uk
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Відкрити в Telegram

EEP Communication

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 15 692 підписників, посідаючи 8 030 місце в категорії Технології та додатки та 2 153 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 15 692 підписників.

За останніми даними від 26 серпня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 143, а за останні 24 години на 13, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 33.48%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 17.12% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 5 250 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 2 685 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 11.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
EEP Communication

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 27 серпня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Технології та додатки.

15 692
Підписники
+1324 години
+207 днів
+14330 день
Архів дописів
የኃይል መሠረተ ልማቶችን ደህንነትን በማስጠበቅ በኩል የመስተዳድር አካላት ሚና ከፍተኛ ነው ....///..... በኦፕሬሽንና በግንባታ ላይ የሚገኙ የኃይል መሠረተ ልማቶችን ደህንነት በማስጠበቅ በኩል የመስተዳድር አካላት ሚና ከፍተኛ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ። በተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ የተመራ የሥራ አመራር ቡድን በኃይል መሠረተ ልማት ጥበቃ እና በካሳ ክፍያ ጉዳዮች ዙሪያ ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት፣ ከዞንና ከአርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ከተውጣጡ ባለድርሻ አካላት ጋር በአርባምንጭ ከተማ ውይይት እያካሄደ ይገኛል። ለውይይቱ መነሻ የሚሆን ጽሁፍ ያቀረቡት የደቡብ ሁለት ሪጅን ዳይሬክተር አቶ ምትኩ ታዬ እንደገለጹት በክልሉ የጊቤ ሦስት የውሃ ኃይል ማመንጫ እና የኢትዮ-ኬንያ ኮንቨርተር ጣቢያን ጨምሮ በርካታ የኃይል መሠረተ ልማቶች በኦፕሬሽን ይገኛሉ። ተቋሙ ከልማት አጋሮች በሚገኘው ብድርና ዕርዳታ እንዲሁም በራሱ ፋይናንስ በመመደብ የክልሉን የኃይል አቅርቦት አስተማማኝነት በዘላቂነት የሚያረጋግጡ የኃይል መሠረተ ልማት ፕሮጀክቶችን በስፋት እያከናወነ ይገኛል ብለዋል። ሆኖም በክልሉ በከፍተኛ የኃይል ማስተላለፍያ መስመሮች ላይ የሚፈጸመው የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ስርቆት እንዲሁም ከወሰን ማስከበር ጋር ተያይዞ ያሉ ችግሮች ለተቋሙ ከፍተኛ ፈተና መደቀናቸውን አንስተዋል። በተቋሙ የደቡብ ሁለት ሪጅን ከ2016 እስከ 2018 ዓ.ም ባለው ጊዜ የታወር ስርቆት እየቀነሰ ቢመጣም በሦስቱ ዓመት ብቻ 34 ሚሊዮን ብር ጉዳት መድረሱን የጠቆሙት አቶ ምትኩ ተጠርጣሪዎች ሲያዙ የሚመለከታቸዉ የመስተዳድርና የጸጥታ አካላት በቂ ትብብር አለማድረጋቸው ለችግሩ አንዱ ምክንያት መሆኑንም ተናግረዋል። በተጨማሪም በክልሉ በከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ሥር በሕግ የተቀመጠውን ወሰን በማለፍ የመኖሪያ ቤት በመገንባትና ሙዝና ማንጎ በኮሪደር ውስጥ በመትከል ለኃይል መቆራረጥ ስለመዳረጋቸውም ጠቅሰዋል። ተቋሙ የደቡብ ክልልን የኃይል አቅርቦት አስተማማኝነት ለማረጋገጥ የሚያከናውነው የብሔራዊ ኤሌክትሪክ ደቡባዊ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት የተጀመረው የተሻሻለው የካሳ አዋጅ ከመውጣቱ በፊት በመሆኑ ከካሳ ጉዳዮች ጋር ተያይዞ ያሉ ችግሮችን በአፋጣኝ ለመፍታት የመስተዳድር አካላት ትኩረት ሰጥተው ሊሰሩ እንደሚገባም ተገልጿል። በጎፋ፣ ባስኬቶ እና ደቡብ ኦሞ ዞኖች ውስጥ በግለሰቦች የሚደረጉ የፕሮጀክት መዳረሻ መንገዶችን የመዝጋት እንዲሁም የግንባታ ሥራዎችን የማስተጓጎል ችግሮች የፕሮጀክቱን አፈጻጸም እያዘገዩ በመሆኑ ክልሉ አፋጣኝ እርምጃ ሊወስድ እንደሚገባም ገልጸዋል። የኃይል መሠረተ ልማቶችን ከጥቃትና ከስርቆት በማስጠበቅ እና ከካሳ ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ ችግሮችን በመቅረፍ በኩል የኃይል አቅርቦቱን አስተማማኝነትና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ በየደረጃው ያሉ የመስተዳድር አካላት ሚናቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል። በቀረበው የመነሻ ጽሁፍ ላይ ውይይት እየተደረገም ይገኛል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+8

የተቋሙ አመራሮችና የክልሉ የሥራ ኃላፊዎች የማከፋፈያ ጣቢያውን የግንባታ አፈፃፀም ጎበኙ ...///.... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ የተመራ የተቋሙ የሥራ አመራር ቡድን እና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልና የዞን የሥራ ኃላፊዎች የብሔራዊ ኤሌክትሪክ ደቡባዊ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት አካል በሆነው በአርባምንጭ ሁለተኛ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ላይ የመስክ  ምልከታ አድርጓል። የመስክ ምልከታው የተቋሙ አመራር እና የክልሉ የሥራ ኃላፊዎች ፕሮጀክቱ የደረሰበትን የመጨረሻ ምዕራፍ የግንባታ አፈፃፀም በመጎብኘት እያጋጠሙ የሚገኙ ተግዳሮቶች ዙሪያ መፍትሄና ግብረ መልስ ለመስጠት ያለመ መሆኑ ተገልጿል። በመስክ ጉብኝቱ ወቅት ለከፍተኛ የሥራ አመራር ቡድኑ ገለፃ ያደረጉት በፕሮጀክቱ የምዕራፍ አንድ የሣይት ሥራ አስኪያጅ ኢንጅነር አበበ ሚጀና እንደተናገሩት የአርባ ምንጭ ሁለተኛ ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ቀደም ሲል የነበረውን የአርባ ምንጭ ቁጥር አንድን ኃይል የመስጠት አቅም በአራት እጥፍ የሚያሳድግ ነው፡፡ ግንባታው ሲጠናቀቅ በ120 ኪሎ ሜትር ርቀት ውስጥ ለሚገኙ የአካባቢው ማህበረሰቦች እንዲሁም አርባ ምንጭ ላይ ለመገንባት ለታሰበው የተቀናጀ የግብርና ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርክ አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ የሚያስችል መሆኑንም አብራርተዋል። የአርባ ምንጭ ሁለተኛ ማከፋፈያ ጣቢያ ከወላይታ ሶዶ 230 ኪሎ ቮልት፣ ከኦሞ ኩራዝ አንድ በ230 ኪሎ ቮልት መስመርና ከአርባ ምንጭ አንድ በ132 ኪሎ ቮልት መስመር የሚገናኝ ሲሆን በ33 ኪሎ ቮልት አስር እንዲሁም በ15 ኪሎ ቮልት አምስት በድምሩ 15 ወጭ መስመሮች እንዳሉትም ተናግረዋል፡፡ እያጋጠሙ ያሉ ተግዳሮቶቹን በአጭር ጊዜ በመፍታት ፕሮጀክቱን በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ በሚደረገው ጥረት የመስክ ምልከታው ከፍተኛ ሚና እንዳለውም ኢንጂነር አበበ አስገንዝበዋል። የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በበኩላቸው ከክልሉ የመስተዳድር አካላት እና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመነጋገር ለተነሱ ችግሮች አፋጣኝ እልባት ይሰጣል ብለዋል። ፕሮጀክቱ እያጋጠሙት ያሉትን ተግዳሮቶች በመፍታት በአጭር ጊዜ እንዲጠናቀቅ የተቋሙ አመራሩ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግም አረጋግዋል። የአርባ ምንጭ ሁለተኛ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያ ከ37 ነጥብ 09 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ በጀት ተይዞለት ሃዮሰንግ ሄቪይ ኢንደስትሪስ ኮርፖሬሽን በተባለ የደቡብ ኮሪያ ሥራ ተቋራጭ ግንባታው የተጀመረው ሕዳር 2016 ዓ.ም ነው። የተቋሙ የልዑካን ቡድኑ እስከ ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ.ም በሚኖረው ቆይታ ከአርባምንጭ ሁለተኛ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት በተጨማሪ በኢትዮ-ኬኒያ ኮንቨርተር ጣቢያ፣ በጊቤ ሦስት ኃይል ማመንጫና በኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የመስክ ምልከታ ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ.ም

የሀገርን ማዕዘናት በንጹህ ኃይል የማብራት ጉዞ   ሀገራችን ኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል ምንጮችን በጥቅም ላይ በማዋል የምስራቅ አፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል ለመሆን አበክራ እየሰራች ትገኛለች። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንደገለፁት "የታዳሽ ኃይል አማራጮቻችንን በስፋት በማሳደግ፣ የሀገራችንን እያንዳንዱን ማዕዘን እያበራን እንገኛለን" የጠቅላይ ሚኒስትሩ መልዕክት ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ኤኮኖሚና በኃይል ዘርፍ የያዘችውን ሀገራዊ ራዕይና በተግባር ያሳካቻቸውን ስኬቶች ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው።   ሀገርን በታዳሽ ኃይል ለማብራት ከተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት መካከል፡- 1. የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ 5,150 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው ግዙፍ የውሃ ኃይል ማመንጫ ሲሆን የሀገሪቱን ኤሌክትሪክ የማመንጨት አቅም ከእጥፍ በላይ አሳድጓል። ለሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪዎች፣ ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች እንዲሁም ለዜጎች አስተማማኝ ኃይል ከማቅረቡ ባሻገር ለጎረቤት ሀገራት ኃይል በመሸጥ የውጭ ምንዛሬ እያስገኘ ይገኛል።   2. የታዳሽ ኃይል ምንጮች አሰባጥሮ መጠቀም                 ኢትዮጵያ እንደሀገር ከውሃ ኃይል ማመንጫዎች በተጨማሪ እንደ አሸጎዳ፣ አዳማ 1 እና 2፣ አይሻ 2 እና አሰላ ያሉ የንፋስ ኃይል ማመንጫዎች ሥራ መጀመር ከንፋስ የማመንጨት አቅምን 504 ሜጋ ዋት ያደረሱ ናቸው፡፡  ማሳደግ እንዲሁም የአይሻ የንፋስ ኃይል ፕሮጀክትን የመሳሰሉ አዳዲስ ግንባታዎችን በማጠናቀቅ የኃይል አማራጩን ማሰፋፋት ተችሏል። በአሉቶ ላንጋኖ እና በቱሉ ሞዬ እየተካሄዱ ያሉ የጂኦተርማል ፕሮጀክቶች የወደፊት የኃይል ዋስትና ስብጥርን ከሚያረጋግጡ የታዳሽ ኃይል አማራጮች መካከል ይጠቀሳሉ። ከዋናው ግሪድ ርቀው ለሚገኙ የገጠር አካባቢዎች የፀሐይ ኃይል አነስተኛ ግሪዶችን (Mini-grids) እና የቤት ውስጥ ሶላር ሲስተሞችን መስፋፋት የኃይል ተደራሽነትን lማሳደግ ተዐማሪ አቅም ፈጥሯል፡፡   3. የኃይል ተደራሽነትን ማፋጠን በገጠርና ከከተሞች ራቅ ባሉ አካባቢዎች የሚኖሩ ዜጎችን የኃይል ተጠቃሚ ለማድረግ በሚደረገው ጥረት በሺዎች የሚቆጠሩ መንደሮችና አነስተኛ ከተሞች የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ መሆን ጀምረዋል፡፡ የመኖሪያ ቤቶች፣ ትምህርት ቤቶች፣ የጤና ጣቢያዎችና የግብርና ምርት ማቀናበሪያዎች ኃይል እንዲያገኙ በማድረግ የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎቶችን ጥራት ማሻሻል ተችሏል።   4. ቀጣናዊ የኃይል ትስስር ኢትዮጵያ ከታዳሽ የኃይል ምንጮች የሚመነጭ ንፁህ ኢነርጂ ወደ ሱዳን፣ ጅቡቲ፣ ኬንያ እና ታንዛኒያ በመላክ የኃይል ትስስር ፈጥራለች፡፡   5. የግል አልሚዎች ወደ ዘርፉ መግባት ዘርፉን ለማዘመን በተከናወኑ የፖሊሲ ማሻሻያዎች የሀገር ውስጥና የውጭ የግል አልሚዎች (Private Developers) በኃይል ማመንጨት ሥራ ላይ በር የሚከፍት የፖሊሲ ማዕቀፍ ተዘጋጅቷል።   በአጠቃላይ የታዳሽ ኃይል አማራጮችን ማስፋፋት የዜጎችን የዕለት ተዕለት ህይወት ከማሻሻሉም በላይ ሀገራችንን ወደ ተሻለ የኢንዱስትሪ እና የኢኮኖሚ እድገት የሚያሸጋግር የታሪካዊ ጉዞ አወንታዊ ማሳያ ነው። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content

የኤሌክትሪክ አቅርቦት ጥራትን ማሻሻል ….///…. በአንድ ሀገር ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እድገት ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት የሚጫወተው ሚና ወደር የለውም። የኤሌክትሪክ ኃይል ለኢንዱስትሪዎች
የኤሌክትሪክ አቅርቦት ጥራትን ማሻሻል  ….///…. በአንድ ሀገር ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እድገት ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት የሚጫወተው ሚና ወደር የለውም። የኤሌክትሪክ ኃይል ለኢንዱስትሪዎች መንቀሳቀስ፣ ለንግድ ተቋማት መስፋፋት፣ ለጤና እና ትምህርት አገልግሎቶች መዘመን እንዲሁም ለዜጎች የዕለት ተዕለት ህይወት መሻሻል ዋነኛ መሰረት ነው። ይሁንና ዘላቂና ሁለንተናዊ እድገትን ለማረጋገጥ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነትን ማስፋፋት እና የአገልግሎት ጥራትን ማሻሻል ትኩረት የሚፈልጉ ጉዳዮች ናቸው፡፡   የኤሌክትሪክ ተደራሽነት ማለት አገልግሎቱ ያልደረሳቸውን የህብረተሰብ ክፍሎች በተለይም በገጠርና ከከተሞች ራቅ ባሉ አካባቢዎች የሚኖሩ ዜጎችን ከዋናው ግሪድ የኃይል ተጠቃሚ ማድረግ ማለት ነው። ይህን ማድረግ ከተቻለ አገልግሎቱን ለሁሉም የህብረተሰብ ክፍል በፍትሐዊነት በማድረስ ማህበራዊ ፍትህን ለማረጋገጥ ያስችላል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኤሌክትሪክ-አቅርቦት-ጥራትን-ማሻሻል&lang=am "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 15 ቀን 2018 ዓ.ም

"ተቋሙ የሚያካሂዳቸው ግዥዎች ከህግ ጥሰትና ከሙስና የጸዱ መሆን አለባቸው” ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ….///…. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የግዥ ሂደቶች ከሕግ ጥሰትና ከሙስና የጸዱ፣ በረጅም ጊዜ
+9
"ተቋሙ የሚያካሂዳቸው ግዥዎች ከህግ ጥሰትና ከሙስና የጸዱ መሆን አለባቸው” ኢንጂነር አሸብር ባልቻ  ….///…. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የግዥ ሂደቶች ከሕግ ጥሰትና ከሙስና የጸዱ፣ በረጅም ጊዜ ዕቅድ ላይ የተመሠረቱ እና በቴክኖሎጂ የተደገፉ ሊሆኑ እንደሚገባ  የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ አሳሰቡ።   ለተቋሙ የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተቋሙ በሚያከናውናቸው የግዥ ሂደቶችና የአሠራር ማሻሻያዎች ላይ ትኩረት ያደረገ የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት ተካሂዷል።   የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ ላይ እንደገለጹት ሕግና መመሪያን የተከተለ የግዥ አሠራር ሂደት ለተቋማዊ ዕድገትና ለመልካም አስተዳደር ወሳኝ ነው። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ተቋሙ-የሚያካሂዳቸው-ግዥዎች-ከህግ-ጥሰት&lang=am "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 15 ቀን 2018 ዓ.ም

የተቋሙን የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች ተጠቃሚ የሚያደርግ የብድር አቅርቦት ስምምነት ተፈረመ ……..///…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለሥራ መሪዎቹና ሠራተኞቹ የረጅም ጊዜ የብድር አገልግሎት ለማቅ
+3
የተቋሙን የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች ተጠቃሚ የሚያደርግ የብድር አቅርቦት ስምምነት ተፈረመ ……..///…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለሥራ መሪዎቹና ሠራተኞቹ የረጅም ጊዜ የብድር አገልግሎት ለማቅረብ የሚያስችል የመግባቢያ ሥምምነት ከኦሮሚያ ህብረት ሥራ ባንክ ጋር ተፈራርሟል፡፡ ሥምምነቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እና የኦሮሚያ ህብረት ሥራ ባንክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደርቤ አስፋው ተፈራርመዋል፡፡ የተቋሙ የኮርፖሬት ፋይናንስና ሀብት አስተዳደር ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ ስለስምምነቱ እንደተናገሩት ተቋሙ ከፋይናንስ ተቋማት ጋር የሚፈጥረው አጋርነት የሠራተኞችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ከመፍታት ባሻገር ለወደፊት የፕሮጀክት ሥራዎች ማስፈፀሚያ የሚሆን የፋይናንስ ምንጭ ለማመቻቸት ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የተቋሙን-የሥራ-መሪዎችና-ሠራተኞች-ተጠቃ&lang=am "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 14 ቀን 2018 ዓ.ም

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የታችኞቹን ተፋሰስ ሀገራት ከጎርፍ አደጋ እየጠበቃቸው ነው ….///…. በአባይ ወንዝ ላይ የተገነባው የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የታችኞቹን የተፋሰስ ሀገራት በየዓመ
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የታችኞቹን ተፋሰስ ሀገራት ከጎርፍ አደጋ እየጠበቃቸው ነው ….///…. በአባይ ወንዝ ላይ የተገነባው የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የታችኞቹን የተፋሰስ ሀገራት በየዓመቱ ከሚደርስባቸው የጎርፍ አደጋ እና መፈናቀል እየጠበቃቸው መሆኑን በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የውኃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የሃይድሮሎጂ እና ውኃ ሀብት ተባባሪ ፕሮፌሰር ደመላሽ ወንድምአገኘሁ (ዶ/ር) ገለፁ። ደመላሽ (ዶ/ር) ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት ለረጅም ጊዜ የታችኞቹ የናይል ተፋሰስ ሀገራት በተለይም የሱዳን እና የግብፅ ሕዝቦች በክረምት ወቅት ለጎርፍ አደጋ፣ ለንብረት ውድመት እና መፈናቀል ይዳረጉ ነበር። የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መገንባት አፈር በከፍተኛ ጎርፍ ተጠርጎ እንዳይወስድ በማድረግ የታችኞቹ ሀገራት ውሃውን እና አፈሩን በተሻለ እና ውጤታማ በሆነ መንገድ እንዲጠቀሙበት እያገዛቸው መሆኑን አብራርተዋል።   ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ታላቁ-የኢትዮጵያ-ህዳሴ-ግድብ-የታችኞቹን&lang=am "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 14 ቀን 2018 ዓ.ም

የኤሌክትሪክ ግሪድ ዲጂታላይዜሽን ምንድነው? ....///..... የኤሌክትሪክ ግሪድ ዲጂታላይዜሽን ማለት የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት፣ ማስተላለፍና ማከፋፈል ሥርዓትን ዘመናዊ የዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን
የኤሌክትሪክ ግሪድ ዲጂታላይዜሽን ምንድነው?  ....///..... የኤሌክትሪክ ግሪድ ዲጂታላይዜሽን ማለት የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት፣ ማስተላለፍና ማከፋፈል ሥርዓትን ዘመናዊ የዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የበለጠ ቀልጣፋ፣ አስተማማኝና ዘመናዊ ማድረግ ነው። ይህ ሂደት ተለምዷዊውን የኤሌክትሪክ ግሪድ ከኢንተርኔት፣ ሴንሰሮች፣ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI)፣ ዳታ ትንተናና ሌሎች ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች ጋር በማዋሃድ እንደ “ስማርት አውታር” (Smart Grid) እንዲኖር የማድረግ ሂደት ነው።   ይህ አሰራር የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫዎችን፣ ማከፋፈያ ጣቢያዎችን እና የተጠቃሚዎችን ቆጣሪዎች በአንድ ዲጂታል ኔትወርክ በማገናኘት አጠቃላይ ስርዓቱ እርስ በእርሱ እንዲናበብና በራስ-ሰር (Automatically) እንዲቆጣጠር ያስችለዋል። በሌላ አገላለጽ፣ ዲጂታላይዜሽን የኤሌክትሪክ ግሪዱን “ባለ አእምሮ” ሥርዓት ያደርገዋል — ሥርዓቱ በራሱ መረጃ መሰብሰብ፣ መተንተንና በመተንተን ላይ ተመስርቶ ውሳኔ መስጠት ይችላል።   ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኤሌክትሪክ-ግሪድ-ዲጂታላይዜሽን-ምንድ&lang=am "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 13 ቀን 2018 ዓ.ም

የኤሌክትሪክ ግሪድ ዲጂታላይዜሽን ምንድነው? ....///..... የኤሌክትሪክ ግሪድ ዲጂታላይዜሽን ማለት የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት፣ ማስተላለፍና ማከፋፈል ሥርዓትን ዘመናዊ የዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን
የኤሌክትሪክ ግሪድ ዲጂታላይዜሽን ምንድነው?  ....///..... የኤሌክትሪክ ግሪድ ዲጂታላይዜሽን ማለት የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት፣ ማስተላለፍና ማከፋፈል ሥርዓትን ዘመናዊ የዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የበለጠ ቀልጣፋ፣ አስተማማኝና ዘመናዊ ማድረግ ነው። ይህ ሂደት ተለምዷዊውን የኤሌክትሪክ ግሪድ ከኢንተርኔት፣ ሴንሰሮች፣ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI)፣ ዳታ ትንተናና ሌሎች ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች ጋር በማዋሃድ እንደ “ስማርት አውታር” (Smart Grid) እንዲኖር የማድረግ ሂደት ነው።   ይህ አሰራር የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫዎችን፣ ማከፋፈያ ጣቢያዎችን እና የተጠቃሚዎችን ቆጣሪዎች በአንድ ዲጂታል ኔትወርክ በማገናኘት አጠቃላይ ስርዓቱ እርስ በእርሱ እንዲናበብና በራስ-ሰር (Automatically) እንዲቆጣጠር ያስችለዋል። በሌላ አገላለጽ፣ ዲጂታላይዜሽን የኤሌክትሪክ ግሪዱን “ባለ አእምሮ” ሥርዓት ያደርገዋል — ሥርዓቱ በራሱ መረጃ መሰብሰብ፣ መተንተንና በመተንተን ላይ ተመስርቶ ውሳኔ መስጠት ይችላል።   ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኤሌክትሪክ-ግሪድ-ዲጂታላይዜሽን-ምንድ&lang=am "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 13 ቀን 2018 ዓ.ም

ተቋሙ በጥናቱ ላይ ተመስርቶ አገልግሎት አሰጣጡን ለማዘመን ይሰራል ....///..... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚሰጠውን አገልግሎት በጥናት ላይ ተመስርቶ ለማዘመንና የተጣለበት ሀገራዊ ኃላፊነት
+6
ተቋሙ በጥናቱ ላይ ተመስርቶ አገልግሎት አሰጣጡን ለማዘመን ይሰራል ....///..... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚሰጠውን አገልግሎት በጥናት ላይ ተመስርቶ ለማዘመንና የተጣለበት ሀገራዊ ኃላፊነት በብቃት ለመወጣት ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ በተቋሙ የኢትዮ ፓወር አካዳሚ የምርምርና ልማት ሥራ አስኪያጅ አቶ ቢትወደድ ገብረአሊፍ ገለጹ፡፡ በደንበኞች እርካታ፣ በድርጅታዊ ባህል፣ በሠራተኞች የሥራ እርካታ እና ተሳትፎ ዙሪያ በኢትዮ ፓወር አካዳሚ እና በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የምርምርና የልማት ቡድን በጋራ የተከናወኑ ጥናቶች ለተቋሙ አመራሮች ቀርቧል፡፡ በውይይት መድረኩ ላይ የጥናቶቹ ዓላማ፣ ስልትና ሞዴል፣ የመረጃ አሰባሰብ ዘዴዎች፣ የናሙና አወሳሰድ፣ ንጽጽር፣ ግኝትና ምክረ ሀሳቦች በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ መምህራን ቀርበዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ተቋሙ-በጥናቱ-ላይ-ተመስርቶ-አገልግሎት-አ&lang=am "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 13 ቀን 2018 ዓ.ም

የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተደራሽነት እና አስተማማኝነት - ለእድገት ......///....... የኤሌክትሪክ አቅርቦት ተደራሽነት (accessibility) እና አስተማማኝነት (dependability) የ
የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተደራሽነት እና አስተማማኝነት - ለእድገት ......///....... የኤሌክትሪክ አቅርቦት ተደራሽነት (accessibility) እና አስተማማኝነት (dependability) የማህበረ-ኢኮኖሚያዊ ትራንስፎርሜሽን ቁልፍ ሞተሮች እና የዘመናዊ እድገት መለኪያ ጠቋሚዎች ናቸው። ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ለማሳለጥ፣ የዜጎችን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል እና ቀጣይነት ያለው ልማትን ለማረጋገጥ ወሳኝ መሠረቶች ናቸው። በልማት ኤኮኖሚክስ እና በኃይል ፖሊሲ ዘርፍ የተደረጉ ጥናቶች እንደሚያመለክቱት አስተማማኝ እና ፍትሐዊ የኃይል አቅርቦት የኢንዱስትሪ ምርታማነትን ለማሳደግ፣ የሰው ኃይል አቅምን ለማጎልበት እና የተቀናጀ ሀገራዊ ዘላቂ የልማት ለማሳካት አስፈላጊ ግብዓት ነው።   1. የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተደራሽነት (Accessibility) የኤሌክትሪክ ተደራሽነት ማለት አገልግሎቱን በከተማም ሆነ በገጠር ለሁሉም የህብረተሰብ ክፍል በፍትሐዊነት፣ በጥራት እና በተመጣጣኝ ዋጋ ማድረስን የሚያመለክት .... ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኤሌክትሪክ-አገልግሎት-ተደራሽነት-እና&lang=am "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 12 ቀን 2018 ዓ.ም

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ ......///....... ለበለጠ መረጃ .... 👇 https://www.eep.com.et/?amh-announcement=የፈተና-ጥሪ-ማስታወቂያ-5&lang=am "ንፁህ ኢነርጂ
+9
የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ ......///....... ለበለጠ መረጃ .... 👇 https://www.eep.com.et/?amh-announcement=የፈተና-ጥሪ-ማስታወቂያ-5&lang=am "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 12 ቀን 2018 ዓ.ም

ጥናቱ ለተቋሙ አመራሮች እየቀረበ ነው ….….///….…. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢትዮ ፓወር አካዳሚ እና በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የምርምርና የልማት ቡድን በጋራ የተከናወነው ጥናት ለተቋሙ አ
+6
ጥናቱ ለተቋሙ አመራሮች እየቀረበ ነው ….….///….…. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢትዮ ፓወር አካዳሚ እና በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የምርምርና የልማት ቡድን በጋራ የተከናወነው ጥናት ለተቋሙ አመራሮች እየቀረበ ነው፡፡ የኢትዮ ፓወር አካዳሚ ዳይሬክተር ዶ/ር ወንዶሰን ካሳ ጥናቱ በደንበኞች እርካታ፣ በድርጅታዊ ባህል፣ በሠራተኞች የሥራ እርካታ እና በተሳትፎ ደረጃ ላይ ትኩረት ያደረገ ነው፡፡ ጥናቱ የአገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል፣ ድርጅታዊ ባህልን ለማጠናከር እና የበለጠ ቁርጠኝና ደስተኛ ሠራተኛን ለመገንባት የሚያግዝ ስለመሆኑም ገልጸዋል። መድረኩ ከተቋሙ አመራር በጥናቱ ላይ ግብረ መልስ ለማሰባሰብና እና በቀጣይ በጥናቱ ግኝት አፈጻጸም ላይ የባለቤትነት ስሜት ለመፍጠር ያለመ መሆኑን ዳይሬክተሩ ገልጸዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 12 ቀን 2018 ዓ.ም

ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ ......///....... "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/E
ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ ......///....... "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 11 ቀን 2018 ዓ.ም

የብሔራዊ ኤሌክትሪክ ግሪድ ሚና .....///..... ብሔራዊ ኤሌክትሪክ ግሪድ በሀገሪቱ ውስጥ የሚመረት ማናቸውንም የኃይል አቅርቦት በደህንነት፣ በጥራት እና በብቃት ለአገልግሎት ለማዋል የሚያስችል
የብሔራዊ ኤሌክትሪክ ግሪድ ሚና  .....///..... ብሔራዊ ኤሌክትሪክ ግሪድ በሀገሪቱ ውስጥ የሚመረት ማናቸውንም የኃይል አቅርቦት በደህንነት፣ በጥራት እና በብቃት ለአገልግሎት ለማዋል የሚያስችል ሀገራዊ የኃይል ኔትወርክ ነው። ይህ ኔትወርክ በልዩ ልዩ አካባቢዎች የሚገኙ የውሃ፣ የነፋስ፣ የፀሐይ እና የጂኦተርማል ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችን ወደ አንድ ማዕከላዊ ሥርዓት ያገናኛል።   ዋነኛ ተግባራት፦ ኃይል ማጓጓዝ፦ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በሚገኙ ከፍተኛ ቮልቴጅ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች አማካይነት ኤሌክትሪክን ከተመረተበት ቦታ ወደ ሩቅ ከተሞችና የኢንዱስትሪ ማዕከላት ያጓጉዛል። ፍላጎትና አቅርቦትን ማመጣጠን፦ በየቀኑ እና በየሰዓቱ የሚቀያየረውን የኤሌክትሪክ ፍላጎት (Demand) እና ማመንጫዎች የሚያቀርቡትን ኃይል (Supply) በማመጣጠን የኃይል መቋረጥን ይከላከላል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የብሔራዊ-ኤሌክትሪክ-ግሪድ-ሚና&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 11 ቀን 2018 ዓ.ም

አረንጓዴ አሻራ - ለዘላቂ የኃይል ዋስትና .....///..... በኢትዮጵያ በየዓመቱ የሚካሄደው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የአካባቢ ጥበቃ እና የደን ሽፋን ማሳደጊያ ስልት ብቻ አይደለም። ከዚህ
አረንጓዴ አሻራ - ለዘላቂ የኃይል ዋስትና  .....///..... በኢትዮጵያ በየዓመቱ የሚካሄደው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የአካባቢ ጥበቃ እና የደን ሽፋን ማሳደጊያ ስልት ብቻ አይደለም። ከዚህ ባሻገር የሀገሪቱን የኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት ለሆኑት የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድቦች ህልውና እና ዘላቂነት እጅግ ወሳኝ የሆነ ግብዓት ነው። ከ90% በላይ የሚሆነውን የኤሌክትሪክ ኃይል ከውሃ የምታመነጨው ኢትዮጵያ የግድቦቿን ህልውና ለማስጠበቅ እና አቅማቸውን ለማጎልበት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ከግድቦች ደህንነት እና ጥበቃ ጋር በቀጥታ የተሳሰረ ነው።  የአረንጓዴ አሻራ ከአባባቢ ጥበቃ በዘለለ በርካታ ጠቀሜታዎች ይኖሩታል፡፡ 1. የደለል ክምችትን የመከላከል ሚና የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድቦች በአግባቡ ኃይል እንዳያመነጩ ከሚያደርጓቸው ችግሮች መካከል አንዱ የደለል ክምችት ነው። የደን ጭፍጨፋ እና የአፈር መሸርሸር በሚኖርበት ጊዜ ከባድ የክረምት ዝናብ ለም አፈርን እያጠበ ወደ ወንዞች እና በቀጥታ ወደ ግድቦች እንዲገባ ያደርጋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=አረንጓዴ-አሻራ-ለዘላቂ-የኃይል-ዋስትና&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 9 ቀን 2018 ዓ.ም

የኤልኒኖ (El Nino) ክስተት እና የኃይል አቅርቦት ብዙ ጊዜ የኤልኒኖ ክስተት ሲነሳ አእምሯችን ወደ ድርቅ፣ የምግብ እጥረት እና የግብርና መስተጓጎል ያደላል። ነገር ግን ኤልኒኖ ከአየር ጠባይ መ
የኤልኒኖ (El Nino) ክስተት እና የኃይል አቅርቦት   ብዙ ጊዜ የኤልኒኖ ክስተት ሲነሳ አእምሯችን ወደ ድርቅ፣ የምግብ እጥረት እና የግብርና መስተጓጎል ያደላል። ነገር ግን ኤልኒኖ ከአየር ጠባይ መዛባት ባሻገር በቀጥታ ከምንጠቀመው የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት እና ደህንነት ጋር እጅግ ጥብቅ የሆነ ትስስር አለው። በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አብዛኛው የኤሌክትሪክ ኃይላቸውን ከውሃ (Hydropower) በሚያመነጩ ሀገራት ላይ የኤልኒኖ መከሰት በኃይል አቅርቦት ስርዓቱ ላይ ግዙፍ ፈተና ይደቅናል።   1. የኤልኒኖ ክስተት ምንድን ነው? ኤልኒኖ በፓሲፊክ ውቅያኖስ አካባቢ የሚከሰት የአየር ጠባይ መዛባት ሲሆን የውቅያኖሱ ወለል የሙቀት መጠን ከተለመደው በላይ ሲጨምር የሚከሰት ነው። ይህ የሙቀት መጨመር፡- ·         የዓለም አቀፍ የንፋስና የዝናብ ስርጭትን ያዛባል። ኢትዮጵያን ጨምሮ በምስራቅ አፍሪካ የክረምት ዝናብ ስርጭትን በመቀነስ ለከፍተኛ ድርቅ እና የውሃ እጥረት ይዳርጋል። በሌሎች የዓለም ክፍሎችም ያልተለመደ ከባድ ጎርፍ ያስከትላል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኤልኒኖ-el-nino-ክስተት-እና-የኃይል-አቅርቦት&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 8 ቀን 2018 ዓ.ም

ከማብሪያና ማጥፊያ የሚዘለው የብርሃን ጉዞ ……///…….. ብዙዎቻችን ቤታችን ስንገባ እንደምናገኘው የማብሪያና ማጥፊያ ቁልፍ ኃይልን የምናገኝበት እና ሲቋረጥም ወደነበረበት የምንመልስበት ሂደት ቀላል
ከማብሪያና ማጥፊያ የሚዘለው የብርሃን ጉዞ  ……///…….. ብዙዎቻችን ቤታችን ስንገባ እንደምናገኘው የማብሪያና ማጥፊያ ቁልፍ ኃይልን የምናገኝበት እና ሲቋረጥም ወደነበረበት የምንመልስበት ሂደት ቀላልና አፍታ የማይወስድ ተግባር ይመስለናል። ነገር ግን ማብሪያና ማጥፊያውን በተጫንንበት ቅጽበት በቤታችን ወይም በሥራ ቦታችን የሚበራው የኤሌክትሪክ ኃይል እኛ ዘንድ ለመድረስ የሚያልፍበት መንገድ እጅግ ውስብስብ፣ አደገኛ እና በሺዎች የሚቆጠሩ የዘርፉ ባለሙያዎችን የሌሊትና ቀን የማይቋረጥ አድካሚ ጥረት የሚጠይቅ መሆኑን ምን ያህል እንረዳለን፡፡   በሸለቆዎችና በበረሃዎች የሚጀመር የኃይል ማመንጨት ሂደት የኃይል አቅርቦት ጉዞው የሚጀምረው ከኃይል ማመንጫዎች ነው። በኢትዮጵያ አብዛኞቹ የውሃ ኃይል ማመንጫዎች የሚገኙት ከመኖሪያ በራቁ አካባቢዎች፣ ከፍተኛ ንፋስና ሙቀት ባለባቸው በረሃዎች እና ሸለቆዎች ውስጥ ነው። በእነዚህ አስቸጋሪ አየር ጠባይና መልክዐ ምድር ውስጥ የሚሰሩ መሐንዲሶችና ቴክኒሻኖች ግዙፍ የውሃ እና የንፋስ ተርባይኖችንና ጄነሬተሮችን በከፍተኛ ጥንቃቄ... ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ከማብሪያና-ማጥፊያ-የሚዘለው-የብርሃን-ጉ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 7 ቀን 2018 ዓ.ም