገ-መንግሥታዊ ማዕቀፍ ወጥቶ በልዩ ሁኔታ መንቀሳቀስ ይጠይቃል። አዋጁ መንግሥት የቫይረሱን ስርጭት ለመከላከል አስፈላጊ የሆኑ እርምጃዎችን በሚወስድበት ጊዜ የተሻለ ነጻነት እና አቅም እንዲኖረው፣ የመንግስት ሥልጣን ላይ ያሉ ገደቦች ወይም የሰብዓዊ መብት ድንጋጌዎች በተለየ ሁኔታ ለጊዜው ተፈጻሚነታቸው ቀርቶ በሙሉ ኃይል፣ በተቀላጠፈ እና በተቀናጀ መልኩ ለወረርሽኙ ምላሽ መስጠት እንዲቻል በማሰብ ይህ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ታውጆዋል። ወረርሽኙን ለመከላከል የሚወሰዱ እርምጃዎችን ለማሳለጥ እና ከሕግ አንጻር አስቻይ ሁኔታን ከመፍጠር ባለፈ፤ የዚህ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አላማ፣ ከቫይረሱ ስርጭት ጋር ተያይዘው የሚመጡ ተጓዳኝ ተግዳሮቶችን በተመለከተ አስፈላጊውን እርምጃዎች የመደንገግ ስልጣን ለስራ አስፈጻሚው የመንግ

የኮሮና ወረርሽኝ እየተባባሰ በመምጣቱ ምክንያት የኢትዮጵያ መንግሥት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አውጇል፡፡ የኮቪድ19 ወረርሽኝ በዓለም አቀፍም ሆነ በሀገር ደረጃ መስፋፋቱን በመቀጠሉ የሚኒስቴሮች ምክር ቤት በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 93 በተደነገገው መሠረት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅን ደንግጓል፡፡ ሁሉም ሰው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ድንጋጌዎች ተፈጻሚ እንዲያደርግ እና የጤና ሚኒስቴር ያወጣውን ቫይረሱን የመከላከል መመሪያ በጥብቅ እንዲተገብር ማሳሰቢያ ተሰጥቷል፡፡ እኛ ቤት እንድንውል እነርሱ 24 ሠዓት ውጪ በመሆን የሚያገለግሉ የህክምና ባለሙያዎች ፣ የመከላከያና የፖሊስ ሰራዊት አባላት፣ የኤሌክትሪክና የውሃ አገልግሎት እንዳይቋረጥ የሚሰሩ ባለሙያዎች እንዲሁም የሚዲያ ሰዎች ተገቢውን ምስጋናና ድጋፍ ሊሰጣቸው ይገባል ተብሏል፡፡ መጋቢት 30/2012 ዓ.ም https://www.facebook.com/Ethioelectric/posts/512223462785825

ሀገሬ እና ቤተሰቤ እኔን ይፈልጉኛል፡፡ ስለዚህ ከፈጣሪ ጋር ራሴንና የምወዳቸውን ሁሉ ከኮሮና ቫይረስ እጠብቃለሁ፤ እጠነቀቃለሁ፡፡ ምንም እንኳን የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የኦፕሬሽን ሠራተኛ በመሆ
ሀገሬ እና ቤተሰቤ እኔን ይፈልጉኛል፡፡ ስለዚህ ከፈጣሪ ጋር ራሴንና የምወዳቸውን ሁሉ ከኮሮና ቫይረስ እጠብቃለሁ፤ እጠነቀቃለሁ፡፡ ምንም እንኳን የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የኦፕሬሽን ሠራተኛ በመሆኔ ህዝቤን ለማገልገል በቤት ውስጥ መቀመጥ ባልችልም አካላዊ ርቀቴን በመጠበቅና አስፈላጊውን ጥንቃቄ በማድረግ የተጣለብኝን ሀገራዊ ግዴታ እወጣለሁ፡፡ እጄን ስታጠብም ቢያንስ ለ20 ሰከንድ በሳሙና በደንብ አሽቼ እታጠባለሁ፡፡ ፊቴን ፣ አይኔን ፣ አፌን፣ አፍንጫዬንና እና ጆሮዬን በእጄ ላለመንካት ትልቅ ጥንቃቄ አደርጋለሁ፡፡ እርስዎስ? ፈጣሪ ህዝባችንን ፣ ሀገራችንን እና ምድራችንን ይጠብቅ!!!

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ - የብሔራዊ ቁጭታችን መቋጫ አብርሃም በላይ (ዶ/ር) የኢ.ኤ.ኃ የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ የታላቁ ህዳሴ ግድብ የመሰረት ድንጋይ የተቀመጠበትና ግንባታው የተጀመረበትን 9ኛ ዓመት በማስመልከት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ለመላው ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ያስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት፡፡ የዘመናት ሰረገላ በሚዘወርባት በዓለማችን በጊዜያት መካከል ጐልተው የሚዘከሩ የታሪክ አሻራዎቻቸውን ለማኖር ህዝቦቿ ያለማቋረጥ ይታትራሉ፡፡ ኢትዮጵያዊያንም ባለ ብዙ መልክ የዘመናት ታሪካቸውን፣ የሥነ ህንፃ እንዲሁም ረቂቅ የመንፈሳዊና የስልጣኔ መገለጫ ተጠቃሽ ስራዎቻቸውን ለዓለም አበርክተው አልፈዋል፡፡ ምንም እንኳን በቅርብ ጊዜ ታሪካችን ድህነት፣ ርሀብና ድንቁርና ላለፋት በርካታ ዓመታት ቢፈራረቁብንም እንደ ህዝብ ካሸለብንበት ረጅም ሰመመን በመንቃት፣ ችግሮቻችንን በጥልቀት በመመርመርና የመፍትሄ ሀሳቦችን በማፍለቅና በመተግበር የትውልድ ተልዕኳችንን ለመወጣት በየመስኩ እንቅስቃሴ ማድረግ ከጀመርን ሰነባብተናል፡፡ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ሀገራችን ለመሰረተ ልማት ግንባታ፣ ለቀጣናዊ ትስስር የልማት መርሀ ግብሮችና ለሚሊኒየም የልማት ዕቅዶች መሳካት ባደረገችው ጥረት በአንፃራዊነት አጥጋቢ ውጤቶችን በማስመዝገብ በዓለም ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት ካስመዘገቡ ሀገሮች ተርታ መሰለፍ መጀመሯን መመልከት ችለናል፡፡ የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድባችን ለኛ በዚህ ዘመን ላለን ኢትዮጵያዊን፣ ለቀጣዩ ትውልድ፣ ብሎም ለተቀረው ዓለም በተፈጥሮ ሀብታችን በመጠቀም ከድህነት ለመውጣትና ዘላቂ የልማት ኘሮግራሞቻችንን ለማሳካት፤ እንደ ትውልድ ህዝባዊ ቁርጠኝነታችንን ለማስመስከር የጀመርነው ብሔራዊ ኘሮጀክታችን ነው፡፡ https://www.facebook.com/ethiopian.electrcpower.1/posts/213296669900116

የሀገር አለኝታነታችን የምናረጋግጥበት ወሳኝ ወቅት አሁን ነው፡፡ የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) በዓለም ላይ በከፍተኛ ፍጥነት እየተስፋፋ የመጣ እና አደገኛ ወረርሺኝ ሲሆን በሀገራችንም መከሰቱን በጤና ሚኒስቴር በኩል ይፋ መደረጉ ይታወሳል፡፡ ይህንኑ ተከትሎ መንግስት ሊወሰዱ የሚገቡ የጥንቃቄ እርምጃዎችን በመውሰድ የተለያዩ ውሳኔዎችን በየጊዜው እያስተላለፈ ይገኛል፡፡ ቫይረሱ እንዳይስፋፋ እና ዜጎችቻችን ላይ የሚደርሰውን አደጋ ለመከላከል ሁሉም ዜጎች የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡም ጭምር ብሄራዊ ጥሪ ተደርጓል፡፡ በሽታውን ከመከላከል ረገድ ሁሉም ዜጎች ካለባቸው ኃላፊነት በተጨማሪ የመንግስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ደግሞ የተለየ ወሳኝ ሚና ይጠበቅባቸዋል፡፡ የህብረተሰቡን ጤና የመጠበቅ ኃላፊነት በዋናነት የጤና ሚኒስቴር ቢሆንም ሌሎች አገልግሎት ሰጪዎችም ወረርሽኙን ለመከላከልና እንዳይስፋፋ ለማድረግ የራሳቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ ይጠበቃል፡፡ ለተጨማሪ https://www.facebook.com/ethiopian.electrcpower.1/posts/212987096597740

#ኮሮናን መከላከል ይቻላል!! #ኮሮናን መከላከል የሚቻለው የቫይረሱን ስርጭት ለመከላከል በሚመለከታቸው የጤና ተቋማት የወጡ የጥንቃቄ እርምጃዎችን፣ ህጎችን፣ ስርዓትና መመሪያዎችን አክብሮ በመንቀሳቀስ ነው፡፡ ዛሬ ላይ ሆኖ ስለነገ የሚጨነቅ፣ ስለራሱና በዙሪያው ስላሉት ሰዎች ኃላፊነት የሚሰማውና የራሱን የጥንቃቄ ድርሻ እየተወጣ ፈጣሪውን የሚማጸን ማህበረሰብ ሲኖር ነው። ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይጠብቅ!!

ጤና ይስጥልን!! ከኮርና ቫይረስ ተጠንቀቁ፡፡ እጃችሁን በሳሙና በደንብ ታጠቡ፡፡ ከቤት ውጭ እንቅስቃሴ ቀንሱ፤ ከቻላችሁም አቋርጡ ፡፡ መጨባበጥን ቀንሱ፡፡ ዋናው ጥንቃቄ ነውና ጥንቃቄ መቼም ቢሆን አታቋርጡ፡፡ መልካም ቀን!!

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የኮቪድ-19 ሁለተኛ ሰለባ ለሆኑት ኢትዮጵያዊ ቤተሰብና ወዳጆች መጽናናትን ተመኙ ********** ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የኮቪድ-19 ሁለተኛ ሰለባ ለሆኑት ኢትዮጵያዊ ቤተሰብ እና ወዳጆች ልባዊ መጽናናትን ተመኝተዋል። "የፈጣሪ ጸጋ ከሁላችን ጋር ይሁን፤ ፈተናውን በአብሮነት እንወጣዋለን" ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ። ሁሉም ሰው መንግሥት ያወጣቸውን ደንቦች እና የጤና ሚኒስቴርን መመሪያዎች በጥብቅ ተፈጻሚ እንዲያደርግ አሳስበዋል።

Pls invite your staff and colliques the new Ethiopian Electric Power Communication Telegram Channel @EEPCommuication

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በኮቪድ19 ሕይወቷ ላለፈው ኢትዮጵያዊት የተሰማቸውን ሀዘን ገልጸዋል፡፡

በኮሮና ቫይረስ ምክንያት በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ሞት ተመዘገበ ***************** የጤና ሚኒስቴርና ኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የኮሮና በሽታ (ኮቪድ-19) በቻይና ውሃን ከተማ ከተቀሰቀሰበት ግዜ አንስቶ ወደ ሀገራችን ቫይረሱ እንዳይገባ እንዲሁም ከገባ ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል ዝግጅት እያደረጉ መቆየቱ ይታወቃል፡፡ ቫይረሱ ወደ ሀገራችን ከገባ ጀምሮ ህብረተሰቡ የጥንቃቄ እርምጃዎችን ተግባራዊ እንዲያደርግ ቅስቀሳዎችን እያደረገና የተጠቂዎችን ቁጥርና የጤና ሁኔታቸው እያሳወቀ ነው፡፡ አንዲት የ60 ዓመት ታማሚ መጋቢት 19 ፣2012 ዓ.ም በኮሮና ቫይረስ በሽታ ምልክት ታይቶባቸው በለይቶ ማከሚያ ገብተው የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው የነበረ ሲሆን በመጋቢት 22፣2012 ዓ.ም በኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው መረጋገጡ ይታወሳል፡፡ ይሁንና ከመጋቢት 22 አንስቶ ላለፉት ስድስት ቀናት በፅኑ ህክምና ላይ የነበሩ ሲሆን በዛሬው እለት ህይወታቸው አልፏል፡፡ የጤና ሚኒስቴርና የኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በህልፈተ ህይወታቸው የተሰማውን ሀዘን እየገለፀ ለቤተሰቦቻቸው መፅናናትን ይመኛል፡፡ ህብረተሰቡ በዚህ ሳይደናገጥ ለተለያዩ ጉዳዮች በአንድ ቦታ መሰባሰብን በማስወገድ፣ እጅን አዘውትሮ በመታጠብ፣ በአካል ንክኪ የሚደረግ ሰላምታን በመተውና አካላዊ መራራቅን (ቢያነስ አንድ ሜትር) ተግባራዊ በማድረግ የበሽታውን ስርጭት እንዲከላከል በጥብቅ እናሳስባለን፡፡

የኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ ስርጭት ዕለታዊ መረጃ

photo content

Ethiopian Electrc Power Just now · ዋና ሥራ አስፈፃሚው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል የተደረገውን ዝግጅት ተመለከቱ፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል የተደረገውን ዝግጅት ተመለከቱ፡፡ በማዕከሉ ሁሉም የኦፕሬሽን ሠራተኞች ተገቢውን ጥንቃቄ እያደረጉና አካላዊ ርቀት እየጠበቁ ስራቸውን እንደሚሰሩ በስፍራው በመገኘት ተመልክተው ግብረ መልስ ሰጥተዋል፡፡https://www.facebook.com/Ethioelectric/photos/pcb.509618773046294/509618589712979/?type=3&__tn__=HH-R&eid=ARA5gvWL0i_1ocnaJqFxX2sLPbLrZLa3psNMFiEnvf0VocEYM_TAKiUHHX_KDmqtpjTKBa5jX-hJpQyd&__xts__%5B0%5D=68.ARBfaebGncZCQdM7qrE-4r4qCJiKiX7Wf0C69S1xyStpgjUGKvzRs2D6LzRO8Iin8uxHeFrLnO5qu0-ZFK8A_6jJxFxrGG_92LlquMo4MdEJYi-tJ8ctkOoXRUqcuwqxHi5m2n_eGLDIfJ9CrBbZlAa2VrDODXzQipHkZ5942nLyS1Z024jcMoYbUjR_4taTPITLrlGWpi6t74ZgLJyPpFfkjkvdMyq81FVN29lncvQy6xMGCibLzKIVGdpx9IjaryMur3QOyRDiA-hOeHERbeX-S52evmIYynXFnpby_2ZUzGL1yf2ZMbFSwK_BL5qrG09OYublxavylH2idbwcQKg

ቅድሚያ ጤና! በዓለማችን ላይ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ከ አንድ ሚሊየን በላይ ሆኗል፡፡ ዛሬ ላይ በሀገራችን በቫይረሱ ተያዙት ሰዎች ቁጥር ምንም እንኳ 35 ቢሆንም አድርጉ የተባልነው የጥንቃቄ እርምጃ የማንወስድና በተገቢው መንገድ ጥንቃቄ የማናደርግ ከሆነ በጣልያን ፥ ስፔን ፥ አሜሪካ፥ ቱርክ እና በሌሎች ሀገራት እየሆነ እንዳለው ራሳችንን አልያም የምንወዳቸውን ሰዎች በቫይረሱ ማጣታችን አይቀሬ ይሆናል ፡፡ ስለዚህ ለራሳችን እና ለምንወዳቸው ስንል እንጠንቀቅ!!