የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️
Відкрити в Telegram
5 400
Підписники
-22624 години
-2 2007 днів
-2 65830 день
Архів дописів
ኢራን ከአጋሯ ሩሲያ ጋር በህንድ ውቅያኖስ ላይ ወታደራዊ ልምምድ እያካሄደች ነው
ኢራን በቀጣናው ከአሜሪካ ጋር ለገባችበት ውጥረት ከሩሲያ እና ቻይና ጋር ወታደራዊ ትብብር በማድረግ ምላሽ እየሰጠች ነው።
https://bit.ly/4eOlElb
ከየትኛውም የሀገራችን አቅጣጫ ሊከፈቱ የሚችሉ ጥቃቶችን መከላከል የሚችል የአየር ሀይል ተገንብቷል።
ሌተናል ጀኔራል ይልማ መርዳሳ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጥቅምት 10 ቀን 2017 ዓ.ም
ከየትኛውም የሀገራችን አቅጣጫ ሊከፈቱ የሚችሉ ጥቃቶች ለመከላከል የሚችልና የሚመጡ አደጋዎችን ለመቀልበስ የሚያስችል የአየር ሀይል ተገንብቷል ሲሉ
የኢፌዴሪ አየር ሀይል አዛዥ ሌተናል ጀኔራል ይልማ መርዳሳ ተናግረዋል።
ሌተናል ጄኔራል ይልማ አየር ሀይል ከነበረበት ውድቀት ለማንሳት በፀጥታ ዘርፉ የተሰሩት ሪፎርሞች ከፍተኛ ለውጥ ማምጣታቸውን ተናግረው፣ በፕሮፌሽናል የሰው ሀይል ግንባታ ፣ በትጥቅና በውጊያ መሠረተ ልማት ዘርፎች ላይ ከፍተኛ ውጤት መገኘቱን ገልፀዋል።
ለታላቅ ሀገር የሚመጥን ታላቅ የአየር ሀይል የመገንባት ጥረታችን ዕውን ለማድረግና የነገውን ጠንካራ የአየር ሀይል ለመገንባት ከምልመላ ጀምሮ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝና ፕሮፌሽናል ፣ ሀገሩንና ሙያውን የሚወድ ፤ ከፖለቲካና ሌሎች ተፅዕኖዎች ነፃ የሆነ ፤ ኢትዮጵያን የሚመስል ስብጥር ያለው አመራርና ባለሙያ እየተገነባ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።
ያሉትን የአየር ሀይል ትጥቆች ከማሻሻል ባለፈ ዓለም የደረሰባቸው ዘመናዊ ትጥቆችን እየታጠቅን እንገኛለን ያሉት አዛዡ በቅርቡ ከአፍሪካ ጠንካራ አየር ሀይሎች ጎን ለመሠለፍ የሚያስችል ስራዎች እየተሰሩ እንደሚገኙ ተናግረዋል።
ታሪካዊ ጠላቶቻችን በሀገራችን ላይ የከፈቷቸው የስነልቦና ውጊያዎች መኖራቸውና ለማስፈራራት ከመሞከር ባለፈ የሚያመጡት ውጤት አለመኖሩን ገልፀው ፤ ተላላኪዎችን እየደገፉ ያሉ ጠላቶች ጥቃት ለመክፈት ከሞከሩ እንደአመጣጣቸው ለመመለስ በተሟላ ዝግጁነት ላይ እንገኛለንም ብለዋል።
ሀገራችንንና የአየር ሀይሉን ስም ለማጠልሸት በፅንፈኞች የማህበራዊ ሚዲያዎች የተከፈቱት ዘመቻዎች መሠረተ ቢስ መሆናቸውን የገለፁት አዛዡ በግምት የሚደረግ ምንም ነገር አለመኖሩንና ዘመኑ በፈጠረው ቴክኖሎጂ ተፈላጊ ዒላማን በተፈለገው ቦታና ጊዜ ለይቶ እርምጃ መውሰድ እንደሚቻል ነው የገለፁት።
ሆን ተብሎ ሲቪሎች ላይ ጉዳት እንደደረሰ ለማስመሰል የሚደረጉ የውሸት የሚዲያ ዘመቻዎች በዘርፉ ዕውቀቱ የሌላቸውን ለማሳሳትና ሽንፈታቸውን ለመደበቅ መሆኑን ገልፀው ሲቪሎች ላይ ጉዳት እንዳይደርስ ከፍተኛ ጥንቃቄ ከመደረጉም ባለፈ ዒላማዎችን በቁጥር ጭምር መለየት ይቻላልም ነው ያሉት።
በሀገራችን የመጣውን ለውጥ ተከትሎ ከሁሉም ሀገራዊ የፀጥታ ተቋማት ጋር በትብብር እየተሰራ እንደሚገኝና ለጋራ ተልዕኮ በጋራ የመስራት እንቅስቃሴው ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባው ገልፀዋል።
ለመከላከያ ሠራዊቱ ለአየር ሀይሉና ለሌሎች የፀጥታ ዘርፎች ውጤታማነት የክቡር ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ የቅርብ ክትትልና ድጋፍ ከፍተኛ መሆኑና የተሻሻለው ፖሊሲ ፣ ስትራቴጂና የሠራዊቱ የግንባታ መመሪያ ተቋማትና አባሉ ከፖለቲካ ወገንተኛነት በመውጣት ሀገራቸውን እንዲያገለግሉና ሙያዊ አቅማቸውን እንዲያጎለብቱ ማስቻሉንም ጠቅሰዋል።
ለሀገር መስዋዕትነት ከፍለው ሀገርን ያቆዩና ታሪክ የሰሩ ጀግኖች ክብር ይገባቸዋል ያሉት አዛዡ በተለያዩ ሀገራት ከሚገኙና ተቋሙን ካገለገሉ ጀግኖች ጋር አብሮ በመስራት ሙያተኞች ተቀጥረው እንዲያገለግሉ ከማድረግ ባለፈ በተለያዩ ምክንያቶች አቅም ያነሳቸውን በተቻለ መጠን እገዛ እየተደረገ እንደሚገኝም ገልፀዋል።
ዘጋቢ ብዙአየሁ ተሾመ
"ኢትዮጵያ ለሶማሊያ ሰላምና መረጋጋት ከፍተኛ ዋጋ ከፍላለች" - የቀድሞ በሶማሊያ የአፍሪካ ኅብረት ሰላም አስከባሪ ሠራዊት አዛዥ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጥቅምት 09 ቀን 2017 ዓ.ሞ
ኢትዮጵያ ለሶማሊያ ሰላምና መረጋጋት ከፍተኛ ዋጋ እንደከፈለችና በቀጣይም በቀጠናው ብቻ ሳይሆን በመላው አፍሪካ ሰላም ለማስፈን በሚደረገው ጥረት ሚናዋን ልታጠናክር እንደሚገባ የቀድሞ በሶማሊያ የአፍሪካ ኅብረት ሰላም አስከባሪ ሠራዊት አዛዥ ገልፀዋል።
የቀድሞ በሶማሊያ የአፍሪካ ሕብረት ሰላም አስከባሪ ኃይል (አሚሶም)ና የአፍሪካ ሕብረት የሽግግር ልዑክ (አትሚስ) አዛዥና አሁን ላይ የብሩንዲ መከላከያ ሚኒስቴር ከፍተኛ አማካሪ ሜጀር ጄኔራል ዲጌያ ዲዮሜዴ ኢትዮጵያ በቀጠናው ያላትን ሚና በተመለከተ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል።
በቆይታቸውም ኢትዮጵያ በአፍሪካ በተለይም በምስራቅና በአፍሪካ ቀንድ ሰላምና መረጋጋትን ለማምጣት በሰላም ማስከበር ተልዕኮ ላይ ከፍተኛ ሚና መጫወቷን አስታውሰዋል።
በተለይም ሶማሊያ የአፍሪካ ሕብረት ሰላም አስከባሪ ኃይል(አሚሶም) ሥር ኢትዮጵያ ወታደራዊ ኃይል በማሰለፍ ለሶማሊያ ሰላም ከፍተኛ ሚና ተጫውታለች ብለዋል።
ኢትዮጵያ ባላት ጠንካራ የጸጥታ ኃይል ለቀጠናው ሰላምና መረጋጋት በምታደርገው አስተዋጽኦ ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት መነሳሳትን የፈጠረ መሆኑን ጠቁመዋል።
ኢትዮጵያ ለዛሬዋ ሶማሊያ ጸንቶ መቀጠል የማይተካ ሚና መጫወቷን ጠቅሰው፤ በአህጉሪቱ ሰላም እንዲረጋገጥ ሚናዋን አጠናክራ መቀጠል አለባት ነው ያሉት።
ኢትዮጵያ በዘመናዊ የጸጥታና ደኅንነት ተቋማት ግንባታ ላይ ያስመዘገበችው ለውጥ የሚበረታታ መሆኑን ጠቅሰው፤ በቀጣይ በመከላከያ ዘርፍ በትብብር መሥራት እንደሚፈልጉ ጠቁመዋል።
በኢትዮጵያ የደቡብ ሱዳን ኤምባሲ ወታደራዊ አታሼ ብርጋዴር ጄኔራል ጆክ አንጎክ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ ለምስራቅ አፍሪካ ሰላምና መረጋጋት ያበረከተችው አስተዋጽኦ እውቅና የሚሰጠውና በየትኛውም የአፍሪካ ሀገር የማይካድ ሃቅ መሆኑን አንስተዋል።
በአፍሪካ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት በማምጣት የበለጸገችና ለዜጎቿ ምቹ አህጉርን ለመፍጠር የጸጥታ ተቋማት የተቀናጀ እርምጃ ወሳኝ መሆኑንም አስተያየት ሰጪዎቹ በአጽንዖት ተናግረዋል።
እስራኤል በሶማሌላንድ የጦር ሰፈር ልትመሰርት ነው
------------
እስራኤል በሶማሌላንድ የጦር ሰፈር ለማቋቋም ማቀዷን የኳተሩን #ሚድያ ሚድል ኢስት ሞኒተርን በመጥቀስ የእስራኤል ዋንኛ የዜና አውታር ጀሩሳሌም ፓስት ዘግቧል።
ሶማሌላንድ 740ኪ.ሜ ከሚሆነው የህንድ ውቅያኖስ አዋሳኝ የባህር ጠረፏ ላይ ነው ለጦር ሰፈር የሚሆን ቦታ ልትሰጥ እንደሆነ በመነገር ላይ ያለው።
እስራኤል ከየመን #ሃውቲ ሃይሎች የሚቃጣባትን ጥቃት ለመመከት እና የመርከቦቿን ደህንነት ለመጠበቅር ሰፈር ማቋቋም እንዳስፈለጋትገልጿል።
የእስራኤልን ደህንነት ከርቀት በአስተማማኝ ሁኔታ ለማስጠበቅ የሚያስችሉ ስትራቴጂ አንድ አካል የሆነው ይህ እቅድ ገቢራዊ የመሆን እድሉ ሰፊ እንደሆነ ይነገራል።
ለዚህ ዋንኛው ምክኒያት ለጦር ሰፈር የሚሆን ቦታ ሶማሌላንድ የምትሰጥ ከሆነ እስራኤል በአንፃሩ ከሶማሌላንድ ጋር መደበኛ ግንኙነት ለመጀመር ፍቃደኛ ናት ተብሏል።
ይህም #ሶማሌላንድ ዋንኛ አላማ ለሆነው #እውቅና የማግኘት ጉዳይ በሰፊው መንገዱን ያመቻችላታል።
አዲስ መረጃን ከቻናላችን ያግኙ
+2
ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ የውጪ ጉዳይ ሚንስቴር ሚንስትር ሆነው ተሾሙ
***
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዛሬው ዕለት የተለያዩ ሹመቶችን ሰጥተዋል።
በዚሁ መሰረት ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ የውጪ ጉዳይ ሚንስቴር ሚንስትር፣ ወ/ሮ ሰላማዊት ካሳ የቱሪዝም ሚንስቴር ሚንስትር፣ ወ/ሮ ሃና አርአያስላሴ፦ የፍትህ ሚንስቴር ሚንስትር ሆነው ተሾመዋል።
+2
#Update
#ሰበር_ዜና
አዲሱ የሃማስ መሪ በእስራኤል ጥቃት ተገደሉ።
የሰንደቅ ዓላማ ቀን የፊታችን ሰኞ ይከበራል፤
የሰንደቅ ዓላማ ቀን የፊታችን ሰኞ ጥቅምት 4 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚከበር የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስታወቀ።
የዘንድሮው የሰንደቅ ዓላማ ቀን “ሰንደቅ ዓላማችን ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ከፍታ!” በሚል መሪ ሃሳብ ለ17ኛ ጊዜ በመላው ሀገሪቱ ለማክበር ዝግጅት እየተደረገ እንደሚገኝ ምክር ቤቱ አስታውቋል፡፡
በፌደራል፣ በክልሎች እና በሁለቱም የከተማ አስተዳደሮች ከሰንደቅ ዓላማ መርሆዎች ጋር ተገናዝቦ በኢፌዲሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መሪነት በመላው ሀገሪቱ እንደሚከበርም አክሏል፡፡
ዕለቱ በፌደራል የመንግስት ተቋማት፣ በክልሎችና በሁለቱም ከተማ አስተዳደሮች፣ በመከላከያ ሰራዊት ካምፖች፣ በኢትዮጵያ ኤምባሲዎች እና ሚሲዮኖች በተመሳሳይ ሰዓት ከረፋዱ 4፡30 ሰዓት ላይ ሰንደቅ ዓለማ በመስቀልና በሰንደቅ ዓላማ ፊት ቃለ መሐላ በመፈፀም በተለያዩ ስርዓቶችና ዝግጅቶች በደማቅ ሁኔታ እንደሚከበር ነው ምክር ቤቱ ያስራወቀው፡፡ መረጃ
የብሔራዊ ሰንደቅ ዓላማ ቀን በዓል በየዓመቱ መከበሩ ለብሔራዊ አንድነት፣ ለኢትዮጵያ ሉዓላዊነትና ከፍታ እንዲሁም ብሔራዊ መነቃቃትን ለመፍጠር ትልቅ ትርጉም እንዳለው መገለጹን ከምክር ቤቱ መረጃ አግኝቻለሁ ሲል የዘገበው የኢትዮጵያ ዜና አግልግሎት ነው፡፡
ተጨማሪ መረጃዎችን join አድርጉ፣ለሌሎች ጋብዙ👇👇
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
https://www.youtube.com/@%E1%88%B0%E1%89%A0%E1%88%AD_%E1%8B%9C%E1%8A%93
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
በግብርናው ዘርፍ ባስመዘገብነው እምርታ Africa IOAን ሀገራችንን የምግብ ዋስትና ካረጋገጡ ምርጥ የአፍሪካ ሀገሮች ተርታ ኢትዮጵያን ሁለተኛ አድርጓታል። እንኳን ደስ አላችሁ ✍️🇪🇹🙏
ተጨማሪ መረጃዎችን join አድርጉ፣ለሌሎች ጋብዙ👇👇
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
https://www.youtube.com/@%E1%88%B0%E1%89%A0%E1%88%AD_%E1%8B%9C%E1%8A%93
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
ግብፅ እና ኤርትራ የሶማሊያን ሉዋላዊነት ለማክበርና የሀገሪቷን ጦር ለማጠናከር ተስማምተናል አሉ‼️
ግብፅ እና ኤርትራ የሶስትዮሽ ጋዜጣዊ መግለጫ ሲሰጡ ፕሬዝዳንት አብደል ፈታህ ኤል ሲሲ፣ የኤርትራ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ እና የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀመድን ጨምሮ ለሶማሊያ ማንኛውንም አይነት ድጋፍ ለመስጠት መስማማታቸውን ሃሙስ እለት አስታውቀዋል።
የኤርትራ፣ ግብጽና ሱማሊያ መሪዎች ትናንት አሥመራ ላይ ባደረጉት ስብሰባ፣ የጋራ ትብብራቸውን ለማጠናከር በውጭ ጉዳይ ሚንስትሮቻቸው ደረጃ የሦስትዮሽ የጋራ ኮሚቴ ለማቋቋም ወስነዋል።
መሪዎቹ፣ የሱማሊያ መንግሥት ተቋማት የውስጥና የውጭ አደጋዎችን መመከት እንዲችሉ ድጋፍ ለማድረግም ተስማምተዋል።
አገራቱ፣ የቀጠናው አገራትን የግዛት አንድነትና ሉዓላዊነት ለማክበር ከስምምነት መድረሳቸውንም ገልጸዋል።
የኤርትራ እና ግብፅ መሪዎች በሶማሊያ መረጋጋትን ለመደገፍ እና የፌደራል መንግስቷን አቅም ለማጠናከር የሚያደርጉትን ጥረት በደስታ ተቀብለዋል።
በተጨማሪም ግብፅ በሶማሊያ ሰላም ለማስከበር በሚደረገው ጥረት ኃይሏን ለማበርከት ያቀረበችውን ጥያቄ አወድሰዋል።
ተጨማሪ መረጃዎችን join አድርጉ፣ለሌሎች ጋብዙ👇👇
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
https://www.youtube.com/@%E1%88%B0%E1%89%A0%E1%88%AD_%E1%8B%9C%E1%8A%93
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
የግብጽ፣ ሶማሊያና ኤርትራ መሪዎች በምን ጉዳይ ላይ ተወያዩ፤ የደረሷቸው ስምምነቶስ ምንድን ናቸው?
የግብጽ፣ ሶማሊያና ኤርትራ መሪዎች በአስመራ የሶስትዮሽ ምክክር አድርገዋል። ምክክሩ የሶስቱን ሀገራት ትብብርና በአፍሪካ ቀንድ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ያተኮረ እንደነበር ተገልጿል።
ዝርዝሩን በተከታዩ ሊንክ ይመልከቱ፤ https://bit.ly/3ZXOpak
አፍሪካ አሜሪካ ላይ ማዕቀብ መጣል ምትጀምረው መቼ ነው ?
------------
አነጋጋሪው የኡጋንዳ ጦር ሃይል አዛዥ እና የኘሬዝደንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ ልጅ ሙሆዚ ካይኔሩግባ የአፍሪካውያን ደም ያፈሰሱ የአሜሪካ ሃላፊዎች ላይ እርምጃ ተወስዶ እንደማያውቅ በመግለፅ ፤ ይህ ሚቀጥል ከሆነ አፍሪካ በአሜሪካዉያኑ ላይ ማዕቀብ ወደ መጣል ትሸጋገራለች ብሏል።
ይሆን ይሆን ??🤗
ወጣ ባሉ ንግግሮቹ የሚታወቀው ሙሆንዚ በኡጋንዳ የአሜሪካ አምባሳደርን የሶሰት ቀናት ጊዜ ገደብ በመስጠት ይቅርታ እንዲጠይቁት በሰጠው ማሳሰቢያ መሰረት አምባሳደሩ ሰኞ ዕለት ይቅርታ መልዕከት አስተላልፈዋል።
አምባሳደሩ የኡጋንዳን መንግሰት እና የመሪያችንን ክብር አጉድፈዋል በሚል ነበር አርብ ዕለት የቀን ገደብ አሰቀምጦ ይቅርታ እንዲጠይቁ ያሳሰባቸው።
ተጨማሪ መረጃዎችን join አድርጉ፣ለሌሎች ጋብዙ👇👇
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
https://www.youtube.com/@%E1%88%B0%E1%89%A0%E1%88%AD_%E1%8B%9C%E1%8A%93
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
+2
ማርክ ዙከበርግን ጨምሮ የአመቱ 50 ተፅዕኖ ፈጣሪ አይሁዳውያን ተመረጡ
---
የእስራኤል ሚድያ ጀሩሳሌም ፓስት የ2024 የላቀ ተፅኖ ፈጣሪ ያላቸውን 50 አይሁዳውያን እና የአይሁድ የዘር ግንድ ያላቸውን ግለሰቦች ይፋ አድርጓል። ተመራጮቹ በፓለቲካ ፣ በጦር መሪነት ፣ በንግድ ፣ በፈጠራ ፣ በአድቮኬሲ ፣ በሚድያ ስራዎች ለእስራኤል ጥቅም በአመቱ ውስጥ ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክተዋል የተባሉ ናቸው። በምርጫው የእስራኤል ዜግነት ያላቸው እና የእስራኤል ዜግነት የሌላቸው ግን ከፍተኛ ተፅዕኖ ነበራቸው የተባሉ አይሁዳውያን ተመርጠዋል። በምርጫው ውስጥ ከተካተቱት መካከል ፦
👉 ደግ ኢምሆፎ- የአሜሪካ ምክትል ኘሬዝደንት ካማላ ሃሪስ ባለቤት
👉 አንቶኒ #ብሊንከን -የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር
👉 ማርክ #ዙከንበርግ- የፌስቡክ ( meta) ባለቤት
👉ቢል አክማን -አሜሪካዊ ቢሊየነር
👉ቪክቶሪያ #ስታንመር - የእንግሊዝ ጠ/ሚር ኬር ስታንመር ባለቤት
👉ጆሹዋ ሻፒሮ -የፔንሲልቫኒያ አስተዳዳሪ
👉ቭላድሚር #ዘሌንስኪ -የዩክሬን ኘሬዝደንት ይገኙበታል።
እነኚህ በተለያዩ ሃገራት በከፍተኛ ደረጃ የሚገኙ ተፅዕኖ የነበራቸው የአይሁድ ሰዎች ሲሆኑ የእስራኤል መንግስትን እየመሩ ያሉ ከፍተኛ ሃላፊዎችንም በአመቱ ተፅዕኖ ፈጣሪ ዝርዝር ውስጥ ጀሩሳሌም ፓስት አካቷል። ከነዚህም መካከል ጠ/ሚር ቤንጃሚን #ኔታንያሁ ፣ ኘሬዝደንት ይሳቅ ሄርዞግ ፣ ዮአቭ ጋላን የመከላከያ ሚኒስትር ፣ ዴቪድ ባርኒ የ #ሞሳድ መሪ ፣ ዳንኤል ሃጋሪ የእስራኤል ጦር ቃል አቀባይ ፣ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎቹ ያኢር ላፒድ እና ቤን ጋዝ ተጠቃሾች።
እስራኤል ከሃማስ ጋር ጦርነት የጀመረችበት አንደኛ አመት ኦክቶበር 7 የሚከበር ሲሆን በዚህ ጊዜ ውስጥ የጎላ ተፅዕኖ ነበራቸው በሚል ነው ግለሰቦቹ የተመረጡት።
እንኳን ለደማቁ የእሬቻ በአል አደረሳችሁ፣ አደረሰን!
Baga Irreecha Baranaa Geenye!
መልካም በአል!
ተጨማሪ መረጃዎችን join አድርጉ፣ለሌሎች ጋብዙ👇👇
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
https://www.youtube.com/@%E1%88%B0%E1%89%A0%E1%88%AD_%E1%8B%9C%E1%8A%93
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
ዛሬ የሚደረጉ ጨዋታዎች
🏴በእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ
08:30 | ኒውካስትል ከ ማንችስተር ሲቲ
11:00 | አርሰናል ከ ሌስተር ሲቲ
11:00 | ብሬንትፎርድ ከ ዌስትሃም
11:00 | ቼልሲ ከ ብራይተን
11:00 | ኤቨርተን ከ ክሪስታል ፓላስ
11:00 | ኖቲንግሃም ከ ፉልሃም
01:30 | ወልቭስ ከ ሊቨርፑል
🇪🇹በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ
10:00 | መቻል ከ ሲዳማ ቡና
01:00 | ድሬደዋ ከተማ ከ ወላይታ ድቻ
🇩🇪በጀርመን ቡንደስሊጋ
10:30 | ሞንቼግላድባህ ከ ዩኒየን በርሊን
10:30 | ፍራይበርግ ከ ፓውሊ
10:30 | ሜንዝ ከ ሃይደናየም
10:30 | ሌፕዚግ ከ ኦግስበርግ
10:30 | ወልቭፍስበርግ ከ ስቱትጋርት
01:30 | ባየር ሙኒክ ከ ባየር ሌቨርኩሰን
🇮🇹በጣልያን ሴሪ ኤ
10:00 | ዩድንዜ ከ ኢንተር ሚላን
01:00 | ጄኖዋ ከ ጁቬንቱስ
03:45 | ቦሎኛ ከ አታላንታ
🇫🇷በፈረንሳይ ሊግ 1
12:00 | ሌንስ ከ ኒስ
02:00 | ለ ሃቫሬ ከ ሊል
04:00 | ሞናኮ ከ ሞንፔሌ
🇪🇸 በስፔን ላሊጋ
09:30 | ሄታፌ ከ አላቬስ
12:15 | ራዮ ቫልካኖ ከ ሌጋኔስ
01:30 | ሪያል ሶሴዳድ ከ ቫሌንሲያ
04:00 | ኦሳሱና ከ ባርሴሎና
ተጨማሪ መረጃዎችን join አድርጉ፣ለሌሎች ጋብዙ👇👇
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
https://www.youtube.com/@%E1%88%B0%E1%89%A0%E1%88%AD_%E1%8B%9C%E1%8A%93
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
አሜሪካ ወታደሮቿን ሙሉ ለሙሉ ከኒጀር አስወጣች!
አሜሪካ ወታደሮቿን ከኒጀር አስወጥታ ማጠናቀቋን አንድ ከፍተኛ የዩናይትድ ስቴትስ ባለስልጣን ትላንት ሰኞ አስታውቀዋል፡ የፔንታገን ቃል አቀባይ የሆኑት ሳብሪና ሲንግ፣ በኒጀር የሚገኘውን የዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲ ለመጠበቅ ጥቂት ወታደሮች ብቻ መቅረታቸውንም ለጋዜጠኞች ተናግረዋል፡፡
በአውሮፓዊያኑ 2024 መግቢያ ላይ፣ የኒጀር ወታደራዊ ጁንታ የዩናይትድ ስቴትስ ወታደሮች በምዕራባዊቷ አፍሪካ ሃገር ያላቸውን ተልዕኮ የፈቀደውን ስምምነት እንዲያበቃ አድርጓል፡፡
የሁለቱ ሃገራት ባለሥልጣናት ከጥቂት ወራት በኋላ በጋራ ባወጡት መግለጫም፣ የአሜሪካ ወታደሮች በመስከረም ወር አጋማሽ ላይ ሙሉ ለሙሉ ለቀው እንደሚወጡ ማስታወቃቸው የሚታወስ ነው፡፡ ዩናይትድ ስቴትስ የመጨረሻውን የጦር ሰፈሯን ከአንድ ወር በፊት ለአካባቢው ባለስልጣናት ያስረከበች ሲሆን፤ ከ20 በላይ የሚሆኑ ወታደሮቿ ለቆ ከመውጣት ጋር ለተያያዙ የተለያዩ አስተዳደራዊ ስራዎች በሃገሪቱ ቀርተው ነበር ሲሉ ሲንግ አስታውቀዋል፡፡
ከቅርብ ወራት ወዲህ ኒጀር ከምዕራባዊያን አጋሮች በመራቅ፤ ለደህንነት ጉዳዮች ፊቷን ወደ ሩሲያ አዙራለች፡፡ የሩሲያ ወታደራዊ አሰልጣኞች የሃገሪቱን የአየር መከላከያ ሠራዊት ለማሰልጠን ባለፈው ሚያዚያ ኒጀር ገብተዋል፡፡
[VoA]
ተጨማሪ መረጃዎችን join አድርጉ፣ለሌሎች ጋብዙ👇👇
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
https://www.youtube.com/@%E1%88%B0%E1%89%A0%E1%88%AD_%E1%8B%9C%E1%8A%93
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
ግብጽ ህወሓት እና ኤርትራን ማደራደር እንደምትፈልግ ማስታወቋ ተነገረ
የህወሓት ሊቀመንበር ዶክተር ደብረፅዮን በቅርቡ በሰጡት መግለጫ የትግራይ ክልልና የኤርትራ ባለስልጣናት ንግግር መጀመራቸውን መግለጻቸው ይታወሳል።
https://bit.ly/3XB48JQ
