የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️
Відкрити в Telegram
4 889
Підписники
-25624 години
-1 8217 днів
-3 02830 день
Архів дописів
ሐሙስ ማለዳ! ሚያዝያ 12/2015 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች
1፤ መከላከያ ሠራዊት ትናንት ዲሽቃ፣ ሞርታርና ሌሎች የቡድን ጦር መሳሪያዎችን ከሕወሃት መረከብ መጀመሩን ፋና ብሮድካስት ዘግቧል። የቡድን ጦር መሳሪያዎቹ ልዩ ስሙ ደንጎላት በተባለ ቦታ ላይ የተሰበሰቡ እንደኾኑ ዘገባው ጠቅሷል። የቡድን መሳሪያዎች ርክክብ እስከ ሚያዝያ 16 ይቀጥላል መባሉን ዘገባው ጠቅሷል። ሠራዊቱ በመጀመሪያው ዙር ከባድ የጦር መሳሪያዎችንና በሁለተኛው ዙር የአየር ኃይል መሳሪያዎችን ከሕወሃት ኃይሎች መረከቡ ይታወሳል።
2፤ የቡድን 7 አገራት ውጭ ጉዳይ ሚንስትሮች የኢትዮጵያ መንግሥት ለሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት የጀመረው የሽግግር ፍትህ ሂደት እንዲጠናከር፣ ተጠያቂነት እንዲሠፍንና የሰብዓዊ መብት ጥሰት ተቆጣጣሪዎች በነጻነት እንዲንቀሳቀሱ ባወጡት መግለጫ አሳስበዋል። ውጭ ጉዳይ ሚንስትሮቹ፣ አፍሪካ ኅብረት በኢትዮጵያ ፌደራል መንግሥትና በሕወሃት መካከል የሰላም ስምምነት እንዲደፈረም ያደረገውን አዎንታዊ ጥረት በመግለጫቸው አድንቀዋል። የቡድን-7 ውጭ ጉዳይ ሚንስትሮች ይህን ያሉት፣ በጃፓን ሒሮሺማ ከተማ ባደረጉት ስብሰባ ላይ ባወጡት መግለጫ ነው።
3፤ የተመድ ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ትግራይን እንዳይጎበኙ የኢትዮጵያ መንግሥት አግዷቸዋል ተብሎ ስለወጣው መረጃ ቃል አቀባያቸው ስቲፋኒ ዱጃሪች ትናንት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተጠይቀው ነበር። ኾኖም ዱጃሪች ጥያቄውን በቀጥታ በመመለስ ፋንታ፣ ጉተሬዝ ወደ ኢትዮጵያ በሄዱበት ወቅት ወደ ትግራይ እንዳልሄዱ በወቅቱ ግልጽ አድርገናል በማለት መልሰዋል። ጉተሬዝ ባለፈው የካቲት በአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ወደ ኢትዮጵያ በተጓዙበት ወቅት፣ ትግራይን እንዳይጎበኙ መንግሥት እንደከለከላቸው ዋሽንግተን ፖስት ከአሜሪካ መንግሥት ያፈተለኩ የስለላ መረጃዎችን ጠቅሶ ትናንት ዘግቦ ነበር።
4፤ የኬንያው ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ የሱዳኑ ግጭት ዓለማቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ሕግጋት የሚጣሱበት ደረጃ ላይ ደርሷል ሲሉ በማለት ተናግረዋል። ሩቶ፣ የሱዳን ጀኔራሎች ግጭቱ ከአገሪቱ ድንበር አልፎ የቀጠናው ስጋት እንዲኾን የሚያደርግ ኹኔታ ፈጥረዋል አስጠንቅቀዋል።.ካርቱም ውስጥ ሕዝብ በሚኖርባቸው መንደሮች ውጊያ እየተካሄደ መኾኑንና በውጭ ዲፕሎማቲክ አካላት ላይ የተፈጸሙ ጥቃቶችን ሩቶ በአስረጅነት ጠቅሰዋል። ሩቶ እና የጅቡቲውና የደቡብ ሱዳኑ አቻቸው ለግጭቱ ሰላማዊ መፍትሄ ለመፈለግ ትናንት ካርቱም ለመሄድ ይዘውት የነበረው ዕቅድ ሳይሳካ ቀርቷል።
5፤ የሱዳን ጦር ሠራዊትና ፈጥኖ ደራሽ ሠራዊት ለ24 ሰዓት ተኩስ አቁም ለማድረግ ትናንት ምሽት ላይ ለሁለተኛ ጊዜ በተናጥል የደረሱበት ስምምነት በድጋሚ እንደተጣሰ የውጭ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። የ24 ሰዓታት ተኩስ አቁም ለማድረግ ቀድሞ ዝግጁነቱን የገለጠው ፈጥኖ ደራሽ ሠራዊት ሲሆን፣ ጦር ሠራዊቱም ዘግየት ብሎ ፍቃደኛነቱን አሳውቆ ነበር። #ሼር በማድረግ ተባበሩን🙏
👉ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ👇👇👇
መንግሥት እና ህወሃት ጥቅምት 23 ቀን 2015 ዓ.ም በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ የተፈራረሙትን የሰላም ስምምነት ተግባራዊ የማድረግ አካል የሆነው የህወሃት ታጣቂዎችን ትጥቅ የማስፈታት ስራ እየተከናወነ ይገኛል።
በስምምነቱ መሰረትም የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት በመጀመሪያው ዙር ትጥቅ የማስፈታት ሂደት ከባድ መሣሪያዎችን በሁለተኛው ዙር ደግሞ የአየር ኃይል መሳሪያዎችን ከህወሃት መረከቡ ይታወቃል።
ባለፈው ሳምንት ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር አመራሮች ጋር ትጥቅ ማስፈታት ሂደቱ ላይ ውይይት ያደረጉት የብሔራዊ ተሐድሶ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ብርጋዴር ጀኔራል ደርቤ መኩሪያ ከዚህ ሳምንት ጀምሮ እስከ ሚያዚያ 16 የቡድን መሳሪያዎች ርክክብ እንደሚደረግ ገልጸው ነበር።
በዚሁ መሰረት በዛሬው ዕለት ደንጎላት የተሠበሠቡ የተለያዩ ቡድን መሳሪያዎች የመከላከያ ሠራዊት እና የህወሃት ተወካዮች በተገኙበት የመጀመሪያ ዙር የቡድን መሳሪያዎች ርክክብ መደረጉን ብርጋዴር ጀኔራል ደርቤ ተናግረዋል።
በቀጣይ ቀናትም በተለያዩ ካምፖች የሚገኙ የቡድን መሳሪያዎች ርክክብ እንደሚፈጸም ጠቁመዋል።
በስፍራው የተገኙት የመከላከያ ሠራዊት ተወካይ ኮሎኔል ጉደታ ኦፍካ፤ በዛሬው ዕለት ሞርታር ዲሽቃና መሰል በርካታ የቡድን መሳሪያዎችን መረከባቸውን ገልጸዋል።
የህወሃት ተወካይ ሙሉጌታ ገብረ ክርስቶስ በበኩላቸው በስምምንቱ መሰረት የህወሃት ታጣቂዎች የቡድን መሳሪያዎችን በመፍታት ለመከላከያ ሰራዊት እያስረከቡ መሆኑን ገልጸዋል።
ተወካዮቹ አክለውም የትጥቅ ማስፍታት ሂደቱ በመልካም ሁኔታ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸው መንግስት እና ህወሃትም ለሰላም ስምምነቱ ተፈጻሚነት አዎንታዊ እርምጃዎችን እየወሰዱ ነው ብለዋል።
የሰላም ስምምነቱ አተገባበርም ለሀገር ዘላቂ ሰላምን ለማምጣት ተስፋ የሚጣልበት ሆኗል ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
#Update
በጎረቤት ሱዳን ያለው ውጊያ ዛሬ ለሶስተኛ ቀን መቀጠሉን ለማወቅ ተችሏል።
ከካርቱም ጨምሮ ከሌሎች ከተሞች በወጡ መረጃዎች ዛሬም በከባባድ መሳሪያ የታገዘ የከተማ ውስጥ ውጊያ እየተካሄደ ነው።
በተለይም በካርቱም ሰሜናዊ እና ደቡባዊ ክፍል የከባድ መሳሪያ ውጊያ እንዳለ ተነግሯል።
የሠራዊቱ ጠቅላይ ዋና መሥሪያ ቤት በር ፊት ለፊት ውጊያ እየተካሄደ ሲሆን አርኤስኤፍ (RSF) ከቅዳሜ ጀምሮ ይህንን ትልቅ የሰራዊት ተቋም ለመቆጣጠር እየሞከረ ነው ተብሏል።
ይህንን ተቋም መቆጣጠር በራሱ ሰራዊቱን እንደመቆጣጠር ነው የሚታሰበው።
በሌላ በኩል ፤ በሜሮዌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ አካባቢ ግጭት መኖሩ ተገልጿል። ይህ ግጭት እንደገና የተቀሰቀሰ ሲሆን የከባድ መሳሪያ ድምፆችም ይሰማሉ ተብሏል።
በሜሮዌ የሚገኙ ሆስፒታሎች በተጎዱ ሰዎች የተሞሉ መሆናቸውን ከህክምና ምንጮች ለማወቅ መቻሉን አልጀዚራ ዘግቧል።
ተጨማሪ መረጃዎች ፦
- በካርቱም ውጊያ በመኖሪያ መንደሮች ጭምር እየተደረገ ነው።
- በሱዳን ባለፉት ሶስት ቀን የሞቱ ሰላማዊ ሰዎች ከ100 ተሻገረዋል። እጅግ በጣም በርካታ ሰዎች ተጎድተው ሆስፒታሎች ተጨናንቀዋል።
- የRSF የፖለቲካ አማካሪ የሱፍ ኢዛት ለአልጀዚራ በሰጡት ቃል ማንኛውም የተኩስ አቁም ለማድረግ በሠራዊቱ ውስጥ የ "አመራር መኖር"ን ይጠይቃል ብለዋል። " ሠራዊቱ ምንም ዓይነት አመራር የለውም። " ያሉት አማካሪው " የተኩስ አቁም መቼ እንደሚሆን የምንወስነው እኛ ብቻ ነን " ብለዋል።
- RSF " ወንጀለኛ ናቸው " ሲል የጠራቸውን አልቡርሃንን በቁጥጥር ስር ለማዋል ፍለጋ ላይ መሆኑን አሳውቋል።
- በጄነራል ቡርሃን የሚመራው የሱዳን ጦር የRSF ሚሊሻዎች ሰላማዊ ሰዎችን ከለላ አድርገው እየተንቀሳቀሱ መሆኑን በመግለፅ ሰላማዊ ሰዎች እንዳይጎዱ ጥብቅ በሆነ ወታደራዊ ጥንቃቄ ኦፕሬሽኑን እየሰራ መሆኑን ገልጿል።
በጃዊ ወረዳ በፈንደቃ ከተማ የተቀነባበረ የጥፋት ሃይሎች ሴራ በመከላከያ ሠራዊቱ መክሸፉን ኮሎኔል መልካሙ በየነ ገለፁ።
ኮሎኔል መልካሙ በየነ እንዳሉት በከተማው የታጠቁ ሃይሎች በመግስት እና በሕዝብ ተቋማት ላይ ውድመት እና ዘረፋ ለማድረስ ቢንቀሳቀሱም በአካባቢው የሚገኝ የሜካናይዝድ ክፍለጦር በፍጥነት ወደ አካባቢው በመገስገስ የተቀነባበረውን የጥፋት ሴራ መቆጣጠር ተችሏል።
የጥፋት ሃይሎች በተቀናጀ መልኩ የቡድን እና የነፍስ ወከፍ መሳሪያዎችን በሕገ ወጥ በመታጠቅ በመንግስት እና በህዝብ ተቋማት ላይ ጥቃት ማድረስ ብሎም በስኳር ፋብሪካው የሚገኙ የውጭ ዜጎች ተረጋግተው ስራቸውን እንዳይሰሩ ማድረግ የጥፋት ሃይሉ እቅድ እንደነበር ኮሎኔል መልካሙ በየነ ገልፀዋል፡፡
በአካባቢው በአሁኑ ሥዕት የሜካናይዝድ እና እግረኛ ክፍለጦሮች ግዳጃቸው በአግባቡ እየፈፀሙ ሲሆን በወረዳው በተለያዩ ጊዜ የሚከሰቱ የጥፋት ሴራዊችን በዘላቂነት ለማስወገድ ያፈነገጡ የጥፋት ሃይሎች በሰማዊ መንገድ ትጥቅ እንዲፈቱ በአገር ሽማግሌዎች እና በሃይማኖት አባቶች እንዲሁም ከተለያዩ አካላት ጋር መግባባት ተደርሷል፡፡
በሌላ ዜና በጃዊ ወረዳ ለሚገኙ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ለበአል መዋያ የሚሆን 06 የእርድ ሰንጋ በስጦታ መልክ ከፈንደቃ ከተማ ነዋሪዎች ተበርክቶላቸዋል፡፡
ለሰራዊቱ የተደርገውን ድጋፍ በመረከብ ምስጋና ያቀረቡት ሻምበል ባምላኩ ጨመረ የተደረገው ድጋፍ ህዝቡ ለሠራዊቱ ያለውን መልካም ነገር የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል።
የአካባቢው ማሕበረሰብ በግዳጅ ቀጠና ከሚያደርግልን ድጋፍ በተጨማሪ ሰራዊቱ በበአል ወቅት በቤተሰብ ናፍቆት ሳይጎዳ በግዳጅ ቀጠናው ደስተኛ ሆኖ በአልን እንዲያሳልፍ ታሳቢ የተደረገ ነው ሲሉ ሻምበል ባምላኩ ተናግረዋል።
የፈንደቃ ከተማ ምክትል አስተዳዳሪ በበኩላቸው ለጀግናው ሰራዊታችን የተደረገው የሠንጋ ድጋፍ ሕዝባዊ ወገንተኝነታችንን እና ከስራዊታችን ጎን መሆናችንን የሚያረጋግጥ ነው ሲሉ ተናግረዋል።
ግብፅ በሱዳን የሚገኙ ወታደሮቿን ደህንነት ለማስጠበቅ በተጠንቀቅ ላይ እንደሆነች አስታወቀች
---------------------
በሃምዳን ደጋሎ የሚመራው የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ጦር በሜሮዌ ከተማ ሰፍረው የነበሩ የግብፅ አየር ሃይል ሰራዊት አባላትን መማረኩን ካስታወቀ በኋላ የግብፅ መንግሰት ማምሻውን መግለጫ አውጥቷል።
መግለጫው ግብፅ ከሱዳን ጋረሰ ታደርግ በነበረው የጋር ወታደራዊ ልምምድ በሱዳን የሚገኙ ወታደሮቿ አሁን በተቀሰቀሰው ጦርነት ደህንነታቸው አደጋ ላይ መሆኑን የተጠቆመ ሲሆን ፤ የሰራዊት አባሎቿን ለመታደግ ከሚመለከታቸው የሱዳን ወታደራዊ ሃላፊዎች ጋር እየተሰራ መሆኑም ተገልጿል።
የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ሰራዊት ዛሬ ወደ ለየለት ውጊያ ከሃገሪቱ ጦር ጋር ከመግባቱ በፊት በቅድሚያ ከሰፈረባቸው ቁልፍ አካባቢዎች አንዱ ከግብፅ ድንበር 200ኪሜ ርቀት ላይ የሚገኘውን እና የግብፅ ሰራዊት ጦር ሰፈር የሚገኝበት የሜሮዌ ከተማ ነበር።
የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ሃይል ይህን ያደረገበት ዋናው ምክኒያት ከአልቡርሃን ሰራዊት የግብፅ ወታደሮችን እገዛ እንዳያገኝ ለመቁረጥ እና በጦር ሰፈሩ የሚገኘውን የአየር ሃይል በቁጥጥር ስር ለማዋል እንደነበር እየተገለፀ ነው።
ግብፅ በሱዳን እየሆነ ያለውን በቅርብ እየተከታተልኩ ነው የሚል ድፍን ያለ መግለጫ ታውጣ እንጂ አልቡርሃንን ለመታደግ ሌሎች ሽፋን ምክኒያቶችን በማስቀመጥ ሰራዊቷን ልታዘምት ትችላለች የሚል ግምት ያላቸው አካላት በዝተዋል።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሚያዚያ 07 ቀን 2015 ዓ.ም
''የክልል ልዩ ሀይሎችን መልሶ ማደራጀቱ ህብረ-ብሄራዊ ሰራዊት ለመገንባት ሚናው የጎላ ነው።''
ኮሎኔል ጌትነት አዳነ
የመከላከያ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር
ወቅታዊ ሁኔታዎችን መነሻ አድርገው ኮሎኔል ጌትነት አዳነ በሚከተሉት ዋና ዋና ነጥቦች ላይ መግለጫ ሰጥተዋል።
~ በአሁኑ ጊዜ እየተተገበረ ያለው የየክልሎችን ልዩ ሀይሎች መልሶ የማደራጀት ተግባር በኢፌዴሪ ህገመንግስት በተቀመጠው አንቀፅ-87 መሰረት ሚዛናዊ ተዋፅኦን ያካተተ ህብረ-ብሄራዊ ሰራዊት ለመገንባት የሚያግዝ ሂደት ነው።
~ በሁሉም ክልሎች እየተከናወነ ባለው መሰረት የየክልሉ ልዩ ሀይሎች ወደመረጡት እንዲገቡ ከተደረገ በኋላ አስፈላጊውን የማዋሃድ ስልጠና ተሰጥቷቸው እንደየ አደረጃጀቱ በሚሰጣቸው መሰረት የሚሰማሩ ይሆናል።
~ የክልል ልዩ ኃይሎችን መልሶ ለማደራጀት እንቅስቃሴ መጀመሩን ተከትሎ አንዳንድ አካላት በተቀናጀ መልኩ የህዝባችንን አንድነት የሚሸረሽሩና የፀጥታ ሀይሎችን የተልዕኮ አፈፃፀም የሚያናጉ ሀሰተኛ መረጃዎች በማሰራጨት ላይ ናቸው፡፡
~ ከክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ እና ከክቡር ጄኔራል አበባው ታደሰ ጀምሮ የመከላከያ ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮችን የትውልድ አካባቢ እና የወጡበትን ህዝብ በማንሳት በመለየት የማጥላላትና አላስፈላጊ ተቀፅላ በመስጠት ላይ የተሰማሩ አፍራሽ አካላት በተቋሙ መሪዎች ላይ የሚሰነዝሩት ማንኛውም የስም ማጥፋት ዘመቻ አገር እንደማፍረስ ይቆጠራል።
~ የሁሉም ክልሎች የሚመለከታቸው አካላት የእስካሁኑን ሂደት ገምግመው በደረሱበት ውሳኔ መሰረት ከዛሬ ጀምሮ የየትኛውንም ክልል ልዩ ሀይሎች ወታደራዊ አልባሳት ፣ ስምና መለዬ የሚሰጥና የሚፈፀም ግዳጅ አይኖርም።
~ የመከላከያ ሰራዊቱ ከቦታ ቦታ ተንቀሳቅሶ ግዳጁን እንዳይፈፅም የሚያደርጉ ተግባራት በመፈፀም ላይ ሲሆኑ ሰራዊቱ ከዚህ በፊት በፈፀማቸው አገር የማዳን ተልዕኮዎች ሁሉ ሲደግፈው የነበረው ህዝብ በሰራዊቱ ላይ መጠራጠር እንዲያድርበት የሚያደርጉ ነጣጣይ ዝንባሌዎች ላይ የተሰማሩ አካላት ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ ይገባል።
~ በአንዳንድ ሀላፊነት በጎደላቸው የማህበረሰብ አንቂ ነን ባዬች በሚዘወሩ የማህበራዊ ትስስር ገፆች አማካኝነት እየተሰነዘሩ ያሉ አፍራሽ ትችት ፣ ወቀሳና አላስፈላጊ የሆኑ ስም መስጠቶች ተቀባይነት የላቸውም።
~ ከዚህ በኋላ ማንኛውም የማይመለከተው አካል በየትኛውም አካባቢ የመከላከያ ሰራዊቱን የደምብ አልባሳት ይዞ ወይም ለብሶ መገኘት የሰራዊቱን ተልዕኮ እንደመቃረን ይቆጠራል።
~ የሰራዊቱን የዕዝ ሰንሰለት የሚያናጉ እኩይ ዓላማ አንግበው በሚንቀሳቀሱ እና ሰራዊቱ ትናንት የፈፀማቸውን ተግባራት በሚያጥላሉ ጉዳዬች በተሰማሩ አካላት ላይ በህግ አግባብ አስፈላጊው እርምጃ ይወሰዳል።
በመጨረሻም:-
~ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ልክ እንደወትሮው ሁሉ አሁንም ወደፊትም ማንኛውንም የመስዋዕትነት ዋጋ ከፍሎ የአገራችንን ሉዓላዊነት ለማስከበር እና የህዝባችንን ዙሪያ መለስ ክብርና ጥቅም ለማስጠበቅ የተሟላ ብቃት ላይ እንደሚገኝ አረጋግጠዋል።
#ተነስቷል ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለትንሣኤ በዓል አደረሳችሁ፣ አደረሰን!
መልካም በዓል!
በትግራይ ክልል “የቡድን ትጥቆችን የማስረከብ ሂደት” ከመጪው ሰኞ ጀምሮ እንደሚከናወን የተሃድሶ ኮሚሽን አስታወቀ!
በትግራይ ክልል የሚገኙ የቡድን ትጥቆችን ሰብስቦ ለመከላከያ ሰራዊት የማስረከብ ሂደት በመጪው ሰኞ ሚያዝያ 9፤ 2015 እንደሚጀመር ብሔራዊ የተሃድሶ ኮሚሽን አስታወቀ። የኢትዮጵያ ጎረቤት በሆነችው ሱዳን ሀገር የሚገኙ ኃይሎችን ጨምሮ በተለያዩ ቦታዎች ያሉ የትግራይ ታጣቂዎችን የማሰባሰብ ስራም በአጭር ጊዜ እንደሚጀምር ኮሚሽኑ ገልጿል።
የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽኑ ይህን የገለጸው፤ ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች ጋር ከተወያየ በኋላ ትላንት አርብ በሰጠው መግለጫ ነው። የተሃድሶ ኮሚሽኑን በኮሚሽነርነት የሚመሩት ተሾመ ቶጋ እና ሁለት ምክትሎቻቸው የተገኙበት ይህ ውይይት፤ በውጊያ ላይ የቆዩ ኃይሎችን “ትጥቅ የማስፈታት፣ እንዲበተኑ የማድረግ እና እንደገና ወደ ህብረተሰቡ የመዋሃድ” ሂደትን በተመለከተ “ቀሪ ስራዎችን በፍጥነት ማጠናቀቅ” ላይ ትኩረት ያደረገ ነበር ተብሏል።
የቀድሞ ታጣቂዎችን እንዲበተኑ ከማድረግ በፊት መጠናቀቅ ያለበት አንዱ ስራ “ትጥቅ ማስፈታት” መሆኑን በመግለጫው የጠቀሱት ኮሚሽነር ተሾመ ቶጋ፤ እስካሁን የተከናወነው እንደተጠበቀ ሆኖ “የቡድን መሳሪያዎችን የማስረከብ ስራ ቶሎ መጠናቀቅ እንዳለበት” ከስምምነት ላይ መደረሱን አስታውቀዋል። የቡድን መሳሪያዎችን የማስረከብ ሂደቱ፤ “ከሰኞ ጀምሮ በጣም ባጠረ ጊዜ ውስጥ እንደሚጠናቀቅም” ገልጸዋል።
የሃምዳን ደጋሎ ሰራዊት በሰሜን ሱዳን ሰፍረው የነበሩ የግብፅ ወታደሮችን መማረኩን አስታወቀ
-------------------
🔹ወታደሮቹ ኢትዮጵያ ለማስፈራራት እና የአልቡርሃንን መንግሰት ለመደገፍ በሚል ሰፍረው ነነበሩ ናቸው።
ከማለዳ ጀምሮ በሱዳን ብሄራዊ ሰራዊት እና በሱዳን ፈጥኖደራሽ ሰራዊት ( RSF)መካከል በተጀመረው ጦርነት በሰሜን ሱዳን ሰፍረው የነበሩ በርካታ የግብፅ ወታደሮች በሃምዳን ደጋሎ ሰራዊቶች ተማርከዋል።
ወታደሮቹ ግብፅ በአባይ ጉዳይ ኢትዮጵያን ለማስፈራራት እና የአብዱልፈታ አልቡርሃንን መንግስት ለመደገፍ በሚል በሰሜን ሱዳን ሜሮዌ ከተማ የጦር ሰፈር መስርታ ያሰፈረቻቸው ነው።
የሃምዳን ደጋሎ ፈጥኖ ደራሽ ሰራዊት ከትላት ቀስቲያ ሰራዊቱን አንቀሳቅሶ በቅድሚ በቁጥጥሩ ውስጥ ያስገባው የሜሮዌ ከተማንን ፣ በዚያ የሚገኘውን አየር ሃይል ጣቢያ እና የግብፅ ሰራዊት የሰፈረበትን የጦር ሰፈር ነበር።
በጦር ሰፈሩ የነበሩ ቁጥራቸው ያልተገለፁ የግብፅ ወታደሮች በቁጥጥር ስር የገቡ ሲሆን ይህን የሚያሳን ቪድዮም የፈጠኖ ደራሽ ሰራዊቱ በማህበራዊ ገፁ ለቋል።
የ IMF ትንበያ፦
ኢትዮጵያ እኤአ በ2023 ከሰሃራ በታች የአፍሪካ አገራት ሦስተኛው ግዙፍ ኢኮኖሚ እንደሚኖራት ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይ.ኤም.ኤፍ) ተነበየ።
ዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋም ባለፈው ጥር አውጥቶት የነበረው የአገራት የኢኮኖሚ ዕድገት ትንበያ በመከለስ ዳግም ይፋ አድርጓል።
በዚህ መሰረት ኢትዮጵያ 156 ነጥብ 1 ቢሊዮን ዶላር ጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት በማስመዝገብ በፈረንጆቹ 2023 ከሰሃራ በታች ሦስተኛ ግዙፍ የኢኮኖሚ ባለቤት አገር እንደምትሆን ትንበያው አመልክቷል።
ቀደም ሲል የኢትዮጵያን አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት 126 ቢሊዮን ዶላር እንደሚሆን ያስቀመጠው የአይ.ኤም.ኤፍ ትንበያ ዳግም ሲከለስ ወደ 156 ነጥብ 1 ቢሊዮን ዶላር ከፍ እንዲል አስችሎታል።
ናይጄሪያ በ 506 ነጥብ 6 ቢሊዮን ዶላር ጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት ቀዳሚ ስትሆን ደቡብ አፍሪካ ደግሞ በ 399 ቢሊዮን ዶላር ትከተላለች።
ኬንያ በምሥራቅ አፍሪካ ለበርካታ አመታት የኢኮኖሚ የበላይነት ነበራት።
ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን
ሚያዝያ 06 ቀን 2015 ዓ.ም
ለተጨማሪ መረጃዎች የቴሌግራምና የዩቲዩብ ቻናሎቻችንን ይቀላቀሉ!
Telegram
https://t.me/CommandoAndAirborneHeadQurter
YouTube
https://youtu.be/hhcmZ_R7MQE
ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን
ካርቱም ውስጥ ምን እየሆነ ነው ?
በሱዳን በአገሪቱ ጦር ሠራዊት እና በተጽእኖ ፈጣሪ ነው በሚባለው " ፈጥኖ ደራሽ ሚሊሻ " መካከል በካርቱም ውጊያ ተቀስቅሶ ከተማው በቶክስ እየተናወጠ ነው።
ዛሬ በመዲናዋ ከፍተኛ የተኩስ እና ፍንዳታ ተሰምቷል።
ፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ የካርቱም ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያን ተቆጣጥሪያለሁ ያለ ሲሆን፤ የብሔራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያን ለመቆጣጠር የተኩስ ልውውጥ እየደረገ መሆኑን ከሰዓታት በፊት አሳውቋል።
ፍጥጫው እንዴት ጀመረ ?
በሁለቱ ኃይሎች መካከል ለተፈጠረው ፍጥጫ ምክንያት በወታደራዊ አስተዳደር ስር የቆየችውን ሱዳን ወደ ሲቪል መንግሥት ለማሻገር በቀረበው ሃሳብ የተነሳ ነው።
ሄምቲ በሚለው ቅጽል ስማቸው በሚታወቁት በጀነራል መሐመድ ሐምዳን ዳጋሎ የሚመራው ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ወደ አገሪቱ ጦር ስለሚቀላቀልበት ሁኔታ አንዲሁም ኃይሉን ማን ይመረዋል በሚለው አለመግባባት ተፈጥሮ ባለፉት ቀናት ውጥረት ሰፍኖ ነበር።
ሁለቱ አካላት ምን አሉ ?
ዛሬ የተኩስ ድምጽ መሰማት የጀመረው በማዕከላዊ ካርቱም ውስጥ በሚገኘው የአገሪቱ ጦር ሠራዊት ዋና መሥሪያ ቤት አቅራቢያ ነበር።
(አርኤስኤፍ) የሚባለው ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ምን አለ ?
በዋና ከተማዋ በስተደቡብ ከሚገኙት ካምፖቹ መካከል አንዱ ላይ ጥቃት እንደተሰነዘረበት ገልጿል።
የሱዳን ጦር ሠራዊት ምን አለ ?
የፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ተዋጊዎች የጦር ኃይሉን ዋና መ/ቤት ለመቆጣጠር ጥረት እያደረጉ ነው ብሏል።
የፈጥኖ ደራሽ ኃይል ተዋጊዎች በካርቱም እና በሌሎች የሱዳን ክፍሎች ውስጥ የሚገኙ በርካታ የጦር ሠራዊት ካምፖች ላይ ጥቃት ፈጽመዋል ብላል።
ግጭቶች እየተካሄዱ መሆኑ የገለፀው ጦሩ ፤ ሠራዊቱ አገሪቱን የመጠበቅ ኃላፊነቱን እየተወጣ ነው ብሏል።
ሱዳን ...
ከሁለት ዓመት በፊት በሱዳን ውስጥ መፈንቅለ መንግሥት ከተካሄደ በኋላ የጦር ጄኔራሎች ሉዓላዊ ምክር ቤት የሚባል አካል አቋቁመው አገሪቱን እየመሩ ይገኛሉ።
አርኤስኤፍ የተባለው ፈጥኖ ደራሽ ሚሊሻ በኃያሉ ጄኔራል እና የምክር ቤቱ ምክትል ፕሬዝዳንት ሞሐመድ ሐምዳን ዳጋሎ የሚመራ ነው።
የሉዓላዊ ምክር ቤቱ ፕሬዝዳንት የሆኑት ጄኔራል አብደል ፋታህ አል-ቡርሐን ደግሞ የአገሪቱን ጦር ኃይል ይመራሉ።
ሱዳንን ወደ ሲቪል መንግሥት ለማሸጋገር የቀረበው ዕቅድ የአርኤስኤፍ ኃይሎችን ከአገሪቱ ጦር ሠራዊት ጋር በማዋሃድ የጊዜ ሰሌዳ ዙሪያ ከስምምነት ሳይደረስበት ቆይቷል።
አርኤስኤፍ ውህደቱ በአስር ዓመታት እንዲዘገይ ፍላጎት ያለው ሲሆን፣ የአገሪቱ ሠራዊት ግን በሁለት ዓመታት ውስጥ ተግባራዊ እንዲሆን ይፈልጋል።
በሁለቱ ወገኖች መካከል ያለው ውጥረት በተካረረበት ጊዜ አርኤስኤፍ ኃይሎቹን ሐሙስ ዕለት ሜሮዌ ውስጥ ባሉ የመንግሥት ኃይሎች አቅራቢያ አሰማርቷል።
ጄኔራል ቡርሃን በሚቋቋመው ሲቪል መንግሥት ውስጥ የሚመሠረተውን የተዋሃደ የአገሪቱን ጦር ማን መምራት አለበት በሚለው ጥያቄ ዙሪያ የተፈጠረውን አለመግባባት ለመፍታት ከጄኔራል ዳጋሎ ጋር ለመነጋገር ፈቃደኛ መሆናቸውን ገልጸው ነበር።
(ቢቢሲ)
ከዛሬ ጀምሮ የክልል ልዩ ኃይል የሚባል አደረጃጀት የለም - ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
ከዛሬ ጀምሮ የክልል ልዩ ኃይል የሚባል አደረጃጀት የሌለ መሆኑን የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ገለጹ።
የክልል ልዩ ሃይሎችን በፌዴራልና የክልል የጸጥታ ተቋማት መልሶ የማደራጀት ስራ የመከላከያ ጀነራሎች፣ ፌዴራል ፖሊስ እና የክልል የስራ ኃላፊዎች በተገኙ ተገምግሟል።
በመድረኩ ላይ የተገኙት የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፤ የክልል ልዩ ሃይሎች እንደገና በመደራጀታቸው ህብረ ብሄራዊ ጠንካራ የጸጥታ ተቋም ይገነባል ብለዋል።
ኢትዮጵያ ከነበረችበት የጸጥታ ችግር በፍጥነት መውጣቷን የገለፁት ፊልድ ማርሻሉ፤ የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት በመልካም ሁኔታ እየተከናወነ መሆኑንም ጠቁመዋል።
የክልል ልዩ ኃይሎች አደረጃጀት ህጋዊ አለመሆን፣ በክልሎች መካከል እንደ ስጋት መተያየት እንዲሁም ችግሮችን በሃይል ለመፍታት የሚደረገው እንቅስቃሴ አደረጃጀቱን ለመቀየር አስገድዷል ብለዋል።
በአሁኑ ወቅት በሁሉም ክልሎች መልሶ የማደራጀት ስራው ተጠናክሮ መቀጠሉን ጠቁመው "ከዛሬ ጀምሮ የክልል ልዩ ኃይል የሚባል አደረጃጀትና መዋቅር የለም" ብለዋል።
በመሆኑም የጸጥታ መዋቅሩ መከላከያ፣ ፌዴራል ፖሊስና የክልል ፖሊስ ሲሆን በክልል ልዩ ኃይሎች ስም ተልዕኮም ሆነ ግዳጅ የሚቀበል ኃይል አይኖርም ሲሉ አረጋግጠዋል።
ከዚህ በኋላ በመረጡት አደረጃጀት መሰረት ሁሉንም ወደ ተመደቡበት የማጓጓዝና ወደ ስልጠና የማስገባት ስራ ይከናወናል ብለዋል።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሚያዚያ 04 ቀን 2015 ዓ.ም
የመከላከያ ኮንስትራክሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ በግንባታ ላይ ያሉ ፕሮጀክቶችን ጎበኙ፡፡
የመከላከያ ዋር ኮሌጅ ማስፋፊያ ፕሮጀክት እና በጎፋ ካምፕ የሚገኘው የሠራዊት አባላት መኖሪያ ህንጻ ግንባታ ፕሮጀክት ሥራ አፈጻጸም በመስክ ምልከታው ተቃኝቷል፡፡
በመከላከያ ኮንስትራክሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር አህመዲን መሐመድ፣ የተመራው ቡድን አዲስ እየተገነባ የሚገኘውን የመከላከያ ዋር ኮሌጅ ማስፋፊያ ፕሮጀክት እና በጎፋ ካምፕ የሠራዊት አባላት መኖሪያ ህንጻ ግንባታ ፕሮጀክት አፈጻጸምን ተዘዋዉሮ ተመልክቷል፡፡
ዶክተር አህመዲን ከጉብኝት በኃላ ጠንካራ የሥራ ስምሪት በማድረግ ግንባታዎቹ በፍጥነት እንዲጠናቀቁ እና በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ አገልግሎት መስጥት እንዲችሉ የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ፣ የመከላከያ ኮንስትራክሽን ዲዛይን ድርጅት እና የመከላከያ ግንባታ ግብዓት ማምረቻ ድርጅት በጥምረት ሥራቸውን በመስራት ለውጤት ማብቃት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል፡፡
በፌዝ 1 በዋር ኮሌጁ ማስፋፊያ የሚቀሩ ሥራዎች የሲቪል ወርክ፣ ሳኒተሪ እና ኤሌክትሪካል ሥራዎችን እስከ ሰኔ መጨረሻ ድረስ ማጠናቀቅና በፌዝ 2 ያሉት ሥራዎችም ክረምቱ ከመግባቱ በፊት እንዲከናወኑ በትኩረት መሥራት እንደሚገባ ዶክተር አህመዲን አሳስበዋል፡፡
በጎፋ ካምፕ የሚገኘው የሠራዊት አባላት መኖሪያ ህንጻ ግንባታ ለማፋጠን በቂ የሰው ኃይል መጠቀም፣ ስራው በፈረቃ ሳይቆራረጥ እንዲሰራ ማድረግ አሥፈላጊ መሆኑን ጠቁመው በሰራዊቱ መኖሪያ ህንጻ ግንባታ ላይ የመከላከያ ግብዓት ማምረቻ ድርጅት የኮንክሪት ሙሌቶቹን በፍጥነት ሞልቶ ወደ ቀጣዩ የስትራክቸር ሥራ እንዲገባ ጥረት ማድረግ አሥፈላጊ መሆኑን ሚኒስትር ዲኤታው ጠቁመዋል ፡፡
በመስክ ምልከታው ላይ ሚኒስትር ዲኤታውን ጨምሮ የመከላከያ ዋር ኮሌጅ አዛዥ የመከላከያ ኮንስትራክሽን ዘርፍ የሥራ ኃላፊዎችና ተወካዮች ተገኝተዋል፡፡
የኮንስትራክሽን ዘርፍ ስነ ልቦና ክፍል
የሩሲያው ተዋጊ ዋግነር ግሩፕ አብዛኛውን የባክሙት ክፍል መቆጣጠሩን ገለጸ
የዩክሬን ከፍተኛ ወታደራዊ ባለስልጣናት ስጉዳዩ በቀጥታ ባይናገሩም ኃይሎቻቸው አሁንም ከተማዋን በመከላከል ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል።
https://am.al-ain.com/article/russian-wagner-group-bakhmut
