የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️
Відкрити в Telegram
5 066
Підписники
-25624 години
-1 8217 днів
-3 02830 день
Архів дописів
ከፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል የተሰጠ መግለጫ
በአማራ ክልል ሕገ-መንግስታዊ ሥርዓቱን በማፍረስ ክልላዊ ስልጣንን በኃይል ለመያዝ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት በህቡዕ ተደራጅተውና ተቀናጅተው በሚንቀሳቀሱ ጽንፈኛ ኃይሎች ላይ የማያዳግም ህጋዊ እርምጃ እየወሰደ መሆኑን የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ-ኃይል ሚያዚያ 20 ቀን 2015 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ ማስታወቁ ይታወሳል።
በመሆኑም የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ- ኃይል እየወሰደ ባለው እርምጃ በዚህ ህቡዕ አደረጃጀት ውስጥ ሲንቀሳቀሱና የሽብር ተግባር ሲፈጽሙ የተገኙ 47 ተጠርጣሪዎችን ከበርካታ የነፍስ ወከፍና የቡድን መሣሪያዎች፣ ቦንቦችና ተቀጣጣይ ፈንጂዎች እንዲሁም ከሳተላይት መገናኛ መሣሪያዎች እና የተለያዩ መረጃዎችን ከያዙ ላፕቶፖች ጋር በቁጥጥር ሥር ማዋሉን ለመገናኛ ብዙኃን በላከው መግለጫ አመልክቷል።
ተጠርጣሪዎቹ የአማራ ክልል ከፍተኛ አመራሮችን የግድያ ዒላማ በማድረግ፤ ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል በመናድ የክልሉን መንግሥታዊ መዋቅር በመቆጣጠር የፌደራል መንግሥትን ለመጣል በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት ተደራጅተው እና ተቀናጅተው በህቡዕ ሲንቀሳቀሱ እንደተደረሰባቸው አስታውቋል።
ግብረ-ኃይሉ ለመገናኛ ብዙኃን በላከው መግለጫ፤ መንግስት የዴሞክራሲ ምህዳሩን ለማስፋት እና ለሐሳብ ትግል ሰፊ ዕድል በመስጠቱ እንዲሁም ችግሮች በውይይት እንዲፈቱ ባደረገው ጥረት ብዙዎች ይሄንን ዕድል መጠቀማቸውን አስታውሷል።
ይሁንና የአማራን ህዝብ የማይወክሉ እነዚህ ጽንፈኛ ኃይሎች የመንግሥትን ሰላማዊ አማራጭ በመግፋት በውጭ ከሚገኙ ግብረ-አባሮቻቸው ጋር በህቡዕ በመገናኘት የፖለቲካ፣ የወታደራዊ፣ የኢንተለጀንስ፣ የሚዲያ እና የፋይናንስ ክንፍ ማቋቋምቸው እንደተደረሰበት መግለጫው አመልክቷል።
የጋራ ግብረ-ኃይሉ መግለጫ እንዳመለከተው፤ የጽንፈኛ ኃይሎችን የፖለቲካ፣ የወታደራዊ፣ የኢንተለጀንስ፣ የፋይናንስ እና የሚዲያ ክንፍ የሚመራው ዶ/ር ወንድወሰን አሰፋ የተባለ ግለሰብ ሲሆን፤ ይህ ክንፍ በተለያዩ የውጭ ሀገራት ከሚገኙ 16 ጽንፈኛ የዲያስፖራ አባላት ጋር ትስስር በመፍጠር በሚያገኛቸው የሎጀስቲክስ እና የፋይናንስ ድጋፎች በአማራ ክልል ከባህርዳር ከተማ ጀምሮ በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች ታጣቂዎችን የመመልመል፣ የማሰልጠን፣ የማስታጠቅና የማሠማራት ተግባር በማከናወን በክልልና በፌደራል ደረጃ ሽብር እና ግድያ እንዲፈጽሙ ተልዕኮ ሲሰጥ እንደነበር በተደረገ ክትትል እና ምርመራ ተደርሶበታል ብሏል መግለጫው።
ለዚህም በለጠ ሸጋው እና ምሕረት ወዳጆ ወይም በቅጽል ስሙ ምሬ ወዳጆ በተባሉት የጽንፈኛ ኃይሉ ታጣቂ መሪዎች እና ግብረ-አባሮቻቸው ሰሞኑን በትውልድ በቀኤአቸው ግፍና ጭካኔ በተሞለበት አኳሃን የተገደሉት የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ አባልና የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ግርማ የሺጥላ እና የጥቃት ሰለባ የሆኑ የሥራ ባልደረቦቻቸው ማሳያ ናቸው ብሏል የጋራ ግብረ-ኃይሉ መግለጫ።
የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል መግለጫ አክሎም፤ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት የሚገኙ እነዚህ ጽንፈኛ ኃይሎች በፈጠሩት ህቡዕ አደረጃጀት እኩይ ዓላማቸውን ለማስፈጸም በአማራና በሌሎች አካባቢዎች በሚገኙ 130 ወረዳዎች የመለመላቸውንና በህቡዕ ያዘጋጇቸውን 450 ግለሰቦች የአማራ ክልል ህዝብ የመረጣቸውንና በተለያዩ የአመራር እርከኖች ላይ ያስቀመጣቸውን በኃይል በማስወገድ በራሳቸው መዋቅር የመተካት ሥራ ሲሰሩ እንደነበር በክትትል እና በምርመራ የተደረሰባቸው መሆኑን አስታውቋል።
በተጨማሪም ጽንፈኛ ኃይሎች የክልሉን የፀጥታ ኃይልንም በራሳቸው ታጣቂዎች ለመቀየር ተዘጋጅተው እንደነበር የተገኛው መረጃ ማመላከቱን ገልጿል።
ዶ/ር መሥፍን ኃ/ማርያም፣ ዶ/ር ግሩም ላቀውና ሌሎችም በተለያዩ የውጭ ሀገራት የሚኖሩ የጽንፈኛ ኃይሉ ተባባሪዎች ከውጭ ሆነው የፖለቲካ ክንፉን እንደሚያስተባብሩ፤ አንተነህ ብርሃን፣ ወርቁ ጓዴና ሌሎችም ከሀገር ውስጥና ከውጭ የሚላከውን ገንዘብ እንዲቀበሉና ለሽብር ተልዕኮ ማስፈፀሚያ እንዲያውሉ የባንክ አካውንት እንደተከፈተላቸው በክትትልና በተደረገው ምርመራ መረጋገጡን የገለፀው የጋራ ግብረ-ኃይሉ መግለጫ፤ ቴዎድሮስ አስፋውን ጨምሮ ሌሎችም በዚሁ የሽብር እንቅስቃሴ ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን መግለጫው አስታውቋል።
መግለጫው አያይዞም የእነዚህ ጽንፈኛ ኃይሎችን የሚዲያና ፕሮፓጋንዳ ክንፍ የሚመራው መስከርም አበራ በተባለች ግለሰብ መሆኑን ጠቅሶ፤ በዚህ ህቡዕ አደረጃጀት ውስጥ ከሀገር ውስጥ ዳዊት በጋሻው የተባለ ግለሰብ እንዲሁም ከተለያዩ የውጭ ሀገራት ደግሞ ከኢትዮ 360 እና መረጃ ቲቪ ሀብታሙ አያሌው፣ ምንአላቸው ስማቸው፣ ብሩክ ይባስ እና እየሩሳሌም ተ/ፃዲቅ በተጨማሪም ዘመድኩን በቀለ እና ልደቱ አያሌው ከአንከር ሚዲያ መሳይ መኮንን እንዲሁም ሌሎች ግለሰቦች የዚህ እኩይ ዓላማ አስፈፃሚ አባላት መሆናቸውን በምርመራ መረጋገጡን ገልጿል።
እነዚህ ጽንፈኛ ኃይሎች የሀሰት ወሬዎችን በመፍጠር እና ከፍተኛ የሽብር ፕሮፓጋንዳ በመንዛት ህዝቡን በብሄር እና በሀይማኖት በመከፋፈልና በማጋጨት የክልል እና የፌደራል መንግሥትን በኃይል ለመጣል እንዲሁም ሀገሪቱ ከጀመረችው የለውጥና የልማት መንገድ ወጥታ ወደ ለየለት ሁከትና ትርምስ እንድትገባ በህቡዕ ተደራጅተው እየሠሩ መሆናቸውን የገለፀው የጋራ ግብረ ኃይሉ፤ በሀገር ውስጥና በውጭ ሆነው በሀሰት ሀገር ለማፍረስ የሚሰሩ እነዚህን ጨምሮ ሌሎችም በህቡዕ አደረጃጀቱ ውስጥ ያሉ ግለሰቦችም ጭምር በሽብርተኝነት ምርመራ እየተጣራባቸው መሆኑን መግለጫው አመልክቷል።
እነዚህ የሽብር ኃይሎች ከሚኖሩባቸው ሀገራት በአለም አቀፍ የፖሊስ ድርጅት (ኢንተርፖል) እንዲሁም እነሱ ከሚኖሩባቸው ሀገራት መንግሥት የፀጥታ እና የደኅንነት ተቋማት ጋር በተመሠረቱ የትብብር ማዕቀፎች አማካኝነት ወደ ሀገር ቤት ተላልፈው እንዲሰጡ በህግም እንዲጠየቁ እየሰራ መሆኑን እና ይህንኑ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጿል።
የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል መግለጫ አክሎም፤ እነዚህ ውጭ ሀገር የሚኖሩ ተፈላጊዎች ከውጭ ሀገር በሚያገኙት እና በሀገር ውስጥ ያላቸውን ሀብት ተጠቅመው ለዚህ እኩይ ተግባር እያዋሉ መሆኑን በምርመራ የተደረሰበት ስለሆነ በሀገር ውስጥ ያላቸውን ሀብት የመለየት እና በህግ የመቆጣጠር ስራ እየተሰራ መሆኑንም ጭምር አስታውቋል።
ሕገ-መንግሥቱንና ሕገ-መንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለማፍረስ እየተንቀሳቀሱ የነበሩ እነዚህ ጽንፈኛ ኃይሎች የኢትዮጵያን አንድነት ከማይፈልጉ የውጭ ፀረ ሰላም ኃይሎች ጋር ተቀናጅተው መንግሥትን በኃይል ለማስወገድ ሲሰሩ በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራባቸው የሚገኝ መሆኑን ያመለከተው የጋራ ግብረኃይሉ መግለጫ፤ ኅብረተሰቡ የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ የሚወሰደውን እርምጃ ከትጥቅ ማስፈታት ጋር በማያያዝ ውዥንብር ለመፍጠርና የተሳሳተ መረጃ ለማሰራጨት ከሚጥሩ አካላት ራሱን እንዲጠብቅ በጋራ እንዲታገል ጥሪ አቅርቧል።
በመጨረሻም የተጀመረው ህጋዊ ኦፕሬሽን ከግቡ እንዲደርስ ህብረተሰቡ እያደረገ ላለው ከፍተኛ ተሳትፎ የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል ምስጋና እያቀረበ፤ በህግ ቁጥጥር ሥር እንዲውሉ ጥብቅ ክትትል እየተደረገባቸው ያሉ ተፈላጊዎችን ካሉበት ጠቁሞ እንዲያሲዝ በዚህ አጋጣሚ ጥሪውን እያቀረበ በቀጣይ የምንደርስበትን ውጤት ለህዝብ እየገለፀ እንደሚሄድ ያስታውቃል።
የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል
👉 እጃችሁን አንሱ‼️(መነበብ የሚገባው ትንታኔ‼️)👇👇👇
እኛ ተኝተን ስናድር፣ እሱ ቆሞ ሌሊቱን ለሚያነጋው፤ እኛ በነፃነት እንድንኖር፣ እርሱ መስዕዋትነት ለሚከፍለው፤ እኛ ከቤተሰቦቻችን እና ከልጆቻችን ጋር በሠላም እንድንኖር፤ እርሱ ቤተሰቡን ትቶ ግንባር ለሚሰለፈው፤ ስለ እኛ ለሚራበው ለሚጠማው፤ ስለ እኛ ለሚጎሰቆለው አካለ ጎዶሎ ለሚሆነው ለጀግናው የመከላከያ ሠራዊታችን ልናደርግለት የምንችለው በጣም ጥቂት ነገር፤ ምስጋና ማቅረብ ነው። ክብር ለመከላከያ ሠራዊታችን‼️
ማርቲን ሉተር ኪንግ “የሚሞትለት ነገር የሌለው ሰው፤ መኖር የሚገባው ሰው ሊሆን አይችልም” ይላል። ኢትዮጵያውያን የሀገራቸውን ክብር ለማስጠበቅ ለመሞት የማያመነቱ ዜጎች በመሆናቸው፤ በነጻነት መኖር የሚገባቸው ህዝቦች መሆናቸውን ደጋግመው አረጋግጠዋል፡፡ ታዲያ የዚህ አኩሪ የነጻነት ታሪክ ወራሽ እና ግንባር ቀደም ተሰላፊ ደግሞ የመከላከያ ሠራዊታችን ነው፡፡ የመከላከያ ሠራዊታችን በሀገራችን ብቻ ሳይሆን በተለያየ ጊዜ በተሰጠው ዓለም አቀፋዊ እና አህጉራዊ ግዳጆች አገርን የሚያኮራ ገድል የፈጽመ በወርቅ የተጻፈ ድንቅ ታሪክ ያለው ሠራዊት ነው፡፡ ይህ ሠራዊት ሊከበር የሚገባው ሠራዊት ነው፡፡ ሆኖም አንዳንዶች ጉዳዩን በውል ባለመገንዘብ ወይም ባለማጤን አሊያም ተራ የፖለቲካ ትርፍን በማስላት፤ የሠራዊታችንን ዝግጁነት፣ አንድነት እና ህዝባዊነት የሚጎዱ ሠራዊቱን የማይወክሉ አስተያየቶችን ይሰነዝራሉ፡፡ ይህ በጣም አደገኛ ጉዳይ ነው‼️
ሠራዊቱን የአንድ ወገን ጥቅምን ለማስከበር የሚንቀሳቀስ እና የብሔር አጀንዳ ያለው አስመስሎ በማቅረብ፤ የሠራዊቱ ግርማ የሆነው የሚታዩ መሪዎቹን ስም በማጠልሸት፤ በሠራዊቱ አባላት እና በመሪዎቹ እንዲሁም በሕዝቡ መካከል ያለመተማመን በመፍጠር፤ የሠራዊቱን ወይም የተቋሙን ወትሮ ዝግጁነት የሚጎዳ የጠላት ተግባር የሚፈጽሙ ወገኖች አሉ፡፡
በተሳሳተ ቅስቀሳ የተነሱ የህዝብ ልጆች ሲተኩሱበት ጭምር መሣሪያውን የሚዘቀዝቅ ይህን ህዝብ አክባሪ ሠራዊት፤ የራሱን ስንቅ ለህዝብ አድሎ ጦም የሚያድር ይህን የሀገር እና የህዝብ አለኝታ የሆነ ሠራዊት፤ በእጅጉ ማክበር ይኖርብናል፡፡ እንኳን በሀሰት በእውነትም ቢሆን የአንድነታችን ተምሣሌት እና የአገራዊ ህልውናችን ዋልታ በሆነው ሠራዊታችን ላይ ትችት ለመሰንዘር ሰባ ጊዜ ማሰብ ይኖርብናል፡፡ ብንወድም ብንጠላም ዘወትር ችግር በማያጣው የአፍሪካ ቀንድ የምንኖር በመሆናችን፤ የመከላከያ ሠራዊታችን ጥንካሬ ለአገራዊ ሰላም እና ደህንነታችን መከበር ያለው ድርሻ ወሳኝ ሆኖ መቀጥሉ ሳይታለም የተፈታ ጉዳይ ነው፡፡ ከአሁናዊ አገራዊ ሁኔታ አንጻር ብቻ ሳይሆን፤ ትናንትም ሆን ወደፊት የኢትዮጵያን ሙሉ ገጽታ ተላብሶ የምንወዳትን አገር ህልውና እና አንድነት ለማስጠበቅ መስዋዕት የሚሆነው የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት ነው‼️
የጀግናው የመከላከያ ሠራዊታችን የዘወትር መዝሙር ኢትዮጵያ ነች፡፡ የመከላከያ ሠራዊታችን፤
"የኩሩ ህዝቦች መኖሪያ፤ የህብረ ብሔር ቡቃያ፤
የሰላም ተምሳሌት አርማ፤ የቀለሞች ህብር ኢትዮጵያ" እያለ የሚዘምር ተቋም ነው።
"ኢትዮጵያ በኛ ደም ደምቃ፣ በአጽማችን ፍላፃ ተከብራ፤
እንደ ታፈረች እንድትኖር፣ ከዘመን ዘመን ተከብራ፤
ከመሞትም በላይ እንሙት፣ ደማችን ሺህ ጊዜ ይፍሰስ፤
አየር አፋሩ ይባረክ፣ ስሟ ምንጊዜም ይታደስ" የሚል ቃል ኪዳን ያለውን፤ ለሀገር እና ለሕዝብ ክብር መጠበቅ የማይተካ ህይወቱን አሳልፎ የሚሰጠውን የመከላከያ ሠራዊታችንን መልካም ስም የሚጎዳ ቅስቀሳ ማድረግ ሃጢያት፣ ወንጀል እና ፀያፍ ተግባር ነው፡፡ ስለዚህ ከመከላከያ ሠራዊታችን ላይ እጃሁን አንሱ‼️
አንድ ተቋም በመሪው ይወክላል። በወታደራዊ ተቋማት ደግሞ የመሪ ጉዳይ ልዩ ትኩረት የሚሰጠው ነው፡፡ የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት የአባላቱ ድምር ሲሆን፤ መሪው የተቋሙ ምስል ነው። ወታደሮች የመሪዎችን ሚና ትልቅነት ለመግለጽ፤ “በበግ ከሚመራ የአንበሳ መንጋ፤ በአንበሳ የሚመራ የበግ መንጋ ይበልጣል” ይላሉ። የሠራዊታችን ታሪካዊ፣ ባህላዊ፣ ስልጠናዊ፣ ትጥቃዊ፣ ልምዳዊ በአጭሩ ተቋማዊ የጥንካሬ ምንጮች እንዳሉ ሆነው፤ የመከላከያ ሠራዊት የአንበሳ ግርማ የሚሆኑት መሪዎቹ ናቸው‼️
በወታደራዊ ጉዳዮች የመሪው ሚና ወሳኝ ነው፡፡ በመሆኑም በተቋሙ መሪዎች ላይ የሚሰነዘሩ ስም የማጥፋት ዘመቻዎች፤ በመሪውና በተመሪው መካከል ክፍተት በመፍጠር፤ የተቋሙን ብቃት የሚጎዳ በመሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ ድርጊቱ ከህግ አንጻር ሀገርን ከመክዳት ወንጀል የሚታሰብ፤ ከሞራል አንፃር ደግሞ ነውር ነው፡፡ ስለዚህ በመከላከያ ተቋም ላይ የሚሰነዘሩ እና የተቋሙን መልካም ዝና የሚጎዱ አስተያየቶች እና ትችቶች ሀገርን የሚጎዳ አፍራሽ ውጤት ያላቸው መሆኑን ተገንዝበን መጠንቀቅ ይኖርብናል‼️
የመከላከያ ሠራዊታችን ከለውጡ በፊትም ሆነ በኋላ በዚህች አገር የተከሰቱትን መከራዎች ሁሉ ተሸክሞ፤ የሀገር ህልውና እና አንድነት ተጠብቆ እንዲዘልቅ ለማድረግ በላብ፣ በደም እና በህይወት ከፍተኛ መስዋዕነት የከፈለ ሠራዊት ነው፡፡ ከሁሉም በላይ ሕገ መንግሥታዊ ግዳጆቹን በውል ተገንዝቦ እና አክብሮ ለመጓዝ ጥረት ያደረገ እና ተቋማዊ ሪፎርም በማካሄድ የኢትዮጵያን ሠላም ለማረጋግጥ አብዝቶ የለፋ እና ራሱን እያጠናከረ የመጣ ተቋም ነው፡፡
የመከላከያ ሠራዊታችን አንዳንድ ፖለቲከኞች ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ባለመወጣቸው ሳቢያ በሚከሰቱ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ግፊት የሚቀሰቀሱ ህዝባዊ ቁጣዎች፤ ሀገራዊ የደህንነት ሥጋት የሚፈጥሩበት ሁኔታ እየተፈጠረ በተደጋጋሚ እሣት የማጥፋት ሥራዎችን ለመስራት እየተገደደ፤ እረፍት አጥቶ ደፋ ቀና የሚል የሀገር ዋልታ ሠራዊት ነው‼️
ጀግናው መከላከያ ሠራዊታችን በኢትዮጵያዊ እሴቶች ታንጾ፣ "ከራስ በፊት ለሕዝብና ለሀገር" የሚል ተቋማዊ እሴት የተገነባ የሀገራችን የመጨረሻ ምሽግ ነው፡፡ በመሆኑም፤ ሕዝባዊው ሠራዊታችን መመስገን ሲገባው፤ በማወቀም ይሁን ባለማወቅ መልካም ስሙን የሚያጠለሽ ቅስቀሳ ከማድረግ መቆጠብ ይገባል፡፡ የሠራዊታችን ታሪካዊ፣ ባህላዊ፣ ስልጠናዊ፣ ድርጅታዊ እና ልምዳዊ የጥንካሬ ምንጮች እንዳሉ ሆነው፤ የመከላከያ ሠራዊታችን ግርማ እና ሞገስ መሪዎቹ ናቸው፡፡ ስለዚህ ሠራዊቱን የአንድ ወገን ጥቅምን ለማስከበር የተሰለፈ እና የብሔር አጀንዳ ያለው አስመስሎ በማቅረብ በመሪዎቹ እና በአባላቱ መካከል ያለመተማመን በመፍጠር፤ የተቋሙን ወትሮ ዝግጁነት የሚጎዳ የስም ማጥፋት መንዛት የምንወዳትን ሀገር የሚጎዳ የጠላት ተግባር በመሆኑ፤ በዚህ እኩይ እሳቤ ውስጥ ያላችሁ ሁሉ፤ ከሠራዊታችን ላይ እጃችሁን አንሱ‼️
Via~አዲስ ዋልታ መፅሔት
⚽ የእሁድ ማለዳ የወጡ የቅድመ ዝውውር ወሬዎች፡ ኔይማር፣ ኬን፣ ባሌ፣ ካንቴ፣ ሚልነር፣ ኮቫቺች፣ ኮሎ ሙአኒ፣ ጁድ ቤሊንግሃም፣ ጋሬዝ ቤል፣ ማቲዎ ኮቫቺች፣ ጆናታን ዴቪድ
🆕➥ በሼክ ጃሲም እየተመራ ያለው የኳታር ክለቡን ለመግዛት የቀረበው ጥያቄ የሚሳካ ከሆነ ማንቸስተር ዩናይትዶች የ31 አመቱ የፓሪስ-ሴንት ዠርማን ብራዚላዊ አጥቂ ኔይማርን ለማዘዋወር ይፈልጋሉ። (Sun)
🆕➥ የ 19 አመቱ የቦርሲያ ዶርትመንድ እንግሊዛዊ አማካይ ጁድ ቤሊንግሃም ወደ ሪያል ማድሪድ መቀላቀልን መርጧል። ነገርግን ስምምነቱ የስፔኑ ክለብ ለተጭዋቹ ዝውውር የ 120m ዩሮ ለመክፈል ፍቃደኛ ባለመሆናቸው ምክንያት ዝውውሩ የመጠናቀቅ ችግር ገጥሞታል። (AS - in Spanish)
🆕➥ ቶተንሃሞች የ 29 አመቱ እንግሊዛዊ አጥቂ ሃሪ ኬን ለማስፈረም ከቼልሲ ጥያቄ እንደሚቀርብላቸው እየጠበቁ ሲሆን፣ ሰማያዊዎቹ ማውሪሲዮ ፖቸቲኖን በአሰልጣኝነት ለመሾም መቃረባቸውን ተከትሎ በአጥቂው ላይ ያላቸው ፍላጎት ጨምሯል። (Talksport)
🆕➥ የስፐርሱ ሊቀመንበር ዳንኤል ሌቪ ኬንን ለማንችስተር ዩናይትድ ወይም ቼልሲ በቀላሉ እንደማይሸጥ የሚጠበቅ ሲሆን፣ ድርድሩን ጠንከር ያደርጉባቸዋል ተብሎ ይጠበቃል። ቀያይ ሰይጣኖቹ የ24 አመቱን የናፖሊ ናይጄሪያዊ አጥቂ ቪክቶር ኦሲምሄን እና የጁቬንቱሱን የ23 አመት ሰርቢያ አጥቂ ዱሳን ቭላሆቪች ለማስፈረም በአማራጭ ዝርዝር ውስጥ አካተዋቸዋል። (Daily Mail)
🆕➥ የ33 አመቱ የቀድሞ የቶተንሃም፣ የሪያል ማድሪድ እና የዌልስ አጥቂ ጋሬዝ ቤል የሬክስሃም ባለቤት የሆኑት የሆሊውዶቹ ሪያን ሬይኖልድስ እና ሮብ ማኬልሄኒ ወደ ከፍተኛው እግር ኳስ ሊግ ማደጋቸውን ተከትሎ፣ ክለቡን እንዲቀላቀል ያቀረቡለትን ጥያቄ ውድቅ አድርጓል። (Sky Sports)
🆕➥ ብራይተን የ 37 አመቱ የሊቨርፑል ጀምስ ሚልነርን ለማዘዋወር በዝግጅት ላይ ናቸው። የቀድሞ እንግሊዛዊ አማካይ በክረምቱ ከኮንትራት ነፃ ሲሆን ወደፈለገው ክለብ ማምራት ይችላል። (The Athletic - subscription required)
🆕➥ ቼልሲዎች የ 27 አመቱን የኢንተር ሚላን እና የካሜሩን ግብ ጠባቂ አንድሬ ኦናናን የዝውውር ስምምነት አካል አድርገው የ 28 አመቱ ስፔናዊ ጠባቂ ኬፓ አሪዛባላጋ ለኢንተር መስጠት ይፈልጋሉ። ነገር ግን የጣሊያኑ ክለብ በዚህ ሃሳብ ምንም ፍላጎት የላቸውም። ኢንተፎች ከኬፓ ይልቅ የ 23 አመቱ እንግሊዛዊ ተከላካይ ትሬቮህ ቻሎባህ እና አማካዩን ሩበን ሎፍተስ ቼክን ያደንቃሉ። (Gazzetta - in Italian)
🆕➥ ቼልሲዎች የ28 አመቱን ክሮሺያዊ አማካኝ ማቲዮ ኮቫቺችን ከፕሪምየር ሊግ ውጪ ላለ ክለብ መሸጥ ይመርጣሉ። የቀድሞ የሰማያዊዎቹ አለቃ ቶማስ ቱቸል በባየር ሙኒክ ከአማካዩ ጋር በድጋሚ የመገናኘት ፍላጎት አላቸው። (Evening Standard)
🆕➥ ሊቨርፑል እና አርሰናል ለቼልሲው እንግሊዛዊ አማካኝ ሜሰን ማውንት የዝውውር ጥያቄ አቅርበዋል። የ24 አመቱ ተጫዋች አሁን ያለው ስምምነት በ2024 ክረምት ላይ ያበቃል። (Football Insider)
🆕➥ አርሰናል የ32 አመቱን የቼልሲ እና ፈረንሳዊ አማካኝ ንጎሎ ካንቴ ለማዘዋወር እያሰበ ሲሆን። መድፈኞቹ የለንደኑ ተቀናቃኞቻቸው በቀጣይ ክረምት የቡድናቸውን ተጭዋቾች መጠን መቀነስ እንዳለባቸው ስለሚያውቁ አዲስ ኮንትራት ያቀርቡለታል ብለው አይጠብቁም። (Mirror)
🆕➥ የ24 አመቱ የዌስትሃም እና የእንግሊዝ አማካኝ ዴክላን ራይስ የአርሰናል ዋና የክረምቱ የዝውውር ኢላማ የሆነ ሲሆን፣ ፈረንሳዊው ሌዠንድ መድፈኞቹን ከለቀቀ ከ8 አመታት በኋላ ራይስ የክለቡ 'አዲሱ ፓትሪክ ቪየራ' ሊሆን ይችላል ተብሎ ይጠበቃል። (Express)
🆕➥ የፓሪስ ሴንት ዠርሜይን አጥቂ Kylian Mbappe የኢንትራክት ፍራንክፈርት የፊት መስመር ተጫዋች እና የ24 አመቱ የፈረንሳይ ብሄራዊ ቡድን አጋሩ ራንዳል ኮሎ ሙአኒ ክለቡን እንዲቀላቀል ለማሳመንና ለማበረታታት እየሞከረ ነው። (Christian Falk)
🆕➥ ሊቨርፑሎች የ25 አመቱን የፓሪስ ሴንት ዠርሜይን ሬናቶ ሳንቼስን በቅርበት እየተከታተሉት ይገኛሉ። ፖርቹጋላዊው አማካኝ የአንፊልዱ ቡድን ቀጣይ ክረምት ትልቅ የመልሶ ግንባታ አካል ለማድረግ የታቀደ ሲሆን የሊግ 1 ክለብን ሊለቅ ይችላል ተብሏል። (Football Insider)
🆕➥ የ23 አመቱ ካናዳዊ አጥቂ ጆናታን ዴቪድ በዚህ ክረምት የፈረንሳዩን ክለብ ሊል እንደሚለቅ ይጠበቃል። ይህንም ተከትሎ ቶተንሃም ፣ማንቸስተር ዩናይትድ ፣ቼልሲ እና ፓሪስ ሴንት ዠርሜይን የተጭዋቹ ፈላኪ ከሆኑ በርካታ ክለቦች ውስጥ መሆናቸውን አሳውቀዋል። (L'Equipe)
🆕➥ አርሰናሎች የ23 አመቱን ቤልጄማዊ አጥቂ ሎይስ ኦፔንዳ ከፈረንሳዩ ሌንስ ለማስፈረም እንቅስቃሴ ሊያደርጉ ይችላሉ ፣ምንም እንኳን አስቶንቪላዎችም በዝውውሩ ላይ ፍላጎት እንዳላቸው ቢረዱም። (Daily Mail)
🆕➥ ኤቨርተኖች የ23 አመቱን የስቶክ ሲቲ አጥቂ ታይሬስ ካምቤልን በዚህ ክረምት ለማስፈረም አቅደዋል። (Football Insider)
🆕➥ አርሰናል፣ ኒውካስል እና አስቶንቪላ ሀሙስ በቫሌንሲያ 2-1 በተሸነፉበት ጫወታ የ18 አመቱን የሪያል ቫላዶሊድ የቀኝ መስመር ተከላካይ ኢቫን ፍሬስኔዳ እንቅስቃሴ ተመልክተዋል። (90min com)
🆕➥ ኒውካስል እና ክሪስታል ፓላስ የሬንጀርስ እና ስኮትላንዳዊው አማካኝ ካሎም አደምሰን ዝውውር ተስፋቸውን ሊያጡ ነው። የ15 አመቱ ወጣት በግላስጎው ክለብ የመጀመሪያውን ፕሮፌሽናል ኮንትራቱን ሊፈርም ነው ተብሏል። (Daily Record via Mirror)
📌 ከተመቻችሁ LIKE ማድረጋችሁን አትርሱ!
📌 ጓደኞቻችሁ እንዲያነቡት SHARE ያድርጉላቸው!
📌 አስተያየት ካላችሁም ከታች COMMENT አድርጉ!
ግርማ የሺጥላን እንደገደሉት ያደረጉት የስልክ ልውውጥ ነው። በለጠ ሸጋው የተባለው የሸዋ ፋኖ መሪ ከምሬ ወዳጆ የምስራቅ አማራ (ወሎ) ፋኖ መሪ ጋር በስልክ ሲነጋገሩ ነው።
ቤተሰብ ይሁኑ!
ቴሌግራም፦ #ሼር #Join
https://t.me/CommandoAndAirborneCommand
You Tube ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉን🙏🇪🇹🙏
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.youtube.com/@theredtigers_4034
ሰበር መረጃ‼️
የግርማ የሺጥላን ህይወት በጎዳና ላይ ያስቀረው በለጠ ጋሻው የተባለ የፅንፈኛ ሀይሉ ቡድን መሪ ነው:: ክፍል 1
ነገሩ እንዲህ ነው ለአማራ ህዝብ እልፍ ሲልም ለሀገሩ ደከመኝ ሰለቸኝ የማይለው የአማራ ብልጽግና ጽ/ቤት ሀላፊ ግርማ የሺጥላ በትውልድ ቅየው በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ እንዲሉ አንድም ቤተሰቦቹን በሌላ በኩል ደግሞ የቀየውን ማህበረሰብ የሰላምና የልማት ጥያቄዎች ተቀብሎ ለመፍታት ሲያወያይ ቆይቶ ሀገር ሰላም ነው ብሎ ከቤተሰቦቹ፡ከስራ ባልደረቦቹና ከጠባቂዎቹ ጋር በ6 ተሸከርካሪዎች ወደ አዲስ አበባ ሲመለሱ መንገድ ላይ አድፍጠው በጠበቁት የበለጠ ጋሻው ጅቦች ህይወቱን አጥቷል፡፡የምስራቅ አማራ ፋኖ ብርጌድ አዛዥ የሆነው በለጠ ጋሻው የኋላሸትና ጌታቸው ከሚባሉ የፅንፈኛ ሀይሉ አስተባባሪዎች ጋር 40 ታጣቂ ቡድኑን በመያዝ ሰሜን ሸዋ ዞን መንዝ ጌራ ወረዳ 020 ደፈርጌ ቀበሌ በተለምዶ ዋስሎጅ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ እንደ ጅብ ከተደበቁበት በመውጣት የጥይት እሩምታ በመክፈት የግርማ የሺጥላን ህይወት ቀጥፈውታል፡፡
ቤተሰብ ይሁኑ!
ቴሌግራም፦ #ሼር #Join
https://t.me/CommandoAndAirborneCommand
You Tube ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉን🙏🇪🇹🙏
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.youtube.com/@theredtigers_4034
በአማራ ክልል ሕገመንግስታዊ ስርዓቱን በማፍረስ ክልላዊ ስልጣንን በኃይል ለመቆጣጠር በሚጥሩ ጽንፈኛ ኃይሎች ላይ የማያዳግም እርምጃ እየወሰደ መሆኑን የጸጥታና የደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታወቀ
በአማራ ክልል ሕገመንግስታዊ ስርዓቱን በማፍረስ ክልላዊ ስልጣንን በኃይል ለመቆጣጠር በሚጥሩ ጽንፈኛ ኃይሎች ላይ የማያዳግም እርምጃ እየወሰደ መሆኑን የጸጥታና የደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታወቀ ፡፡
የጸጥታና የደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው÷ ለአማራ ህዝብ እንታገላለን በሚል በውስጥም በውጭም በመቀናጀት የራሳቸውን ህቡዕ አደረጃጀት የፈጠሩ አካላት ከመሰል ቡድኖች ጋር በመቀናጀት የህዝቡን የቁርጥ ቀን ልጆች መልሰው እየበሉ ይገኛሉ፡፡
እነዚህ ፅንፈኛ ኃይሎች በትናንትናው ዕለትም የአማራ ክልል ብልፅግና ጽ/ቤት ሓላፊ እና የክልሉ የቁርጥ ቀን ልጅ የሆነውን ግርማ የሺጥላን በመግደል አስነዋሪ ድርጊታቸውን አሰመስክረዋል፡፡
ይሄንን እኩይ የጥፋት ሴራ እየፈፀሙ ያሉ ፅንፈኛ ኃይሎች የአማራ ህዝብ የልማትና የሰላም ተጠቃሚ እንዳይሆንና የተረጋጋ ህይወት እንዳይኖረው እንዲሁም በመንግስት የሚወሰኑ ውሳኔዎች እንዳይተገበሩ እንቅፋት ሲፈጥሩ መቆየታቸውን የጋራ ግብረ ኃይሉ መግለጫ አመልክቷል፡፡
ቤተሰብ ይሁኑ!
ቴሌግራም፦ #ሼር #Join
https://t.me/CommandoAndAirborneCommand
You Tube ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉን🙏🇪🇹🙏
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.youtube.com/@theredtigers_4034
📰⚽ የዓርብ ምሽት ቅድመ ዝውውር ወሬዎች፡ ቤሊንግሃም፣ ናግልስማን፣ ካሴሚሮ፣ ኮቫቺች፣ ግራቨንበርች፣ ቶኒ፣ ፌሊክስ፣ ዲላን ራይስ፣ ኪራን ቲየርኒ፣ ጆአዎ ፔድሮ፣ ታንጉይ ንዶምቤሌ፣ ቫንደርሰን
🆕➥የሪያል ማድሪድ ባለስልጣናት የ19 አመቱ የቦሩሲያ ዶርትሙንድ እንግሊዛዊ አማካይ ጁድ ቤሊንግሃም በዚህ ክረምት የስፔኑን ክለብ እንዲቀላቀል ለማሳመን በዚህ ሳምንት ወደ ጀርመን ይጓዛሉ። (Marca - in Spanish)
🆕➥የ24 አመቱ የዌስትሃም እና የእንግሊዝ አማካኝ ዴላን ራይስ በዚህ ክረምት በአርሰናል የዝውውር ዝርዝር ሊስት በቀዳሚነት ተቀምጦ ላይ ይገኛል። (Telegraph - subscription required)
🆕➥የ31 አመቱ የማንቸስተር ዩናይትድ እና ብራዚላዊ አማካይ ካሴሚሮ በባየር ሙኒኩ አለቃ ቶማስ ቱቸል ይፈለጋል። የጀርመኑ ክለብ የክረምቱ የዝውውር ኢላማ ነው። (Kicker - in German)
🆕➥በተጨማሪም የባየርኑ አለቃ ቱቸል ከ 28 አመቱ የቼልሲ እና ክሮሺያ አማካኝ ማቲዮ ኮቫቺች ጋር እንደገና በሙኒክ አብሮ የመስራት ፍላጎት አላቸው። (Sport1 - in German)
🆕➥ምንም እንኳን የሊቨርፑል፣ ማንቸስተር ዩናይትድ እና አርሰናል በተጭዋቹ ላይ ፍላጎት እንዳላቸው ቢረረዱም፣ ባየርኖች ግን የ20 አመቱን ኔዘርላንዳዊ አማካኝ ሪያን ግራቨንበርች በዚህ ክረምት የመሸጥ ፍላጎት የላቸውም። (CaughtOffside)
🆕➥የአርሰናል ሪከርድ ፈራሚ ኒኮላስ ፔፔ በድጋሚ ለክለቡ የመሰለፍ እድል እንደሌለው ተቆጥሯል። አርሰናል የጣሊያኑ ቡድን ከመውረድ ከተረፈ እና የሚፈለገውን የጨዋታ መጠን ካደረገ ፓብሎ ማሪን ለሞንዛ በመሸጥ 6 ሚሊየን ፓውንድ የሚያስገቡ ይሆናል። (CaughtOffside)
🆕➥የቀድሞ የባየር ሙኒክ አለቃ ጁሊያን ናጌልስማን ቀጣዩ የቶተንሃም ሆትስፐር አሰልጣኝ ለመሆን ከቀረቡት አራት አማራጮች ዝርዝር ውስጥ አናት ላይ ተቀምጠዋል። ነገርግን የ35 አመቱ ጀርመናዊ ጥቅል ኮንትራት ፓኬጅ ለለንደኞቹ በጣም ውድ ሊሆን ይችላል። (Telegraph - subscription required)
🆕➥የቀድሞ የማንቸስተር ዩናይትድ ጊዜያዊ አሰልጣኝ ራልፍ ራንኒክ፣ ኔጌልስማን ቀጣዩ የቶተንሃም አለቃ እንዲሆኑ ምክራቸውን ሰጥተዋል። (Guardian, via Sky Sports Germany)
🆕➥ማንቸስተር ሲቲዎች የአርሰናሉን የግራ መስመር ተከላካይ ኪይራን ቲየርኒ ለማስፈረም እየፈለጉ ሲሆን አስቶንቪላ እና ኒውካስል ዩናይትዶችም የ25 አመቱን ስኮትላንዳዊ ኢንተርናሽናል ማስፈረም ይፈልጋሉ። (Football Insider)
🆕➥አስቶንቪላዎች የብሬንትፎርዱን እንግሊዛዊውን አጥቂ ኢቫን ቶኒ ለማስፈረም እየሞከሩ ነው። (Football Insider)
🆕➥ፖርቹጋላዊው አጥቂ ጆአዎ ፊሊክስ በክረምቱ ወደ አትሌቲኮ ማድሪድ አይመለስም። የ23 አመቱ ተጫዋች በቼልሲ ያለውን የውሰት ውል ሊያራዝም ነው ተብሏል። (Sun)
🆕➥ብራይተን የ21 አመቱን ብራዚላዊ አጥቂ ጆአዎ ፔድሮን ከዋትፎርድ ለማስፈረም ተቃርቧል። (Mail)
🆕➥በተጨማሪም የብራይተኑ አለቃ ሮቤርቶ ዴ ዘረቢ የደቡብ-ባህር ዳርቻውን ክለብ ወደፊት እንዴት እንደሚመራ ከክለቡ ቁልፍ ሰዎች ጋር ለመነጋገር አቅደዋል፣ ጣሊያናዊው አሰልጣኝ የተጭዋቾችን ምልመላ በተመለከተ ተጨማሪ ቁጥጥር መብት እንዲሰጠው ለማድረግ ይፈልጋል። (Nicolo Schira)
🆕➥ናፖሊ የ26 አመቱን ፈረንሳዊ አማካኝ ታንጉይ ንዶምቤሌን ከቶተንሃም በቋሚ ውል ለማስፈረም ኮንትራቱ ላይ የሰፈረውም የ 30m ዩሮ (£26.5m) አንቀፅ አይጠቀሙበትም። (Fabrizio Romano)
🆕➥ማንቸስተር ዩናይትዶች የሞናኮውን የ21 አመቱን ብራዚላዊ የቀኝ መስመር ተከላካይ ቫንደርሰንን ለማስፈረም ጥያቄ ሊያቀርቡ እየተዘጋጁ ቢሆንም ከሌሎች የፕሪሚየር ሊግ ቡድኖች ፉክክር ሊገጥማቸው ይችላል። (RMC Sport via Sun)
🆕➥ኤሲ ሚላን በመድፈኞቹ አዲስ ኮንትራት ያልፈረመው የ23 አመቱ እንግሊዛዊ የክንፍ መስመር ተጫዋች ሬይስ ኔልሰን ሁኔታ እየተከታተሉት ነው። ተጭዋቹ ከሲዝኑ መጠናቀቅ በኃላ ከውል ነፃ ይሆናል። (Calciomercato via Football Italia - in Italian)
🆕➥ኤሲ ሚላን የ27 አመቱን የቼልሲ እንግሊዛዊ አማካይ ሩበን ሎፍተስ ቼክን ማስፈረም ይፈልጋሉ። (90min)
🆕➥ብሬንትፎርድ፣ ፉልሃም እና ብራይተን በዚህ የውድድር አመት ለቤልጂየሙ ሊግ መሪ ጌንክ 14 ግቦችን ያስቆጠረውን የ25 አመቱ ጋናዊ አጥቂ ጆሴፍ ፓይንትሲልን ለማስፈረም እየተከታተሉት ነው። (Telegraph - subscription required)
📌 ከተመቻችሁ LIKE ማድረጋችሁን አትርሱ!
📌 ጓደኞቻችሁ እንዲያነቡት SHARE ያድርጉላቸው!
📌 አስተያየት ካላችሁም ከታች COMMENT አድርጉ!
ቤተሰብ ይሁኑ!
ቴሌግራም፦ #ሼር #Join
https://t.me/CommandoAndAirborneCommand
You Tube ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉን🙏🇪🇹🙏
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.youtube.com/@theredtigers_4034
ምሳሌ!
የትውልዱ ሽልማት
(በሳሙኤል ሙሉጌታ)
እግር ኳስን ከጉልበታሞች ትግል ወደ አእምሯዊ የጥበብ ጨዋታ ከፍ ካደረጉት ተጫዋቾች መካከል ስሙ በቀዳሚነት ይጠቀሳል፡፡ እሱ በሜዳ ውስጥ ካለ አንድ የእግር ኳስ ተአምር ይኖራል፡፡ ኳስ በግራ እግሩ ታግዛ አንዳች አስማት ትሰራለች። ጥበበኛው ተጫዋች እግሩ ስር የገባችውን ኳስ የሚገባትን የክብር ካባ አልብሶ ወዲህ ወዲያ እያደረገ ሲያንሸራሽራት ለተመለከተ አብሮት የሚጫወት ሰው ያለ አይመስልም፡፡ እሱ ዘንድ ጓንቱን የማይሰጥ በረኛ፣ ከኋላው የማይሮጥ ተከላካይ፣ እጁን በአፉ የማይጭን ደጋፊ የለም፡፡ እሱ ለእግር ኳስ ስፖርት አፍቃሪያን የተሰጠ የዚህ ትውልድ ታላቅ ሽልማት ነው፡፡ ሊዮኔል አንድሬስ ሜሲ!
ዘመን በተሻገረው ስፖርት ውስጥ የራሱን ህያው ታሪክ በተመልካች ልብ ውስጥ ይፅፍ ዘንድ እ.ኤ.አ በ1987 በአርጀንቲናዋ ሮዛሪዮ ሳንታፌ ከተማ ተወለደ። ገና በልጅነት እድሜውና ባልጠነከረ አጥንቱ አጥንትን የሚያለመልም ጥበብ በጎዳናዎች ላይ ማሳየት የጀመረው ሜሲ ለግዙፎች ብቻ የተሰጠ በሚመስለው ስፖርት ላይ አዲስ አብዮት ፈጠረ፡፡ በእድሜም በቁመትም ከሚበልጡት ተጫዋቾች ጋር ቢጫወትም በሚያሳያቸው እግር ኳሳዊ ውሳኔዎችና ድሪብሎች ከሁሉም በላይ ያለ እድሜው ገዘፈ።
ይህን ችሎታውን ያዩት ኒውልስ ኦልድ ቦይስ (Newell's Old Boys) እ.ኤ.አ በ1995 የዛሬውን የሜዳ ላይ ልዑሉን “ሀ” ብለው ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ቡድናቸው ቀላቀሉት፡፡ ከ5 ዓመታት ቆይታ በኋላም የአርጀንቲናው ሀያል ክለብ ሪቨርፕሌት ሊያስፈርሙት ፈልገው የነበረ ቢሆንም በጥቃቅን ነገሮች ሳይስማሙ ትተውት በመሄድ ታሪካዊ ስህተት ሰሩ፡፡
በወቅቱ በአማካይ ከ5 ሺሕ ህፃናት ውስጥ በአንድ ብቻ የሚከሰተው የእድገት ሆርሞን እጥረት (Growth Hormone Deficiency) ችግር በሜሲም ላይ የነበረ ሲሆን ወላጅ አባቱ ልጄ ወደ ታላቅነቱ የሚያደርገውን ጉዞ የሚገታ እንቅፋት ነው ብለው በእጅጉ ይጨነቁ ነበር፡፡ ተፈጥሮ ለሊዮኔል ሜሲ በእግር ኳስ ስፖርት ላይ የሚጠበብበትን ጥበብ በትልቁ ለግሳው ስታበቃ ከቁመቱ ግን ቀነሰችበት፡፡ ነገር ግን ሊዮ አንዴ ለታላቅነት ተፈጥሯልና ጋሬጣውን የሚሻገርበት አጋጣሚ አላጣም፡፡
የዛሬ አያያዙን አይተው የነገ መድረሻውን ለመገመት ያልከበዳቸው የባርሴሎና አመራሮች ግን ትንሹን ልጅ የህክምና ወጪውን ችለው ለመውሰድ ተስማሙ፡፡ ሊዮም ከትውልድ ሀገሩ ተሻግሮ ወደ ሀገረ ስፔን አመራ፡፡ ድንቅ ድንቅ እግር ኳሰኞችን በማፍራት ወደ ሚታወቀው ወደ ላሜሲያ አካዳሚም ተቀላቀለ፡፡ ባርሴሎናዎች አልተሳሳቱም ነበር! ህክምናው በተሳካ ሁኔታ ሲጠናቀቅ እንደተባለውና እንደተገመተው ሜሲ በእግር ኳስ ሙሉ ሰው ሆነ፡፡ በአጭር ጊዜ ውስጥም ከላሜሲያ ደምቆ በመውጣት ወደ ዋናው ቡድን ተሻገረ፡፡
በዚህም እ.ኤ.አ በ2005 ባርሴሎና ከአልባሴቴ በሚያደርጉት ጨዋታ ላይ ተቀይሮ በመግባትና በወቅቱ የቡድን አጋሩ ከሆነው ከሌላኛው ጥበበኛ ሮላንዲኒሆ ጎቾ የተሻገረለትን ኳስ በድንቅ ሁኔታ በማስቆጠር የጎል አካውንቱን ከፈተ፡፡ ከዚህ በኋላ ሊዮኔል አንድሬስ ሜሲ የሚለው ስም በእግር ኳስ ኮሜንታተሮችና በስፖርቱ አፍቃሪያን ዘንድ ከአፍ የማይጠፋ ማር ሆነ፡፡ ሜሲ ጎል አስቆጥሯል የሚሉ የጠዋት ዜናዎች የተለመዱ ሆኑ፡፡ በምትሀተኛ ግራ እግሮቹ አቅልን የሚያስቱ የሜዳ ላይ ተአምሮች፣ ለማየት በሚማርኩት የማይቆራረጥ ድሪብሎቹ፣ በሚደንቁ ጎሎቹና በአስገራሚ አሲስቶቹ ለደጋፊዎቹ የደስታ ምንጭ፤ ለተቃራኒ ቡድን ተከላካይና በረኞች ደግሞ የሜዳ ላይ ቅዠት ሆነ፡፡
የባላንዶር ሽልማትን ሰባት ጊዜ ማሸነፍ የቻለው ሊዮ እስካሁን ካደረጋቸው ከ1 ሺሕ በሚልቁ ጨዋታዎች ውስጥ ከ800 በላይ ጎሎችን ከመረብ ማሳረፍ ችሏል፡፡ ከነዚህ ውስጥ ደግሞ 57 የሚሆኑቱ ሦስታዎች (ሀትሪኮች) ናቸው፡፡ ጎሎችን ማስቆጠር ብቻም ሳይሆን ለቡድን አጋሮቹ አመቻችቶ በማቀበል የማይታማው ጥበበኛው ከ350 በላይ ኳሶችን በዚሁ ሂደት ውስጥ ለጎል አመቻችቶ አቀብሏል፡፡ ሌሎች ተደምጠው የማይጠገቡ፤ ተፅፈው የማያልቁ ብዙ ሪከርዶችም በስሙ ተመዝግቧል፡፡
ብቻ ሊዮኔል አንድሬስ ሜሲ ሁለት አስርት ዓመታት በሚጠጋው የሜዳ ላይ ቆይታ ብዙ ነገር መስራት የቻለ ምሳሌ ነው፡፡ ከሌላኛው የዘመን ተቀናቃኙ ክርስቲያኖ ሮናልዶ ጋር በመሆን የትውልዱን የእግር ኳስ ስፖርት ዘመን አሳምሯል፡፡ ታዳጊዎች የሜዳ ላይ ጥበቡን እየተመለከቱ አርአያ አድርገውታል፡፡ እግር ኳስም በምላሿ ከስፔን ላሊጋ እስከ ፈረንሳይ ሊግ አንድ ዋንጫ፣ ከሻምፒዮንስ ሊግ እስከ ንጉስ ዋንጫና ሌሎች ክብሮችን በመሸለም የሰራላትን እልፍ አዕላፍ ውለታ ለመክፈል ሞክራለች፡፡ ሜሲ አንድ ይወቀስበት የነበረውን “ለሀገሩ አልሰራም” ትችትንም ከቡድን አጋሮቹ ጋር በመሆን በኳታሩ የዓለም ዋንጫ ላይ የውድድሩ ኮከብ በመባል ሳይቀር ክብሩን ተጎናፅፏል፡፡ እሱ ለዘመኑ የእግር ኳስ አፍቃሪያን የተበረከተ ታላቅ ሽልማት ነው፡፡ ሊዮኔል አንድሬስ ሜሲ!
ቤተሰብ ይሁኑ!
ቴሌግራም፦ #ሼር #Join
https://t.me/CommandoAndAirborneCommand
You Tube ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉን🙏🇪🇹🙏
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.youtube.com/@theredtigers_4034
ምሳሌ!
የትውልዱ ሽልማት
(በሳሙኤል ሙሉጌታ)
እግር ኳስን ከጉልበታሞች ትግል ወደ አእምሯዊ የጥበብ ጨዋታ ከፍ ካደረጉት ተጫዋቾች መካከል ስሙ በቀዳሚነት ይጠቀሳል፡፡ እሱ በሜዳ ውስጥ ካለ አንድ የእግር ኳስ ተአምር ይኖራል፡፡ ኳስ በግራ እግሩ ታግዛ አንዳች አስማት ትሰራለች። ጥበበኛው ተጫዋች እግሩ ስር የገባችውን ኳስ የሚገባትን የክብር ካባ አልብሶ ወዲህ ወዲያ እያደረገ ሲያንሸራሽራት ለተመለከተ አብሮት የሚጫወት ሰው ያለ አይመስልም፡፡ እሱ ዘንድ ጓንቱን የማይሰጥ በረኛ፣ ከኋላው የማይሮጥ ተከላካይ፣ እጁን በአፉ የማይጭን ደጋፊ የለም፡፡ እሱ ለእግር ኳስ ስፖርት አፍቃሪያን የተሰጠ የዚህ ትውልድ ታላቅ ሽልማት ነው፡፡ ሊዮኔል አንድሬስ ሜሲ!
ዘመን በተሻገረው ስፖርት ውስጥ የራሱን ህያው ታሪክ በተመልካች ልብ ውስጥ ይፅፍ ዘንድ እ.ኤ.አ በ1987 በአርጀንቲናዋ ሮዛሪዮ ሳንታፌ ከተማ ተወለደ። ገና በልጅነት እድሜውና ባልጠነከረ አጥንቱ አጥንትን የሚያለመልም ጥበብ በጎዳናዎች ላይ ማሳየት የጀመረው ሜሲ ለግዙፎች ብቻ የተሰጠ በሚመስለው ስፖርት ላይ አዲስ አብዮት ፈጠረ፡፡ በእድሜም በቁመትም ከሚበልጡት ተጫዋቾች ጋር ቢጫወትም በሚያሳያቸው እግር ኳሳዊ ውሳኔዎችና ድሪብሎች ከሁሉም በላይ ያለ እድሜው ገዘፈ።
ይህን ችሎታውን ያዩት ኒውልስ ኦልድ ቦይስ (Newell's Old Boys) እ.ኤ.አ በ1995 የዛሬውን የሜዳ ላይ ልዑሉን “ሀ” ብለው ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ቡድናቸው ቀላቀሉት፡፡ ከ5 ዓመታት ቆይታ በኋላም የአርጀንቲናው ሀያል ክለብ ሪቨርፕሌት ሊያስፈርሙት ፈልገው የነበረ ቢሆንም በጥቃቅን ነገሮች ሳይስማሙ ትተውት በመሄድ ታሪካዊ ስህተት ሰሩ፡፡
በወቅቱ በአማካይ ከ5 ሺሕ ህፃናት ውስጥ በአንድ ብቻ የሚከሰተው የእድገት ሆርሞን እጥረት (Growth Hormone Deficiency) ችግር በሜሲም ላይ የነበረ ሲሆን ወላጅ አባቱ ልጄ ወደ ታላቅነቱ የሚያደርገውን ጉዞ የሚገታ እንቅፋት ነው ብለው በእጅጉ ይጨነቁ ነበር፡፡ ተፈጥሮ ለሊዮኔል ሜሲ በእግር ኳስ ስፖርት ላይ የሚጠበብበትን ጥበብ በትልቁ ለግሳው ስታበቃ ከቁመቱ ግን ቀነሰችበት፡፡ ነገር ግን ሊዮ አንዴ ለታላቅነት ተፈጥሯልና ጋሬጣውን የሚሻገርበት አጋጣሚ አላጣም፡፡
የዛሬ አያያዙን አይተው የነገ መድረሻውን ለመገመት ያልከበዳቸው የባርሴሎና አመራሮች ግን ትንሹን ልጅ የህክምና ወጪውን ችለው ለመውሰድ ተስማሙ፡፡ ሊዮም ከትውልድ ሀገሩ ተሻግሮ ወደ ሀገረ ስፔን አመራ፡፡ ድንቅ ድንቅ እግር ኳሰኞችን በማፍራት ወደ ሚታወቀው ወደ ላሜሲያ አካዳሚም ተቀላቀለ፡፡ ባርሴሎናዎች አልተሳሳቱም ነበር! ህክምናው በተሳካ ሁኔታ ሲጠናቀቅ እንደተባለውና እንደተገመተው ሜሲ በእግር ኳስ ሙሉ ሰው ሆነ፡፡ በአጭር ጊዜ ውስጥም ከላሜሲያ ደምቆ በመውጣት ወደ ዋናው ቡድን ተሻገረ፡፡
በዚህም እ.ኤ.አ በ2005 ባርሴሎና ከአልባሴቴ በሚያደርጉት ጨዋታ ላይ ተቀይሮ በመግባትና በወቅቱ የቡድን አጋሩ ከሆነው ከሌላኛው ጥበበኛ ሮላንዲኒሆ ጎቾ የተሻገረለትን ኳስ በድንቅ ሁኔታ በማስቆጠር የጎል አካውንቱን ከፈተ፡፡ ከዚህ በኋላ ሊዮኔል አንድሬስ ሜሲ የሚለው ስም በእግር ኳስ ኮሜንታተሮችና በስፖርቱ አፍቃሪያን ዘንድ ከአፍ የማይጠፋ ማር ሆነ፡፡ ሜሲ ጎል አስቆጥሯል የሚሉ የጠዋት ዜናዎች የተለመዱ ሆኑ፡፡ በምትሀተኛ ግራ እግሮቹ አቅልን የሚያስቱ የሜዳ ላይ ተአምሮች፣ ለማየት በሚማርኩት የማይቆራረጥ ድሪብሎቹ፣ በሚደንቁ ጎሎቹና በአስገራሚ አሲስቶቹ ለደጋፊዎቹ የደስታ ምንጭ፤ ለተቃራኒ ቡድን ተከላካይና በረኞች ደግሞ የሜዳ ላይ ቅዠት ሆነ፡፡
የባላንዶር ሽልማትን ሰባት ጊዜ ማሸነፍ የቻለው ሊዮ እስካሁን ካደረጋቸው ከ1 ሺሕ በሚልቁ ጨዋታዎች ውስጥ ከ800 በላይ ጎሎችን ከመረብ ማሳረፍ ችሏል፡፡ ከነዚህ ውስጥ ደግሞ 57 የሚሆኑቱ ሦስታዎች (ሀትሪኮች) ናቸው፡፡ ጎሎችን ማስቆጠር ብቻም ሳይሆን ለቡድን አጋሮቹ አመቻችቶ በማቀበል የማይታማው ጥበበኛው ከ350 በላይ ኳሶችን በዚሁ ሂደት ውስጥ ለጎል አመቻችቶ አቀብሏል፡፡ ሌሎች ተደምጠው የማይጠገቡ፤ ተፅፈው የማያልቁ ብዙ ሪከርዶችም በስሙ ተመዝግቧል፡፡
ብቻ ሊዮኔል አንድሬስ ሜሲ ሁለት አስርት ዓመታት በሚጠጋው የሜዳ ላይ ቆይታ ብዙ ነገር መስራት የቻለ ምሳሌ ነው፡፡ ከሌላኛው የዘመን ተቀናቃኙ ክርስቲያኖ ሮናልዶ ጋር በመሆን የትውልዱን የእግር ኳስ ስፖርት ዘመን አሳምሯል፡፡ ታዳጊዎች የሜዳ ላይ ጥበቡን እየተመለከቱ አርአያ አድርገውታል፡፡ እግር ኳስም በምላሿ ከስፔን ላሊጋ እስከ ፈረንሳይ ሊግ አንድ ዋንጫ፣ ከሻምፒዮንስ ሊግ እስከ ንጉስ ዋንጫና ሌሎች ክብሮችን በመሸለም የሰራላትን እልፍ አዕላፍ ውለታ ለመክፈል ሞክራለች፡፡ ሜሲ አንድ ይወቀስበት የነበረውን “ለሀገሩ አልሰራም” ትችትንም ከቡድን አጋሮቹ ጋር በመሆን በኳታሩ የዓለም ዋንጫ ላይ የውድድሩ ኮከብ በመባል ሳይቀር ክብሩን ተጎናፅፏል፡፡ እሱ ለዘመኑ የእግር ኳስ አፍቃሪያን የተበረከተ ታላቅ ሽልማት ነው፡፡ ሊዮኔል አንድሬስ ሜሲ!
ኢትዮጲያ በሱዳን የተቀሰቀሰው ግጭት ተከትሎ ግብረ ሃይል አቋቋመች
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃለ አቀባይ አምባሳደር መለስ አለም በዛሬው እለት የሚኒስቴሩን ሳምንታዊ የስራ ማብራሪያና ከጋዜጠኞች ለተናነሱ ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል።በሱዳን ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ ጋር በተመለከተ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከሱዳን ፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ አል ቡርሃን ጋር እና ከፈጣን ድጋፍ ሰጪ ሀይሎች መሪ ዳጋሎን ጋር የስልክ ውይይት ማድረጋቸውን አምባሳደር መለስ አለም ተናግረዋል።
ለሱዳን ህዝብ ሰላም እንዲመጣ ሁለቱ መሪዎች እድል መስጠት እንደሚያስፈልጋቸው እና የውስጥ ችግር ለመፍታት በቂ አቅም ያላቸው ስለመሆናቸው በስልክ ውይይቱ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ተናግረዋል።ከሱዳን ወቅታዊ ሁኔታ ጋር በተየያ በሀገር አቀፍ ደረጃ የተቋቋመ ግብረ ሃይል መኖራቸውን ባለሙያዎች እስከ ጋራ ድንበር ተልከው እየተሰራ መሆኑን አምባሳደር መለሰ ተናግረዋል።
ግጭቱ ኢትዮጵያ ላይ ጉዳት እንዳያደርስ ለማድረግ፣ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡ ዜጎች ካሉ በምን መልኩ እናስተናግድ በሚል እና ዜጎች የቆንስላ አገልግሎት እያገኙ ወደሃገራቸው እንዲመጡ ግብረ ሀይሉ ይሰራል ተብሎ ይጠበቃል።ሱዳን ውስጥ ከ 100 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን አሉ ሁሉም ዜጎች ሰላም እንዲሆኑ እንሰራለን ብለዋል። እስካሁን በ100 የሚቆጠሩ የተለያዩ ሃገራት ዜጎች ከሱዳን በኢትዮጵያ ስለማለፋቸውም ጨምረው ተናግረዋል።
ቤተሰብ ይሁኑ!
ቴሌግራም፦ #ሼር #Join
https://t.me/CommandoAndAirborneCommand
You Tube ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉን🙏🇪🇹🙏
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.youtube.com/@theredtigers_4034
ታይዋን በተዋጊ ድሮኖች ተከብቢያለሁ አለች
ታይዋንን እንደራሷ ግዛት የምታያት ቻይና ባለፉት ሶስት አመታት በደሴቷ ዙሪያ የምታደርገውን ወታደራዊ እንቅስቃሴ ጨምራለች።
https://am.al-ain.com/article/taiwan-says-china-encircles-island
ቤተሰብ ይሁኑ!
ቴሌግራም፦ #ሼር #Join
https://t.me/CommandoAndAirborneCommand
You Tube ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉን🙏🇪🇹🙏
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.youtube.com/@theredtigers_4034
የኢፌዴሪ መከላከያ ሚያዚያ 20 ቀን 2015 ዓ.ም
"ለቃል ኪዳኑ የታመነ ጀግና"
ምንም ሆነ ምን ጀግናዬን ሀገር ከማጽናት ጉዞው ማናጠብ አይቻልም።
የሚያደርገውን ጠንቅቆ ያውቃል።ህላዌዌ ነው ብሎ የሚያምነው በጀግንነት የሚፋለምላት ሀገሩን ነው።
ብሄሬም ፣እምነቴም፣ሁሉ ነገሬ ነሽ ይላታል ኢትዮጵያችንን።ይህንን ሲል ደግሞ የለበጣ ሳይሆን ያለ የሌለ ነገሩን ሁላ ፈቅዶና ወዶ ሰጥቷት ነው።
ነጋዴው ትርፉን ሲያሰላ፤እርሱ የሀገሩን ሰላም ያሰላል።
ትርፉም፣ ስኬቱም፣ውጤቱም የሀገሩና ህዝቡ ሰላምና ሰላም ብቻ ነው።
አንዴውኑ ነፍሱንም ለመስጠት ቃል ገብቷል ለአካልና ህይወቱም ቅንጣት ላይሳሳ ነው ቆርጦ የተሰለፈው። በደመ-ነፍስ ሳይሆን በጸና ኢትዮጵያን ባይ እምነት። ውሳኔው እስከቀራኒዮ የዘለቀ ነውና ህመም ስቃዩ በዝቶ እስከ ሞት አፋጣጭ ሆኖ ምንም ያህል ቢከብድ፤ በመስዋዕትነቱ ቤዛ በመሆን ውሳኔው በቆራጥነት ይኖርላታል እየኖረላትም ነው።
የሃሳብ መነሻው ኢትዮጵያ፣መዳረሻውም እራሷ ኢትዮጵያ ናትና ስለሷ የከፈለውን ዋጋ እንደ ኩራት ክብሩ እንጂ እንደ ውለታ አይቆጥረውም።
በተለየ ሴራ የግል ጥቅም አሳዳጆች በየራሳቸው የልዩነት ከረጢት ሊከቱት ቢቅበዘበዙምና በሀሰት ልፈፋቸው ላይ ታች ቢቃብዙም ጀግናው የሀገሬ ወታደር ሁሌም በአላማው ፅኑ ነው ፡፡ በሱ ፅናት ኢትዮጵያን ለማጽናት ከታሪካዊ በድል የታጀበ ጉዞው የሚያቆመው አንዳችም ሃይል እንደሌለ ጠንቅቆ ያውቃል።
ጀግናዬ የሀገር ጠባቂነት ክብር የተጎናጸፈበትን መለዮ ሲያጠልቅ በሰንደቅ ዓላማ ፊት እጁን አንስቶ ለገባው ቃል ኪዳን እስከወዲያኛው ታምኖ ለመኖር የሚያበቃውን ጽናት የሰነቀ ነው ፤ልክ እንደ ጦር መሳሪያው ሁሉ መገለጫ እምነትና ፅናቱን ዘወትር ታጥቆ ከመንቀሳቀስ በፍጹም ወለም ዘለምን አያውቅም።
ከምንም በላይ ሀገሬን ባዩ እሱ፤ ስለሀገሩ ሰላም የማይወጣው አቀበት የማይወርደው ቁልቁለት የለም፤ ለምን ቢባል?ሞያዊ ብቃትና ዲሲፕሊኑ ምርኩዙ ናቸው። መቼም የማይበርድ የጋለ የሀገር ፍቅሩም አብሪ ኮከቡ ነው።ጀግንነቱንም የሚተማመንበት ክንዱ አድርጎ ሁሌም በተጠንቀቅ ቆሞ አለና ነው ።
ኑሮዬ፣ ህይወቴ ፣ ደስታና ምቾቴ አይልም።
ሁሉም ነገሩና የእርካታው ምንጭ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያ እንደሆነች ስለሰላሟ እንደ ተጋ ይቀጥላል። በበዛ ተስፋ፣በጸና እምነትና በማይታበል እውነት ሀገሩ ኢትዮጵያ ከፍ ብላና በሚገባት የክብር ስፍራ ላይ እስክትገኝ በመስዋዕትነት የታጀበ ጉዞው ለሰከንድ አይገታም።
"ክብር ለጀግናው የሀገሬ ወታደር"
ቤተሰብ ይሁኑ!
ቴሌግራም፦ #ሼር #Join
https://t.me/CommandoAndAirborneCommand
You Tube ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉን🙏🇪🇹🙏
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.youtube.com/@theredtigers_4034
⚽ 📰 ሀሙስ ምሽት የወጡ ዝውውር ወሬዎች፡ ኬን፣ ሊቫኮቪች፣ ፖቸቲኖ፣ ራያ፣ ቶኒ፣ ሉካኩ፣ ሜሲ፣ ስሚዝ ሮው፣ ሰር ጂም ራትክሊፍ፣ ጁድ ቤሊንግሃም፣ ሊዮኔል ሜሲ፣ ራፋኤል ሌኦ፣ ሮሜሉ ሉካኩ..
🆕➥ ማንቸስተር ዩናይትዶች የ29 አመቱን እንግሊዛዊ አጥቂ ሃሪ ኬንን ማስፈረም ይፈልጋሉ። ነገርግን ከቶተንሃም ጋር የዝውውር ክፍያን በተመለከተ ከክለቡ ቼርማን ዳን ሌቪ ጋር ረጅም ድርድር ውስጥ ከመግባት ይልቅ በግዜ ሌሎች አማራጮችን ለማስፈረም ይመርጣሉ። (ምንጭ: Star)
🆕➥ ሰር ጂም ራትክሊፍ ክለቡን ለመግዛት በሚያቀርበው ፕሮፖዛል ላይ የማንቸስተር ዩናይትዶች ባለቤቶች የግሌዘር ቤተሰብ 20% ድርሻ ይዘው እንዲቆዩ ለማድረግ ይፈቅዳል ተባለ። (ምንጭ: Times - subscription required)
🆕➥ ማውሪሲዮ ፖቸቲኖ የቼልሲ ቀጣይ ዋና አሰልጣኝ ሆነው ለመቀጠር ሲደራደሩ ወኪል እየተጠቀሙ አይደለም ተብሏል። (ምንጭ: Times - subscription required)
🆕➥ ፖቸቲኖን የክለቡን ቀጣይ አሰልጣኝ ለማድረግ ከቼልሲ ጋር የቃል ስምምነት ላይ ተደርሷል። (ምንጭ: Talksport)
🆕➥ ሁለቱ የብሬንትፎርድ ተጭዋቾች የ27 አመቱ ስፔናዊ ግብ ጠባቂ ዴቪድ ራያ እና እንግሊዛዊው አጥቂ ኢቫን ቶኒ በክረምቱ ወደ ቼልሲ እንዲዛወሩ ክትትል እየተደረገባቸው ነው። (ምንጭ: Football London)
🆕➥ ቼልሲዎች በውሰት ስለሰጡት የ29 አመቱ ቤልጄማዊ አጥቂ ሮሜሉ ሉካኩ እንዲሁም የካሜሩን ግብ ጠባቂ አንድሬ ኦናና ከኢንተር ሚላን ስለማስፈረም ጥረት በሚያደርጉበት ሁኔታ ላይ ከኢንተር ጋር ሊገናኙ ነው። (ምንጭ: Evening Standard)
🆕➥ ሊቨርፑሎች የ19 አመቱ እንግሊዛዊ አማካኝ ጁድ ቤሊንግሃምን በክረምቱ ማስፈረሙን ሃሳብ ቦሩሲያ ዶርትሙንዶች በጠየቁት ከፍተኛ ዋጋ ምክንያት ፍላጎታቸውን ካቀዘቀዙት በኃላ፣ በምትኩ የ 26 አመቱ የኢንተር ሚላን እና የጣሊያን አማካኝ ኒኮሎ ባሬላ ለማስፈረም በአማራጭበት ይዘውታል። (ምንጭ: Sport Mediaset via Express)
🆕➥ አርሰናል ፣ቶተንሃም እና ኒውካስል ሁሉም የ 26 አመቱን ብራዚላዊ የፊት መስመር ተጫዋች ራፊንሀን ይፈልጋሉ ፣ባርሴሎና ምናልባት የ35 አመቱን አርጀንቲናዊ አጥቂ ሊዮኔል ሜሲን ከፓሪስ ሴንት ዠርሜይን ለማስፈረም በሚያዘርጉት ጥረት ላይ ራፊሂናን መሸጥ የክለቡን ፋይናንስ ወጪ ስለሚቀንስ ሊሸጡት ፍቃደኛ ሊሆኑ ይችላል። (ምንጭ: AS - in Spanish)
🆕➥ አስቶንቪላዎች የአርሰናሉን እንግሊዛዊ አማካኝ ኤሚሌ ስሚዝ ሮዌን ማስፈረም ይፈልጋሉ። (ምንጭ: Football 365)
🆕➥ ብራይተኖች ስሙ ከአርሰናል ዝውውር ጋር ሲያያዝ ከነበረው የ25 አመቱ ጃፓናዊ አማካኝ ካኦሩ ሚቶማ ጋር የተሻሻለ ኮንትራት ሊስማሙ እንደሚችሉ እርግጠኞች ናቸው። (ምንጭ: Football Insider)
🆕➥ የ23 አመቱ የኤሲ ሚላኑ ፖርቱጋላዊ የፊት አጥቂ ራፋኤል ሌኦ ወደ ሪያል ማድሪድ እና ቼልሲ ለመቀላቀል የቀረበለትን ጥያቄ ውድቅ አድርጓል። (ምንጭ: La Gazetta dello Sport - in Italian)
🆕➥ ይህ በእንዲህ እንዳለ ሚላን የ22 አመቱን ቤልጄማዊ አማካኝ ቻርለስ ዴ ኬቴላየርን በክረምቱ የዝውውር መስኮት ከዌስትሃሙ የ 24 አመት ጣሊያናዊ አጥቂ ጂያንሉካ ስካማካ የመለዋወጥ ጥያቄ ሊቀርቡ ይችላሉ። (ምንጭ: Telelombardia, via Inside Futbol)
🆕➥ የኤም.ኤል.ኤስ ኮሚሽነር ዶን ጋርበር የፓሪስ ሴንት ዠርሜይን እና አርጀንቲናዊውን የፊት መስመር ተጫዋች ሊዮኔል ሜሲን ወደ ዩናይትድ ስቴትስ ለማምጣት ስምምነት ላይ ለመድረስ "ከፍተኛ የሆነ" ተጭዋቹን የማሳመን ጥረት ይጠይቃል ብለዋል። (ምንጭ: Goal)
🆕➥ የ26 አመቱ ቱርካዊ ኢንተርናሽናል የሌስተር ሲቲው የመሀል ተከላካይ ካግላር ሶዩንኩ ከቀበሮዋ ጋር ያለው ውል ሲያልቅ በቀጣይ ክረምት በነፃ ዝውውር አትሌቲኮ ማድሪድን ይቀላቀላል። (ምንጭ: Fabrizio Romano)
📌 ከተመቻችሁ LIKE ማድረጋችሁን አትርሱ!
📌 ጓደኞቻችሁ እንዲያነቡት SHARE ያድርጉላቸው!
📌 አስተያየት ካላችሁም ከታች COMMENT አድርጉ!
ቤተሰብ ይሁኑ!
ቴሌግራም፦ #ሼር #Join
https://t.me/CommandoAndAirborneCommand
You Tube ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉን🙏🇪🇹🙏
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.youtube.com/@theredtigers_4034
የኢፌዴሪ መከላከያ ሚያዚያ 19 ቀን 2015 ዓ.ም
"ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ የኢትዮጵያን ከፍታ የሚመጥንና ትውልድን የሚያኮራ አየር ኃይል እየተገነባ ነው"
የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፡፡
ኢትዮጵያ በየዘመናቱ ባፈራቻቸው ጀግኖች ልጆቿ ተጋድሎና መስዋዕትነት በቅኝ ግዛት ያልተገዛችና ለጠላቶቿ ያልተንበረከከች ሀገር ናት፡፡
በተለያዩ ጊዜያቶች ተደጋጋሚ ጥቃቶችንና ወረራዎችን በጀግንነት በመመከት ሀገርን ያፀኑ የአሸናፊ ጀግኖች መፍለቂያ ሀገር ፤የአንድነትና የነፃነት ተምሳሌት የሆነች ምድር በመሆንም ትታወቃለች፡፡
ተቋማችን መከላከያ በአሁኑ ወቅት ዘላቂ ሠላም እንዲሰፍንና ህዝቦች በሠላም ወጥተው በሠላም እንዲገቡ ዘመናዊ ሠራዊት ለመገንባት ለተቋማዊ ሪፎርም ግንባታ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡
ውትድርናን ከሌላው የሚለየው ደግሞ አባሉ በሰላም ወቅት በዝግጁነት፤ በውጊያ ወቅት ደግሞ በተግባር ጦርነት ውስጥ መሆኑ ነው፡፡የሠራዊት ዓለም ምን ጊዜም ተንቀሳቃሽ ንቁና የማያቋርጥ ወጣትነት ነው፡፡
እኛ ወታደሮች ዘወትር ስለ ጦርነት ማወቅ ይገባናል፡፡ያ ማለት ግን ጦርነትን እንወዳለን ማለት አይደለም፡፡ እንደ ወታደር ሊተነኩሱን የሚያስቡ ጠላቶቻችንን ለመከላከልና ለማጥቃት ያዘጋጀናል እንጂ ፡፡
የአንድ ሠራዊት ወትሮ ዝግጁነት መረጋገጥ ለሚሰጠው ግዳጅ አስተሳሰቡን ዝግጁ ማድረግ፤ የታጠቁትን የጦር መሳሪያ በማንኛውም ጊዜና ቦታ ለመጠቀም የሚያስችል ብቃትንና ዕውቀትን መላበስ እንዲሁም በየትኛውም የአየር ፀባይና መሬት ግዳጅን ለመወጣት የሚያስችል አካላዊ ፤ ስነ-ልቦናዊና ሞራላዊ ብቃት መኖር ማለት ነው፡፡
በሌላ በኩል እንደ ወታደር ደግሞ የነፍስ ወከፍም ሆነ የቡድን መሳሪያዎችን መንከባከብ ፤ማወቅና በሚገባ መጠቀም እንዲሁም እራሱን በአካላዊ ብቃት መግራትና የዘወትር ልምምድ ማድረግ አንዱ የወትሮ ዝግጁነት አካል ነው፡፡
ከስመ-ጥር ተቋሞቻችን አንዱ የሆነው አንጋፋው የኢፌዴሪ አየር ኃይል በርካታ ተቋማዊ የሪፎርም ስራዎችን በማከናወን ዛሬ ላይ በየትኛውም መስክ የሚፈራ፤የሚሰጡትን ግዳጆች በድልና በስኬት መወጣት የሚችል ፤ሀገሩንና ወገኑን የሚያኮራ፤በሌሎች ተቋማት ዘንድ እንደ ሞዴል የሚወሰድ፤ውብና ማራኪ የቱርስት መዳረሻ ሆኖ በመገንባት ላይ ይገኛል፡፡
ሰሞኑንም የአየር ሃይሉን የዕድገት ከፍታ የሚያሳይ አንድ ትልቅ መድረክ በአየር ሃይል ደረጃ ተዘጋጅቶ ነበር፡፡ በዚህ ዝግጅት ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ "የኢፌዴሪ አየር ኃይልን ዘላቂ ተቋም አድርገው የመገንባት ስራ ከሌሎች የፀጥታ ተቋማት ሪፎርም ጋር ተዳምሮ ባለፉት ዓመታት ሲሰራበት ቆይቷል"ብለዋል፡፡
በዚህም በተለያዩ ግዳጆች ተፈትኖ ውጤት ማምጣት የቻለ ተቋም መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ የኢትዮጵያን ከፍታ የሚመጥንና ትውልድን የሚያኮራ የአየር ኃይል እየተገነባ መምጣቱንም ተናግረዋል፡፡
ከአሁን በኋላ እየተገነባ ያለው አየር ኃይል የማይፈርስ፤ካለፈው ውድቀት ትምህርት የሚወስድ ነው ያሉት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ዛሬ ላይ ትጥቆቻችን ብልሽት ሲገጥማቸው እዚሁ በመጠገንና በማደስ ወደ ዲጅታላይዝድ እንድንገባ በመደረጉ አየር ኃይሉ በከፍተኛ የዕድገት ጎዳና ላይ ይገኛልም ብለዋል፡፡
የኢፌዴር አየር ኃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ በበኩላቸው "አየር ኃይሉ በተለያዩ ጦርነቶች ላይ በመሳተፍ የላቀ ውጤት ማምጣቱንና በሪፎርም ስራም በርካታ ተቋማዊ ተግባራት ማከናወን መቻሉን ተናግረዋል፡፡ባለፉት ተከታታይ ዓመታት ለተቋሙ የሪፎርም ግንባታ ወሳኝ የሆኑ ተልዕኮዎችን ፈፅመዋል"፡፡
ከእነዚህ ተላላቅ ተልዕኮዎች መካከል የሠው ኃይል ግንባታ ፤ትጥቆችን የማዘመን፤የውጊያ መሠረተ-ልማት ግንባታና የአየር ኃይል የስራ አካባቢ ተቋሙን በሚመጥን ደረጃ የማልማትና የማስዋብ ስራዎች ላይ ትኩረት በመስጠት በርካታ ተግባራት ተከናውነዋል፡፡ውጤቱም ፍሬ አፍርቶ በማየት ላይ እንገኛለን ብለዋል፡፡
በዕለቱ የተመረቀው ዘጋቢ ፊልም የአየር ኃይሉን የሪፎርም ስራዎችና ገድሉን በሚያሳይ መልኩ ተዘጋጅቶ የቀረበ ሲሆን ታሪኩም ተሰንዶ ለቀጣይ ትውልድ እንዲተላለፍ ልምድና ተሞክሮ እንዲወሰድበት፤ህዝባችን ተቋሙን ለማዘመን የተጓዘበትን ርቀትና ያለበትን ደረጃ እንዲገነዘብ ፍላጎት ያለውና መመዘኛውን የሚያሟሉ ወጣቶች ተቋሙን እንዲቀላቀሉ ታሳቢ ያደረገ ነዉ፡፡
ዘጋቢ ፊልሙ ትልቅ አስተዋፅኦ የሚያበረክት ከመሆኑ በተጨማሪ ተቋሙ ለወደፊት ሊደርስበት ያሰበውን ራዕይ የሚያሳይ ሆኖ መዘጋጀቱ ጠቀሜታዉ የጎላ መሆኑም ተጠቁሟል፡፡
ይህ ተቋማዊ የሪፎርም ስራ ግንባታ ወሳኝ የሆኑና የአየር ኃይሉ የደረሰበትን ተቋማዊ ግንባታ የሚያሳይ የፎቶ አውደ ርዕይና "ሰማዩ የኛ ነው" በሚል ርዕስ የተዘጋጀው ዘጋቢ ፊልም የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላን ጨምሮ ጄኔራሎች መኮንኖች፤ ሚኒስትሮች፤ አርቲስቶችና ዲፕሎማቶች በተገኙበት ተመርቆ ለእይታ በቅቷል፡፡
ቤተሰብ ይሁኑ!
ቴሌግራም፦ #ሼር #Join
https://t.me/CommandoAndAirborneCommand
You Tube ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉን🙏🇪🇹🙏
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.youtube.com/@theredtigers_4034
ከአንድሮይድ ስልኮች በፍጥነት መጥፋት ያለባቸው መተግበሪያዎች
ማልዌርፎክስ የተሰኘው የቴክኖሎጂ ኩባንያ 19 ከስማርት ስልኮች ላይ ሊጠፉ የሚገቡ አደገኛ መተግበሪያዎችን ይፋ አድርጓል።
https://am.al-ain.com/article/19-android-apps-we-should-delete-right-now
ቤተሰብ ይሁኑ!
ቴሌግራም፦ #ሼር #Join
https://t.me/CommandoAndAirborneCommand
You Tube ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉን🙏🇪🇹🙏
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.youtube.com/@theredtigers_4034
