የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️
Відкрити в Telegram
4 889
Підписники
-25624 години
-1 8217 днів
-3 02830 день
Архів дописів
መስከረም 1 ቀን 2015 ዓ.ም
የክቡር የኢፌዴሪ ጠ/ሚኒስትርና የጦር ኃይሎች ጠ/አዛዥ ዶ/ር አብይ አሕመድ መልዕክት ፦
ውድ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች፣ እንኳን ለአዲሱ ዓመት በሠላም አደረሳችሁ!!
ኢትዮጵያ የጀግኖች ሀገር ናት። በጦር ሜዳ ውሎ ብዙ ጀብዱዎችን የፈጸሙ፣ ጦር ሰብቆና ድንበር ጥሶ የመጣ ጠላትን አንገት አስደፍተው የመለሱ፣ ለሀገር ሉአላዊነትና ለዜጎች ነጻነት መሞትን እንደ ክብር የሚቆጥሩ ብርቅዬ ልጆችን አፍርታለች። ስለ ታሪኳ የጻፉ የታሪክ አዋቂዎች አስቀድመው ከሚጠቅሷቸው ነገሮች መካከል አንዱ ጀግንነትና አልሸነፍ ባይነታችንን ነው።
ከጥንታውያኑ የግሪክ አፈታሪኮች አንስቶ እስከ አድዋው ዘመን የአውሮፓ ጋዜጦች ላይ የኢትዮጵያውያን ጀግንነት በስፋት ተወድሷል።
እኛ የዛሬ ዘመን ልጆች ከአያት ቅድመ አያቶቻችን የወረስነውን ይኼን የጀግንነት ስም አስጠብቀን ሳይሸራረፍ ለቀጣይ ትውልድ የማውረስ ኃላፊነት አለብን። ይኼ የትውልድ አደራ ቀላል ኃላፊነት አይደለም። አሁን ዘመኑ ተለውጧል። የውጊያ መልክና ቅርጹ በእጅጉ ተቀይሮአል።
በአድዋ እና በሁለተኛው የጣልያን ወረራ ወቅት በአርባ ዓመታት ውስጥ የተለወጠው የቴክኖሎጂና የዓለም ሥርዓት በብዙ እጥፍ አድጎና ተመንድጎ አሁን ዘመን ላይ ደርሷል። እኛ የምንጠቅሰው ሀገራዊ ጀግንነት በእነዚህ መለዋወጦች ምክንያት ምን ያህል እንደተፈተነ በሁለተኛው የጣልያን ወረራ ወቅት አይተን ነበር። የእኛ የዝግጁነት መጠን ከዓለም ለውጥ ጋር አብሮ ያለመሄዱ ሀገር እስከማሳጣት የሚያደርስ ከፍተኛ ዋጋ ሊያስከፍለን ይችላል።
ዛሬም ጠላቶቻችን እንደ ድሮው በቀጥታ ውጊያ ሳይገጥሙን የሚያሸንፉበትን መንገድ ከመንደፍ ወደኋላ አይሉም። በድንበር አካባቢ ከሚሰነዘሩብን ቀጥተኛ ጥቃቶች ባለፈ የሽብር ሥልጠና የወሰዱ ሰዎችን አስርገው በማስገባት የሚያካሂዱት የሽብር ተግባር ምን ያህል ፈተና ውስጥ እንደሚያስገባን ይታወቃል።
የሀገር ውስጥ ታጣቂዎችንና ያኮረፉ ኃይሎችን ተጠቅመው ሀገራችንን ገዝግዘው ለመጣል ዘወትር እንደቋመጡ ነው። በአንድ በኩል እኛ በምድርና በአየር የሚሰነዘሩ ጥቃቶችን በተጠንቀቅ ስንጠብቅ፣ በሌላ በኩል የሳይበርና የፕሮፓጋንዳ ዘመቻው ፋታ በሚያሳጣ መልኩ ይጎርፋል። ይህ ነባራዊ እውነታ ዘወትር ነቅተን እንድንጠብቅ ግድ ብሎናል።
ጠላቶቻችንን በስትራቴጂ በልጠን እስካልተገኘን ድረስ ሉአላዊነታችን በአስተማማኝ መሰረት ላይ አይቆምም፤ በተለይ አሁን። የኢትዮጵያን ተስፋ የሚያለመልሙ አጋጣሚዎች በየአቅጣጫው የተከፈቱበት ወቅት ስለሆነ፣ በአንድ በኩል የሕዳሴ ግድብ ወደ መጠናቀቁ ላይ መሆኑ፣ በሌላ በኩል በምግብ ራሳችንን የመቻል እርምጃችን ውጤት ማምጣት መጀመሩ፣ እንዲሁም ቀጠናዊና አህጉራዊ ተጽዕኖአችን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱ “ይቺ ባቄላ ካደረች አትቀቆረጠምም” በሚል ብሒል ተስፋችንን በእንጭጩ ለማስቀረት የሚቋምጡ ኃይሎች በዝተዋል። ሕልም ተፈርቶ ሳይተኛ አይታደርምና፤ እኛም ጠላት እንዳይበዛብን ብለን ወደ ከፍታው ከምናደርገው ጉዞ አንገታም። በልበ ሙሉነት ከተነሳን የኢትዮጵያ የኃያልነት ዘመን ሩቅ አይሆንም።
አዲስ ዓመት በተበሰረ ቁጥር የኢትዮጵያም ተስፋ እየተበሰረ እንደሆነ እያሰብን መስራት አለብን። እናንተም የመጪዋ ኃያል ሀገር የመከላከያ ሠራዊት አባላት ብቻ ሳትሆኑ የኢትዮጵያ ተስፋ ጠባቂዎች መሆናችሁን አውቃችሁ መስራት ይኖርባችኋል።
ታላቁ የጦርነት ጠበብት ሳን ዙ እንደሚለው፣ ጠንካራ ሰራዊት በሰላም ጊዜ ለጦርነት የሚዘጋጅ ነው። የኢትዮጵያ ተስፋ እውን የሚሆነውና ሕልውና በዘላቂነት ሊረጋገጥ የሚችለው እናንተም “በሰላም ጊዜ ለጦርነት ስትዘጋጁ” ብቻ ነው። ይኽ ሲባል ሠራዊቱ ጠባጫሪ ይሆናል ማለት አይደለም። ጠባጫሪነት በታሪካችን የለም። ደፍሮ የመጣን ኃይል አሳፍረን እንመልሳለን እንጂ በማን-አለብኝነት በሌላ ሉአላዊ ግዛት ላይ የኃይል ጥቃት የመሰንዘር ታሪክ አናውቅም።
ሠራዊት በሰላም ጊዜ ለጦርነት የሚዘጋጀው አውዳሚ የሆነ ጦርነትን ለማስቀረት የሚያስችል አቅም ለማዳበር ነው። እናንተም "አቅማችሁን ለማደርጀት ዘወትር መትጋት አለባችሁ" ስንል ሌሎች ላይ ጥቃት ለመሰንዘር እያሰብን ሳይሆን ሀገራችንን ከጠላት ትንኮሳ በብቃት መከላከል እንድንችል በማሰብ ነው።
ጠላቶቻችን አርፈው የሚቀመጡት በሁሉም ዘርፍ ብቃት ላይ መገኘታችንን ሲያውቁና በስትራቴጂም ይሁን በቁሳቁስና በቴክኖሎጂ አቅም በልጠው ሊያሸንፉን እንደማይችሉ ሲያውቁ ብቻ ነው። ይኼንን መቼም፣ መቼም ቢሆን እንዳትረሱ!!
በድጋሚ እንኳን ለዘመን መለወጫ በዓል በሠላም አደረሰን አደረሳችሁ!! አዲሱ ዓመት የሠላም፣ የጤና፣ የተግባርና የስኬት እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ!!
"መከታ" መፅሔት
🌼እንኳን አደረሰን አደረሳችሁ🌼
አዲሱ አመት 2015 በጤና በፍቅር እንዲሁም ህልሞቻችን የምናሳካበት አልፎም ከራሳችን አልፈን ለብዙሀኑ የምንተርፍበት አመት ይሁንልን።
🌼መልካም አዲስ አመት ይሁንልን🌼
✍️ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/CommandoAndAirborneHeadQurter
#ሪከርድ !
ዩናይትድ አረብ ኤሚሬትስ 120 የቱርክ ባይራክታር ድሮኖችን ለመግዛት ጥያቄ አቀረበች ።
ይህን ያክል ቁጥር ያለው የሰው አልባ የጦር ጄት ( ድሮን ) ግዥ ሲቀርብም ይህ ከፍተኛው ነው ።
በመላው አለም ዝናቸው የናኘውንና በቴክኖሎጂ ልህቀት ከየትኛውም ሀገር በላይ የተራቀቁትን የቱርክ ድሮኖችን ለመግዛት ሀገራት የቱርክን በር ማንኳኳት ከጀመሩ ቆዩ ። የአውሮፓና የኤዥያ ሀገራትን ጨምሮ እጅግ በርካታ ሀይላት እነዚህን የቱርክ የእጅ ስራ ውጤቶች ለመቀበል አሰፍስፈው እየጠበቁ ነው ።
የዩናይትድ አረብ ኤሚሬትስ ( ኢማራት ) ግን ከሁሉም የገዘፈውን ጥያቄዋን አቅርባለች ። በአንድ ጊዜ 120 ድሮን ! ኢማራት ለዚህ ግዥዋ ከ 2 ቢሊዮን ዶላር በላይ በጅታለች ። ይህም ከአሜሪካ ጦር መሳሪያዎች ውጭ የበጀተቻው ትልቁ የጦር በጀቷ ነው ።
ቱርክ የጦር ቴክኖሎጃዋ እየተራቀቀ በመምጣቱ የአለም ሀገራት ትኩረት ሁናለች ። ዛሬ ከሩሲያ እስከ እንግሊዝ ያሉ ሀገራት የቱርክን ድሮኖች እና የጦር መሳሪያዎችን አብዝተው የሚፈልጉበት ጊዜ ላይ ደርሰናል ።
ሀገራችን ኢትዮጵያ የቱርክ ድሮኖች ባለቤት ከሆኑ ሀገራት መካከል አንዷ ናት ። ቱርክ ለሀገራችን እነዚህን ጨዋታ ቀያሪ ድሮኖችን የሸጠችልን ደግሞ ምእራባውያን የመሳሪያ እገዳ በጣሉብን ጊዜ መሆኑ ትርጉሙን ትልቅ ያደርገዋል ።
ቱርክና ኢማራት በቅርቡ ወዳጅነታቸውን ማደሳቸው ይታወሳል ።
#Seid_Mohammed_Alhabeshiy
አዲግራት... 🇪🇹
የትግራይ ሁለተኛ ትልቋ ከተማ እና የምስራቅ ትግራይ ዋና ከተማ በኢትዮጵያ የፀጥታ ሀይሎች ተከባለች።
ድል ለኢትዮጵያ🇪🇹🇪🇹
አሜሪካ ለሩሲያ ድሮን ሸጠዋል በሚል የጠረጠረቻቸውን የኢራን ኩባንያዎች ላይ ማዕቀብ ጣለች
ሩሲያ ከዩክሬን ጋር ጦርነት መጀመሯን ተከትሎ የጦር መሳሪያ እጥረት እንደገጠማት አሜሪካ ታምናለች።
ይሄንን የጦር መሳሪያ እጥረት ለማስታገስም ሩሲያ ከኢራን እና ሰሜን ኮሪያ እየገዛች ነው በሚል በይፋ አሜሪካ ተናግራለች።
አራት የኢራን ኩባንያዎችም ከቴህራን ወደ ሞስኮ ሰው አልባ አውሮፕላን ወይም ድሮን እንዳጓጓዙ የአሜሪካ ወታደራዊ ተቋማትን መረጃ ዋቢ አድርጎ ቪኦኤ ዘግቧል።
ሳፊራን ኤርፖርት ሰርቪስ፣ ፓራቫር ኩባንያ፣ ባሀርስታን እና ፓርስ የዲዛይን ኩባንያ ደግሞ ድሮኖቹን ወደ ሞስኮ እንዳጓጓዙ በአሜሪካ የተጠረጠሩ ተቋማት ናቸው።
በዚህም ምክንያት እነዚህ ኩባንያዎች በአሜሪካ ግምጃ ቤት ማዕቀብ ተጥሎባቸዋል ተብሏል።
በተመድ የሩሲያ አምባሳደር በበኩላቸው የጦር መሳሪያ እጥረት እንዳልገጠማት፣ ከሰሜን ኮሪያም ሆነ ከኢራን የጦር መሳሪያ እንዳልገዛች ገልጻ አሜሪካ መረጃ ካላት ይፋ ታድርግ ሲሉ ገልጸዋል።
ከአሸባሪው ትህነግ ተልዕኮ ተቀብለው በአዲስ አበባ እና አካባቢው የህዝብን ሰላም ሲያውኩ የነበሩ 19 የሽብር ቡድን አባላት በተደረገው ከፍተኛ ኦፕሬሽን በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታወቀ
የአዲስ አበባ ፖሊስ፣ ከመከላከያ ሠራዊት፣ ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ፣ ከብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎትና ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ጋር በመሆን ባደረገው የተቀናጀ ኦፕሬሽን እነዚህ የወንጀል ቡድኖች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስታውቋል፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ በጉዞ ርቀት የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ በተለምዶ ራይድ ተብለው የሚጠሩ ተሽከርካሪዎች ላይ ትኩረት በማድረግ ተሳፋሪ መስለው ከገቡ በኋላ ወደ ሰዋራ ስፍራ ወስደው በአሽከርካሪዎቹ ላይ የግድያ እና የውንብድና ወንጀሎችን ሲፈፅሙ የቆዩ፡-
1ኛ. ሸዊት ሐዲስ፣
2ኛ. ዳዊት አለሙ፣
3ኛ. በሪሁ ናይዝጊ፣
4ኛ. ሃይለአብ ወርቁ የተባሉት ፖሊስ ባደረገው የሌት ተቀን ክትትል በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆኑ ገዳይ ቡድኑን በማሰማራት፣ ድጋፍ በማድረግ፣ የተዘረፉ ንብረቶችን በመሸጥና በሽያጩ የተገኘውን ገንዘብ መልሶ ለወንጀል ተግባር እንዲውሉ በማድረግ በአጠቃላይ ለገዳይ ቡድኑ የቁሳቁስና የፋይናንስ ድጋፍ ሲያደርጉ የነበሩ፡-
1ኛ. በረከት መዝገበ፣
2ኛ. ሰናይ ሐይላይ፣
3ኛ. ማዕረጉ በርሔ፣
4ኛ. ይኩኖአምላክ አማረ፣
5ኛ. ፀሀዬ ተስፋዬ እና
6ኛ. ዳንኤል ገ/ማርያም የተባሉት ተጠርጣሪዎችን ጥምር የፀጥታ ሃይሉ ባደረገው ብርቱ ክትትል በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እየተጣራባቸው ይገኛል፡፡
በሌላ በኩል በጦር መሳሪያ የተደገፈ ዘረፋ፣ የመግደል ሙከራ እና የውንብድና ወንጀሎችን በየካ፣ በለሚኩራ፣ በቦሌ እና በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተሞች ውስጥ እየተንቀሳቀሱ ሲፈፅሙ የቆዩ፡-
1ኛ. ፊሊሞን ህንፃ፣
2ኛ. አቡሽ ገ/እግዚአብሄር፣
3ኛ. መሰለ አባዲ ፣
4ኛ. ቸርነት ውዱ ፣
5ኛ. አቡሽ ግደይ፣
6ኛ. ህሉፍ ፈፀጉ፣
7ኛ. ወልደ ገብርኤል ህይወት፣
8ኛ. ሄኖክ ብርሃኔ እና
9ኛ. ክብሮም ንጉሱ የተባሉ ተጠርጣሪዎችን ፖሊስ በብርቱ ክትትል በቁጥጥር ሥር ያዋላቸው ሲሆን ግለሰቦቹ ስለፈፀሙት ወንጀል በተጨባጭ ማስረጃ የተረጋገጠባቸው ከመሆኑም ባሻገር ወንጀል መፈፀማቸውን አምነው ቦታውንና አፈፃፀሙን ለፖሊስ መርተው አሳይተዋል፡፡
በተወሳሰበ መንገድ በየጊዜው የሚፈፀሙ የወንጀል ድርጊቶች አሳሳቢነታቸውን በመገንዘብ እና ፖሊስ ከህብረተሰቡ ያገኛቸውን መረጃ መነሻ በማድረግ የአዲስ አበባ ፖሊስ የወንጀል ምርመራና የክትትል አባላት ባደረጉት ብርቱ ክትትል እና ጥምር የፀጥታ ሃይሉ ባካሄደው ሰፊ ኦፕሬሽን በአጠቃላይ 19 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር የዋሉ ሲሆን የወንጀሉ ፍሬ የሆኑ 12 ልዩ ልዩ ተሽከርካሪዎች፣ ለዕኩይ አላማ ማስፈፀሚያ ይጠቀሙባቸው የነበሩ የተለያዩ ሐሰተኛ ሰነዶች እና ልዩ ልዩ የፀጥታ አካላት የደንብ ልብስም ተይዘዋል፡፡
ከዚህ ባሻገር በፖሊስ ላይ ጥቃት ለመፈፀም በሞከሩ ሁለት የዘረፋ ቡድኑ አባላት ላይ ዕርምጃ የተወሰደባቸው መሆኑን ፖሊስ አስታውቋል፡፡
ሽብርተኛው የትህነግ ቡድን በግንባር የከፈተብንን ጥቃት እንደማያዋጣው ሲያውቅ የከተማ ላይ ሽብር ለመፍጠር የሽብር ቡድኑን አባላት መልምሎ በድብቅ ወደ አዲስ አበባ ላስገባቸው ተላላኪዎቹ ልዩ ልዩ የጥፋት ተልዕኮ ሰጥቶ ቢያሰማራቸውም በጥምር ፀጥታ ኃይሉ የሚያኮራ ብርቱ ተግባር በቁጥጥር ሥር ውለው ምርመራ እየተጣራባቸው ይገኛል፡፡
ፖሊስ የህብረተሰቡን ሰላምና ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥሉ ተግባራትን ለመከላከል በፀጥታ ኃይሉ የሚደረገው የተቀናጀ ኦፕሬሽን ተጠናክሮ እንደሚቀጥል እየገለፀ ሁሌም ለሰላማችን መረጋገጥ ከጎናችን ያልተለየው ህዝባችን ቀና ተባባሪነቱን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡
"መከላካያ ሠራዊታችንን ማጠናከር የሀገርን ህልውና ማረጋገጥ ነው"
የሀገርን ህልውና ለማስጠበቅ የሀገር መከላከያ ሠራዊትን መቀላቀል እንደሚገባ ጥሪ ቀርቧል
ሀገራችን ኢትዮጵያ አሁንም ሆነ በቀጣይ በቅርብና በሩቅ ባሉት ጠላቶቿ ጥርስ ተነክሶባት እና ጦርነት ተከፍቶባት ካለፈው ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ ከፍተኛ የሆነ የህልውና አደጋ ዘመቻ ላይ ትገኛለች፡፡ በመሆኑም ይህንን በጠላት የተደቀነብንን የህልውና አደጋ በቀጣይነት ለመመከትና ዘላቂ ልማታችን ለማሳካት የመከላከያ ኃይላችንን ማጠናከር ለዚህ ትውልድ አማራጭ ሳይሆን ግዴታ ሆኖ ቀርቧል፡፡
ስለሆነም አያት ቅድመ አያቶቻችን በከፈሉት መስዋዕትነት ከነሙሉ ክብሯ ያስረክቡንን ሀገር ህልውናዋ ተረጋግጦ፣ ለምታና ሉዓላዊነቷ ተከብሮ እንድትቀጥል ማድረግ የሁሉም ዜጋ የቅድሚያ ቅድሚያ የምንሰጠው ተግባር ነው፡፡ በመሆኑም ከአጭር ጊዜ አኳያ የተጋረጠብንን አደጋ ለመታደግ ዕድሜውና አቅሙ የፈቀደለት እንዲሁም የመከላካያ ሠራዊቱን የመመልመያ መስፈርት የሚያሟሉ ወጣቶች በሙሉ ይህንን ሀገር የማዳን ጥሪ ተቀብለው የሀገር መከላከያ ሠራዊቱን ሊቀላቀሉ ይገባል ለማለት እንወዳለን፡፡
ይህ በዚህ እንዳለ የሀገር መከላከያ ሠራዊታችንን መቀላቀል ማለት በውስጣችን ያለውን ኢትዮጵያዊነት ስሜት መግለጽ የምንችልበትና የእውነተኛ ዜግነት ማረጋጋጫ ተቋምን የመቀላቀልና የመገንባት ጉዳይ ነው፡፡ ስለዚህ ዛሬ ሀገሬ በባርነት ስር አትወድቅም፣ ወላጆቻችን ክብራቸው ተጠበቆ ሊኖሩ ይገባል፣ መጪው የሀገራችን መፃዒ ዕድልም በብሩህ ተስፋ የተሞላ ሆኖ እንዲቀጥል የምንሻ ሁሉ ሳንዘገይ መከላከያ ሠራዊቱን ልንቀላቀለው ይገባል፡፡
በሌላ በኩል አሸባሪውና ወራሪው የትህነግ ሀይል መቼም ጊዜ ቢሆን ለአማራ ህዝብ ዕረፍት እንደማይሰጠንና እንደማይተኛ ተረድተን ይህ ሽብርተኛ ቡድን ዳግም ለአማራ ህዝብም ሆነ ለመላ ሀገራችን ስጋት እንዳይህን ለማድረግና ጠላቶቻችንን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለማስወገድ የመከላከያ ሠራዊታችን ማጠናከር ይኖርብናል፡፡
በተጨማሪም የአማራ ክልል ተፈጥሯዊ አቀማመጥ ለውስጥም ሆነ ለውጭ ጠላቶቻችን የተጋለጠ ከመሆኑም አንፃር የአማራ ወጣቶች ዘርፈ ብዙ ኃላፊነት እንዳለባቸው በሚገባ በመረዳትና በሠራዊቱ ውስጥ በመቀላቀል የአማራ ማህበረሰብን የውክልና መጠን በማሳደግ ሀገርን በማዳን ተግባር አኩሪ ሚና ለመጫወት እንዲችሉ መልካም አጋጣሚ እንደተፈጠረላቸው ማወቅና ማስገንዘብ ተገቢ ነው፡፡
በአጠቃላይ የመከላከያ ሠራዊታችንን በማጠናከር እና ወታደራዊ አቅማችንን ይበልጥ በማሳደግ ሰላማችንና ልማታችንን በራሳችን እጅ ልናገረጋጋጥ ይገባል ለማለት እንወዳለን፡፡
ጳጉሜ 4 ቀን 2014 ዓ.ም
ጀግናው መከላከያ ሠራዊታችን የአሸባሪው የህወሃት ታጣቂን በሚገባው ቋንቋ እያናገረው ይገኛል።
በተለያዩ አቅጣጫዎች መጠነ ሰፊ ወረራን በመፈፀም የሰላም አማራጮችን የዘጋው የወንበዴዎቹ ስብስብ አሁን ላይ እራሱ በለኮሰው እሳት ክፉኛ እየተለበለበ ይገኛል።
ጠላትን ድባቅ እየመታ የሚገኘው ሠራዊታችን የተሠነዘረበትን ጦርነት በከፍተኛ ድል እየመከተው ይገኛል።
አሸባሪውን ሀይል በመቅጣት ላይ የሚገኘው ጀግናው ሰራዊታችን በከፍተኛ የሀገር ፍቅር ወኔ ፤ ከእኔ በላይ ተዋጊ ላሳር የሚለውን እብሪተኛ ሀይል እየተከላከለው ይገኛል።
በተፈጥሯዊ እና በሰው ሰራሽ መሰናክሎች መሀል ሀገራዊ ተልዕኮውን እየተወጣ የሚገኘው ሰራዊታችን ስለሀገሩና ስለህዝቡ ህልውና ሲል ከመሰናክሎቹ በላይ ከፍ ብሎ ሀገር አፈርሳለሁ ህዝብን አንበረክካለሁ ባዩን አሸባሪውን ህወሓት አየመከተው ይገኛል።
ቀን03/13/2014 ዓ.ም
ወሎ ከቃሊም ግምባር
በሰሜን ወሎ ዞን የጉባላፍቶ ወረደ አስተዳደር በግምባር እየተፋለመ ለሚገኘው ሠራዊት የእርድ በሬ ስጦታ አበረከተ
የወረዳው የብልፅግና ፓርቲ ሃላፊ አቶ ሃይለሚካኤል ደሳለኝ ከህዝብ የተደረገውን ድጋፊ ስምንት ሰንጋዎችንና ምግብ በወሎ ግምባር ለቃሊም ንዑስ ግምባር ሎጄስቲክስ ሃላፊ አስረክባዋል። አቶ ሃይለሚካኤል ደሳለኝ እንዳሉት የወረዳውን ሁሉን አቀፍ ህዝባዊ የድጋፍ ንቅናቄ ኮሚቴዎችንና የህበረተሰብ ተወከዮችን በመያዝ እስከግምባር ድረስ የተገኘነው በውጊያው ላይ ያለውን ጥምር ጦር ለማበረታታትና ቀጣይነት ያለው ድጋፍ ለማድረግም ጭምር ነው ብለዋል። እስከአሁንም ሶስት መቶ አምሳ ሁለት ሺህ ብር የሚሆን የአይነት ድጋፍ መደረጉን ተነግረዋል።
የሰሜን ወሎ ዞን ህዝባዊ የድጋፍ አስተባባሪ ኮሚቴ ሰብሳቢና የሰሜን ወሎ ዞን የወጣቶች አደረጃጀት ምክትል ሃላፊ ወጣት ግርማ ጥጋቡ እንደገለፁት የወረደው ሁሉም ቀበሌዎች በወሎ ግምባር እየተፋለመ ለሚገኘው ጥምር ጦር በፍቃደኝነት ላይ የተመሰረተ በራስ ተነሳሽነት ዘለቂ ድጋፍ የመሰባሰብ ስራ እየተሰራ በመሆኑ አሁንም ወራሪውን ጁንታ ስርዓተ ቀብሩ እስከሚፈፀም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። የሰሜን ወሎ ዞን ወጣቶች እስከግምባር ድረስ ዘልቆ በመግባት እየተዋጋ ለሚገኘው ሰራዊት ስንቅና ትጥቆችን እያቀረበ ይገኛል።
ታሪኩ ሻሜቦ
ፎቶግራፍ፦ ታሪኩ ሻሜቦ
" የጣልኩባችሁን ማእቀብ እንዳነሳላችሁ ከፈለጋችሁ የጣላችሁብኝን ማእቀብ ቅድሚያ አንሱ "
ይህ ከሩሲያ ለአውሮፓ ሀገራት የተላለፈ ቀጭን ማስጠንቀቂያ ነው ።
ትእቢተኞቹ አውሮፖች ሩሲያ ቬንዙዌላን መስላቸው ይሁን ሰሜን ኮሪያን በኢኮኖሚ ሊያሽመደምዷት የማእቀብ ናዳ አውርደውባት ነበር ። ግና የጣሉት ማእቀብ Backfire አደረገባቸውና ያጠመዱት ወጥመድ ራሳቸውን አጠመዳቸው ። እናም ቁማርተኛዋ ሩሲያ የሀይል አውርቦት ህልቅታቸውን ዘግታ እያንፈራፈረቻቼው ትገኛለች ። ታዲያ ሩሲያን ይህንን ውሳኔዋን ቀይራ በአውሮፓ ላይ የጣለቺውን የሀይል አቅርቦት ማእቀብ እንድታነሳ የአውሮፓ ድፕሎማቶች ሞስኮን ደጅ መጥናት ከጀመሩ ሰነባበቱ ። ሩሲያ ታድያ ምኗ ሞኝ ነው ጠላቶቿ ስለለመኗት አንጀቷ የሚራራው !
እናም " እንሳቅ ካለሽማ ነዶየን መልሺ " እንዲሉ " ለመሆኑ እናንተ የጣላችሁትን ማእቀብ ሳታነሱ እኔ የጣልኩትን ማእቀብ የማነሳው ምኔ ሞኝ ነው ? " ብላ አውሮፓውያንን ኩም አድርጋ መልሳቸዋለች ።
የአውሮፓ ኢኮኖሚ የቁልቁለት ጉዞውን ተያይዞታል ። ዩሮ በታሪክ ዝቅተኛውን ሪከርድ በማስመዝገብ ከሌሎች መገበያያ ገንዘቦች አንፃር መንሸራተቱን ቀጥሎበታል ። የአውሮፓ አክሲዮን ገበያ በአንድ ቀን 13 % አሽቆልቁሏል ። ይህ አስደንጋጭ ነው ።
በታሪክ የትእቢተኞቹ አውሮፓዊያን መድሀኒት የሆኑ ሶስት ህዝቦች አሉ ። እነርሱም ሩሲያዊያን ቱርኮች እና ሞንጎሎች ናቸው ። በተለይ የሩሲያማ አይነገር !
የስዊድኑን ቻርልስ ትእቢት ያስተነፈሰቺው ፣ የጀርመኑን ፍሬደሪክ ያስጎነበሰቺው ፤ የፈረንሳዩን ናፖሊዮን አዋርዳ የሰበረቺው ፤ የጀርመኑን ሂትለር የደመሰሰቺው ሩሲያ ዛሬም እንደልማዷ በአውሮፓዊያን ላይ ጢባጢቤ እየተጫወተቺ ነው ።
ይህ ፑቲን የሚባል ሰው ግን ምን አይነት ጮሌ ፖለቲከኛ ነው !!!
#Seid_Mohammed_Alhabeshiy
እስከ ወሎ ግምባር የዘለቀው ህዝባዊ ድጋፍ ይህንን ይመስላል።
ኢትዮጵያ ታሸንፋለች🙏🇪🇹🙏
ጳጉሜ 1 ቀን 2014 ዓ.ም
የህወሓት የሽብር ሰነድ ሲገለጥ...
አሸባሪው ህወሓት ሀገርን የሚያፈርስበትና የኢትዮጵያን ህዝብ በመበቀል ለመከራ የሚዳርግበት አዲስ ሰነድ አዘጋጅቶ ወደ ተግባር ገብቷል። አሁን እያካሄደ ያለው ውጊያም የዚሁ አካል ነው።
ፅሁፉ ሰፊ ከመሆኑ የተነሳ በማሳጠርና መታየት ያለባቸው ነጥቦች ብቻ ቀርቧል።
ከሰነዱ የተወሰዱ ዋና ወና ሃሳቦች
... የቀጠለ ክፍል 2
ሶማሌ ክልልን በተመለከተ
•በምስራቁ የሀገሪቱ ክፍል በሱማሌ ክልል ከሚንቀሳቀሱ እና የጋራ ጠላታችንን ከሚታገሉ የአልሸባብ ሴሎችና ከኦጋዴን ታጋዮች ጋር የመረጃ ልውውጥ እገዛ እና ስትራቴጂ ሥራዎቻችን ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል።
የውጭ ሃይሎችን ድጋፍ
• በውጭ ያሉ አጋዦቻችንና አጋሮቻችን በአስቸጋሪ እና አጣብቂኝ ጊዜ ውስጥ ቢንሆንም ችግሩን አልፈው ዘመናዊ ትጥቆች እንድንታጠቅ አድርገውናል። ይህም ሆኖ የዚህ ዘመቻ ምዕራፍ መራርና በርካታ መስዋእትነት የሚጠይቅ በመሆኑ አሁንም ቀጣይነት ባለው ሁኔታ ዘመናዊ ትጥቅ ለመከላከያ ሃይላችን እንዲያቀርቡልን የሚያስችሉ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ከውስጥና ከውጪ ተባባሪዎቻችን ጋር ያለንን ስራ አጠናክረን መቀጠል ይኖርብናል።
• በትግራይ የሚገኙ የዓለም አቀፍ የእርዳታ ድርጅቶች ሰብአዊ ድጋፍ ማከማቻ መጋዘኖች ፋሽስቱን ለማስወገድ በምናደርገው ትግል የስንቅ አቅርቦት እንዳይጓደል በቁጥጥራችን ስር ልናደርጋቸው ይገባል።
የስነልቦና ጦርነትና ስጋትን መፍጠር
• በጠላት ላይ ሽብር፣ ፍርሃትና የስነ ልቦና ጫና መፍጠር አስፈላጊ በመሆኑ፣ ሽብር የሚያስፋፉ እና በመሀል ሃገር ያለው ሕዝብ ሳይቀር በመንግሥት አቅም ላይ ያለው እምነት እንዲሸረሸር የሚያደርጉ መረጃዎች በሀገር ውስጥና በውጪ ሚዲያዎች በሙሉ ማዳረስ ያስፈልጋል። ለዚህም ባለቤቶቻቸው አዲስ አበባ የሚገኙ ሚዲያዎችና ዩቲዩብ ቻናሎች ከፍተኛ ድጋፍ ስለሚኖራቸው የመረጃና ፋይናንስ ድጋፋችን ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል።
ልማትን የማደናቀፍ እቅድ
• ዐቢይ ያገኘው ጊዚያዊ አንፃራዊ መረጋጋት፣ ሕዝብ በማንቀሳቀስ የጀመረው የእርሻ ልማት፣ የበጋ ስንዴና ሌሎች የኢኮኖሚ ስራዎች ማደናቀፍ ላይ ትኩረት እናደርጋለን። የእርሻ ዘርፉ እንዲደናቀፍ በየአከባቢው ግጭት በመቀስቀስ እና ግጭት ለመቀስቀስ የሚያስችሉንን ሃይሎች በማገዝ እረፍት በመንሳት፣ የልማት ስራዎችን ትቶ እሳት ማጥፋት ላይ እንዲጠመድ ማድረግ በረዥም ጊዜ የዐቢይ መንግሥትን ለማዳከም የሚያግዝ ሲሆን፤ ባጭር ጊዜም ደግሞ ለሚካሄደው ወታደራዊ ዘመቻ የጠላት አቅም እንዲዳከም ትልቅ ጥቅም አለው። በአማራ ክልል በተወሰነ መልኩም ቢሆን ፊቱን ወደ ልማት ያዞረ ገበሬ እየታየ ነው። ይህ ወደ ልማት ፊቱን ያዞረ ሃይል ትላንት እና ከትላንት ወዲያ የትግራይን መሬት በሃይል የወረረ፣ ሰብል ያቃጠለ፣ ንብረት ያለምንም ይሉኝታ የዘረፈ፣ ሴቶችን የደፈረ ሃይል ነው።
ይቀጥላል ...
ነሐሴ 30 ቀን 2014 ዓ.ም
የህወሓት የሽብር ሰነድ ሲገለጥ...
አሸባሪው ህወሓት ሀገርን የሚያፈርስበትና የኢትዮጵያን ህዝብ በመበቀል ለመከራ የሚዳርግበት አዲስ ሰነድ አዘጋጅቶ ወደ ተግባር ገብቷል። አሁን እያካሄደ ያለው ውጊያም የዚሁ አካል ነው።
ፅሁፉ ሰፊ ከመሆኑ የተነሳ በማሳጠርና መታየት ያለባቸው ነጥቦች ብቻ ቀርቧል።
ከሰነዱ የተወሰዱ ዋና ወና ሃሳቦች
# ስለ ሰላም አማራጮች ያላቸው አቋም:
• የሰላም አማራጭ በሚል ስትራቴጂው፣ በአንድ በኩል ጊዜ ወስዶ ለአጠቃላይ ዘመቻ ለመዘጋጀት በሌላ በኩል ደግሞ ህወሓት ሰላም ፈላጊ አይደለም ብሎ ለዓለም ማህበረሰብ ጥላቻ ለማሰተጋባት እንዲያግዘው በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት የጀመረው አካሄድ በፍፁም የማያዋጣና የትግራይ ህዝብን ጥቅም የማያስከብር መሆኑን ያስቀምጣል።
• የውስጥ ትግላችን በማገዝ የሚንቀሳቀሱ እንደ ኦነግ የመሳሰሉ አጋሮቻችን እንዲሁም በተለያዬ የዓለም መአዘናት የሚገኙ የትግራይ ዲያስፖራና ዓለም አቀፍ አጋዦቻችንና አጋሮቻችን በዚህ ጊዜ የተሳካ ጥምረት በማድረግ ወደ አዲስ አበባ በምናደርገው እንቅስቃሴና ዘመቻ ከጎናችን መሆናቸውን የሚያረጋግጥ መሆኑን የትግራይ መንግስት ፕሬዝዳንት ጋር በዝግ ባደረገው ውይይት አረጋግጧል።
የአማራ ሃይል የተመለከተ
• ይሄ ፅንፈኛ የአማራ ተስፋፊ ሃይል በትግራይ ላይ ካሳየው ጫፍ የወጣ ጥላቻ በላይ፣ በክልሉ ያገኘውን ሕዝባዊ ተቀባይነት ሽፋን በማድረግ እና ጠንካራ ቅንጅት በመፍጠር ከአማራ ክልል መንግሥት የሚስተካከል አቅም መፍጠር በመጀመሩ የዐቢይ አስተዳድር በወሰደው ርምጃ በተወሰነ መልኩ መዳከም ታይቶበታል።
አሁንም ግን የዚህ ሃይል አመራሮች በህዝብ ጉያ ተደብቀው ስለሚገኙ ምቹ ሁኔታ ካገኙ ዳግም ሃይል አግኝተው መነሳታቸው አይቀርም። ይህ ሁኔታ የትግራይ ሰራዊት እንደ ጥሩ አጋጣሚ ሊጠቀምበት የሚገባ ሲሆን፣ ይሄ ሃይል ራሱን “ፋኖ” ብሎ በመጥራቱ የተወሰደበት ርምጃ በርከት ያሉ የአማራ ታጋይ ሃይሎች ከዐቢይ ጎን ተሰልፈው ለመንቀሳቀስ ያላቸውን እንዲቀንስ አድርጎታል። ይህንን መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ሰፊ የፕሮፓጋንዳ ስራ በመስራት የተፈጠረውን መሻከርና ክፍተት የበለጠ እንዲከር ማድረግ ይገባል።
አፋር ክልልን በተመለከተ
• የዓፋር መንግሥት የእርዳታ ተደራሽነት በመቆጣጠር በየጊዜው ምክንያት የሌለው ግጭቶች በመፍጠር በአዋሳኝ አከባቢዎች በዘላቂነት ሰላም እንዳይሰፍን በማድረግ በአከባቢው የሚኖሩ ተጋሩ በስጋት ውስጥ እንዲሆኑ አድርጓል። በአወል አርባ የሚመራ ግጭት ቀስቃሽ ቡድን ከዐቢይ አስተዳድር በሚሰጠው አድናቆትና ቁጥር የሌለው የትጥቅ እገዛ አይኑ የታወረ፣ ጆሮው የተደፈነ በመሆኑ፣ ትግላችን በሚያግዙ የዓፋር የነፃነት ታጋዮችና ቤተሰቦቻቸው አፈናና ግድያ እየፈፀመባቸው ይገኛል።
ኤርትራን በተመለከተ
• ይሄ ፍፁም አምባገነን የሆነ የኤርትራ መንግሥት፣ አሁንም እንደ ትላንት ዋነኛ የሰላምና የትግራይ ህዝብ ነፃነት ጠላት መሆኑ ዳግም እያሳየ ይገኛል። ይሄ ጨቋኝ መንግሥት ባጭር ጊዜ መፍትሄ ካላገኘ ሕዝባችንን ወደ ማያቋርጥ ጦርነትና መከራ ዳግም ለማስገባት የሚችል ስጋት በውስጡ የያዘ ነው። ከዚህ በተጨማሪ፣ በሶማሌና ኦሮሚያ ክልሎች የሚገኙ የዐቢይ ታማኝ አመራሮችና ደጋፊዎች በክልላቸው ውስጥ በምናደርገው እንቅስቃሴ የሚያግዙንን የውስጥ አካላት እያደኑ ማጥቃት ቀጥለዋል።
ከኦነግ ጋር ያለን ግንኙነት
• ከኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት አመራር ጃል ሚልኬሳ ጋር በሚስጢር ባደረግነው ውይይት፣ ባጭር ጊዜ አመራራቸው ወደሚመች አከባቢ ወይም ወደ አጎራባች ሃገሮች ስልታዊ ማፈግፈግ የሚያደርጉበት ሁኔታ እንዲመቻች፣ እንዲሁም የመከላከል አቅምና ዝግጁነት የሌላቸው የሰራዊቱ አባላት ከተቻለ ዩኒፎርማቸውን ጥለው ወደ ሕዝባቸው እንዲቀላቀሉና እንዲደበቁ ካልተቻለም ለመንግሥት ሃይሎች እጃቸውን መስጠት የተሻለ አማራጭ እንደሆነ አንስቶ ነበር።
• በወለጋ ያለው ከኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት አመራር መካከል ጃል ራሣና ጃል ቃንቄ በፋሺስት ዐቢይ ከተከፈተባቸው ከበባ ለመውጣት አስቸኳይ ዘዴ ዘይደው መመርያ በመስጠት ወደሚመች ምስጢራዊ ቦታዎች እንዲንቀሳቀሱ የተደረገው ሙከራ የተሳካ ነው። በዚህ አግባብ በአንዳንድ የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት አመራሮች መካከል የትግል ስልት ልዩነት ቢኖርም በአስቸጋሪ ሁኔታ ሁነንም የመረጃ ልውውጣችን እና መተጋገዛችን የሚቀጥል ይሆናል። የዚህ ግንኙነት ዋነኛ መሰረት፣ የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ለአዲስ አበባ ካላቸው ቅርበትና ለሚታሰበው ዘመቻ ከፍተኛ ትግል በማድረግ ድል ሊያስመዘግቡ የሚችሉ በመሆናቸው ላይ ካለን መተማመን የሚመነጭ ነው።
• ይሁን እንጂ አሁንም የፋሺስት ዐቢይ አህመድና ሽመልስ አብዲሳን አገዛዝ ሽባ በማድረግ ወደ አዲስ አበባ የሚደረገው የመጨረሻ የትግል ምዕራፍ ላይ የቅርብ አጋዦች እነዚህ የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት በመሆናቸው ሊስተካከሉ የሚገባቸው እና ባለፈው ግምገማ የታዩ ክፍተቶች ታርመው ወደ መጨረሻው ምዕራፍ እንዲዘጋጁ ማድረግ አስፈላጊ ነው።
ይቀጥላል ...
ሰበር ዜና‼️
ጠንካራውና የመጨረሻው የሸረሪማ ምሽግ ተሰበረ!
ጥቅምት 30/2013 ዓ.ም ሳምረ የተባለው የትህነግ አሸባሪው ቡድን በማይካድራ ይኖሩ የነበሩ ወደ 2000 የሚጠጉ ንጹሃን የአማራ ተወላጆችን በአማራነታቸው ምክንያት ብቻ በግፍ ጨፍጭፎ፣የኢትዮጵያ ጥምር ጦር ሲደርስበት ወደ ሱዳን መፈርጠጡ አይዘነጋም።ከዚያም የአሸባሪው ቡድን ታጣቂ በሱዳን የሽብር ስልጠና ሲወድ መቆየቱ ይታወቃል።ሽብርተኛው ቡድን ከታሪካዊ የኢትዮጵያ ጠላቶች ጋር በማበርና ተልኮ በመቀበል የወልቃይት ጠገዴን ኮሊደር ለማስከፈት በተደጋጋሚ ትንኮሳ ሲፈጽም ቆይቶል።ቢሆንም ግን በእየ ጊዜው የጀግኖቹን ክንድ እየቀመሰ ተመልሷል።
አሸባሪው ትህነግ ሰሞኑንን በይፋ ሶስተኛውን ወረራ መጀመሩን ተከትሎ በሱዳን የሽብር ስለጠና ሲወስድ የነበረውን በርካታ ሽብርተኛ በሰሜን ምዕራብ ጎንደር ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን በሚገኙት በበረከትና ልጉዲ ግንባር አሰልፎ ጦርነት ከፍቶ ሰንብቷል። ይሁን እንጂ ጀግናው የኢትዮጵያ ጥምር ጦር የመጣውን አሸባሪ በዕርሳስ አረር ቆልቶ፣በቦምብ አንድዶ፣ በመድፍ አዳፍኖ፣በብሬንን ረፍርፎ፣ በስናይፐር ነድሎ...ወደ አፈርነት ቀላቅሎታል። አመድ አድርጎ በትኖታል። ምሽጉ ተደርምሷል።
ዛሬ ደግሞ በሰሜን ምዕራብ ጎንደር ወልቃይት ጠገዴ በረከት ፊት...ለፊት ግዴማ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ልዩ ስሙ ሸረሪማ ወይም ነጭ ድንጋይ እየተባለ በሚጠራው ቦታ አሸባሪው ትህነግ በከፍተኛ ሁኔታ ገንብቶት የነበረው ጠንካራ ምሽግ በጀግናው የኢትዮጵያ ጥምሮ ጦር ክንድ ተደርምሷል። የአሸባሪው ተወጊ ከምሽጉ ጋር አብሮ ተደምስሷል። የሸረሪማው ወይም የነጩ ዲንጋይ ምሽግ የአሸባሪው ትህነግ በግንባሩ ጠንካራውና የመጨረሻው ምሽግ እንደነበር ታውቋል።
via(Amdemariam Ezra)
ወጉማ ተይዟልኮ! ይልቅስ ሄደህ አስሬን ቁጠር በለው!
ትናንት ብሉምበርግ የሚባል ሚዲያ ለትህነግ ተስፋ የሚሆን አንድ ዜና ሰርቶ ነበር። ኢትዮጵያ በሰላም አስከባሪነት የላከቻቸው የትግራይ ተወላጅ መኮንኖች ወደ ኢትዮጵያ አንመለስም ብለው ወደ ሱዳን አቅንተው ነበር። 528 ናቸው። ሁሉም ሰሞኑን ውጊያ በተደረገበት አካባቢ ስልጠና እየሰጡ ነበር። ብሉምበርግ ታዲያ ከትህነግ በተሰጠው የውሸት መረጃ መሰረት እነዚህ መኮንኖች የሚመሩት የትህነግ ታጣቂ ሁመራን ሊይዝ እንደሆነ አድርጎ አውርቶ ነበር። ውሸት ቁርሳቸው፣ ምሳቸው፣ ራታቸውም ነው።
እውነታው ሌላ ሆነ። ጥምር ጦሩ ገና በመጀመርያው ቀን የት ልግባ አስባላቸው። በሁለት ቀን ሁሉም ምሽግ ተሰባብሮ የተረፉት ወደ ሱዳን እግሬ አውጭኝ ሲሉ አብዛኛውን ጥይትና ቀሪውን የተከዜ ውሃ በላው።
ተበታትኖ የሚገኘውን የትህነግ ኃይል ጥምር ጦሩ የማፅዳት ስራ እየሰራ ይገኛል። እንደምንም ወደ ሱዳን የተሻገረው የትህነግ ታጣቂ አሻባ የተባለ ቦታ ላይ የሱዳን ወታደሮች መሳሪያህን አራግፍ እያለው ነው። ሱደን የከረመው የትህነግ ኃይል ሲፎክር ስለከረመ አሁን እግሬ አውጭኝ ሲል ሱዳኖቹ እንዴት ይታዘቡታል?
ከሱዳን አቅጣጫ የመጣው የትህነግ ኃይል ሁመራን እይዛለሁ ብሎ አስወርቶ በጥምር ጦሩ አሳሩን ሲበላ ከፍተኛ አዛዦቹን ጭምር አጥቷል። በዚህ ውጊያ ኮ/ል መኮነን ኃይሉ የተባለ የትህነግ ክ/ጦር አዛዥን ጨምሮ በሺህ የሚቆጥር ሬሳውን ጭኖ ለመሸሽ ሞክሯል። በርካታ ታጣቂ ሲሮጥ ተከዜ ሲወስደው፣ በውጊያ የሞቱበትን ግን በጀልባ እየጫነ ወደ ሱዳን ለመሻገር ጥሯል። ነፍስ ያለውን ወንዝ ላይ ጨምሮ ሙት ተሸክሞ ይሄዳል። ትህነግ በብሉምበርግ ያሰራው ደግሞ በጀግኖቻችን መስዋዕነት ህልም ሆኖ ቀርቷል። ወግ ብቻ!
ነሐሴ 30 ቀን 2014 ዓ.ም
አሸባሪው ህወሓት የሰላም አማራጭን ረግጦ ጦርነት መክፈቱ በትግራይ ህዝብ ጫንቃ ላይ ቆሞ የስልጣን እድሜውን ለማራዘም ነው ሲሉ ምርኮኞች አጋለጡ
****
አሸባሪው ህወሓት የቀረበለትን የሰላም አማራጭ ረግጦ ዳግም ጦርነት መክፈቱ በትግራይ ህዝብ ጫንቃ ላይ ቆሞ የስልጣን እድሜውን ለማራዘም ነው ሲሉ በተለያዩ ግንባሮች እጃቸውን ለጀግናው የሀገር መከላከያ ሰራዊት የሰጡ ምርኮኞች አጋለጡ።
ምርኮኞቹ እንደተናገሩትም የትግራይን ህጻናት ሳይቀር ወደ ጦር ግንባር እየማገደ የሚገኘው አሸባሪው ህወሃት በሃሰተኛ ትርክት የትግራይን ወጣት ራሱ ወደለኮሰው ጦርነት እየማገደ ክልሉን ትውልድ አልባ የማድረግ እኩይ አላማውን ገፍቶበታል።
ይህም ተግባሩ የሽብር ቡድኑን የባንዳነት ትክክለኛ ባህሪ በተጨባጭ እያረጋገጠ መሆኑንም ነው ምርኮኞቹ የተናገሩት።
ምርኮኞቹ አሸባሪው የህወሃት ቡድን በትግራይ ህዝብና ህፃናት ላይ እየፈፀመ ያለውን ስቃይና እንግልት በመቃወም በፕሮፖጋንዳ ተታለው ከገቡበት ጦርነት በመውጣት ለጀግናው የሃገር መከላከያ ሰራዊት እጃቸውን መስጠታቸውን ገልፀዋል።
የሰላም አማራጭ በሰፊው ቀርቦለት ጦርነትን መርጦ ህጻናትን ሳይቀር ወደ ጦርነት እየማገደ ያለው የሽብር ቡድኑ ህወሃት የራሱን የስልጣን ላይ ቆይታ ለማራዘም ትግራይ ላይ ምንም አይነት ጥፋት ከመፈጸም ወደኋላ እንደማይመለስ ምርኮኞቹ አረጋግጠዋል።
"የትግራይ ከፍታ የሚረጋገጠው በኢትዮጵያ መቃብር ላይ ነው" በሚል ቀቢፀ ተስፋ በመነሳሳት ኢትዮጵያን ለማፍረስና ህዝቦቿን ለመበተን ዳግም ጦርነት ቢከፍትም ዓላማ ቢስ ለሆነው የሽብር ቡድኑ አላማ መሰለፍ ከንቱ በመሆኑ እጃቸውን ለመስጠት እንዳስገደዳቸው ተናግረዋል።
በቡድኑ የውሸት ወሬና ፕሮፓጋንዳ ተታለው በመሰለፍ ለፈፀሙት ጥፋት በመፀፀት ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ፤ ለመከላከያ ሰራዊቱና ለሌሎች የፀጥታ ኃይል ይቅርታ ጠይቀው የህወሓት የሽብር ቡድንን ከንቱ ራስ ወዳድ አላማ ለማስፈፀም የተሰለፉ የትግራይ ወጣቶችም የሚጓዙበት መንገድ ፈጽሞ እንደማያዋጣ ተረድተው ፈጥነው እንዲነቁ ምርኮኞቹ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
ምርኮኞቹ በመከላከያ ሰራዊትና በሌሎች የፀጥታ ሃይሎቻችን ለተደረገላቸው መልካም አቀባበልና እንክብካቤም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ከጦርነት ኪሳራ እንጂ ትርፍ እንዳማይገኝ የገለፁት ምርኮኞቹ፤ አሸባሪ ቡድን ለዳግም እልቂት የከፈተውን ወረራ በማውገዝ ወደ ሰላም እንዲመጣ የትግራይ ህዝብ፤ ወጣቶችና ልዩ ኃይል አባላት ጫና መፍጠር እንደሚገባቸው ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
ነሐሴ 30 ቀን 2014 ዓ.ም
አሸባሪው ህወሓት የእርዳታ ድርጅቶች ለርሃብተኞች የሚለግሡትን ምግቦች ለውጊያ እየተጠቀመበት ነው።
የሽብር ቡድኑ ከሠሞኑ በከፈተብን ጦርነት በምግብ እጥረት ለተጎዱ ዜጎች የሚቀርበውን ኮርን ሶያ ብሌንድ /Corn Soya Belend/ የተሰኘ አጣዳፊ የምግብ እጥረትን ለማከም የሚውል የዓለም ጤና ድርጅት /WFP/ መመሪያን አሟልቶ የተዘጋጀውን አልሚ ምግብ ለታጣቂዎቹ ተጠቅሟል።
ይህ አልሚ ምግብ ዜጎችን ከርሀብ ሞት የሚታደግ እና የሚያክም ነው። አሸባሪው የህወሃት ቡድን ዜጎች በርሃብ ጠኔ ታመው እየሞቱ እሱ ግን በምሽግ ከዝኖ ታጣቂዎችን እየቀለበ እንደሚያዋጋበት በከፈተብን ጦርነት ማረጋገጥ ተችሏል።
