EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 525 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 336,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 179 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 525 名订阅者。
根据 07 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 5,过去 24 小时变化为 -2,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 28.59%。内容发布后 24 小时内通常能获得 16.03% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 440 次浏览,首日通常累积 2 489 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 10。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 08 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 525
订阅者
-224 小时
-57 天
+530 天
帖子存档
15 525
ዋና ሥራ አስፈፃሚው የደገሀቡር ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያን ጎበኙ
.........//.........
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ ባለፈው ዓመት አገልግሎት መስጠት የጀመረውን የደገሀቡር ባለ 132/33 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ትናንት ማምሻውን በመጎብኘት ከጣቢያው የኦፕሬሽን ሠራተኞች ጋር ተወያይተዋል።
የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል በተሰሩ ስራዎችና ለጣቢያው መሟላት ባለባቸው የስራ ግብዐቶች ዙሪያም ተነጋግረዋል።
የጣቢያው ኃላፊ አቶ ከድር ዑስማን ስለጣቢያው የኃይል አቅርቦት፣ ከአካባቢው የመስተዳድር አካላት ጋር ስላላቸው ግንኙነትና የጣቢያው ሰራተኞች በራስ ተነሳሽነት የሰሯቸው ስራዎችን በተመለከተ ለዋና ስራ አስፈፃሚው ገለፃ አድርገውላቸዋል።
ዋና ስ ራ አስፈፃሚው በበኩላቸው ቀሪ ስራዎችን በመለየት ከሚመለከታቸው ክፍሎች ጋር በመሆን የማሟላት ስራ እንደሚሰራ ጠቁመዋል።
ጣቢያውን ኃይል ከማቅረብ በተጓዳኝ ለስራና ለዕይታ ምቹ በማድረግ በኩልም ትኩረት ሰጥተው እንዲሰሩ አሳስበዋል።
በስፍራው የተገኙት የክልለሉ መንግስት የስራ ኃላፊዎችም የደገሀቡር እና አካባቢው ኃይል ማግኘት የአካባቢውን ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ እንዳነቃቃው በመግለፅ ተቋሙ ለሚያከናውነው ስራ አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል።
የደገሀቡር ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ካሉት 5 ወጪ መስመሮች መካከል በአሁኑ ሰዓት አገልግሎት እየሰጡ ያሉት ሁለቱ ብቻ ሲሆኑ አሁን ካለው ከእጥፍ የሚበልጥ የኃይል ፍላጎት ቢመጣ እንኳ የማስተናገድ አቅም አለው።
ሚያዝያ 04 ቀን 20122 ዓ/ም
15 525
በጣቢያው የበጎ ፍቃድ ተግባራት በመከናወን ላይ ናቸው
……..///…….
የጊቤ 2 የኃይል ማመንጫ ጣቢያ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል በጣቢያው ውስጥ ባቋቋመው ግብረ ሃይል አማካኝነት የተለያዩ ሥራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡
የጣቢያው ኃላፊ አቶ ሃብታሙ ገረመው እንደተናገሩት የቆሴ እና ፉፋ ኬላዎችን ጨምሮ በኃይል ማመንጫ ቤት እንዲሁም በመኖሪያ ቤቶች አካባቢ 10 የእጅ መታጠቢያ ቦታዎችን በማዘጋጀት ሠራተኛው የእጅ ንፅህናውን እንዲጠብቅ እየተደረገ ነው።
ሃገሪቱ አሁን ካለችበት አስቸጋሪ ሁኔታ እንድትወጣ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ወሳኝነት እንዳለው የተናገሩት ኃላፊው በኃይል ማመንጫ እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ለሚሰሩ ሠራተኞች መንግሥት እና ተቋሙ ልዩ ትኩረት እንዲያደርግ ጠይቀዋል።
ለጣቢያው ሠራተኞች 210 ሊትር የእጅ ማፅጃ ሳኒታይዘር እና ማስኮች እንዲሁም 500 የሜዲካል ግላቮች ከተቋሙ የጤና እና ሴፍቲ የሥራ ክፍል እንደተሰጣቸው አቶ ሃብታሙ የጠቆሙ ሲሆን ከወረዳው ጋር በመነጋገርም ተጨማሪ 50 ጥንድ ጓንት እና ማስክ ከሆጃ ጤና ጣቢያ እንደተበረከተላቸው ተናግረዋል፡፡
በሃገሪቱ ውስጥ የወረርሽኙ የመስፋፋት ሥጋትን በማየት ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በህብረት ይሰራ የነበረውን የጥበቃ ሥራ ለጊዜው በማቋረጥ የተወሰኑ ሰዎችን ብቻ በመምረጥ የጥበቃውን ሥራ በማከናወን ላይ እንደሚገኙ አስታውቀዋል፡፡
ከመኖሪያ ቤት ወደ ኃይል ማመንጫ ይደረግ የነበረውን የሠራተኞች የሰርቪስ አጠቃቀም በማሻሻልም የንክኪ መጠኑን መቀነስ መቻሉን ነው ኃላፊው የጠቆሙት፡፡
የጣቢያው የጥገና ክፍል ኃላፊ አቶ ገበየሁ በላይ በበኩላቸው እንደገለፁት 210 የሚሆኑ የጣቢያውን ሠራተኞች እንደ ሥራ ባህሪያቸው በመክፈል ለ9 ጊዜ ያህል የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን ማከናወን ተችሏል።
15 525
የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የሚያስችሉ ተግባራትን በማከናወን ላይ ይገኛሉ
……………….//……………
የኮሮና ወረርሽኝ በአሁኑ ሰዓት ዓለምን እያስጨነቀ፣ በየሃገራቱ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ እና ማህበራዊ ቀውስን እየፈጠረና የብዙ ንፁሃን ዜጎችን ህይወት እየቀጠፈ የሚገኝ ተላላፊ ቫይረስ ነው፡፡
ይህ ወረርሽኝ በህክምናው ዘርፍ ከፍተኛ ደረጃ ደርሰዋል ለምንላቸውን ኃያላን ሀገራት ራስ ምታት ሆኖ ሲፈታተናቸው እያስተዋልን እንገኛለን፡፡ ለዚህ ደግሞ የቫይረሱ የመተላለፊያ መንገዶች ቀላል መሆን እና የሥርጭት ፍጥነቱ እንደ ዋነኛ ምክንያት ይጠቀሳል፡፡
ኢትዮጵያ እንደሌሎች የዓለም ሃገራት ሁሉ የቫይረሱን የሥርጭት መጠን ለመከላከል በአሁኑ ሰዓት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅን ከማወጅ ጀምሮ ሌሎች በርካታ ወሳኝ እርምጃዎችን እየወሰደች ብትገኝም የቫይረሱ ስርጭት መጠን ግን ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ በመሄድ ላይ ነው፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እንደ ተቋም የቫይረሱን ሥርጭት ከመከላከል አንፃር መጠነ ሰፊ ሥራዎች በዋናው መስሪያ ቤት፣ በኃይል ማመንጫ እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች እንዲሁም ፕሮጀክቶች ላይ እያከናወነ ይገኛል፡፡
ከዚህም ጋር ተያይዞ የጊቤ 1፣ 2 እና 3 የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ቫይረሱን ከመከላከል አኳያ ምን እየሰሩ እንደሆነ ዞረን ለመመልከት ሞክረናል፡፡
የጊቤ 3 የኃይል ማመንጫ ጣቢያ 1870 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም ያለውና በኢትዮጵያ ትልቁ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሲሆን ወረርሽኙን ለመቆጣጠር በጣቢያው ውስጥ የኮሮና ቫይረስ መከላከል ግብረ-ኃይል ተቋቁሞ የተለያዩ ሥራዎች በመሰራት ላይ መሆኑን የጣቢያው ኃላፊ አቶ ሃብታሙ ሰሙ ተናግረዋል፡፡
እንደ አቶ ሃብታሙ ገለፃ የጣቢያውን ሠራተኞች ሙሉ በሙሉ ወሸባ ከቅጥር ግቢው እንዳይወጡና ሌሎች ሰዎችም ወደ ጣቢያው እንዳይገቡ ተደርጓል፡፡
የተቋቋመው ግብረ ኃይል ቀደም ሲል ይደረግ የነበረውን የተናጠል የመሠረታዊ ፍጆታ ሸቀጦች ግዥ በማስቀረት ለሠራተኛው የሚበቃ የጅምላ ግዥ በመፈፀም ላይ ቢሆንም ሂደቱ ግን አስቸጋሪ እንደሆነ አቶ ሃብታሙ ተናግረዋል፡፡
ለጣቢያው ሠራተኞች 300 ሊትር የእጅ ማፅጃ ሳኒታይዘር፣ 51 ማስኮች እና በርካታ የእጅ ጓንቶች ከተቋሙ የጤና እና ሴፍቲ የሥራ ክፍል እንደተሰጣቸው አቶ ሃብታሙ በመጥቀስ የተላኩት የመከላከያ ግብዓቶች ግን ካለው የሠራተኛ ቁጥር አንፃር በቂ እንዳልሆኑ ተናግረዋል፡፡ ይሄንን እጥረት ለመቅረፍም ጣብያውን ከገነባው ከቻይናው ዶንግፋንግ ኢንተርናሽናል ኩባንያ 80 ማስኮች ድጋፍ እንደተደረገላቸው አቶ ሃብታሙ ጨምረው አብራርተዋል፡፡
ከጣቢያው ለሥራም ሆነ ለሌላ ተግባራት የሚወጡ ሠራተኞች ወደ ጣቢያው ሲመለሱ ለ14 ቀናት ራሳቸውን አግልለው እንዲቆዩ እየተደረገ እንደሆነም ነው አቶ ሃብታሙ የጠቆሙት፡፡
በጣቢያው ውስጥ የፅዳት እና የአትክልት ሥራዎችን ይሰሩ የነበሩ 6 ሠራተኞች በግቢው ውስጥ ጊዜያዊ ቤት እንዲሰጣቸው በማድረግ ውጪ ካለው ማህበረሰብ ጋር የነበራቸውን ንክኪ ለመቀነስ ተችሏል ነው ያሉት። እንደ ጣቢያ ኃላፊው ገለፃ በጣቢያው ውስጥ የተቀመጠውን ህግ እና ደንብ አክብረው በማይንቀሳቀሱ ሠራተኞች ላይ የቅጣት እርምጃዎችን መውሰድ ተጀምሯል፡፡
https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=513893655952139&id=320447995296707
15 525
“ግድቡ ከመቼውም ጌዜ በላይ የኢትዮጵያ ህዝብ ትኩረት እየሆነ መጥቷል”
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሠራተኞችን ከኮሮና ቫይረስ ለመከላከል የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የፕሮጀክቱ ምክትል ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር በላቸው ካሳ ገለፁ ።
ምክትል ስራ አስኪያጁ ለኢዜአ እንደገለፁት የህዳሴው ግድብ ፕሮጀክት በሁለት ፈረቃዎች ተከፍሎ ሥራው 24 ሰዓታት እየተከናወነ ነው፡፡.https://www.facebook.com/Ethioelectric/posts/512788792729292
15 525
የኮቪድ-19 ሥርጭትን ለመከላከል፣ ለመቆጣጠር እና የሚያስከትለውን ጉዳት ለመቀነስ የወጣ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በተመለከተ ከኢፌዲሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የተሰጠ ማብራሪያ
**************************************************
መጋቢት 30 ቀን 2012 ዓ.ም
1) የአዋጁ አስፈላጊነት እና አላማ
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ሕገ-መንግሥት ለሃገር እና ለህዝብ አደጋ የሆኑ ሁኔታዎች ሲያጋጥሙ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በማወጅ የሚተዳደርበትን ሥርዓት በአንቀጽ 93 ላይ አስቀምጧል። በአንቀጽ 93 (1) (ሀ) መሰረት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲታወጅ መነሻ ከሚሆኑ ሁኔታዎች አንዱ “የሕዝብን ጤንነት አደጋ ላይ የሚጥል በሽታ ሲከሰት” የሚል ነው።የኮቪድ-19 የሕዝብን ጤንነት በከፍተኛ ደረጃ አደጋ ላይ የሚጥል በሽታ እንደሆነ ዕሙን ነው።
ይህን ወረርሽኝ ለመከላከል፣ ለመቆጣጠር እና የሚያስከትለውን ጉዳት ለመቀነስ የሚወሰዱ እርምጃዎችን ለማሳለጥ እና ውጤታማ ለማድረግ ደግሞ ከተለመደው አሠራር እና ሕገ-መንግሥታዊ ማዕቀፍ ወጥቶ በልዩ ሁኔታ መንቀሳቀስ ይጠይቃል። አዋጁ መንግሥት የቫይረሱን ስርጭት ለመከላከል አስፈላጊ የሆኑ እርምጃዎችን በሚወስድበት ጊዜ የተሻለ ነጻነት እና አቅም እንዲኖረው፣ የመንግስት ሥልጣን ላይ ያሉ ገደቦች ወይም የሰብዓዊ መብት ድንጋጌዎች በተለየ ሁኔታ ለጊዜው ተፈጻሚነታቸው ቀርቶ በሙሉ ኃይል፣ በተቀላጠፈ እና በተቀናጀ መልኩ ለወረርሽኙ ምላሽ መስጠት እንዲቻል በማሰብ ይህ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ታውጆዋል።
ወረርሽኙን ለመከላከል የሚወሰዱ እርምጃዎችን ለማሳለጥ እና ከሕግ አንጻር አስቻይ ሁኔታን ከመፍጠር ባለፈ፤ የዚህ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አላማ፣ ከቫይረሱ ስርጭት ጋር ተያይዘው የሚመጡ ተጓዳኝ ተግዳሮቶችን በተመለከተ አስፈላጊውን እርምጃዎች የመደንገግ ስልጣን ለስራ አስፈጻሚው የመንግ
15 525
የኮሮና ወረርሽኝ እየተባባሰ በመምጣቱ ምክንያት የኢትዮጵያ መንግሥት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አውጇል፡፡
የኮቪድ19 ወረርሽኝ በዓለም አቀፍም ሆነ በሀገር ደረጃ መስፋፋቱን በመቀጠሉ የሚኒስቴሮች ምክር ቤት በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 93 በተደነገገው መሠረት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅን ደንግጓል፡፡
ሁሉም ሰው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ድንጋጌዎች ተፈጻሚ እንዲያደርግ እና የጤና ሚኒስቴር ያወጣውን ቫይረሱን የመከላከል መመሪያ በጥብቅ እንዲተገብር ማሳሰቢያ ተሰጥቷል፡፡
እኛ ቤት እንድንውል እነርሱ 24 ሠዓት ውጪ በመሆን የሚያገለግሉ የህክምና ባለሙያዎች ፣ የመከላከያና የፖሊስ ሰራዊት አባላት፣ የኤሌክትሪክና የውሃ አገልግሎት እንዳይቋረጥ የሚሰሩ ባለሙያዎች እንዲሁም የሚዲያ ሰዎች ተገቢውን ምስጋናና ድጋፍ ሊሰጣቸው ይገባል ተብሏል፡፡
መጋቢት 30/2012 ዓ.ም
https://www.facebook.com/Ethioelectric/posts/512223462785825
15 525
ሀገሬ እና ቤተሰቤ እኔን ይፈልጉኛል፡፡
ስለዚህ ከፈጣሪ ጋር ራሴንና የምወዳቸውን ሁሉ ከኮሮና ቫይረስ እጠብቃለሁ፤ እጠነቀቃለሁ፡፡
ምንም እንኳን የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የኦፕሬሽን ሠራተኛ በመሆኔ ህዝቤን ለማገልገል በቤት ውስጥ መቀመጥ ባልችልም አካላዊ ርቀቴን በመጠበቅና አስፈላጊውን ጥንቃቄ በማድረግ የተጣለብኝን ሀገራዊ ግዴታ እወጣለሁ፡፡
እጄን ስታጠብም ቢያንስ ለ20 ሰከንድ በሳሙና በደንብ አሽቼ እታጠባለሁ፡፡ ፊቴን ፣ አይኔን ፣ አፌን፣ አፍንጫዬንና እና ጆሮዬን በእጄ ላለመንካት ትልቅ ጥንቃቄ አደርጋለሁ፡፡
እርስዎስ?
ፈጣሪ ህዝባችንን ፣ ሀገራችንን እና ምድራችንን ይጠብቅ!!!
15 525
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ - የብሔራዊ ቁጭታችን መቋጫ
አብርሃም በላይ (ዶ/ር)
የኢ.ኤ.ኃ የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ
የታላቁ ህዳሴ ግድብ የመሰረት ድንጋይ የተቀመጠበትና ግንባታው የተጀመረበትን 9ኛ ዓመት በማስመልከት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ለመላው ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ያስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት፡፡
የዘመናት ሰረገላ በሚዘወርባት በዓለማችን በጊዜያት መካከል ጐልተው የሚዘከሩ የታሪክ አሻራዎቻቸውን ለማኖር ህዝቦቿ ያለማቋረጥ ይታትራሉ፡፡ ኢትዮጵያዊያንም ባለ ብዙ መልክ የዘመናት ታሪካቸውን፣ የሥነ ህንፃ እንዲሁም ረቂቅ የመንፈሳዊና የስልጣኔ መገለጫ ተጠቃሽ ስራዎቻቸውን ለዓለም አበርክተው አልፈዋል፡፡
ምንም እንኳን በቅርብ ጊዜ ታሪካችን ድህነት፣ ርሀብና ድንቁርና ላለፋት በርካታ ዓመታት ቢፈራረቁብንም እንደ ህዝብ ካሸለብንበት ረጅም ሰመመን በመንቃት፣ ችግሮቻችንን በጥልቀት በመመርመርና የመፍትሄ ሀሳቦችን በማፍለቅና በመተግበር የትውልድ ተልዕኳችንን ለመወጣት በየመስኩ እንቅስቃሴ ማድረግ ከጀመርን ሰነባብተናል፡፡
ባለፉት ጥቂት ዓመታት ሀገራችን ለመሰረተ ልማት ግንባታ፣ ለቀጣናዊ ትስስር የልማት መርሀ ግብሮችና ለሚሊኒየም የልማት ዕቅዶች መሳካት ባደረገችው ጥረት በአንፃራዊነት አጥጋቢ ውጤቶችን በማስመዝገብ በዓለም ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት ካስመዘገቡ ሀገሮች ተርታ መሰለፍ መጀመሯን መመልከት ችለናል፡፡
የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድባችን ለኛ በዚህ ዘመን ላለን ኢትዮጵያዊን፣ ለቀጣዩ ትውልድ፣ ብሎም ለተቀረው ዓለም በተፈጥሮ ሀብታችን በመጠቀም ከድህነት ለመውጣትና ዘላቂ የልማት ኘሮግራሞቻችንን ለማሳካት፤ እንደ ትውልድ ህዝባዊ ቁርጠኝነታችንን ለማስመስከር የጀመርነው ብሔራዊ ኘሮጀክታችን ነው፡፡
https://www.facebook.com/ethiopian.electrcpower.1/posts/213296669900116
15 525
የሀገር አለኝታነታችን የምናረጋግጥበት ወሳኝ ወቅት አሁን ነው፡፡
የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) በዓለም ላይ በከፍተኛ ፍጥነት እየተስፋፋ የመጣ እና አደገኛ ወረርሺኝ ሲሆን በሀገራችንም መከሰቱን በጤና ሚኒስቴር በኩል ይፋ መደረጉ ይታወሳል፡፡ ይህንኑ ተከትሎ መንግስት ሊወሰዱ የሚገቡ የጥንቃቄ እርምጃዎችን በመውሰድ የተለያዩ ውሳኔዎችን በየጊዜው እያስተላለፈ ይገኛል፡፡ ቫይረሱ እንዳይስፋፋ እና ዜጎችቻችን ላይ የሚደርሰውን አደጋ ለመከላከል ሁሉም ዜጎች የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡም ጭምር ብሄራዊ ጥሪ ተደርጓል፡፡
በሽታውን ከመከላከል ረገድ ሁሉም ዜጎች ካለባቸው ኃላፊነት በተጨማሪ የመንግስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ደግሞ የተለየ ወሳኝ ሚና ይጠበቅባቸዋል፡፡ የህብረተሰቡን ጤና የመጠበቅ ኃላፊነት በዋናነት የጤና ሚኒስቴር ቢሆንም ሌሎች አገልግሎት ሰጪዎችም ወረርሽኙን ለመከላከልና እንዳይስፋፋ ለማድረግ የራሳቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ ይጠበቃል፡፡
ለተጨማሪ https://www.facebook.com/ethiopian.electrcpower.1/posts/212987096597740
15 525
#ኮሮናን መከላከል ይቻላል!!
#ኮሮናን መከላከል የሚቻለው የቫይረሱን ስርጭት ለመከላከል በሚመለከታቸው የጤና ተቋማት የወጡ የጥንቃቄ እርምጃዎችን፣ ህጎችን፣ ስርዓትና መመሪያዎችን አክብሮ በመንቀሳቀስ ነው፡፡ ዛሬ ላይ ሆኖ ስለነገ የሚጨነቅ፣ ስለራሱና በዙሪያው ስላሉት ሰዎች ኃላፊነት የሚሰማውና የራሱን የጥንቃቄ ድርሻ እየተወጣ ፈጣሪውን የሚማጸን ማህበረሰብ ሲኖር ነው።
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይጠብቅ!!
15 525
ጤና ይስጥልን!!
ከኮርና ቫይረስ ተጠንቀቁ፡፡
እጃችሁን በሳሙና በደንብ ታጠቡ፡፡
ከቤት ውጭ እንቅስቃሴ ቀንሱ፤ ከቻላችሁም አቋርጡ ፡፡
መጨባበጥን ቀንሱ፡፡
ዋናው ጥንቃቄ ነውና ጥንቃቄ መቼም ቢሆን አታቋርጡ፡፡
መልካም ቀን!!
15 525
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የኮቪድ-19 ሁለተኛ ሰለባ ለሆኑት ኢትዮጵያዊ ቤተሰብና ወዳጆች መጽናናትን ተመኙ
**********
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የኮቪድ-19 ሁለተኛ ሰለባ ለሆኑት ኢትዮጵያዊ ቤተሰብ እና ወዳጆች ልባዊ መጽናናትን ተመኝተዋል።
"የፈጣሪ ጸጋ ከሁላችን ጋር ይሁን፤ ፈተናውን በአብሮነት እንወጣዋለን" ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።
ሁሉም ሰው መንግሥት ያወጣቸውን ደንቦች እና የጤና ሚኒስቴርን መመሪያዎች በጥብቅ ተፈጻሚ እንዲያደርግ አሳስበዋል።
15 525
Pls invite your staff and colliques the new Ethiopian Electric Power Communication Telegram Channel
@EEPCommuication
15 525
በኮሮና ቫይረስ ምክንያት በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ሞት ተመዘገበ
*****************
የጤና ሚኒስቴርና ኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የኮሮና በሽታ (ኮቪድ-19) በቻይና ውሃን ከተማ ከተቀሰቀሰበት ግዜ አንስቶ ወደ ሀገራችን ቫይረሱ እንዳይገባ እንዲሁም ከገባ ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል ዝግጅት እያደረጉ መቆየቱ ይታወቃል፡፡
ቫይረሱ ወደ ሀገራችን ከገባ ጀምሮ ህብረተሰቡ የጥንቃቄ እርምጃዎችን ተግባራዊ እንዲያደርግ ቅስቀሳዎችን እያደረገና የተጠቂዎችን ቁጥርና የጤና ሁኔታቸው እያሳወቀ ነው፡፡ አንዲት የ60 ዓመት ታማሚ መጋቢት 19 ፣2012 ዓ.ም በኮሮና ቫይረስ በሽታ ምልክት ታይቶባቸው በለይቶ ማከሚያ ገብተው የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው የነበረ ሲሆን በመጋቢት 22፣2012 ዓ.ም በኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው መረጋገጡ ይታወሳል፡፡ ይሁንና ከመጋቢት 22 አንስቶ ላለፉት ስድስት ቀናት በፅኑ ህክምና ላይ የነበሩ ሲሆን በዛሬው እለት ህይወታቸው አልፏል፡፡ የጤና ሚኒስቴርና የኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በህልፈተ ህይወታቸው የተሰማውን ሀዘን እየገለፀ ለቤተሰቦቻቸው መፅናናትን ይመኛል፡፡
ህብረተሰቡ በዚህ ሳይደናገጥ ለተለያዩ ጉዳዮች በአንድ ቦታ መሰባሰብን በማስወገድ፣ እጅን አዘውትሮ በመታጠብ፣ በአካል ንክኪ የሚደረግ ሰላምታን በመተውና አካላዊ መራራቅን (ቢያነስ አንድ ሜትር) ተግባራዊ በማድረግ የበሽታውን ስርጭት እንዲከላከል በጥብቅ እናሳስባለን፡፡
15 525
Ethiopian Electrc Power
Just now ·
ዋና ሥራ አስፈፃሚው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል የተደረገውን ዝግጅት ተመለከቱ፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል የተደረገውን ዝግጅት ተመለከቱ፡፡
በማዕከሉ ሁሉም የኦፕሬሽን ሠራተኞች ተገቢውን ጥንቃቄ እያደረጉና አካላዊ ርቀት እየጠበቁ ስራቸውን እንደሚሰሩ በስፍራው በመገኘት ተመልክተው ግብረ መልስ ሰጥተዋል፡፡https://www.facebook.com/Ethioelectric/photos/pcb.509618773046294/509618589712979/?type=3&__tn__=HH-R&eid=ARA5gvWL0i_1ocnaJqFxX2sLPbLrZLa3psNMFiEnvf0VocEYM_TAKiUHHX_KDmqtpjTKBa5jX-hJpQyd&__xts__%5B0%5D=68.ARBfaebGncZCQdM7qrE-4r4qCJiKiX7Wf0C69S1xyStpgjUGKvzRs2D6LzRO8Iin8uxHeFrLnO5qu0-ZFK8A_6jJxFxrGG_92LlquMo4MdEJYi-tJ8ctkOoXRUqcuwqxHi5m2n_eGLDIfJ9CrBbZlAa2VrDODXzQipHkZ5942nLyS1Z024jcMoYbUjR_4taTPITLrlGWpi6t74ZgLJyPpFfkjkvdMyq81FVN29lncvQy6xMGCibLzKIVGdpx9IjaryMur3QOyRDiA-hOeHERbeX-S52evmIYynXFnpby_2ZUzGL1yf2ZMbFSwK_BL5qrG09OYublxavylH2idbwcQKg
15 525
ቅድሚያ ጤና!
በዓለማችን ላይ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ከ አንድ ሚሊየን በላይ ሆኗል፡፡ ዛሬ ላይ በሀገራችን በቫይረሱ ተያዙት ሰዎች ቁጥር ምንም እንኳ 35 ቢሆንም አድርጉ የተባልነው የጥንቃቄ እርምጃ የማንወስድና በተገቢው መንገድ ጥንቃቄ የማናደርግ ከሆነ በጣልያን ፥ ስፔን ፥ አሜሪካ፥ ቱርክ እና በሌሎች ሀገራት እየሆነ እንዳለው ራሳችንን አልያም የምንወዳቸውን ሰዎች በቫይረሱ ማጣታችን አይቀሬ ይሆናል ፡፡ ስለዚህ ለራሳችን እና ለምንወዳቸው ስንል እንጠንቀቅ!!
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
