uk
Feedback
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

Відкрити в Telegram

Addis abeba Ethiopia

Показати більше
4 648
Підписники
-23224 години
-1 7917 днів
-3 26430 день
Архів дописів
#Egypt_ኢትዮጵያ ከግድቡ ሙሌት ማግስት በዛሬው ዕለት የግብፅ ፕሬዝዳንት አብዱል ፈታህ አል ሲሲ የካቢኔ ሹም ሽር አድርገዋል። በዚህ የካቢኔ ሹም ሽር ላይ የውሃና መስኖ ሚንስትሩ ሞሐመድ አብድል
+2
#Egypt_ኢትዮጵያ ከግድቡ ሙሌት ማግስት በዛሬው ዕለት የግብፅ ፕሬዝዳንት አብዱል ፈታህ አል ሲሲ የካቢኔ ሹም ሽር አድርገዋል። በዚህ የካቢኔ ሹም ሽር ላይ የውሃና መስኖ ሚንስትሩ ሞሐመድ አብድል አቲን (የታላቁ ግዳሴ ግድብን ድርድር የሚመሩ) ከሥልጣን ተነስተው በሌላ ሰው ተተክተዋል። ሞሐመድ አብድል አቲን የተከቱት ዶ/ር ሐኒ ስዌይላም የተባሉ ሰው ሲሆኑ ታዋቂ የውሃ ሃብት ተመራማሪ ናቸው ተብሏል። በካይሮ የአሜሪካ ዩኒቨርስቲም እንደሚያስተምሩ ተነግሯል። ፕሬዝዳንት ሲሲ ሌሎች የካቢኔ ሹም ሽሮችንም ያደረጉ ሲሆን አጠቃላይ የ13 ካቢኔ አባላት ሹም ሽር ነው ያደረጉት። የጤና፣ የቱሪዝም፣ የንግድ እና ኢንዱስትሪ፣ የሲቪል አቪየሽን፣ የትምህርት እና ሌሎች ሚኒስትሮችንም በአዲስ ተተክተዋል ተብሏል። አል ሲሲ የመከላከያ፣ የደህንነት፣ የፋይናነስ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮችን እንዳልቀየሩም  ተገልጿል። ዛሬ አስቸኳይ ስብሰባን ያደረገው የሃገሪቱ ፓርላማም በፕሬዝዳንቱ የቀረበውን ሹም ሽር በሙሉ ድምጽ ማፅደቁን አል ዓይን የሀገሪቱን ሚዲያዎች ዋቢ አድርጎ ዘግቧል። አል ሲሲ የካቢኔ ሹም ሽር ያደረጉት የመንግሥታቸውን የሥራ አፈጻጸም ለማሻሻል እና የግብጻዊያንን ጥያቄ ለመመለስ እንደሆነ አስታውቀዋል።

የካይሮ አዲስ ፀረ-ኢዮጵያ ፕሮጀክት ግብፅ፦ በአፍሪካዊ ወጣቶችና ጋዜጠኞች የኢትዮጵያን ጉዳይ የማራገብ አህጉር-አቀፍ ዘመቻ የዓባይልጅ ✍️ እስሌማን ዓባይ ግብፅ ለዲጂታል ፕሮፓጋንዳ አላማ በተፋሰሱ ሀገራት የተለያዩ ቋንቋዎች የሚሰራጩ የራዲዮ ጣቢያዎች የመክፈት ስራዎችን ባሳለፍነው አመት መጀመሯን የምናስታውሰው ነው። በዚህ አመት ከወሰደችው ርምጃ ውስጥ ዋነኛ የሚባለው የሀገሪቱን የሚዲያ ጥናትና ስልጠና ኢንስቲትዩት በግብፅ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ስር ማድረግ ነበር። ይህን Center for Training and Media Studies በአዲሱ ተጠሪ ተቋም ስር ይሆን ዘንድ የአልሲሲ ትእዛዝ ሲሆን አቅጣጫውን በይፋ የሰጡት ደግሞ የግብፁ ጠቅላይ ሚኒስትር ናቸው፤ ጊዜውም በ 16/2 2022 እኤአ። ይህን ተከትሎም ግብፅ በአፍሪካ ትልቁ ነው የተባለውን አህጉራዊ የጋዜጠኝነት ስልጠና በነገው እለተ እሁድ ይፋ እንደምታደርግ ሰምተናል። የግብፁ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሳሜህ ሹክሪ እና የግብፅ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሊቀመንበር ካራም ጃብር ይከፍቱታል ተብሏል። በሚዲያ እና ፖለቲካዊ ጉዳዮች የግብፅ አንገብጋቢ በተባሉ ጉዳዮች ዙሪያ አውደ ጥናቶች የሚካሄዱበት ነው። ሲደረጉ እንጂ በሽፍንፍን መግለጫቸው በውል ያልተጠቆሙ ድብቅ አጀንዳዎች እንደተጠበቁ ሆነው በሰማነው ደረጃ ራሱ በዋነኛነት "የግብፅ የናይል ጥቅምና አፍሪካዊ የዲፕሎማሲና የግጭት ትርክት" የሚሉ አጀንዳዎችን ጨምሮ ተከታዮቹ የተካተቱበት ይሆናል፦ ▪️በካይሮ እና ካርቱም መካከል የጋራ የሚዲያና ፕሬስ ራዕይ መንደፍ ▪️ማህበራዊ ሚዲያ በመገናኛ ብዙሃን ላይ ስላለው ተፅእኖ በማህበራዊ ሚዲያና መገናኛ ብዙሃን እንዴት መዋጋት እንደሚቻል ▪️ግብፅ በናይል ወንዝና በተፋሰስ ሀገራቱ ላይ የሚኖራትን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲና ጥቅም እንዴት ማስረፅ እንደሚቻል። ▪️አመጽ እና ግጭት ባለባቸው ቦታዎች ትርክትን እንዴት ማስኬድ እንደሚቻል የሚደረግ የውይይት መድረክ፣ ▪️በአፍሪካ የውሃ ሃብቶችና የጎርፍ ስጋቶች ዙሪያ ▪️የዲጂታል ኃይሎች በአለም አቀፍ ግንኙነትና ዲፕሎማሲ እንዲሁም በብሔራዊ ደህንነት ላይ የሚኖራቸውን ሚና የተመለከተ ስልጠና በዚህ የስልጠና መርሃግብር ሰልጣኞቹ ከበርካታ ግብፃዊና አለም አቀፍ ከሆኑ ባለሙያዎች፣ ምሁራንና የግብፅ ሚዲያ መሪዎች ጋር ይገናኛሉ። የጥንቷና የአሁኗ ግብፅ ሀውልቶች በርካታ ውይይቶችና ትምህርታዊ ብሎም የመዝናኛ ጉብኝቶችን የተካተቱበትም ነው። በአፍሪካ ደረጃ ትልቁ የተባለው ስልጠና መርሃ ግብር የሚከተለውን ይመስላል። ▪️የአፍሪካ ሚዲያ የሥልጠና The African media training program ከ 14/8/2022 እስከ 9/8/2022 ለሱዳን ለሚገኙ የሚዲያ ባለሙያዎች ስፔሻላይዝድ የተደረጉ 10 የሥልጠና ኮርሶች ለ 4 ሳምንታት ▪️ለወጣት አፍሪካዊያን ለ (3 ሳምንታት) የሚሰጠው ስልጠና ከ9 ወይም 10 ጀምሮ እስከ 29/9/2022 ታቅዷል። ▪️በመቀጠልም ለእንግሊዘኛ ተናጋሪ አፍሪካዊ ብሮድካስተሮች መሰረታዊ ኮርስ ሲሆን ለ 4 ሳምንታት የሚቆይ ነው። ▪️በመቀጠልም ስፔሻላይዝድ የእንግሊዘኛ ኮርስ ከኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ስልጠናዎች በተመረጡ ዘርፎች ይከተላል ይህም ከ6/11 እስከ 17/11/2022..። ▪️ለደቡብ ሱዳን ጋዜጠኞች በልዩ የተዘጋጀው ስልጠና ከ20/11 እስከ 15/12/2022 ለ4 ሳምንታት ይቀጥላል። ▪️ለፈረንሳይኛ ተናጋሪ አፍሪካውያን ጋዜጠኞች የመሠረታዊ የሥልጠና ኮርስ ተግባራት ከ12/25 እስከ 19/1/2023 የሚቆይ ሲሆን በመቀጠልም ለሁለት ሳምንታት የሚቆይ ልዩ ኮርስ በተመረጠ ዘርፍ የመረጃና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ስልጠና ይሰጣል። ▪️ለአረብኛ ተናጋሪ አፍሪካዊ ጋዜጠኞች ለአንድ ወር የሚቆይ ስልጠና ከ5/2/2023 እስከ 2/3/2023 ▪️የአረብኛ ስፔሻላይዝድ ስልጠና ከ5/3 ጀምሮ ለሁለት ሳምንታት የሚቆይ ይሆናል። ▪️የአፍሪካ የሚዲያ ስልጠና መርሃ ግብር ሲጠናቀቅ የወጣት አፍሪካውያን ጋዜጠኞች ስልጠና ለሳምንታት ከ6/5 እስከ 25/5/2023 የሚቆይ ይሆናል። ይህ እንደ አፍሪካ የጀመረችው የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ መነሻውም ሆነ መድረሻው የዓባይ ጉዳይ ነው። የህዳሴ ግድቡን ምንም ማድረግ ባትችልም ኢትዮጵያዊያኑን በመረጃ ጦርነት ማናከስና ማመሰቃቀል ግን ቀሪ አማራጯ የሆነ ይመስላል። ለዚህ ደግሞ በኢትዮጵያ ስር እየሰደዱ የሚታዩት የጥላቻ ንግግሮችና ግጭቶች አመቺ ሆኖላታል። ይህ የካይሮ የፕሮፓጋንዳ ጦርነት እንደ ሀገር ሁሉንም ባለድርሻ ያቀናጀ አፋጣኝ ዝግጅት የሚጠይቀን ነው። #የዓባይልጅ /

ነሐሴ 7 ቀን 2014 ዓ.ም የኮማንዶና አየር ወለድ ኃይል ዋና አዛዥ ሌ/ጀኔራል ሹማ አብደታ የማሰልጠኛ ማዕከሉን የስራ እንቅስቃሴ ጎበኙ፡፡ የኮማንዶና አየር ወለድ ኃይል ዋና አዛዥ እና የሪፓብሊካን
+5
ነሐሴ 7 ቀን 2014 ዓ.ም የኮማንዶና አየር ወለድ ኃይል ዋና አዛዥ ሌ/ጀኔራል ሹማ አብደታ የማሰልጠኛ ማዕከሉን የስራ እንቅስቃሴ ጎበኙ፡፡ የኮማንዶና አየር ወለድ ኃይል ዋና አዛዥ እና የሪፓብሊካን ጥበቃ ኃይል ምክትል አዛዡ የኮማንዶና አየር ወለድ ማሰልጠኛ ማዕከልን የስራ እንቅስቃሴ ተዘዋውረው ተመልክተዋል፡፡ በጉብኝታቸው ወቅትም ማሰልጠኛ ማዕከሉ ያስገነባውን የኮማንዶ የአካል ብቃት መስሪያ ወረዳዎች እና መሰናክሎችን መርቀው ስራ ያስጀመሩ ሲሆን በማዕከሉ በተካሄደው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ላይም ከሰልጣኝ ኮማንዶዎች ጋር ችግኞችን ተክለዋል፡፡ በማሰልጠኛ ማዕከሉ በስልጠና ላይ የነበሩ የጤና ሙያተኞች በዕለቱ የተመረቁ ሲሆን የኮማንዶና አየር ወለድ ኃይል እና የሪፓብሊካን ጥበቃ አመራሮችም በስልጠና ላይ ከሚገኙ ሰልጣኝ ኮማንዶዎች ጋር የትውውቅ ፕሮግራም አካሃደዋል፡፡ በትውውቅ ማድረኩ ላይ የኮማንዶና አየር ወለድ ኃይል ዋና አዛዥ ሌ/ጀኔራል ሹማ አብደታ እና ምክትል አዛዡ ሜ/ጀኔራል ታገሰ ለምባሞ ለተራራው ኮርስ ሰልጣኝ ኮማንዶዎች ልምድ እና ተሞክሮዎቻቸውን አካፍለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ዘርፈ ብዙ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል፡፡ ዓባይ ላይ ግድብ ለመገንባት ስንነሳ ወንዙን የራሳችን ብቻ የማድረግ ፍላጎት አድሮብን እ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ዘርፈ ብዙ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል፡፡ ዓባይ ላይ ግድብ ለመገንባት ስንነሳ ወንዙን የራሳችን ብቻ የማድረግ ፍላጎት አድሮብን እንዳልሆነ ከመጀመሪያውም ስንናገር ነበር፡፡ እኛ ማግኘት የሚገባንን ጥቅም እናግኝ ስንል ልክ እንደ ኢትዮጵያ ሁሉ ሌሎቹ የዓባይ ሥጦታዎች - ሱዳንና ግብጽ ከወንዙ በየድርሻቸው እንደሚጠቀሙበት እያሰብን ጭምር ነው፡፡ እውነትን ይዘን ተነስተን፣ በገዛ ሐቃችን ገንብተን፣ በቃላችን መሠረት፣ ማንም ላይ ጉዳት ሳናደርስ እነሆ 3ኛውን ዙር ውኃ ሙሌት በታሰበው ጊዜ ማጠናቀቅ ስለቻልን የዓባይ ልጆች ሁሉ እንኳን ደስ ያለን!! የዓባይ ወንዝ ለሺህ ዘመናት ሦስቱን ሀገራት አስተሳስሮ እንዳኖራቸው ሁሉ÷ በእሱ ላይ የተገነባው ግድብ ከሌሎች ጎረቤቶቻችንም ጋር በትብብር እንድንኖር ያስችለናል፡፡ ግድቡ ደለል የሚያስቀር በመሆኑ በጎርፍ ምክንያት በታችኛው ተፋሰስ ሀገራት የሚወድመውን ሀብትና የሚጠፋውን የሰው ሕይወት ቁጥር እንደሚቀንስ ይታወቃል፡፡ ከዚህ ባለፈ ግድቡ የሚያመነጨውን ኤሌክትሪክ - በኃይል ምንጭነት፣ በውኃው አናት ላይ የሚነጠፈውን ውብ ገጽታ -በመዝናኛነት፣ በውኃው ጉያ የሚሰግሩትን አሳዎች - በምግብነት ከጎረቤቶቻችንና ከዓለም ጋር እንጋራዋለን፡፡

✍️ ከሸኔ ምርኮኞችና ወዶ ገቦች አንደበት ❗ ✍️ ሰሞኑን በኦሮሚያ ክልል በሆሩ ጉድሩ ወለጋ ዞን በአከባቢው በተሰማረው በኮማንዶ ክፍለጦር ሰራዊት በተደረገው በአሸባሪው ሸኔ ላይ ዘመቻ በርካታ የቡዱኑ አመራሮችና አባላት ተማርከዋል። ከእነዚህ ከተማረኩት አመራሮች መካከል አንዱ ጃል ጅግሳ አንዱ ነው። ጃል ጅግሳ ትክክለኛ ስሙ ሞቱማ ኡማ ነው። ይህ የአሸባሪው ሸኔ ወታደራዊ ክንፍ መሪ በመከላከያ ሰራዊቱ በተደረገው ዘመቻ የቡድኑ አባላት በሙሉ በመደምሳሰቸው በመጨረሻም እራሱ ተገዶ በጀግናው ሰራዊታችን ተማርኳል። ✍️ ጃል ጅግሳ (ሞቱማ ኡማ) እስከአሁን ባደረገው ድርጊት በመፀፀት ይነገራል። እኔ ወደ ትግሉ የገባሁት በተሳሳተ ቅስቀሳ ነው በማለት ይጀምራል። አባኦ የኦሮሞ የነፃነት ትግል እንደሆነ ተነግሮኝ ቢገባም ከገባሁ በኋላ ያገኘሁት የቡድኑ አላማ በፍጹም ይለያል ይላል። በጣም የስቃይ ኑሮ ነው በጫካ ያለው ፣ ቀምለናል ያለአላማ ነው የታገልነው አሁንም በጫካ ያለው ኑሮ መላውን ታጣቂዎች አሰልችቶታል። የቡድኑ ታጣቂ በሙሉ ከገባ በኋላ ተገዶ ነው ህዝብን የሚያሰቃይ ፣ በላይ አመራሮች በሚሰጠው ትዕዛዝ መሠረት ምልሻና የመንግስት መሰረተኞችን እንገላለን። ይህ ተግባር ደግሞ ትክክል እንዳልሆነ ሁሉም ታጣቂዎች ቢያዉቁም ከትግሉ ከካዱ በኃላ ቤተሰባቸው ላይ የሚደርሰውን ጥቃት በመፍራት ያለአላማ በጫካ ውስጥ ይኖራሉ ይለናል። ✍️ ሌላው የቡድኑን እኩይ ተግባር በመረዳት ቡድኑ የሰጠውን የጃል ወይም የወታደራዊ ክንፍ መሪነት ሃላፊነቱን በመተው ለመከላከያ ሰራዊቱ በሰላማዊ መንገድ እጁን የሰጠው የታጣቂዎቹ ክንፍ መሪ እንዲህ ይለናል። ✍️ ጃል ዴብሳ ኩማ  ይባላል። በሆሩ ጉድሩ ወለጋ ዞን ውስጥ የታጣቂዎቹ ክንፍ መሪ የነበረና በአሁኑ ወቅት በሰላማዊ መንገድ እጁን ለሰራዊታችን የሰጠ ነው። አላውቀውም ነበር። ትግሉ የኦሮሞ ህዝቦች የነፃነት ትግል ነው ሲሉኝ ተነስቼ ነው የገባሁት። ነገር ግን አሁን ተመልሰን የኦሮሞን ህዝብን ነው የወገን ፣ የኦሮሞን ህዝብ ነው የጎደን ፤ የኦሮሞን ህዝብ በስሙ ነግደናል። ህብረተሰቡን ያለፍላጎታቸው ዘርፌናል፣ ገለናል፣ አካል አጉድለናል። ስለሆነም የቡድኑ ክንፍ መሪ በመሆኔም በእጅጉ ተፀፅቼ የቡድን አላማ ትርጉም የሌላ ተራ ውንብድና መሆኑን ስለተገነዘብኩ ቡድኑ የሰጠኝን ሃላፊነት ትቼ በሰላም ለመከላከያ ሰራዊቱ እጄን ሰጥቼለሁ ይለናል። አሁንም ለቡድኑ ታጣቂዎች እንደእኔ እጃችሁን በሰላማዊ መንገድ ለመከላከያ ሰራዊት ሰጥታችሁ ሰላማዊ የሆነ ኑሮአችሁን እንድትኖሩ በማለት የሰላም ጥሪውን አስተላልፏል። ✍️ ሌላው በሰላማዊ መንገድ እጁን ለመከላከያ የሰጣው ጃል ዋዳ (ጫለ አዱኛ) ይባላል። ጃል ዋዳም የታጣቂ ቡዱኑ አባልና አመራር በመሆኑና በሚፈፅሙት ሰይጣናዊ ተግባር በመፀፀት በአከባቢው አባገዳዎች በተደረገው የሰላም ጥሪን ተቀብሎ ከእነሙሉ ትጥቁ እጁን ለመከላከያ ሰራዊታችን መስጠቱን ይገልፃል። አሁን በመከላከያ ሰራዊታችን እጅ በመሆኔ ነፃነትና ሰላም እየተሰመኝ ነው የሚለው ጃል ዋዳ በረሃ ለሚገኙ ታጣቂዎችም የተደረገውን የሰላም ጥሪ ተቀብላችሁ በሰላም እጃችሁን ለመከላከያ ሰራዊቱ እንድትሰጡ በማለት መልዕክቱን ያስተላልፋል። ✍️ በዞኑ እስከአሁን በጀል ማዕረግ የሚጠሩ በቁጥር 13 የታጣቂዎቹ ወታደራዊ ክንፍ መሪዎች በመከላከያ ሰራዊታችን እርምጃ ተወስዶባቸዋል። ታሪኩ ሻሜቦ ፎቶግራፍ፦ ታሪኩ ሻሜቦ

የምስራች‼️ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ውሃ ለሶስተኛ ጊዜ በግድቡ አናት ላይ ፈስሷል የአባይ ውሃ ለሦስተኛ ጊዜ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ አናት ላይ መፍሰስ ጀምሯል ተብሏል። በግድቡ ግንባ
የምስራች‼️ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ውሃ ለሶስተኛ ጊዜ በግድቡ አናት ላይ ፈስሷል የአባይ ውሃ ለሦስተኛ ጊዜ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ አናት ላይ መፍሰስ ጀምሯል ተብሏል። በግድቡ ግንባታ ላይ የተሳተፉ ባለሙያዎችም የደስታ ስሜታቸውን ገልፀዋል። በግድቡ ውስጥ መተከል የነበረባቸው የውሃ ማስተላለፊያ የብረታ ብረት ስራዎችን ተጠናቀው የግድቡን የመካከለኛው ክፍል ከፍታ ከባህር ጠለል በላይ ስድስት መቶ ሜትር እንዲሁም ግራና ቀኙን ስድስት መቶ አስራ አንድ ሜትር ማድረስ ተችሏል፡፡ ከሶስት ዓመት በፊት ከባህር ጠለል በላይ በአምስት መቶ ሜትር ከፍታ ላይ ይፈስ የነበረው የአባይ ወንዝ ዛሬ ለሦስተኛ ዙር በግድቡ አናት ላይ የፈሰሰው ከባህር ጠለል በላይ በስድስት መቶ ሜትር ከፍታ ነው ተብሏል፡፡ በአሁኑ ወቅት የግድቡ ግራና ቀኝ ጠርዝ ከባህር ጠለል በላይ ስድስት መቶ አርባ አምስት ሜትር የደረሰ ሲሆን የግድቡ የሲቪል ሥራዎች ግንባታ 95 በመቶ ፤ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራዎች ፍብረካና ተከላ 61 በመቶ እንዲሁም የብረታ ብረት ሥራ 73 በመቶ፣ አጠቃላይ አፈፃፀሙ ደግሞ 83 ነጥብ 3 በመቶ ደርሷል፡፡ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከፍታ ከመሬት 145 ሜትር ሲሆን ርዝመቱ ደግሞ 1 ነጥብ 8 ኪሎ ሜትር የሚሆን ሲሆን የዋናው ግድብ ውፍረት የግድቡ ግርጌ ላይ 130 ሜትር ፤ የግድቡ ጫፍ ወይም የላይኛው ክፍል ደግሞ 11 ሜትር እንደሚሆን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታዉቋል።

⬆️ #MondayMessage የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን፣ አካውንቶችን እንዲሁም ቻናሎችን እንዴት ቬሪፋይ ማስደረግ ይቻላል? የማህበራዊ ሚዲያ ማረጋገጫ (verification) ለመጀመሪያ ጊዜ ይፋ ሲደረግ ለታዋቂ ግለሰቦች እና ድርጅቶች እንዲሁም ከፍተኛ ተከታዮች ላሏቸው ሰዎች ብቻ ተጠብቆ ነበር። ከጊዜ በኋላ ግን በርከት ያሉ ኩባንያዎችን፣ ጋዜጠኞችን፣ አክቲቪስቶችን፣ የመንግስታት ሀላፊዎችን እና ተጽዕኖ ፈጣሪዎችን ለማካተት ጥረት ተደርጓል፡፡ በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ይህንን ማረጋገጫ (verification) ማግኘት ብዙ ጥቅሞች አሉት። ከእነዚህም መሀል: • ከተከታታዮች ጋር መተማመንን ለመገንባት • ማህበራዊ ማስረጃን (social proof) ለማግኘት • ተመሳስለው የሚከፈቱ አካውንቶችን፣ ገፆችን እና ቻናሎችን በቀላሉ ለመለየት፣ እንዲሁም • የተከታታዮችን እድገት ለማግኘት ወዘተ ሊጠቀሱ ይችላሉ በትዊተር ላይ ማረጋገጫን (verification) ማግኘት: በትዊተር ላይ ማረጋገጫን ለማግኘት በሚከተሉት ምድቦች ውስጥ መገኘት ያስፈልጋል: • የመንግስት አካል • የምርት ድርጅቶች፣ ኩባንያዎች እና ለትርፍ ያልተቋቋሙ ድርጅቶች • ጋዜጠኞች እና የዜና ድርጅቶች ባልደረባ • የስፖርት ድርጅቶች እና ስፖርተኞች • መዝናኛ ኢንደስትሪ ውስጥ ያሉ መሆን • አክቲቪስቶች፣ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች መሆን የትዊተርን ሰማያዊ ባጅ ለመቀበል ገጹ ትክክለኛ (authentic)፣ ታዋቂ (notable) እና ንቁ (active) መሆን አለበት። ትክክለኛ(authentic): የትዊተርን ማረጋገጫ ለማግኘት ትዊተር ማንነትዎን ማረጋገጥ ይፈልጋል። ማንነትዎን ለማረጋገጥ ከሶስቱ ዘዴዎች ውስጥ አንዱን መምረጥ ይቻላል። እነሱም: የተረጋገጠ ድረ-ገፅ፣ መታወቂያ ወይም የኢሜል አድራሻን መጠቀም ይቻላል። ታዋቂ (notable): አካውንቱ ከታወቀ ግለሰብ ወይም ድርጅት ጋር በአንድም ሆነ በሌላ መልኩ የተያያዘ መሆን አለበት። ይህንንም ትስስር ትዊተር በራሱ ወይም አብረው በሚሰሩ ድርጅቶች ይረጋገጣል። ንቁ (active): የትዊተር አካውንቱ የትዊተር ህጎችን ባከበረ መልኩ ንቁ መሆን አለበት። ይኼ ማለት የመገለጫ ስም እና የመገለጫ ምስል ሊኖረው ይገባል። ንቁ አጠቃቀም ማለት ባለፉት 6 ወራት ውስጥ አካውንቱን መጠቀም አለብዎት። ከዚህም በተጨማሪ አካውንቱ የተረጋገጠ የኢሜል አድራሻ ወይም የስልክ ቁጥር ሊኖረው ይገባል። አንዴ የትዊተር ማረጋገጫ ከተሰጠ በኋላ የተጠቃሚ ስምዎን (username) ከቀየሩ፣ አካውንቱ እንቅስቃሴ አልባ ከሆነ፣ ወይም መጀመሪያ መረጋገጫው በተሰጠበት ቦታ ላይ ካልሆኑ የተሰጠው ማረጋገጫ ሊወርድ ይችላል። Note: ትዊተር ከቀናት በፊት የማረጋገጫ ጥያቄዎችን ለግዜው መቀበል እንዳቆመ አስታውቋል። በፌስቡክ እንዴት ማረጋገጫ ይሰጣል? • በመጀመርያ ወደ ፌስቡክ ሰማያዊ ማረጋገጫ ባጅ መጠየቂያ ገጽ (Blue Verification Badge Page) ይሂዱ። ሊንክ: https://www.facebook.com/business/learn/lessons/verify-facebook-instagram-account • የማረጋገጫ ዓይነትዎን (ገጽ ወይም አካውንት) ይምረጡ • ምድብ ይምረጡ፣ አገርዎን ይምረጡ፣ መታወቂያ ያስቀምጡ፣ የእርስዎ መለያ/አካውንት ለምን መረጋገጥ እንዳለበት ያብራሩ፣ ከዛም 'ላክ' የሚለውን ይጫኑ። ለግለሰቦች የመንጃ ፈቃድ ወይም ሌላ በመንግስት የተሰጠ የመታወቂያ ካርድ ይበቃል። ለንግድ ገጽ ደግሞ የምስረታ የምስክር ወረቀትን፣ የኩባንያዎን ስልክ ወይም የፍጆታ ሂሳብ ወይም የግብር ሰነዶችን ማቅረብ ይችላሉ። ጥያቄዎን ከላኩ በኋላ የፌስቡክ ማረጋገጫ ቡድን መረጃዎን ይገመግምና እና ውሳኔ ይሰጣል። ፌስቡክ ጥያቄውን ከተቀበለው በአካውንቱ ላይ ሰማያዊ ባጅ ይታያል። ሆኖም ጥያቄዎ ውድቅ ከተደረገ ከ30 ቀናት በኋላ እንደገና ማመልከት ይችላሉ። የፌስቡክ ማረጋገጫ የብቁነት መስፈርቶች ከኢንስታግራም (Instagram) ጋር ተመሳሳይ ናቸው። እንዲሁ በዩትዩብ (YouTube) ላይ ማረጋገጫ ማግኘት ይቻላል። የዩትዩብ ቻናሉ ለማረጋገጫ ባጅ ብቁ ከሆነ ግራጫ አመልካች ምልክቱን ለማግኘት በማረጋገጫ ባጅ ገጹ ላይ ማመልከት ይችላሉ። ዩትዩብ መስፈርቶቹን የሚያሟላ መሆኑን ለማየት ቻናሉን ይገመግማል። የማረጋገጫ ባጅ ለመቀበል የዩትዩብ ቻናሉ ቢያንስ 100,000 ተመዝጋቢዎች ሊኖረው እና መስፈርቶችን ማሟላት አለበት። ማስታወሻ: ሁሉም የማህበራዊ ሚድያ ድርጅቶች ማረጋገጫ ለመስጠት ገንዘብ አያስከፍሉም፣ ስለዚህ "ማረጋገጫ እንዲሰጥዎት እናደርጋለን" ብለው ገንዘብ ከሚጠይቁ ግለሰቦች እና ድርጅቶች ራስዎን ይጠብቁ። ©EthiopiaCheck

ሌሎችን ደብቃ ውኃውን የምታሾርባቸውን ፕሮጀክቶች መመርመር ይጠይቃል። በሰሞኑ ቀውስ ‹‹የካይሮ እጅ እንዳለበት›› የመንግሥት ባለሥልጣናት በገደምዳሜ ሲናገሩ የሰማን መሰለኝ። መንግሥት በምርመራው ከግምት በላይ ለዚህ መረጃ ካለው፣ በግልጽ በድርድሩ ወቅት አቋሙን ማሳወቅ ይኖርበታል። ይህንን ጥርጣሬውን መንግሥት ለካይሮ ይፋ አድርጎ መሰል ሕገወጥ እንቅስቃሴ በግልጽም ሆነ በይፋ ድጋፏን የሚጠቁሙ ጉዳዮች ካሉ፣ አብሮ ተባብሮ ለመሥራት እንደማይቻል ማሳወቅ ይኖርበታል ብዬ አስባለሁ። ከድርድር በኋላ የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የሚሰጡዋቸው መግለጫዎች በአንድ የጋራ ጉዳይ እየተደራደሩ ሳይሆን፣ የጦር ጄኔራሎች ከጦርነት በኋላ ቀዝቃዛ ጦርነትን አስመልክተው መግለጫ የሚሰጡ ይመስላል። ይህ ደግሞ በድርድሩ ላይ ጫና ለመፍጠር የሚደረግ በመሆኑ ግብፅ ልታውቀው ይገባል። በቅርቡ የግብፅ ተደራዳሪዎች ስለሌላ ግድብ ጉዳይ የማንሳታቸው ወሬ ሲነገር ነበር። ኢትዮጵያ 90 በመቶ እየተስማማን ነው የሚል የዋህ መግለጫ አይጠቅማትም። የቀረው አሥር በመቶ ውስጥ ሰይጣኑ አለ። አብዛኛውን እንደተስማሙበት የሚነገረው እንዲህ የሚያኩራራ አይደለም። በየጊዜው ተለዋዋጭና አዲስ አጀንዳ እያመጣች ድርድሩ እንዲቋረጥ ከምታደረግ አገር ጋር፣ ‹‹አብዛኛው ጉዳይ ላይ ስምምነት››"ተደርሷል ብሎ ‹‹ስለድል›› መናገር ይከብዳል። አደራዳሪው የአፍሪካ ኅብረት መሆኑ አያስፈነድቅም፡፡ ምክንያቱም ተደራዳሪዋ ግብፅ ነች። ኢትዮጵያ የምትጠቀመው ከአደራዳሪዎቹ አፍሪካዊነት ወይም አሜሪካዊ ማንነት ሳይሆን ከእውነታው ላይ መሆን አለበት። ከግብጽ ጋር 99 በመቶ መግባባት ወይም መስማማት እንኳን ቢኖር እንደ ዲፕሎማሲያዊ ድል መውሰድ አይገባም። አንድ በመቶ የሚሆነው አንቀጽ በጥንቃቄ ካልታየ ኢትዮጵያ በዓባይ ወንዝ የመጠቀም መብቷን ቀፍድዶ ዘውትር መነታረኪያ አጀንዳ ሊፈጥር ይችላል። ኢትዮጵያ ሳትፈርም እንኳን ሱዳን ‹‹ውኃ ቀነሰብኝ›› ዓይነት ክስ ማንሳቷ ወደፊት የተፈራረሙበትን አንቀጽ እየመዘዙ መነታረኩ እንደሚኖር ይጠቁማል። ታላቁ የአስዋን ግድብና የቶሽካ ፕሮጀክት ምን ያህል የዓባይ ውኃ ይበቃቸዋል? ኢትዮጵያ ስለታላቁ ህዳሴ ግድብ ውኃ አያያዝ ከመነጋገር ጎን ለጎን ግብፅና ሱዳን ውኃውን እንዴት እየተጠቀሙበትና እያድፋፉት እንደሆነ፣ የእነሱን ነባርና አዳዲስ ፕሮጀክቶች በአግባቡ ማወቅ ይጠቅማል። ያም ሆነ ይህ የሦስቱ አገሮች ድርድር ስምምነት ተደርሷል በሚል የሚደረግ የፊርማ ማሳረጊያ የዓባይ ወንዝን ንትርክ በዘላቂነት ይፈታል ብሎ ማሰብ የዋህነት ነው። ግብፅ ሰነዱን መፈረም የምትፈልገው በተለሳለሰ ቋንቋ የተጀቦነ የቅኝ ግዛቱን ውል ዘመናዊዋ ኢትዮጵያ እንድትቀበል ግፊት በመፍጠር ይሆናል። ልክ እንደ ሱዳን ‹‹ውኃው ቀነሰ ....›› እያሉ ከግድቡ ይለቀቅ በሚል ተፅዕኖ በማሳደር የማያቋርጥ ንዝንዛቸውን ሊፈጥር እንደሚችል ከወዲሁ መገመት ይቻላል።

እ.ኤ.አ. በ2005 መጋቢት ወር የፕሮጀክቱ ዕምብርት የሆነው የሙባረክ ውኃ ማሰራጫ ጣቢያ በይፋ ተመርቋል። የሙባረክ ውኃ መግፊያ ጣቢያ የዓባይን ውኃ ከናስር ሐይቅ ውስጥ ለውስጥ የሚገፋ ግዙፍ ማሰራቻ ነው። ከናስር ሐይቅ በስተስሜን 310 ኪሎ ሜትር የሚደርሰው ቦዩ እ.ኤ.አ. እስከ 2012 ድረስ 60 ኪሎ ሜትር ተሠርቶ ነበር። በዚህ ፕሮጅክት ውኃውን 2340 ካሬ ኪሎ ሜትር የሚሽፍን ሲሆን፣ የዓባይን ሸለቆ በረሃ ወደ ምድረ ገነት የእርሻ መሬት የመለወጥ ዓላማ አለው። የቶሽካ ፕሮጀክት በፕሬዚዳንት አብዱልፈታህ አልሲሲ አማካይነት ዳግም እንዲያንሰራራ እየተደረገ ነው። ግማሽ የሚሆነው መሬት ለኮሌጅ ተመራቂዎች የሚሰጥ ሲሆን፣ ለእያንዳንዳቸው 4046.86 ካሬ ሜትር በመስጠት ‹‹ግብፅ ለዘለዓለም ትኑር ፈንድ›› ከሚባል ተቋም የገንዘብ ድጋፍ ምድረ በዳውን እንዲያለሙ ውጥን አለ። የግብፅ ቶሽካ ፕሮጀክት እ.ኤ.አ. ጃንዋሪ 9 ቀን 1997 በቀድሞ ፕሬዚዳንት ሆስኒ ሙባረክ በተገኙበት መጀመሩ ተበሰረ፡፡ በፕሮጀክቱ ተመጋጋቢ ቦዮችን (ካናሎች) ከናስር ሐይቅ ወደ ግብፅ በረሃማ ሥፍራዎች ለመስኖ እርሻዎች የሚሆን ውኃ የሚያሻግር የመግፊያ ጣቢያ ተሠርቶለት ተጠናቋል። እ.ኤ.አ. በ2020 ወደ ሦስት ሚሊዮን ነዋሪዎችን ማሥፈር የሚያስችል ሆኖ፣ የግብፅን የሚታረስ መሬት አሥር በመቶ የሚያሳድግ ግዙፍ የዓለማችን የውኃና የመስኖ ፕሮጀክት ነው:: ከግብፅ ሕዝብ 20 በመቶ የሚሆኑ ሰዎችን ማሥፈር የሚያስችል ፕሮጀክት ነው፡፡ ይህም ከ20 ሚሊዮን በላይ ሰዎች በሰሃራ በረሃ በዘመናዊ ግብርና እንዲተዳደሩ፣ ብሎም ሌላ ካይሮን የምታህል ከተማ ለመገንባት ውጥን የተያዘበት ነው። በቶሽካ ፕሮጀክት የመጀመሪ ምዕራፍ የሙባረክ የውኃ መግፊያና ማሠራጫ ጣቢያ እ.ኤ.አ. በ2005 በ436 ሚሊዮን ዶላር ወጪ ግንባታው ተጠናቋል:: በአንድ ጊዜ 18 የውኃ መግፊያ መስመሮች የሚሠሩ ሲሆን፣ ሦስቱ ለጥገና ፍላጎት ሌሎች ሶስት ደግሞ እንደ መጠባባቂያ የሚያገለግሉ ናቸው:: የውኃ ማሠራጫ ጣቢያው 50 ሜትር በመሬት ጥልቅ ውኃ መግቢያ ቦይ የተፈጠረለት ነው፡፡ በሰዓት 1.2 ሚሊየን ኪዩቢክ ሜትር ውኃ ይገፋል ፡፡ የካናሉ ውኃ ማስተላለፊያ ቱቦ 30 ሜትር ስፋት አለው:: የውኃ ማሠራጫና ማስተላለፊያ ካናሉ በተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስ መሪ ሼክ ዚያድ አል ናህያን ስም ተሰይሟል:: ቶሽካ ፕሮጀክት በተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስ የገንዘብ ድጋፍ የሚሠራ በመሆኑ ነው በስማቸው የተሰየመው:: ከዚህ ግዙፍ የውኃ ማሠራጫ ጣቢያ የሚጀምሩና መሬት ለመሬት የተቀበሩ 24 የአግድሞሽ ውኃ መግፊያና ማሠራጫ ቱቦዎች በዋና ማከፋፈያ ጣቢያው ዳርና ዳር በሁለት ረድፍ ትይዩ ተሠርተው ተጠናቀዋል:: የውኃ ጫና መቆጣጠሪያና የፍጥነት ማስተካካያ ሥርዓትም ተበጅቶላቸዋል፡፡ የሙባረክ የውኃ መግፊያ (ማሠራጫ) ጣቢያ እ.ኤ.አ. በ2005 ሲጠናቀቅ በሲቪልና በሜካኒካል ምህንድስና ስኬቶቹ የተወደሰ ነው:: ሙሌቱ በብረት የተዋቀረ ሲሆን፣ የመሬት ርዕደትን መቋቋም እንዲችል ተደርጎ የተሠራ ነው:: ሆስኒ ሙባረክ እ.ኤ.አ. በ2011 በፀደይ አብዮት ከሥልጣን በመወገዳቸው የቶሽካ ፕሮጀክት ሒደትን እንደገታው ይነገራል፡፡ በአገሪቱ በተፈጠረው የፖለቲካና የኢኮኖሚ ቀውስ ፕሮጀክቱ መቀዛቀዙ በምክንያትነት ይጠቀሳል፡፡ በቀጭን ክር ቶሽካንና ትውልደ ኢትዮጵያዊውን ሼክ መሐመድ አል አሙዲን ማያያዝ ይቻላል። ‹‹ሳዑዲ ስታር አግሪካልቸራል ዴቨሎፕመን›› ኩባንያ ባለቤት ትውልደ ኢትዮጵያዊ የሳዑዲ ዜጋ ሼክ መሐመድ አል አሙዲ ናቸው፡፡ ኩባንያው በምዕራብ ጋምቤላ ወደ 10,000 ሔክታር መሬት የሚሸፍን እርሻ አለው። ይህ ኩባንያ እ.ኤ.አ. እስከ 2020 ድረስ ወደ 2.5 ቢሊዮን ዶላር መዋዕለ ንዋይ ያፈስበታል ተብሎ ነበር። ይህ ፕሮጀክት ዋና ምርቱ ሩዝ ሲሆን፣ በዋናነትም ለውጭ ገበያ የሚቀርብ እንደሆነ ይነገራል፡፡ ሳዑዲ ስታር የተባለው የሼክ አል አሙዲ ኩባንያም ምርቱን በዋናነት ለሳዑዲ ዓረቢያ ሊያቀርብ የታሰበ ነበር፡፡ ባለሀብቱም ከሳዑዲ ንጉሣዊ ቤተሰቦች ጋር ባላቸው መቀራረብ ተነጋግረው የተጀመረ ግዙፍ ፕሮጀክት እንደሆነ ይነገራል። ይህ የሚያሳየን ሳዑዲ ዓረቢያ በአንድም በሌላም ኢትዮጵያ ውስጥ ካለው የዓባይ ውኃ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የራሷ የሆነ የጥቅም ፍላጎት እንዳላት ነው፡፡ ጋምቤላ ውስጥ ያሉ ወንዞች የዓባይ ገባር መሆናቸውን ይታወቃል፡፡ የሳዑዲ ዓረቢያ ሚና በዚህ ፕሮጀክት ላይ ምንድነው ስንል ታላቅ ኢንቨስትመንትን እናገኛለን፡፡ የሳዑዲው ልዑል አል ዋሊድ ቢን ጣላል ቢን አብዱላዚዝ አል ሳዑድ ‹‹ዘ ኪንግደም አግሪካልቸራል ዴቨሎፕመንት›› የተሰኘ ኩባንያ ባለቤት ሲሆኑ፣ ግብፅ ውስጥ በጥቅሉ ከሁለት ቢሊዮን ዶላር በላይ ካፒታል ያንቀሳቅሳሉ፡፡ በቶሽካ ፕሮጀክት ደግሞ ከአሥር ሺሕ ሔክታር በላይ መሬት ተረክበው የተለያዩ የግብርና ምርቶችን ለማምረት፣ ከግብፅ የውኃና የመስኖ ልማት ሚኒስቴር ጋር ተፈራርመዋል፡፡ በየዓመቱም በሚሊዮኖች ለዚሁ የቶሽካ ፕሮጀክት አካል ለሆነው መሬት ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ እንደሚያፈሱ ይነገራል፡፡ የቶሽካ ፕሮጀክት ሐሳብ አዲስ አይደለም፡፡ የቀድሞ ፕሬዚዳንት ጋማል አብደል ናስር በታላቁ የናስር ግድብ ጀምረውት፣ ግን እ.ኤ.አ. በ1964 የተቋረጠው ግዙፍ ዕቅድ አካል መሆኑ ይነገራል፡፡ የቴክሳስ ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ኦስቲን የዶክትሬት ተማሪዋ ኢማ በግብፅ ሜጋ ፕሮጀክቶች ዙሪያ ባካሄደችው ጥናት የቶሽካ ፕሮጀክት በጀት ከመንግሥትም ሆነ ከሕዝብ የተሰወረ መሆኑን ጠቅሳለች፡፡ ከግብፅ ብቻ ሳይሆን ከኢትዮጵያም የተሰወረ ነው፡፡ ፕሬዚዳንት አልሲሲ ወደ ሥልጣን ሲመጡ ደጋፊዎቻቸው የቀድሞ ፕሬዚዳንት የጋማል አብደል ናስርን ፎቶግራፍ ይዘው በመውጣት ነበር ስለመጪው መሪ አተያይ ለማንፀባረቅ የሞከሩት፡፡ የቀድሞ ፕሬዚዳንት ሆስኒ ሙባረክ ላይ አዲስ አበባ ውስጥ ግድያ መቃጣቱን ተከትሎ የአፍሪካ ኅብረት ስብሰባ በተለይ አዲስ አበባ በሚካሄድ ጊዜ ለብዙ ዓመታት መምጣት በመተዋቸው፣ ኢትዮጵያ ሌሎች የዓባይ ተፋሰስ አገሮችን እንድታስተባብር ዕድል አግኝታ ነበር፡፡ ይህ የገባቸው አልሲሲ ግብፅን ወደ የአፍሪካ ኅብረት መልሰው የወቅቱን ሊቀመንበርነት ከሩዋንዳ እንድትረከብ አደረጉ፡፡ እሳቸው በምርጫ ወደ ሥልጣን የመጡትን መሐመድ ሙርሲን መፈንቅለ መንግሥት በሚባል ዓይነት ከሥልጣን ቢያስወግዱም፣ የአፍሪካ ኅብረት ከማጉረምረም ያለፈ ምንም አላደረጋቸውም፡፡ ቶሽካ የግብፅ ባለሥልጣናት ‹‹የፒራሚዶችን ግንባታ በ20 እጥፍ የሚያስከነዳ›› ግዙፍ የካይሮ ግዙፍ ፕሮጀክት መሆኑን ይናገራሉ። አዲሱን የዓባይ ሸለቆ ሥልጣኔ እንደሚያመጣም ተነግሮለታል። ከአየር ላይ ወደ ታች ለሚመለከት ግዝፈቱ የዘመናችንን የግንባታ ተዓምር ብቻ የሚያሳይ ብቻ ሳይሆን፣ የግብፅን የዓባይ ውኃ የመቆጣጠር ታላቅ ህልም ቁልጭ አድርጎ ያሳያል። ግብፅ በቅርቡ አዲስ ነገር ይዛ መጥታለች ብሎ የተደነቀው የኢትዮጵያ ተደራዳሪ ቡድን፣ በታላቁ የህዳሴ ግድብ ዙሪያ የአገሩን አቋም ማስረዳቱ ብቻ በቂ አይሆንም። የግብፅን ታላቁ የአስዋን ግድብ መጎብኘት ወይም መፈተሽ፣ ከዚያ ግዙፍ ግድብ ጋር ተያይዞ ወደ ዓለማችን ታላቁ ሞቃታማና ምድረ በዳ በረሃ ውስጥ ለውስጥ የተሠራውን በጥርብ ድንጋይና በኮንክሪት ሲሚንቶ የተገነባውን ረዥሙንና ሽንጣሙን ቅንጡ የቶሽካ ፕሮጀክት ይመለከተኛል ብሎ መነሳት ያስፈልጋል። ግብፅ ከዓባይ ወንዝ ድርሻ አብዝታ መጠየቋን እንዳለ መቀበል አያስፈልግም። የኢትዮጵያን ፕሮጀክቶች ያገባኛል ብላ የምትሞግተውን ያህል፣

የግብፅ ጥጥ እርሻዎች የዓባይ ወንዝን ተከትለው መስፋፋት የአውሮፓውያንን ትኩረት መሳቡ አልቀረም:: የአሪቱን የጥጥ ምርቶች በበላይነት የተቆጣጠሩት መሐመድ ዓሊ፣ በናይል ሸለቆ የጥጥ እርሻዎችን አስፋፉ:: መሐመድ ዓሊ በየዓመቱ በቁርጥ ዋጋ በመሸጥ ወደ ግብፅ ካፒታል እንዲፈስ አደርገዋል:: በዚህ አንድ የግብርና ምርት ብቻ የአውሮፓ ገበያን መቆጣጠሯ ዛሬም ቢሆን ለብዙዎች አስገራሚ ነው:: አንድ ሸቀጥ ብቻ ተደርጎ የሚወሰድ ሳይሆን የጥጥ ምርቱን ለመቆጣጠር እንግሊዝና ፈረንሣይ፣ እንዲሁም ሌሎች የአውሮፓ አገሮች ግብፅን የቅኝ ግዛታቸው ለማድረግ አንዳነሳሳቸው ይነገራል፡፡ ዓባይ ከኢትዮጵያ ውኃና ለም አፈር በረሃማዋ ግብፅ ድረስ ያጓጉዛል:: አርሶ አደሮቿ የዘሩት ጥጥ የአውሮፓ የጨርቃ ጨርቅና የአልባሳት ኢንዱስትሪዎች ዋነኛ ግብዓት ምንጭ ሆነ፡፡ ለግብፅ የፈለገችውን እንድትበደር ያደረገ ኃይለኛ የገንዘብ ምንጭ ፈጠረላት፡፡ የጥጥ እርሻዎቿ ለካይሮ የብድር ሥርዓት አምጥተውላታል:: ኢትዮጵያ የዓባይን ውኃ ብቻ ሳይሆን ለም አፈርና ምርጥ የጥጥ ዝርያ ለግብፅ ሰጥታለች፡፡ የአውሮፓ ባንኮች በሚያማልል ወለድ ብድር እንድትወስድ ያግባቧትም ነበር:: ከገንዘቡ ትርፍ ይልቅ ግብፅን የሚያዘምኑ ኢንዱስትሪዎች ለመገንባት ገንዘብ እንድትበደራቸው ይገፋፏት ነበር:: በአውሮፓውኑ ባንኮች ግብፅ ዕዳ ወስጥ ገብታ የነበረ ቢሆንም፣ ከጥጥ ምርቷ ባገኘችው ገቢ መሸፈን ችላለች:: አሜሪካ የእርስ በእርስ ጦርነት እ.ኤ.አ. በ1861 መቀስቀሱን ተከትሎ የግብፅ ጥጥ ምርት ለተወሰኑ ጊዜያት በአስገራሚ ሁኔታ አደገ፡፡ እ.ኤ.አ በ1862 ወደ ወጭ ከላከችው የጥጥ ምርት 16 ሚሊየን ዶላር ገቢ ያገኘች ሲሆን፣ እ.ኤ.አ. በ1854 ወደ 56 ሚሊየን ዶላር ማገኘቷን መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ በወቅቱ ግብፅን ይመሩ የነበሩት የመሐመድ ዓሊ የልጅ ልጅ ኢስማኤል ፓሻ ፈረንሳይ የተማሩና አውሮፓን በመዘዋወር ልምድ የቀሰሙ ነበሩ፡፡ የፈረንሣይ ተፎካካሪ አፍሪካዊት አገር ለመገንባት የሚያልሙት ኢስማኤል ፓሻ "ፓሪስን በዓባይ" ላይ ለመገንባት ብዙ ለፍተዋል፡፡ በዓባይ ዙሪያ የተስፋፉትን የጥጥ እርሻዎች ገቢ በመጠቀም፣ በግብፃውያን ገንዘብና ደም ስዊዝ ቦይ እንዲገነባ ማድረጋቸው ይጠቀሳል:: የአስዋን አነስኛ ግድብ የሚያጠራቅመው የአንድ ዓመት ውኃ ብቻ ነበር፡፡ የሚይዘው የውኃ መጠን ብዙ አልነበረም፡፡ እ.ኤ.አ በ1912 ትውልደ ግሪክና ግብፅ ማሃዲሱ አድሪያና ዳንኒዮስ አዲስ የአስዋን ግድብ ግብፅ ወስጥ ለመገንባት ያቀረበው ውጥን ነበር፡፡ እ.ኤ.አ. በ1946 አነስተኛው (ግልገል) አስዋን ግድብ ዓባይ ወንዝ መሞላት ቢጀምርም የዳንኒዮስ ዕቅድ ንጉሥ ፋሩቅን ብዙም አልሳባቸውም፡፡ የትነት መጠኑ አነስተኛ በሚሆንባቸው ሱዳንና ግብፅ የዓባይን ወንዝ ውኃ ለማጠራቀም ሐሳቡ ይደገፍ ነበር:: የግብፅ ንጉሣዊ አገዛዝ መገርሰሱን ተከትሎ ጋማል አብደል ናስርን ጨምሮ የነፃ መኮንኖች ንቅናቄ (Free Officers Movement) መሪዎች ወደ ሥልጣን በመምጣታቸው፣ የግብፅ አቋም ሙሉ ለሙሉ ተለወጠ:: በዳንኒዮስ ዕቅድ መሠረት የነፃ ወታደራዊ መኮንኖች ንቅናቄ መሪዎች በፖለቲካ ምክንያቶች ሳቢያ የዓባይ ውኃ በግብፅ ውስጥ እንዲጠራቀም በመወሰናቸው፣ በሁለት ወራት የዳንኒዮስን ዕቅድ ተቀበሉት:: ይህም የታላቁ አስዋን ግድብ መገንባት ምክንያት ሆነ:: በዚህ ግዙፍ የዓባይ ወንዝ ግንባታ ላይ ሁለት ጉዳዮች ማንሳት ይጠቅማል። 1. የሱዳን ታላቁ የመረዌ ግድብ የሱዳን ፕሬዚዳንት ኦማር አል በሽር የመጨረሻ ደማቅ ዳንስ የደነሱት እ.ኤ.አ. በ2009 ነበር፡፡ በሱዳን ሙዚቃ ከታጀበው ዳንሳቸው ጀርባ አንድ ትልቅ ግድብ ተጠናቆ እየተመረቀ ነበር፡፡ ሳይጠጡ በደስታ ያሰከራቸው በቻይናውያን ቀያሽነት፣ መሐንዲስነትና አበዳሪነት፣ እንዲሁም በዓረብ አገሮች ድጋፍ የተሠራው የመረዌ ግድብ ተጠናቆ እየተመረቀ ነበር፡፡ አል በሽር ዳንስና ከፊታቸው የሚታየው ፈገግታ በዚህ ግድብ አማካይነት ‹‹አዲዮስ የሱዳን ችግር እንጦሮጦስ ገባ…›› እያሉ ይመስል ነበር፡፡ ሱዳን የዳቦ ቅርጫት ሆና ከመካከለኛ የኑሮ ደረጃ በአንዴ እንደምትገባ እርግጠኛ የሆኑ ይመስል ነበር፡፡ ሱዳን ከአስዋን ግድብ ቀጥሎ በትልቅነቱ ሁለተኛ የሆነውን የመረዌ ግድብ በሰሜናዊ ካርቱም 350 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ እ.ኤ.አ. ከ2003 እስከ 2009 ሠርታ አጠናቀቀች፡፡ የመረዌ ግድብ ለኤሌክትሪክና ለአዲስ የመስኖ እርሻ ታቅዶ የተገነባ ነበር፡፡ በዚህ ወቅት ግብፅ በሱዳን የመረዌ ግድብ አሞላልና አስተዳደር ላይ ምንም ያነሳችው ውዝግብ አልነበረም፡፡ ኢትዮጵያ ይኼ ግድብ እየተሠራ ቢሆንም ምን እየተደረገ እንደነበር የምታውቅም አትመስልም ነበር፡፡ የመረዌ ግድብ ርዝመት 9.2 ኪሎ ሜትር ሲሆን፣ 1250 ሜጋ ዋት የኤሌትሪክ ኃይል እንዲያመነጭ ነበር የተሠራው፡፡ አሁንም ቢሆን ከግብፅ ታላቁ አስዋን ግድብ ቀጥሎ በግዝፈቱ ሁለተኛ ነው፡፡ ይህ ግድብ የሚይዘው ውኃ 174 ኪሎ ሜትር ድረስ የተዘረጋ ነው፡፡ ከቻይና ኤክስፖርት ኢምፖርት ባንክ ብድርና ከዓረብ አገሮች በተገኘ 2.4 ቢሊዮን ዶላር ወጥቶበታል፡፡ የተገነባው በቻይና፣ በጀርመንና በፈረንሣይ ኩባንያዎች ነው፡፡ ግድቡ ሲገነባ ከ50 ሺሕ በላይ ሱዳናውያን ለም ከሆነው የዓባይ ሸለቆ ተፈናቅለው በረሃ ላይ እንዲሠፍሩ ተደርገዋል የሚል ክስ ይቀርብበታል፡፡ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሰብዓዊ መብት ተቋም ሳይቀር እ.ኤ.አ. በ2007 ግንባታው እንዲቆም ሪፖርት አቅርቦበት ነበር፡፡ ፊት ለፊት ባይሆንም ግብፅም አቧራ አስነስታበታለች፡፡ ግን እንደ ኢትዮጵያ በግልጽ ጠንካራ ሙግት አላነሳችበትም፡፡ 2. ቶሽካ ፕሮጀክት የሰሃራ በረሃ የልማት ውጥን የቀድሞው የግብፅ መሪ ሆስኒ ሙባረክ እ.ኤ.አ በ1997 “New Nile Valley Project” (የአዲሱ የናይል ሸለቆ ፕሮጀክት) በማለት ግዙፍ የሆነውን የሰሃራ በረሃን የማልማት ዕቅድ ነድፈው ነበር። ሙባረክ ለዕቅዱ ተግባራዊነት መንቅሳቅስ ጀምረው ነበር፡፡ ይህ ፕሮጀክት በዋናነት ሁለት ምዕራፎች ሲኖሩት አንደኛው በሰሜን ምሥራቅ ግብፅ የሚገኘው የአል ሰላም ቦይ (ካናል) ፕሮጀክት ነው፡፡ እሱም ውኃ ከዓባይ ግርጌ በመጥለፍ ወደ ሲና በረሃ ማሻገር ነው፡፡ ይህን በማድረግ ብዙ መቶ ሺሕ ሔክታር መሬት በማልማት 750 ሺሕ ግብፃውያንን ለማስፈር ያለመ ነው፡፡ ዋናውና ትልቁ ፕሮጀክት ግን የቶሽካ ፕሮጀክት ሲሆን፣ ይህም የደቡብ ምዕራብ ግብፅ በረሃን ለማልማት ያቀደ ፕሮጀክት ነው፡፡ በግብፃውያኑ ዘንድ ይህ ፕሮጀክት አሁን ባለው ሁኔታ እ.ኤ.አ. 2020 ያልቃል ተብሎ ነበር፡፡ ፕሮጀክቱ በዋናነት አዲስ ግብፅ በበረሃው ለመፍጠር ያቀደ ሲሆን፣ የተለያዩ በርካታ የውኃ ቦዮችንና የውኃ መምጠጫ ፓምፖዎችን በመገንባት ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ ይህን በማደረግ በረሃውን በማልማት ወደ ሦስት ሚሊዮን ግብፃውያንን የማስፈር ዕቅድ አላቸው፡፡ እንደ ግብፃውያኑ ከሆነ ይህ ፕሮጀክት ውኃውን የሚያገኘው በናይል ላይ ከተሠራው የአስዋን ግድብ ጀርባ ከሚገኘው የናስር ሐይቅ ነው፡፡ ግብፃውያኑ ይህን ሥራ የትኞቹንም የላይኛውን የተፋሰስ አገሮች ሳያናግሩ ሲሠሩት ውኃውን ከየት እንደሚያመጡት ያውቃሉ፡፡ እነሱ እ.ኤ.አ. በ1959 ከሱዳን ጋር የተፈራረሙት በሌሎቹ አገሮች ውድቅ የተደረገው የቅኝ ግዛት ውሎች መሠረት አብዛኛውን የውኃ ድርሻ መድበው ጨርሰዋል።

ታላቁ የአስዋን ግድብና የቶሽካ ፕሮጀክት ምን ያህል የዓባይ ውኃ ይበቃቸዋል? ሐምሌ 21 ቀን 2012 ሪፖርተር ጋዜጣ - እስክንድር ከበደ ‹‹ሚስትሪ ኦፍ ናይል ሪቭር›› (የናይል ሚስጥር) የሚለው ዘጋቢ ፊልም በጂኦፊዚስቱ ፓስኳልና ባልደረቦቹ የዓባይን ወንዝ ከመነሻ እስከ መድረሻው ያሰሱበትን የ3,000 ማይሎች ጉዞ ያስቃኘናል። በዚህ ዘጋቢ ፊልም ኢትዮጵያዊት ሕፃን የአንገት ጌጥ አውልቃ ለቡድኑ ሴት አሳሽ አንገት ላይ ታደርግላታለች። ይህ የኢትዮጵያዊት ሕፃን ንፁህ ፍቅር እናያለን። ይህ የአንገት ጌጥ የአሳሽ ቡድኑ ግብፅ ሲደርስ የአንገት ጌጡን ከኢትዮጵያዊ ሕፃን ላይ የወሰደቸው የቡድኑ አባል ካይሮ ስትደርስ፣ በተመሳሳይ ዕድሜ ላይ ላለች ግብፃዊት ሕፃን አንገት ላይ ታጠልቅላታለች። የዓባይ ልጅ ኢትዮጵያዊት ሕፃን ለዚያች የግብፅ ሕፃን ጌጥ ብቻ ሳይሆን ፍቅርን ልካለች። ዓባይ ለዘመናት ለግብፅ ለም ውኃና ለም አፈር ስትገብር ቆይታለች። ኢትዮጵያ በተደጋጋሚ በረሃብ ስትጠቃ ይህ ወንዝ የግብፅን ምድረ በዳ እያረስረሰ በግብርና ምርቶች ካይሮን አጥግቦ፣ የባህረ ሰላጤውን አገሮች በግብርና ምርቶች ብቻ ሳይሆን በኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ብዙ ገቢ እንድታገኝ አድርጓታል። ዘመናዊው የግብፅ አስተዳደር የሚጀምረው እ.ኤ.አ. ከ1805 እስከ 1882 በቱርክ ቫይስሮይ መሐሙድ ዓሊ ዘመን መሆኑ ይነገራል:: በወቅቱ ግብፅ የኦቶማን ቱርክ ኤምፓየር አንድ ጠቅላይ ግዛት ነበረች:: እ.ኤ.አ. በ1882 ብሪታኒያ ግብፅን በመቆጣጠር ለአርባ ዓመታት በቅኝ ግዛት አገርነት አስተዳድራታለች:: አገሪቱ እ.ኤ.አ. በ1922 ነፃ ወጥታ በንጉሣዊ አስተዳደር መተዳደር ብትጀምርም፣ የብሪታኒያ ወታደራዊ ኃይል ቁጥጥር ስር መሆኗ የተሟላ ነፃነት እንዳይኖራት አድርጓል:: ናይል ዴልታና ካይሮ አካባቢዎችን በመቆጣጠር የራሷን አስተዳደር መስርታ ነበር:: እ.ኤ.አ. በ1798 ዓ.ም. ፈረንሣይ ከብሪታኒያ ጋር ጦርነት ላይ ነበረች:: ናፖሊዮን ቦናፓርት መጠነ ሰፊ ጦርነትን በማካሄድ በቀጣናው የብሪታኒያን ንግድ ለማስተጓገል ጥረት አድርጎ ነበር:: የናፖሊዮን ጦር በላይኛው ግብፅ በመምሉኮችና በቱርኮች ከፍተኛ መከላከል ገጥሞት የነበረ ሲሆ፣ ፤በ1799 በአሌክሳንደሪያ አቅራቢያ መልህቁን የጣለውን የፈረንሣይ ባህር ኃይል በብሪታኒያ ባህር ኃይል ውድመት ደረሰበት:: ናፖሊዮን ጦሩን ትቶ ለመሸሽ ተገደደ:: የፈረንሣይ ጦር ከሁለት ዓመት በኋላ ግብፅን ለቆ ሲወጣ የፈረንሣይ አገዛዝ አበቃ:: ፈረንሣይ ግብፅን ለቃ ስትወጣ የሥልጣን ክፍተት ተፈጠረ:: ማሙሉኮችም ሆኑ ኡለማዎች፣ እንዲሁም ነጋዴዎች ሥልጣኑን መያዝ አልቻሉም:: የኦቶማን ኤምፓየር የጦር መኮንን መሐመድ ዓሊ በግብፅ ነጋዴዎች በመደገፍ የአገሪቱ መሪነቱን ተቆጣጠረ:: መሐመድ ዓሊና አልጋ ወራሾቹ የመጀመሪያ ዕርምጃዎቻቸው የግብፅ ኢኮኖሚን ማዘመን ነበር:: አዳዲስ የውኃ ቦዮች፣ ወንዝ መገደቢያ ግንባታዎችና ፋብሪካዎች እንዲሠሩ አዘዙ:: በወቅቱ ግብፅ ከፍተኛ ኢንዱስትሪ በብዛት ለመገንባት አልሞከረችም:: ምክንያቱም ከውጭ አምራቾች ጋር ለመወዳደር ገና ነበረች:: ሆኖም ግብርናዋን ለማዘመን ነበር ቅድሚያ የሰጠችው:: አዳዲስ የመስኖ ዘዴዎች በመጠቀም በፊት አንድ ጊዜ ብቻ የነበረውን የሰብል ምርት በዓመት ሦስቴ እንዲሆን አድርጓል:: እ.ኤ.አ. በ1952 የተወሰኑ ወታደራዊ መኮንኖች በጋማል አብደል ናስር መሪነት ንጉሣዊ አገዛዝን በመፈንቅለ መንግሥት በመጣል ግብፅ ሪፐብሊክ አገር መሆኗን አወጁ:: የግብፅ ሕዝብ ቁጥር እየጨመረ መምጣቱና የሚታረስ መሬት እጥረት በመኖሩ አገሪቱ ሕዝቧን መመገብ አልቻለችም:: አገሪቱ በዓባይ ወንዝ ጎርፍ መጥለቅለቅና ወንዙ ይዞት በሚመጣው ደለል መቸገራቸው መፍትሔ ማፈላለግ ነበረባት:: የኮሎምቢያ ዩኒቨርሲቲ ፕሮፌሰር ሮበርት ኦ ኮሊን የግብፅ ሕዝብ "ናይል ግብፅ ነው፣ ግብፅ ናይል ነው" (Nile is Egypt, Egypt is Nile) የሚለው ያለ ምክያንት አይደለም ይሉናል:: በግብፅ ሥነ ጽሑፍ፣ አፈታሪክ፣ ሥነ ቃልና ሙዚቃ ዓባይ ጭብጥ ሆኖ ቢዘልቅም ለዘመናት ግብፅን አቋርጦ ሜዲትራኒያን ባህር ይገባ ነበር:: በ1952 የግብፅ አብዮት በጋማል አብደል ናስር መሪነት ወደ ሥልጣን የመጣው የነፃ ወታደራዊ መኮንኖች ምክር ቤት መጀመሪያው ኢኮኖሚ ማሻሻያና ግዙፍ ዕርምጃው ታላቁ የአስዋን ግድብ እንዲነባ መወሰኑ ነበር:: በዓባይ ወንዝ የምግብ ሰብሎችን ጨምሮ ‹‹ካሸ ክሮፕ›› በመባል ገቢ የሚያስገኙ እንደ ትንባሆ፣ ጥራጥሬዎችና ረዥሙን ጥጥ (በዓለም ምርጥ የሚባለውን ዓይነት) ማምረት ጀመረች:: የግብርና ምርቶችን በ30 በመቶ የጨመረበት፣ የኤሌትሪክ ኃይሏ በስምንት እጥፍ ያደገበት፣ ከራሷ አልፋ የኤሌትሪክ ኃይል ለጎረቤቶቿ እንድትሸጥ የረዳት፣ ራሷን ከመመገብ አልፋ ወደ ውጭ የተትረፈረፈ የምግብ ምርቶችን ወደ ተለያዩ አገሮች የምትልክበት፣ በዓመት አሥር ቢሊየን ኪሎ ዋት በሰዓት ኃይል የምታመነጭበት፣ ግንባታው አሥር ዓመታት ፈጅቶ የተገነባ ግን በሦስት ዓመታት ብቻ ግድቡን ሞልታ ታላቅ ሐይቅ የፈጠረች አገር፣ በዓለማችን ምርጡን ጥጥ አምርታ ወደ ውጭ በመላክ የከበረችበት፣ ብዙ የሚባልለት ታላቁ የአስዋን ግድብ መገንባቷ ሁሉን ነገር ቀየረ። በግብፅ አፈ ታሪክና ጥንታዊ ታሪክ ወስጥ በጎርፍ መጥለቅለቅና የድርቅ፣ እንዲሁም የሰቆቃ ተረኮች የተለመዱ ነበሩ:: በአርሶ አደሮቹ አነስተኛ ክትሮች፣ የውኃ መከላከያ የጭቃ ግንቦችና የጎርፍ መቀየሻ አጥሮች በመገንባት የመስኖ እርሻዎችን በማልማት ይታወቃሉ:: ለግብፅ ለዘመናት ሲፈስ የቆየው የዓባይ ወንዝ ከኢትዮጵያ ይዞላት የሚሄደው ውኃ ብቻ ሳይሆን ለም አፈርም ነው:: በዓለም ላይ በለምነቱ የላቀ አፈር ለእርሻ ምርቷ መጨመር ከፍተኛ ዕገዛ አደርጎላታል:: ዓባይ ይዞ በሚሄደው ደለል አፈር ግብፅ በዓመት ሦስት ጊዜ የሰብል ምርት እንድታመርት ያደርጋል:: እ.ኤ.አ. ከ1517 ጀምሮ ግብፅ በኦቶማን ቱርክ ስትተዳደር ቆይታለች:: እ.ኤ.አ. በ1805 የግብፅ መሥራች አባት ናቸው ሚባሉት ታላቁ መሐመድ ዓሊ የቱርክ አገረ ገዥ ሥልጣን መያዛቸውን ተከትሎ፣ በግብፅ ኢኮኖሚያዊ ማሻሻዎች ይዘው ብቅ አሉ:: ፈረንሣውያን አማካሪዎቻቸው የጥጥ እርሻ እንዲያስፋፉና ምርቱን ወደ አውሮፓ እንዲሸጡ አማከሯቸው:: አዲሱ የግብርና ምርት በቂ ውኃ ያስፈልገው ነበር:: ይህንን ለማድረግ በተለምዶ ግልገል አስዋን ግድብ (Aswan Low Dam or Old Aswan Dam) በደቡባዊ ምሥራቅ ካይሮ ጫፍ በዓባይ ወንዝ ላይ እ.ኤ.አ. በ1899 እና በ1902 እንዲገነባ አድርገዋል:: የግብፅ ጥጥ ምርት ተጠቃሚዋ ብሪታኒያ የመጀመሪያውን ግልገል ግድብ እ.ኤ.አ. በ1898 መገንባት ጀምራ እ.ኤ..አ. ኅዳር 10 ቀን 1902 ነበር ያጠናቀቀችው:: በወቅቱ በዓለም ትልቁ ግድብ እስከ መባል ደርሷል::ዕይህ ግልገል አስዋን ግድብ በሁለት ምእራፍ እንዲሻሻል ተደርጓል:: ግብፅ በ19ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪዎቹ በመሐመድ ዓሊ የአገዛዝ ዘመን ጥጥ ከሚያመርቱ አምስት የዓለማችን አገሮች አንዷ ለመሆን በቅታለች::

✍️ ምሽቱን በጉባ እንቅልፍ የለም ፤ ሌላ ታሪክ አለ ~~~~~~~~~~~~~~~~~~~ ምሽቱን በጉባ የህዳሴ ሰራተኞች በግድቡ ዙሪያ ተሰባስበው ሌላኛውን ልዩ ክስተት እየተጠባበቁ ነው። የሁለተኛ ተባይ
✍️ ምሽቱን በጉባ እንቅልፍ የለም ፤ ሌላ ታሪክ አለ ~~~~~~~~~~~~~~~~~~~ ምሽቱን በጉባ የህዳሴ ሰራተኞች በግድቡ ዙሪያ ተሰባስበው ሌላኛውን ልዩ ክስተት እየተጠባበቁ ነው። የሁለተኛ ተባይን ሃይል ማመንጨት መጀመሩን እያከበሩ ምሽቱን ደግሞ አባይ ከባህር ጠለል በላይ 600ሜትር ከፍታ ላይ የደረሰውን ግድብ አልፎ የሚፈስበትን ታሪካዊ ምዕራፍ ለማየት በቦታው ላይ ናቸው። የቀን ሃሩር የሌሊት ቁር ሳይበግራችሁ ፤ ደማቁን ታሪክ በእውቀት እና በትጋት እየፃፉችሁ የምትገኙ ባለሙያዎቻችን እንዃን ደስ አላችሁ ። ግድባችን ከፍ ማለቱን ፤ አባይም ሞልቶ መፍሰሱን ይቀጥላል !! ሰላም ሙሉጌታ

ቀን 05/12/2014 ሆሩ ጉድሩ ወለጋ ለ42 ቀናት በተደረገው ዘመቻ በአሸባሪው ሸኔ ላይ ድል መቀዳጄቱን የሆሩ ጉዱሩ ወለጋ ዞን አስተዳደር አስታወቀ የዞኑ ዋና አስተዳደሪ አቶ ምሬሳ ፊጤ እንደገለፁት በ42 ቀናት ሁሉን አቀፍ በተደረገው ዘመቻ በአሸባሪው ሸኔ ላይ ከፍተኛ ኪሰራ መድረሱን ገልፀዋል። እንደ አስተዳዳሪው ገለፃ በአጭር ቀናት ውስጥ በተደረገው ዘመቻ 42 የተገደለ ፤ 40 የተማረኩ ፤ 14 በተደረገው ጥሪ በሰላማዊ መንገድ እጅ የሰጡ ፤ 149 የጠላት ሴሌች ፣ 132 መረጃ ሰጪዎችና 60 ወደ ቡዱኑ ለመቀላቀል ከተለያዩ ከኦሮሚያ ዞኖች መጥተው በሆቴሎች ውስጥ የተደበቁ በተደረገው ፍተሻ ተገኝተው በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ እየተደረገባቸው እንደሚገኙ ተነግረዋል። በዞናችን ውስጥ ሁለት አይነት ፅንፈኛ ቡድኖች አሉ ያሉት አቶ ምሬሳ ፊጣ እነርሱም ኦሮሚኛ ተነጋሪ ፅንፈኛ ቡድንና አማርኛ ተነጋሪ የሆኑ ፅንፈኞ ሲሆኑ በዞኑ ሁለቱም በጣምራ ህብረተሰቡን በማጋትና በመዝረፍ ከፍተኛ በደል እያደረሱ በመሆናቸው በሁለቱም ላይ የተቀናጀ እርምጃ እየተወሰደ እንደሚገኝ አብራርተዋል። የሆሩ ጉድሩ ወለጋ ዞን የተቀናጀ የፀጥታ አስተባባሪ በአከባቢው የተሰማራው ኮማንዶ ክፍለጦር አዛዥ ኮሌኔል አደራጀው ሰረባ በበኩላቸው የአከባቢውን ህብረተሰብ በማስተባበር በ42 ቀናት በተደረገው ዘመቻ አመርቂ ድሎች መገኘታቸውን ተነግረዋል። እንደ አዛዡ ገለፃ በዞኑ ውስጥ በሁሉም ወረዳዎች በተደረገው ዘመቻ በርካታ ታጣቂዎች የተደመሰሱ ሲሆን በመሳሪያ በኩልም 13 ክላሽ ፣ 07 ኋለቀር መሰሪያ ፣ 09 ሽጉጥ ፤ 2852 የክላሽ ጥይት ፤ 822 የሽጉጥ ጥይትና 39 የጥይት ካዚና ተማርከዋል ብለዋል። አሁንም በዞኑ ውስጥ በሁሉም ወረዳዎች የተጠናከረ አሰሳና ፍታሻዎችን በማድረግ የሸኔ ታጣቂዎችን ከህብረተሰቡ ነጥለው ለመደምሰስ ህዝቡን በማሳተፍ ሁሉን አቀፍ የተቀናጀ ዘመቻ እየተደረገ እንደሚገኝ አስረድተዋል። በዞኑ ውስጥ የተቀናጀ የግብረሃይል የፌዴራል ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ነፃነት ታደሳ በበኩላቸው ከመከላከያ ሰራዊቱ ኮማንድ ስር ሆነን በመስራታችን በጠላት ላይ ከተገኘው ድል በተጫማሪ ለፌዴራል ፖሊስ ሰራዊቱ በርካታ አቅም የፈጠረ ዘመቻ ነበር ብለዋል። ሪፖርተር፦ ታሪኩ ሻሜቦ ፎቶግራፍ፦ ታሪኩ ሻሜቦ

#BREAKING የታላቁ ኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሁለተኛው ተርባይን የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ጀመረ። ጠ/ሚር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድን ጨምሮ የተለያዩ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች በቤንሻንጉል ጉሙዝ ጉባ
#BREAKING የታላቁ ኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሁለተኛው ተርባይን የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ጀመረ። ጠ/ሚር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድን ጨምሮ የተለያዩ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች በቤንሻንጉል ጉሙዝ ጉባ ወረዳ በታደሙበት ዝግጅት ነው በዛሬው ዕለት 2ኛው ተርባይን ኃይል ማመንጨት የጀመረው። የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ካሉት 13 ተርባይኖች መካከል ዩኒት 9 የሚባለው ሁለተኛው ተርባይን የተሳካ ተከላ እና ሙከራ ከተደረገ በኋላ ኃይል የማመንጨት ስራው እውን መሆኑን ብሄራዊ የቴሌቪዥን ጣቢያ ዘግቧል። ዛሬ በይፋ ሥራ የጀመረው ሁለተኛው ዩኒት 375 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳለው ተገልጿል።

                           ቀን 04/12/2014 ዓ/ም                             ከሆሩ ጉድሩ ወለጋ ዞን በሆሩ ጉዱሩ ወለጋ ዞን ውስጥ አንዲት ቀበሌ በአሸባሪው ሸኔ ላይ ዘመቻ በመክፈት ጀብዱ ፈፀሙ። ነገሩ እንዲህ ነው። በኦሮሚያ ክልል በሆሩ ጉድሩ ወለጋ ዞን ጮማን ጉዱሩ ወረዳ ውስጥ ካሉት ቀበሌዎች መካከል በአንዲት ቀበሌ ውስጥ ታላቅ ጀብዱ ተፈፅሟል። ቀበሌዋ ጉደኔ ጫላ ሲበሬ ትባላለች። እንደወትሮው ሁሉ ህዝቡ ውስጥ ለመደበቅ የአሸባሪው ሸኔ ታጣቂዎች ወደዚህች ቀበሌ ዘልቀው ይገባሉ። ነገር ግን የጉደኔ ጫላ ሲበሬ ቀበሌ አሁን በቃችሁን በማለት 07 ወጣቶች ከታጠቁት ሸኔ ታጣቂዎች ጋር በጦርና በገጀራ ጦርነት ገጠሙ። ከ7ቱ ሶስቱ የዩኒቨሪሲቲ ተማሪዎች ሲሆኑ አራቱ ደግሞ አርሶ ከደር ናቸው። ጩሃቱን የሰማው የቀበሌው ህዝብ በሙሉ በነቂስ ወጥቶ ከታጠቁት ሸኔዎች ጋር በባህላዊ ጦርና ገጀራ ገጠሙ። ይህንኑ ያላሰቡትን የህዝብ ማዕበልና ቁጣ አይተው የተደናበሩት አሸባሪዎች እግር አውጪኝ እያሉ እግር ወደመራቸው አቅጣጫ ሁሉ መሸሽን መረጡ። ነገር ግን የህዝብ ማዕበሉ አንዱን በጦር በመግደል ሶስቱን ደግሞ ከእነትጥቃቸው ማርኮ ለወረዳው አስተዳደርና በአከባቢው ለተሰማራው ለመከላከያ ሰራዊታችን ማንቁርታቸውን አንቀው በጀግንነት አምጥተው አስረክበዋል። ይህንን ጀብዱ የሰሙ አጎራባች የወረዳው ቀበሌዎች በሙሉ በጋራ ሰላማዊ ሰልፍ ወጥተው ለጀግናዋ ቀበሌ ህዝብ የጀግኖች አቀባበል በማድረግ የወረዳ ፤ የዞን አመራሮችንና በአከባቢው የተሰማራውን የመከላከያ ሰራዊት አመራሮችን በመጋበዝ ከታጠቁት ታጣቂዎች ጋር ገጥመው ሞትና ሞርኮ በማድረግ ጀብዱ ለፈፀሙት አባላትና ለቀበሌዋ ህዝብ የዕውቅና ፕሮግራም አዘጋጅተዋል። በፕሮግራሙ ላይ ሶስት ሰንጋዎች ታርደዋል። እህልና መጠጥን ሁሉም ከየጎዳው ይዘው ወጥተዋል። በዝግጅት ፕሮግራም ላይ በመገኘት ለጀግኖቹ የዕውቅና ሽልማት በመስጠት ንግግር ያደረጉት የሆሩ ጉድሩ ወለጋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ መሬሳ ፊጣ የሸኔ በጉያ የማቀፍ ዘመቻ ማብቃቱን አብስረዋል። ከእንግዲህ ሆሩ ጉድሩ ዞን የሰላምና የልማት ዘመቻ እንጂ በቀመኞቹና ዘራፊዎች በሸኔ ታጣቂዎች የመበደል ጊዜ አብቅተዋል። ማብቃቱን ደግሞ የጉደኔ ጫላ ሲበሬ ቀበሌ ህዝቦች በህዝባዊ ማዕበል ጀብዱ በመፈፀም በተግባር አሳይተችሁናልና የጀግንነታችሁ ችቦ ደግሞ በመላው ዞናችን ይቀጣጠላል ብለዋል። ጀብዱ ለፈፀሙት ለዩኒቨርስቲው 03 ተማሪዎች ለእያንዳንዳቸው ሶስት ሶስት ሺህ የተበረከተላቸው ሲሆን ለቀሩት ለአራት አርሶ አደሮች ደግሞ ለእያንዳንዳቸው ጠመንጃና ሰርትፍኬት ተሸልመዋል። በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት በአከባቢው የተሰማራው ክፍለጦር ምክትል አዛዥ ደግሞ ከህዝባችን ጋር የጀመርነውን የአሸባሪው ሸኔን የማፅዳት ዘመቻ አጠናክረን በመቀጠል ዞኑንና መላውን ኦሮሚያን የሰላምና የልማት ቀጠና እናደርጋለን አትጠራጠሩ ብለዋል። በሆሩ ጉዱሩ ወለጋ ዞን በአሁኑ ወቅት የክልሉ ልዩ ሃይል ፤ ህዝባዊ ፖሊስና ሚልሻ ፤ የፌደራል ፖሊስ አባለት በሙሉ በመከላከያ ኮማድ ፖስት ስር ሆኖ ዞኑን ከአሻባሪው ሸኔ በማፅዳት ላይ ይገኛል። ሪፖርተር፦ ታሪኩ ሻሜቦ ፎቶግራፍ፦ በዞኑ መንግስት ኮሙኒኬሽን

ተጨማሪ 19,000 የቼችንያ ጦር ወደ ዩክሬን...🇷🇺👌 ከዚህ ቀደም 4 ስትራቴጂክ ከተሞችን ጨምሮ 36 የጦር ሰፈሮችን ነፃ በማድረግ መላው ሉሃንስክን ከዩክሬን አዞቭስታል ጦር ነፃ በማውጣታቸ ላ
+3
ተጨማሪ 19,000 የቼችንያ ጦር ወደ ዩክሬን...🇷🇺👌 ከዚህ ቀደም 4 ስትራቴጂክ ከተሞችን ጨምሮ 36 የጦር ሰፈሮችን ነፃ በማድረግ መላው ሉሃንስክን ከዩክሬን አዞቭስታል ጦር ነፃ በማውጣታቸ ላደረጉት አስተዋፆ ከቀናት በፊት ከ ሎሀንስክ ህዝቦች ሪፐብሊክ(LPR) ኃላፊ እጅ "የ LPR ጀግና ሜዳልያ" የሪፐብሊኩን ከፍተኛ ሽልማት የተቀበለው ራምዛን ካዲሮቭ አሁን ደግሞ ጦሩ ፊቱን ወደ ዶኔትስክ በማዞር ጦሩ ባለፉት ቀናት ኖቮፔትሮቭካ እና ያኮቭሌቭካ ነፃ ማድረጋቸው ታውቋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ የቼችንያ ሪፐብሊክ ፕሬዝደነት ራምዛን ካዲሮቭ በአሁኑ ወቅት 9,000 በደንብ የሰለጠኑ ደፋር ተዋጊዎችን ከቼቼን ሪፑብሊክ ወደ ዩክሬን ለመላክ መዘጋጀቱንና ተጨማሪ ሌላ 10,000 ወታደሮች በተጠንቀቅ እየጠበቁ እንደሚገኙ አሳውቀዋል።