uk
Feedback
ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ

ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ

Відкрити в Telegram

ይህ በግራር ደ/አባይ ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ ፍኖተ ብርሀን ሰንበት ት/ቤት የተዘጋጀ :- ለምዕመናን : ትምህርትን , ዝማሬዎችን , ኪናዊ ዝግጅቶችን, የቤተ ክርስቲያንን ወቅታዊ ዜናዎችንና በአላትን(ንግስ, ልዮ ልዮ የሰርክ ጉባኤያት ..ወዘተ) በምን መልኩ እንደተከበሩ ለምዕመናን ተዘጋጅቶ የሚተላለፍበት ገፅ ነው።

Показати більше
637
Підписники
Немає даних24 години
-37 днів
-1230 день
Архів дописів
❤ "በስመ አብ  ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤             ❤ #ጥር ፬ (4) ቀን። ❤ እንኳን #ለኢትዮጵያዊው_ጻድቅ ሁል ጊዜ ዐርብ ዐርብ ያከፍሉ ለነበሩት የጌታችንን መከራ እያሰቡ አናታቸውን አቁስለው ሲተላ ትሉን ለወፎች ይመግቡ ለነበሩትና ዋሽራን ለ30 ዓመታት በሹመት ላገለገሉት ለታላቁ አባት #ለአቡነ_መልከጼዴቅ_ዘዋሸራ ለዕረፍታቸው በዓልና ለጸሎት በመቆም ብዛት እግራቸው እስከ ማበጥ ለደረሰ በበትር ሳይመቱ በጥላቸው ብቻ ከይሲውን ለገደሉ ለታላቁ አባት #ለአቡነ_ናርዶስ_ዘደብረ_ቢዘን_ለዕረፍታቸው መታሰቢያ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #አቡነ_መልከጼዴቅ_ዘዋሸራ፦ ከአባታቸው ከዘካርያስና ከእናታቸው ስነ ክርስቶስ የተወለዱት አቡነ መልከጼዴቅ ዘዋሸራ ትውልድ አገራቸው ጎጃም ዋሸራ ሲሆን በታላቅ ተጋድሎና በሹመት ያገለገሉትም በዚሁ፡ነው፡፡ ዲቁናንና ቅስናን ከግብፅ ተቀብለው በዋሽራ 30ዓመት በሹመት አገልግለዋል፡፡ ጻድቁ የሚታወቁበት ትልቁ ተጋድሎአቸው በሕይወት ዘመናቸው ሁሉ ሁል ጊዜ ዓርብ ዓርብ ያከፍሉ ነበር። የመድኃኔዓለምን 13ቱን ሕመማተ መስቀሎች በማሰብ አናታቸውን በድንጋይ እያቆሰሉ ቁስሉ ሲተላ ትሉን ለወፎች ይመግቡ ነበር፡፡ በ40ቀን ውስጥ አንዷን ቀን ብቻ ነው ውኃ ይጠጡ የነበረው፡፡ ጻድቁን የቅኔ ተማሪዎች በዋሸራ ይዘክሯቸዋል፡፡ ምንጭ መዝገበ ቅዱሳንና ቅዱሳን በዓላት።                   

❤ "በስመ አብ  ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤             ❤ #ጥር ፬ (4) ቀን። ❤ እንኳን #ለከበረና_ለተመሰገነ ለታላቁ #ለወንጌላዊው_ለአቡቀለምሲስ_ለቦኤኔርጌስ፣ #ለታኦሎጎስ_ለድንግላዊው_ለቊጹረ_ገጽ፣ #ለፍቊረ_እግዚእ_ለሐዋርያው_ለቅዱስ_ዮሐንስ_ወልደ_ነጐድጓድ_ለፍልሰቱ (ከሞት ለተሰወረበት) ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦# ከከበረ_ከጊዮርጊስ ከሊቀ ጳጳሳት #ከማርቴና_ከሰማዕት_ታኦድራ_ከአባ_ሊቃኖስና #ቀውስጦስ_ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                                                                                          ✝ ✝ ✝ ❤ #ወንጌላዊው_ቅዱስ_ዮሐንስ፦ ለዚህም ቅዱስ ወደ እስያ አገር ይሔድ ዘንድ ዕጣው በወጣ ጊዜ እጅግ አዝኖ አለቀስ እነርሱ ክፉዎች ከሀዲዎች ልባቸው የደነደነ መሆናቸውን አውቋልና ግን ጌታችን ኃይልን መጽናናትን አግኝቶ ከደቀ መዝሙሩ አብሮኮሮስ ጋር ወጥቶ ወደ ክፍሉ ሔደ። ወደ ኤፌሶንም ሊሔድ ወዶ በመርከብ ላይ ተሳፈረ መርከቡም ተሰበረ እየአንዳንዱ በመርከብ ስባሪ ሠሌዳ ላይ ተንጠለጠለ ደቀ መዝሙሩን አብሮኮሮስንም የባሕሩ ማዕበል ወደአንዲት ደሴት አደረው ቅዱስ ዮሐንስ ግን በባሕሩ ማዕበል መካከል አርባ መዓልት አርባ ሌሊት ኖረ። ❤ ከዚህም በኋላ ደቀ መዝሙሩ አብሮኮሮስ ወዳለበት ወደ የብስ ባሕሩ ተፋው ስለ መገናኘታቸውም እግዚአብሔርን አመሰገኑት በዚያን ጊዜም ተነሥተው ወደ ኤፌሶን ከተማ ገቡ ግን በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ይሰብኩ ዘንድ አልተቻላቸውም እነዚያ  ያገር ሰዎች እጅግ የከፉ ናቸውና። ስለዚህም ምክንያት ፈጥረው ዮሐንስ ሮምና ለምትባል ሴት የውሽባ ቤት እሳትን የሚያነድ ሆነ ረድኡ አብርኮሮስም አጣቢ ሆነ ያች ሴትም እጅግ ታሠቃያቸው ነበር መጻተኞችም ስለሆኑ ታጐሳቁላቸዋለች ትደበድባቸዋለች ትረግማቸዋለች ባሮቿም እንደሆኑ ጽፈውላታልና ከእርሷ ባሮች አደረገቻቸው በዚህ በታላቅ ጒስቊልና ውስጥ ኖሩ። ❤ ከዚህም በኋላ በአንዲት ዕለት ይታጠብ ዘንድ የአገረ ገዥው ልጅ ገባ በዚያም የውሽባ ቤት ከተሠራ ጀምሮ የሰይጣን ኃይል አለ የመኰንኑም ልጅ አንቆ ገደለው በዚያንም ጊዜ የአገር ሰዎች ለዚያ ለሞተው ሊያለቅሱለት ተሰበሰቡ የከበረ ዮሐንስም እርሳቸው ጋር መጥቶ እንደ ሰው ሁሉ ሊያይ በዚያ ቆመ። ሮምናም በአየችው ጊዜ ረገመችው "አንተ በጌታዬ ልጅ ሞት ደስ ብሎህ ልትዝትብኝ መጣህ" አለችው ቅዱሱ ግን በቅንነት "አይዞሽ አትዘኝ" አላት ይህንንም ብሎ ወደ ሞተው ቀረብ ብሎ በመስቀል ምልክት አማተበበት በፊቱም ላይ እፍ አለበት። በዚያንም ጊዜ ያ የሞተው ድኖ ተነሣ የአገር ሰዎችም ደነገጡ ሮምናም "ወዮልኝ እግዚአብሔር የሚሉት አምላክ አንተ ነህን? አለች። እርሱም "አይደለሁም እኔ አገልጋይ ሐዋርያው ነኝ እንጂ" አላት በእነርሱ ላይ የሠራችውን በደል ሁሉ ይቅር ይሏት ዘንድ መሪር ልቅሶ በማልቀስ ሐዋርያትን ለመነቻቸው እነርሱም አረጋጓት አጽናኗትም። ❤ ከአገሩም ሰዎች ብዙዎቹ በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ። የክርስትና ጥምቀትንም አጠመቃቸው በፊታቸውም ብዙዎች የሆኑ ድንቆች ተአምራትን አደረገ ይህንንም አይተው የአገሩ ሰዎች ሁሉም በጌታችን አመኑ። ከጣዖታቱ አገልጋዮች በቀር እነርሱም ሰይጣን በእርሱ ላይ ስለሚያነሣቸው ሊገድሉት ይሹ ነበር ነገር ግን ምርጦቹን እግዚአብሔር ጠበቃቸው። የከበረ ዮሐንስም ሁሉንም እግዚአብሔርን ወደ ማወቅ እስከመለሳቸው ድረስ ታላቅ ድካምና ጭንቅ የሆነ መከራ ደረሰበት። የከበረ ሐዋርያ ቅዱስ ጳውሎስም ስለ ልቡናቸው ደንዳናነት ጣዖታትን ስለመውደዳቸውም ስለ እነርሱ መስክሮአል። እርሱም ቅዱስ ዮሐንስ በታላቅ ድካም ወደ ቀናች ሃይማኖት መለሳቸው። ከዚህም በኋላ ኤጲስቆጶሳትን፣ ቀሳውስትን፣ ዲያቆናትን ሾመላቸው። ከዚህም በኋኋ ከእስያ በዙርያዋ ወዳሉ አገሮች ሁሉ ወጥቶ አስተማረ እግዚአብሔርንም ወደማወቅ መለሰላቸው። ❤ ይህም የከበረ የተመሰገነ ቅዱስ ዮሐንስ በዚህ ዓለም ዘጠና ዓመት ኖረ እጅግም ሸመገለ ግን እንደ ባልጀሮቹ ሐዋርያት በሰይፍ ሞትን አልቀመሰም። ስለ ድንግልናውና ስለ ንጽሕናው ይህ ሆነ ሁሉም በክብር ይስተካከሉ ዘንድ እርሱም ወንጌልን ቀለምሲስ የሚባለውን ራእይ ሦስት መልክታትን የጻፈ ነው። ራት ሲበሉ በጌታ ኢየሱስ አጠገብ የተቀመጠውና "የሚያሲዝህ አቤቱ ማነው?" ያለው ይህ እርሱ ነው። ጌታችንም በተሰቀለ ጊዜ ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጋር በመስቀሉ አጠገብ የቆመ እናቱንም "እነሆ ልጅሽ ያላት" እርሱን ደቀ መዝሙሩንም "እነኋት እናትህ" ያለው ነው። ❤ ቅዱስ ጴጥሮስም እርሱን ሲከተለው በአየው ጊዜ ስርሱ ጌታ ኢየሱስን "አቤቱ ይህስ እንዴት ነው?" ብሎ የተናገረ ጌታ ኢየሱስም "እስክመጣ ድረስ ይኖር ዘንድ ከወደድኩ አንተ ምን አለህ አንተ ግን ተከተለኝ ያለለት" ይህ ነው። ❤ የተመሰገነ ቅዱስ ዮሐንስም ከዚህ ዓለም የሚወጣበት ሰዓት እንደ ቀረበ በአወቀ ጊዜ ሕዝቡን ጠራቸው ጸሎትንም ጸለየና ኅብስቱን ባርኮ ቆረሰ ይህም የጌታችን ሥጋውንና ደሙን ሰጣቸው በቀናች ሃይማኖትም እንዲጸኑ አዘዛቸው ባረካቸው አጽናናቸውም። ❤ ከዚህም በኋላ ደቀ መዝሙሩ አብሮኮሮስን ከወንድሞችም ሌሎች ሁለቱን መቆፈሪያ ይዘው ይከተሉት ዘንድ አዘዘ። ከኤፊሶንም ከተማ ወጭ ወጣ ጒድጓድ እንዲቆፍሩም አዘዘ ከውስጥዋም ወርዶ ቆመ ልብሱንም አስወገደ ከአንድ የበፍታ ቀሚስ በቀር አላስቀረም። እጆቹንም አንሥቶ ጸለየና ወደ ከተማ ይመለሱ ዘንድ አሰናበታቸው በክርስቶስም ሃይማኖት ይጸኑ ዘንድ ለሕዝቡ ይነግሩአቸው ዘንድ አዘዛቸው በጎ ሥራዎችንም ይሠሩ ዘንድ ጌታችን ለሁሉም እንደ ሥራው ይከፍለው ዘንድ አለውና። ❤ ሁለተኛም እንዲህ አላቸው "እኔ ከሁላችሁም ደም ንጹሕ ነኝ ከእግዚአብሔር ትእዛዝና ሕግ ሳልነግራችሁ የተውኩት ምንም ምን የለምና እናንተም ከእንዲህ ከቶ ፊቶን አታዩኝም"። ይህንንም በተናገረ ጊዜ አለቀሱ እጆቹንና እግሮቹን ስመው በጒድጓዱ ውስጥ ትተውት ወደ መንደር ተመለሱና የሆነውን ሁሉ ለሰዎች ነገሩዋቸው ሁሉም ደንግጠው መጡ ግን ልብስና ጨማ እንጂ መቃብሩን አላገኙም እጅግም አደነቁ ደቀ መዝሙሩ ዮሐንስን በዚህ በጎ ዕረፍት ያሳረፈው እግዚአብሔርንም አመሰገኑት። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ በከበረ አባት በሐዋርያ ቅዱስ ዮሐንስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥር 4 ስንክሳር።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "አልቦ ነገር ወአልቦ ነቢብ ዘኢተሰምዐ ቃሎሙ። ውስተ ኵሉ ምድር ወፅአ ነገሮሙ"። ወእስከ አፅናፈ ዓለም በጽሐ ነቢቦሙ"። መዝ18፥3-4። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 4፥17-ፍ.ም።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ወበኀቤየሰ ፈድፋደ ክቡራን አዕርክቲከ እግዚኦ። ወፈድፋደ ፀንዑ እምቀደምቶሙ። እኌልቆሙ እምኆፃ ይበዝኁ"። መዝ 138፥17-18። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ጢሞ 6፥1-11፣ 1ኛ ዮሐ 1፥1-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 4፥8-24። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 21፥20-25። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ ነው። መልካም የሐዋርያው የቅዱስ ዮሐንስ የስዋሬ  በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።                  

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ እንኳን #ለጌታችን_ለመድኃኒታችን_ለኢየሱስ_ክርስቶስ_ለልደቱ_መታሰቢያ_የመጀመሪ_ሳምንት_ዕለተ_ሰንበት እግዚአብሔር አምላክ በሰላም ጤና አደረሰን።                          ✝ ✝ ✝ ❤ #የዚህ_ሳምንት_መዝሙር፦ ሃሌ ሉያ "#ይሠርቅ_ኮከብ_እምያዕቆብ ወየዐትት ኀጢአተ እም፳ኤል #ወአነሂ_በኵርየ_እሬስዮ ልዑል ውእቱ እምነገሥተ ምድር ወይከውን ምስማከ ለኵሉ ምድር ውስተ አርዕስተ አድባር #ዮምሰ_በሰማያት_ይትፌሥሑ_ሠራዊተ_መላእክት"። ትርጉም፦ #ከያዕቆብ_ኮከብ_ይወጣል፤ ከእስራኤል ኀጢአትን ያስወግዳል፤ #እኔም_በኩሬ_አደርገዋለሁ ከምድር ነገሥታት በላይ ታላቅ ነው፤ ለምድር ሁሉ በተራሮች ራሶች ላይ ምስባክ ይሆናል #ዛሬም_በሰማያት_የመላእክት_ሠራዊት_ደስ_ይላቸዋል። #ሊቁ_ቅዱስ_ያሬድ_በድጓው_ላይ።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ወአነሂ በኲርየ እሬስዮ። ወልዑል ውእቱ እምነገሥተ ምድር። ወለዓለም አዐቀብ ሎቱ ሣህልየ"። መዝ 88፥27-28። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 11፥25-ፍ.ም፣ 1ኛ ዮሐ 4፥1-9 እና የሐዋ ሥራ 7፥17-23።  የሚነበበው ወንጌል ማቴ 2፥1-13። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ቅዳሴ ነው። መልካም የቅዱስ ዮሐንስ የስዋሬ በዓል፣ የብርሃነ ልደት በዓል ሰሞን፣ በዓል  ዕለተ ሰንበት። ለሁላችንም ይሁንልን።               

❤ "በስመ አብ  ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤               ❤ #ጥር ፫ (3) ቀን። ❤ እንኳን #ደብረ_ሊባኖስ_ገዳም_በስማቸው ለተሰየመላቸው ከዐለት ጠበል እያፈለቁ ድውያንን ለሚፈውሱት ለተአምረኛው ለታላቁ አባት #ለአቡነ_ሊባኖስ (መጣዕ) ለዕረፍት በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                        ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #አባ_ሊባኖስ፡- አባታቸው አብርሃም እናታቸው ንግሥት ይባላሉ፡፡ እነርሱም በወርቅና በብር እጅግ የበለጸጉ ሮማዊ ናቸው፡፡ ልጃቸውን አባ ሊባኖስን በሃይማኖት በምግባር ኮትኩተው ካሳደጓቸው በኋላ ዕድሜያቸው ሲደርስ በቤተ ክርስቲያን ሥርዓት ያጋቧቸው ዘንድ ከቁስጥንጥንያ አገር ሚስት ባመጡለት ጊዜ እርሱ ግን ፈጽሞ እምቢ አለ፡፡ ወደጫጉላቤትም መግባትን እምቢ አለ፡፡ በዚህም ጊዜ ነቢዩ ሳሙኤልን እንደጠራው አባታችንንም እግዚአብሔር ሦስት ጊዜ በስማቸው ጠራቸውና ‹‹ከአባትህ ተለይ አንተ የመንግሥተ ሰማያት ሙሽራ ነህ እንጂ የዚህ ምድራዊ ዓለም ሙሽራ አይደለህም›› አላቸው፡፡ አባታችንም "ወዴት እሄዳለሁ? ምንስ ላድርግ?" ባሉ ጊዜ ወዲያው የታዘዘ መልአክ በሌሊት መጥቶ ከአባታቸው ቤት አውጥቶ ታላቁ አባት አባ ጳኩሚስ ዘንድ አደረሳቸው፡፡ ታላቁ አባት አባ ጳኩሚስም ለአባ ሊባኖስ በዓት በመስጠት ገዳመ ሥርዓትን፣ አስኬማ መላእክትን፣ ቅናተ ዮሐንስን አስተምረዋቸው አመነኮሷቸውና ከ8ቱ ቅዱሳን ጋር እንዲገናኙ አደረጓቸው፡፡ ❤ ከዚህም በኋላ ያ ከአባታቸው ቤት ወስዶ አባ ጳኩሚስ ገዳም ያደረሳቸው ያ መልአክ ድጋሚ ተገለጠላቸውና "ወደ ቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ ሂድና ተጋድሎህን በዚያ ፈጽም ዝናህ በስፋት ይነገራል፣ ለብዙዎችም አባት ትሆናቸዋለህ" አላቸው፡፡ ቀጥሎም ራሱ መልአኩ ወደ ኢትዮጵያ አመጣቸውና በአክሱም ተቀመጡ፡፡ በዚያም ብዙ ከተጋደሉ በኋላ ወደ ሸዋ መጡና ወንጌልን ዞረው አስተምረው ብዙ ድውያንን ፈውሰው ከዓመታት ቆይታ በኋላ ተመልሰው አክሱም ሄዱ፡፡ ❤ በአክሱምም 7 የተለያዩ ጸበሎችን ከድንጋይ ላይ በተአምራት አፍልቀው ድውያንን ፈውሰው ዕውራንን አበሩ፡፡ በዓታቸውንም ከአክሱም ጽዮን ፊት ለፊት አድርገው ሲኖሩ ከዕለታት በአንደኛው ቀን አባታችን በተአምራት ከጭንጫ ካፈለቁት ጸበል "ተራ ውሃ ነው" ብላ አንዲት ሴት ልጇን አዝላ ልትቀዳ መጣች፡፡ ወዲውም ከቦታው ስትደርስ አድጧት ወደቀችና ልጇም አምልጧት ልቡን ድንጋይ መቶት ሞተ፡፡ ሴትዮዋም ስትጮህ አባ ሊባኖስ ፈጥነው ወጡና በልጁ ላይ ጸልየው በመስቀል ምልክት አማትበው ከሞት አስነሥተውታል፡፡ ሕፃኑ ልጅ ከሞት እንደተነሣ "አምላከ አባ ሊባኖስ" ብሎ አመሰገነ፡፡ ይህንንም ደግ ሥራቸውንና ተአምራታቸውን ያዩ አንዳንድ እኩይ ካህናት በቅናት ተመልተው "ምትሃት ነው የሚያሳየው" ብለው በጻድቁ ላይ ሕዝቡን አሳደሙባቸው፡፡ ❤ አባታችንም ካህናቱን ለመምከር ቢሞክሩም አላስቀምጥ አሏቸው፡፡ ይልቁንም ጦር ጦራቸውን ይዘው አሳደዷቸው፡፡ አባታችንም በዚህ እጅግ አዝነው ከአክሱም ተነሥተው ደርቃ ወደምትባል ቦታ ሄዱ፡፡ በዚያም በጾም በጸሎት እየተጋደሉ ሲኖሩ በእነዚያ በጠሏቸውና በክፋት በተነሡባቸው ካህናት አገር ግን ለ3 ዓመት ምንም ዝናብ ሳይዘንብ ቀረ፡፡ አባታችን በተሰደዱባት በደርቃ አገር ግን ብዙ ዝናብ ይዘንብ ነበር፡፡ አባታችን በዚያችም አገር እንደልማዳቸው ከዐለት ላይ ውኃ አፍልቀው በውኃው ብዙ ድውያንን ፈውሰውበታል፡፡ በዚያም ትልቅ በዓት መሥርተው በተጋድሎ ሲኖሩ በክፉ የተነሡባቸው እኩይ የሆኑ ካህናት መጥተው "አባታችን በከንቱ አምተንሃል በድለንሃልና ይቅር በለን፣ በድርቅ ማለቃችን ነውና ዝናብም እንዲዘንብልን ጸልይን" ብለው ከእግራቸው ሥር ወደቁ፡፡አባታችንም ይቅር ብለው ከፈጣሪ አማለዷቸው፡፡ ዝናቡም ወዲያው ዘነበላቸውና በአገሪቱ ጥጋብ ሆነ፡፡ ❤ ከዚህም በኋላ አባታችን አስቀድመው ወዳዩአት ወደ ሸዋ ምድር ግራርያ መጡና በዓታቸውን በአሰቦት ጫካ አደረጉ፡፡ ነገር ግን መልአኩ ተገልጦላቸው "ሊባኖስ ሆይ! ከዚህ ቦታ የአንተ መኖሪያ አይደለም፣ በዚህ ቦታ ላይ እግዚአብሔርንና ሰውን የሚያገናኝ የሚያስታርቅ ታላቅ ጻድቅ ይወጣበታልና ይህ ቦታ የእርሱ ርስት ነው፣ የብዙ መነኰሳትም መንደር ይሆናል ነገር ግን የቦታው ስም በአንተ ስም ይጠራልሃል" አላቸው፡፡ በኋላ አባታችን ተክለ ሃይማኖት ተወልደው በዓታቸውን በዚያ ቦታ ላይ ሲያጸኑ ቦታው ግን "ደብረ ሊባኖስ" ተብሎ በመጀመሪያው አባት ስም ተሰየመ፡፡ መልአኩም በሌሊት እየመራ ወደ አክሱም ወሰዳቸው፡፡ ከዚያም "ታሪክ ወደምትሠራበት ዕጣ ክፍልህ ወደሆነው ቦታ አደርስሃለሁ" አላቸውና ወደ ኤርትራ አካለ ጉዛይ አውራጃ ልዩ ስሙ መጣዕ ወደተባለው ቦታ ወሰዳቸው፡፡ በዚያም አባታችን ድውያንን እየፈወሱ፣ ለምፃሞችን እያዳኑ፣ ሙታንን እያስነሡ ብዙ ተአምራትን እያደረጉ ወንጌልን እየሰበኩ "ሊባኖስ ዘመጣዕ" የሚባለውን ትልቁን ገዳማቸውን መሠረቱ፡፡ በወቅቱ የነበረው ዐፄ ገብረ መስቀልም የመጀመሪያውን ቤተ ክርስቲያን አሠራላቸው፡፡ ❤ ቅዱስ ላሊበላ 23 ዓመት ሙሉ ካነጻቸው እጅግ ድንቅ 11 ቤተ መቅደሶች ውስጥ አንደኛውን በአባ ሊባኖስ ስም ሰይሞላቸዋል፡፡ በዐፄ ገብረ መስቀል ያሠራላቸው ሌላኛው ገዳማቸው ትግራይ ተንቤን ውስጥ ይገኛል፡፡ እጅግ ድንቅ ድንቅ ተአምራትን በማድረግ የሚታወቁት አባታችን እንደ ተሰዓቱ ቅዱሳን ከሮም በመምጣት በሀገራችን ላይ ብርሃንን አብርተዋል፡፡ በመጨረሻም ጥቅምት 2 ቀን ተፀንሰው ሐምሌ 3 ቀን ተወለደው ጥር 3 ቀን በታላቅ ክብር ዐርፈዋል፡፡ ቅዳሴ ቤታቸው ደግሞ ሐምሌ 3 ቀን ነው፡፡ ይኸውም ለመጀመሪያ ጊዜ በዐፄ ገብረ መስቀል ጊዜ በስማቸው ቤተ ክርስቲያን ተሠርቶ የተመረቀበት ዕለት ነው፡፡ ከአባ ሊባኖስ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያድለን በጸሎታቸውም ይማረን!። ምንጭ፦ ከገድላት አንደበት።                             ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_ለሊባኖስ_እምቤተ_አቡሁ_ዘወጽአ። ከመ ቃለ መልአክ ሰምዐ። ኰኵሐ ዘቢጦ ማየ አንቀዐ። ሰላም ለአድኃኒ ወዓዲ አስትዓ በውስተ ገዳም ምስሌሁ ዘነበሩ ስንዐ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የጥር_ 3።                

❤ "በስመ አብ  ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤               ❤ #ጥር ፫ (3) ቀን። ❤ እንኳን #በቤተ_ልሔምና_አውራጃው ላሉ ንጉሥ ኄሮድስ በግፍ ለገደላቸው #ለዐሥራ_አራት_እልፍ_አራት_ሺህ_ለንጹሐን_ሕፃናት ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው መታሰቢያ በዓልና  ከዘጠኙ ቅዱሳን ቀድመው ወደ አገራች ኢትዮጵያ ለመጡ እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ የሴቶችን ጠጉር ሹሩባ ሲሠሩ ከኖሩ# ከአባ አሞን፣ ከታላቁ ነቢይ #ከቅዱስ_ኢሳይያስና_ከቅዱስ_ስምዖን ግብፃዊ ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                                                   ✝ ✝ ✝ ❤ በዚች ቀን ኄሮድስ ከሰብአ ሰገል እንደ ተረዳው ዘመን ልክ ሁለት ዓመት የሆናቸው ከዚያም በታች የሆኑ በቤተ ልሔምና በአውራጃዋ ሁሉ ያሉ ሕፃናት ተገደሉ። ቊጥራቸውም ዐሥራ አራት እልፍ ከአራት ሺህ ነው እነርሱም ከሴቶች እንደ ተወለዱ ንጹሐን የሆኑ ናቸው። ❤ በከበረ ወንጌል እንደተነገረ ሰብአ ሰገልም ከሔዱ በኋላ "እነሆ ኄሮድስ ሕፃኑን ሊገድለው ይሻዋልና ተነሣ ሕፃኑንና እናቱን ይዘህ ወደ ምድረ ግብጽ ሽሽ ተመለስ ብዬ እስከምነግርህም ከዚያ ኑር" ብሎ የእግዚአብሔር መልአክ ለዮሴፍ በሕልም ነገረው። እርሱም በሌሊት ተነሥቶ ሕፃኑንና እናቱን ይዞ ወደ ግብጽ ሔደ ኄሮድስ እስቲሞት ድረስም በዚያ ኖረ ከእግዚአብሔር ዘንድ "ልጄን ከግብጽ ጠራሁት" ተብሎ በነቢይ የተነገረው ይፈጸም ዘንድ። ከእነዚህ ውስጥ የክብር ባለቤት ጌታችን ክርስቶስ አንዱ እንደሚሆን ኄሮድስ አስቧልና። ❤ ጌታችንም ሥራውን ሁሉ ከብቻዋ ከኃጢአት በቀር ሠራ በረቀቀ ጥበቡም ከኄሮድስ ፊት ሸሸ ኄድሮስ አግኝቶት ሊገድለው ቢአስብ ያለ ጊዜው መግደል ባልተቻለውም ነበርና ሰነፎች ሰዎች ሰው መሆኑን ምትሐት ነው ብለው በአሰቡ ነበር ስለዚህ የክብር ባለቤት ጌታችን ሸሸ ሁለተኛም እግዚአብሔር "በፈጣን ደመና ተቀምጦ ወደ ግብጽ ይወርዳል" ተብሎ የተነገረው ትንቢት ይፈጸም ዘንድ ዳግመኛም ከክፉ ነገር እንድንሸሽ ለእኛ ሊአስተምረን የግብጽንም ጣዖታት ያጠፋቸው ዘንድ ነው። ❤ ይህን ያህል ብዛት ያላቸውን ሕፃናት መሰብሰብና መግደል ለኄሮድስ እንዴት ተቻለው ተንኰለኛ ኄሮድስ ምክንያት ፈጥሮ "የሁለት ዓመትና ከዚያም ያነሱ ሕፃናትን አሳድገን ጭፍራ እንሠራለት ዘንድ የሚያዝ የንጉሥ ነገሥት ቄሣር ደብዳቤ ከእኔ ዘንድ ደርሷል ወርቅ፣ ብር፣ ቀለብ ልብስም እንሰጣለን" ብሎ ወደ አገሩ ሁሉ ላከ። ስለዚህም ከእናቶቻቸው ጋር ተሰብሰቡ ያን ጊዜ ከእርሱ ዘንድ አንድ ሽህ ሁለት መቶ ወታደሮችን አውጥቶ በተራራ ላይ አረዱአቸው። ነቢይ ኤርምያስም የተናገረው ተፈጸመ "ራኄል ስለ ልጆቿ ስታለቅስ ብዙ መከራ ጨኸት ሙሾ ልቅሶ ዋይታ በራማ ተሰማ ልቅሶ መተውን መጽናናትን እምቢ አለች ልጆቿ ልጆችን አልሆኗትምና"። ❤ ዮሐንስም በራእዩ እንዲህ አለ "በታላቅ ቃል ጮኹ የተመሰገንህ እውነተኛ አቤቱ እስከ መቼ ነው ስለ ደማችን ተበቅለህ በምድር ላይ በሚኖሩ ሰዎች አትፈርድባቸውምን?" አሉ። ከእነርሱም ወገን ለየአንዳንዱ ብሩህ ልብስ ሰጥተው "እንግዲህ ጥቂት ቀን ዕረፉ" አሉዋቸው። እንነርሱ ይሞቱ ዘንድ ያላቸው ወንድሞቻቸው እስከሚፈጸሙበት ቀን ድረስ እንዲህ የእሊህን ሕፃናት ነፍሳቸውን አይቷልና። ❤ ዳግመኛም እንዲህ አለ "በዙፋኑ ፊት በአራቱ እንስሶችና በሃያ አራቱ አለቆች ፊት አዲስ ምስጋና ያመሰግናሉ ከግብጽ ምድር ከተዋጁ ከዐሥራ አራት እልፍ አራት ሽህ በቀር ያቺን ምስጋና ሊያውቃት የሚቻለው የለም። እነርሱ ከሴቶች እንደ ተወለዱ ንጹሐን የሆኑ ናቸው"። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                                                                                ✝ ✝ ✝ ❤ በዚች ዕለት የሴቶችን ጠጉር ሹርባ ሲሠራ የኖረ #የአባ_አሞን መታሰቢያው ነው። እንዲህ ባለ ሥራም ሲኖረሰ የኃጢአት ማዕበል ሊአሠጥመወሰ አልቻለም በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አመረን። ምንጭ፦ የጥር 3 ስንክሳር።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "በርህ ሠረቀ ለጻድቃን። ወለርቱዐነ ልብ ትፍሥሕት። ይትፌሥሑ ጻድቃን በእግዚአብሔር"። መዝ 96፥11-12 ወይም መዝ 43፥22-23። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 5፥1-17 ወይም ማቴ 2፥13-ፍ.ም።                 

አዘዘ መሞቱን አውቆ አማንያን ከሆኑ መርከበኞች አንዱን እንዲህ ብሎ አዘዘው "ወደ ወደቡ ስትደርሱ ሥጋየን በኮረብታ ላይ አድርግ" እርሱም እንዳዘዘው አደረገ። ❤ ከዚህም በኋላ ምዕመናን ሰዎች መጥተው ሥጋውን ወስደው ገነዙት የስደቱም ወራት እስቲያልፍ በእነርሱ ዘንድ አኖሩት ቤተ ክርስቲያንም ሠርተው ሥጋውን በውስጧ አኖሩ ከእርሱም ታላላቅ የሆኑ ድንቆች ተአምራቶች ተደረጉ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ አላኒቆስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኚ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥር 2 ስንክሳር።                                                     ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ወይንዕዋ ለነፍሰ ጻድቅ። ወይኴንን ደመ ንጹሐ። ወኮነኒ እግዚአብሔር ፀወንየ"። መዝ 93፥21። የሚነበቡት መልዕክታት ዕብ 11፥1-8፣ 1ኛ ዮሐ 3፥6-13 እና የሐዋ ሥራ 12፥18-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 23፥13-23። የሚቀደሰው ቅዳሴ የሠለስቱ ምዕት ቅዳሴ ነው። መልካም የቅዱስ አቤል የዕረፍት በዓልና የብርሃን ልደቱ በዓል ሰሞን ለሁላችንም ይሁንልን።                   

❤ "በስመ አብ  ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤               ❤ #ጥር ፪ (2) ቀን። ❤ እንኳን #ለሙታን_መዠመርያ በወንዱሙ ቃየን ተገድሎ ደሙ በግፍ ለፈሰሰ #ለጻድቁ_ለቅዱስ_አቤል ለዕረፍት በዓል መታሰቢያና #ለሕርቃስም_ልጅ ሕልምን ለምትተረጒም #ለነቢዪት_ለቅድስት_ሳቤላ ለዕረፍት በዓል መታሰቢያ እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከከበረ አባት ከኤጲስቆጶስ #ከአባ_አላኒቆስ በሰማዕትነት ከዐረፈ፣ ከእስክድርያ ዐሥራ ስድስተኛ ሊቀ ጳጳስ ከከበረ አባት #ከአባ_ቴዎናስ ዕረፍት፣ በአባ ሲኖዳ ገዳም ውስጥ #የእመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም ቤተ ክርስቲያኗ ከከበረችበት፣ #ከቅዱስ_ፊላታዎስ ጋር ሰማዕትነት ከተቀበሩ #ከዘጠኝ_ሽህ_ሰባት_መቶ ሰዎች ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                                                                         ✝ ✝ ✝ ❤ #የሙታን_በኵር_ጻድቁ_ቅዱስ_አቤል፦ ምክንያቱም አዳም የእግዚአብሔርን ትዕዛዝ ተላልፎ እንዳይበላው የታዘዘውን ዕፅ በላ ያን ጊዜ በእርሱና በልጆቹ ላይ ሞት ሠለጠነ ለኃጢአትም ተገዥ ሆነ። ሰይጣንም ሰውን ለማሳት ሠለጠነ ከዚህም በኋላ አዳም ከገነት ወጥቶ ወደታችኛዋ ምድር ወረደ ስለ በደለና የፈጣሪውንም ትዕዛዝ በመተላለፉ ፈጽሞ እያዘነና እያለቀሰ መቶ ዓመት ኖረ። ✝ ከዚህም በኋላ አዳም ሔዋንን በግብር አወቃት ፀንሳ ቃየልንና እኅቱን ኤልዩድን ወደለች ሁለተኛም ዐወቃት አቤልንና እኅቱን አቅሌማን ወለደቻቸው አዳምም ሔዋንን "እነሆ ልጆችሽ አካለ መጠን አደረሱ ጐለመሱ ቃየል የአቤልን እኅት አቅሌማን ያግባት አቤልም የቃየልን እኅት ኤልዩድን ያግባት" አለ። ቃየልም እናቱን ሔዋንን እንዲህ አላት "ለእኔ ከእኔ ጋር የተወለደች እኅቴን ማግባት ይገባኛል አቤልም ከእርሱ ጋር የተወለደች እኅቱን ያግባ" ቃየል ከእርሱ ጋር የተወለደ ኤልዮድም እናቷ ሔዋንን የምትመስል እጅግ የምታምር መልከ መልካም ናትና። ❤ አዳምም ይህን ነገር በሰማ ጊዜ እጅግ ጭንቅ ሆነበት ቃየልንም "አብራህ የተወለደች እኅትህን ታገባት ዘንድ አይገባህም አለዚያም ለእግዚአብሔር መሥዋዕትን አቅርቡና መሥዋዕቱን ለተቀበለው ይሁን" አለው። መሥዋዕትንም በአቀረቡ ጊዜ የአቤልን መሥዋዕት እግዚአብሔር ተተቀበለ የቃየልን ግን አልተቀበለም ስለዚህም ቃየል ፈጽሞ አዘነ ሰይጣንም ተገናኘውና "ምን ያሳዝንሃል?" አለው ቃየልም "ለወንድሜ ለአቤል እኅቴን እተውለት ዘንድ አባቴ አዘዘኝ" አለው። ሰይጣንም "ምክርን ከኔ ስማ ወንድምህን ወደ ውኃ ምንጭ ይዘኸው ሒድ ውኃንም ሲጠጣ ራሱን በደንጊያ ምታው በሞተ ጊዜ ሁለቱንም ታገባቸዋለህ የሚከለክልህ ማነው" አለው ለቃየልም የሰይጣን ምክር ደስ አሰኘው ልቡም በዝሙት እሳትነት ነደደ ሰይጣን እንዳስተማረውም ወንድሙን አቤልን ገደለው ለሴት ስለ መቅናትም ጻድቁ አቤል በወንድሙ እጅ ሞተ እንዲህም ሞት ወደ ዓለም ገባ። ❤ እግዚአብሔርም ቃየልን "ወንድምህ አቤል ወዴት ነው" አለው። ቃየንም "አላውቅም በውኑ እኔ የአቤል ጠባቂው ነኝን" አለው። እግዚአብሔርም እንዲህ አለው "ቃየል ምን አድርገሃል የወንድምህ የአቤል ደም ጩኸት ከምድር ወደኔ ደርሷል። አሁንም በእጅህ የፈሰሰውን የወንድምህን ደም ትጠጣ ዘንድ አፍዋን የከፈተች ምድር የተረገመች ትሁን አንተ ታርሳታለህና በረከቷን ትሰጠሰህ ዘንድ አትጨምርም በምድር ላይ ፈሪ ተቅበዝባዥ ሁን"። ይህም መርገም ዘሩ በጥፋት ውኃ ከምድር ገጽ እስከ ሚደመሰስ በቃየል ላይ የበዛ ሆነ። ❤ የክብር ባለቤት ጌታችንም ጸሐፍት ፈርሳውያንን ሲዘልፋቸው እንዲህ አላቸው "ስለዚህ ነቢያትን፣ ሊቃውንትን፣ ጥበበኞችን ወደናንተ እልካለሁ ከነርሱ የምትገድሉት አለ የምትሰቅሉትም አለ በምኵራባችሁ የምትገርፋት አለ ካንድ አገር ወዳንድ አገር ታሳድዷቸዋላችሁ። ከጻድቁ ከአቤል ጀምሮ በቤተ መቅደስና በመሠዊያው መካከል እስከገደላችሁት እሰሰከ በራክዩ ልጅ እስከ ዘካርያስ ደም ድረስ በዓለም የፈሰሰው የጻድቃን ደም ሁሉ በእናንተ ላይ ይደርስ ዘንድ"። ❤ ቅዱስ ጳውሎስም አለ "ቃየን ካቀረበው መሥዋት ይልቅ አቤል በሃይማኖት ለእግዚአብሔር ያቀረበው መሥዋዕት ተሻለ" ስለ እርሱም ደግ እንደሆነ መሰከረለት መሥዋዕቱንም በመቀበሉ ምስክሩ እግዚአብሔር ነው ደግ እንደሆነም ከሞተ በኋላ ተናገረ። ❤ ከዚህም በኋላ አዳም ልጁን በአጣው ጊዜ "ወንድምህ አቤል ወዴት አለ" ብሎ ቃየልን  ጠየቀው ቃየልም በቁጣ "አላውቅም" ብሎ መለሰ አዳምም ልጁን ይፈልግ ዘንድ ወደ ዱር ሮጠ በወንዝ ዳርም በድንኑን አገኘና አንገቱን አቅፎ "ማን ገደለህ?" አለው ከበድኑም "ወንድሜ ቃየን ገደለኝ" የሚል ቃል ወጣ። አዳምና ሔዋንም በልጃቸው በአቤል ሞት ሃያ ስምንት ዓመት ያህል ሲያለቅሱ ኖሩ። ❤ ከዚህም በኋላ መላእክት ወደ አዳም መጥተው "የዓለሙ ሁሉ አባቶች አባት አዳም የምሥራች እነሆ ልጅህ አቤል የገነትን ዛፎች ተሳለመ ነፍሱም እንደ ተወደደ መሥዋዕቶ ወደ እግዚአብሔር ዐረገች" አሉት። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን የአባቶቻችንም በረከት ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                                                         ✝ ✝ ✝ ❤ #አባ_ቴዎናስ፦ እርሱም ለእስክንድር ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ዐሥራ ስድስተኛ ነው። ይህም ቅዱስ አዋቂ ብልህ በቀናች ሃይማኖት የጸና በሥራው ሁሉ ያማረ ስለ ዕውቀቱም ሰዎች ሁሉ የሚወዱትና የሚሹት ነው። በዚያም ወራት ከሀድያንን በመፍራት በሥውር ከዋሻ ውስጥ በቀር በግልጥ ሊጸልዩና ሊቀድሱ ለክርስቲያኖች አልተቻላቸውም ነበር ይህም አባት አብያተ ክርስቲያናትን እስከሠሩ ድረስ አግባባቸው በእመቤታችንም በቅድስት ድንግል ማርያም ስም ያማረች ቤተ ክርስቲያን ሠሩ ከከሀድያንም ብዙዎችን መልሶ የክርስትና ጥምቀትን አጠመቃቸው። ❤ በተሾመባት በመጀመሪያ ዓመት ተፍጻሜተ ሰማዕት የሆነ ሊቀ ጳጳሳት ጴጥሮስን ያጠመቀው እርሱ ነው። በተሾመ በአምስተኛ ዓመቱም አናጒንስጢስነት ሾመው በዐሥራ ሁለተኛም የሹመቱ ዓመት ቅስና ሾመው። ❤ በዚህም አባት ዘመን አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ አንድ ገጽ የሚል ከሀዲ ሰባልዮስ በእስክንድርያ አገር ተነሣ ይህም አባት አውግዞ ለየው የከፋች ሃይማኖትንም አጠፋት። ዳግመኛም በዘመኑ ቆዝሞስና ድምያኖስ ወንድሞቻቸው እናታቸው ቴዎዳዳም በሰማዕትነት ሞቱ ይህም አባት ያመረ ጒዞውን በመጓዝ እግዚአብሔርን አገልግሎ በዚች ቀን በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ቴዎናስ ጸሎት ይማረን በረከቱ ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #ኤጲስ_ቆጶስ_አባ_አላኒቆስ፦ ጣዖታቱን እንዲአቃልሉ ለሰዎች እንደሚያስተምራቸው ከሀዲው ንጉሥ በሰማ ጊዜ ይዘው ጽኑ ሥቃይን ያሠቀሠዩት ዘንድ መልክተኞችን ላከ። የንጉሥ መልክተኞች መላካቸውን የተመሰገነ አላኒቆስ ሰምቶ በአገረ ስብከቱ ያሉትን ሕዝቦች ሰበሰባቸውና የቊርባን ቅዳሴን ቀድሶ ሥጋውንና ደሙን አቀበላቸው። ከዚህም በኋላ "በቀናች ሃይማኖት ጽኑ ከእንግዲህ ፊቱን አታዩኝም" አላቸው። እነርሱም አለቀሱ ሊስተውትም አልተቻላቸውም ወጥቶም ራሱን ለንጉሥ መልክተኞች አሳልፎ ሰጠ እነርሱም ወስደው ለእዴናው አገር መኰንን ሰጡት። እነርሱም ወደ አገረ እንድኩ ወስዶ በዚያ ጽኑዕ ሥቃይን አሠቃየው ማሠቃየቱም በሰለቸው ጊዜ ትከሻውን በሰይፍ ይሠነጥቁ ዘንድ ራሱንም ይቆርጡ ዘንድ

❤ አርያኖስም አክሚም ከተማ በደረሰ ጊዜ ኤጲስቆጶስን አባ ብኑድያኖስን ያዘውና አሥሮ ወደ አገር ውስጥ ገባ። የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤልም ለዲዮሰሰቆሮስና ለሰከላብዮስ ተገለጸላቸው ወደ መኰንኑም ሒደው የምስክርነት አክሊልን እንዲቀበሉ ነገራቸው እነርሱም ታኅሣሥ ሃያ ስምንት ቀን  ሃያ አራት መነኰሳት ሁነው ሔዱ። ወደ አክሚም ከተማም ሲደርሱ በመድኃኒታችን ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የከበረ የልደትን በዓል ለማክበርና ስለ ከበረ ስሙም ይሞቱ ዘንድ የክርስቲያን ወገኖችን ከሴቶቻቸውና ከልጆቻቸው ጋር ተሰብስበው አገኙአቸው ኤጲስቆጶሱ አባ ብኑድያኖስም ከእርሳቸው ጋር ገባ። በማግሥቱም አባ ብኑድያኖስ ቀደሰ አግዮስ ወደሚባለው በደረሰ ጊዜ መላእክት እንዲህ ብለው በታላቅ ድምጽ አመሰገኑ "ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እግዚአብሔር አሸናፊ ፍጹም የጌትነትህ ምስጋና በሰማይና በምድር የመላ ነው"። ያን ጊዜ መድኃኒታችንን በመሠዊያው ታቦት ላይ ተቀምጦ መላእክትም በዙሪያው ቁመው ቊርባኑን እያነሣ በካህኑ እጅ ላይ በማድረግ የተሰበሰቡትን ሲያቆርባቸው ቅዱሳኑ አዩት። ❤ በዚያንም ጊዜ መኰንኑ አርያኖስ ደረሰ ተቆጥቶም ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብቶ ስማቸው ብሕዋፋና ውኒን የሚባሉ ሁለት የአገር አለቆችን ይዞ ራሳቸውን በሰይፍ ቆረጠ ከእነርሱም በኋላ ዲያቆናትን ንፍቀ ዲያቆናትን መዘምራንን የቤተ ክርስቲያን ሹሞች ደማቸው ከቤተ ክርስቲያን ደጃፍ ወጥቶ ሃያ ክንድ ያህል እስቲጎርፍ ሴቶችና ልጆችንም ሳያስቀር አረዳቸው። ❤ ከዚህም በኋላ ኤጲስቆጶሱን አባ ብኑድያስን ዲዮስቆሮስን ሰከላብዮስን ከእርሳቸውም ጋር ያሉ መነኰሳትን ከእርሱ ጋር ወሰዳቸው ለጣዖትም ይሰግዱ ዘንድ ሸነገላቸው እምቢ በአሉትም ጊዜ ዐጥንቶቻቸው እስከሚለያዩ ድረስ ይደበድቧቸው ዘንድ አዘዘ የእግዚአብሔርም መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ተገልጾላቸው አዳናቸው የአርያኖስም የጭፍሮቹ ታላላቆች ኮርዮንና ፊልሞና ከጭፍሮችም አርባ ሰዎች ይህን ድንቅ ተአምር አይተው በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ ወደ እሳት ማንደጃም እንዲጥሏቸው አዘዘ። ተጋድሏቸውንም ታኅሣሥ ሠላሳ ቀን ፈጸሙ ከተሰበሰቡትም ውስጥ ብዙዎች የሚያስገድዳቸው ሳይኖር በእውነተኛ አምላክ በክርስቶስ እናምናለን እያሉ ወደ እሳቱ ማንደጃ ራሳቸውን ወረወሩ ምስክርነታቸውንም እንደዚህ ፈጸሙ። ❤ ከዚህም በኋላ ጥር አንድ ቀን ቅዱሳን ዲዮስቆሮስና ሰከላብዮስ ታሥረው ሳሉ የመላእክት አለቃ ቅዱሰሰ ሚካኤል ተገለጠላቸውና ምስክርነታቸውን እንደመፈጽሙ አበረታቸው በነጋም ጊዜ ለአማልክት ስለ መስገድ አርያኖስ ተናገራቸው አይሆንም በአሉትም ጊዜ የዲዮስቆሮስን ዐይኖቹን ያወልቁ ዘንድ አዘዘ ቅዱሱም የወለቁ ዐይኖቹን አንሥቶ ወደ ቦታቸው መለሳቸው መኰንኑ ሉክዮስ አይቶ ከሠራዊቱ ጋር በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመነ ወደ እሳትም ወርውረዋቸው ምስክርነታቸውንም ፈጸሙ። ❤ ከዚህም በኋላ የከበሩ ሰማዕታትን ይገደሏቸው ዘንድ አርያኖስ አዘዘ ሲጸልዩም የክብር ባሌበት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገለጠላቸው ስማቸውን ለሚጠረሠ መታሰቢያቸውንም ለሚያደርግ ገድላቸውንም ለሚጽፍ ከቅዱሳን አንድነት ይቈጥረው ዘንድ ቃል ኪዳን ሰጣቸው። ከዚህም በኋላ ወታደሩ ቀርቦ የቅዱስ ዲዮስቆሮስን ራሱ ቆረጠ ሰከላብዮስንም ከወገቡ ላይ ቆረጡት ሃያ አራቱን መንኰሳትም ከቁመታቸው ሠነጠቋቸው በዚች በጥር አንድ ቀን ተቆረጡ ከዘመዶቻቸው የሆነ ሳሙኤልም በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም በከበረች ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ቀበራቸው በአገረ አክሚም የተገደሉ ሰማዕታትም ቊጥራቸው ስምንት ሺህ አንድ መቶ አርባ ሆነ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በሁሉ ቅዱሳን ሰማዕታት ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥር1 ስንክሳር።                          ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ወይርአዩ አሕዛብ በቅድመ አዕይንቲነ። በ­ቀለ ደሞሙ ለአግብርቲከ ዘተክዕወ። ይባዕ ቅድሜከ ገዐሮሙ ለሙቁሓን"። መዝ78፥10-11። የሚነበበው ወንጌል ማር13፥9-23።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "እስመ በጻሕኮ በበረከት ሠናይ። ወአንበረከ አክሊለ ዲበ ርእሱ ዘእምዕንቊ ክቡር። ሐይወ ሰአለከ ወወሀብኮ"። መዝ 20፥3-4። የሚነበቡት መልዕክታት ዕብ 11፥32-ፍ.ም፣ 1ኛ ጴጥ 4፥12-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 7፥51-58። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 21፥33-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ቅዳሴ ነው። መልካም የብርሃነ ልደቱ ሰሞን፣ የቅዱስ እስጢፋኖስ የልደትና የዕረፍት በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።                 

❤ "በስመ አብ  ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ #የተባረከ_የጥር_ወር_የመዓልቱ_ሰዓት_ዐሥር ነው ከእንግዲህ ይጨመርለታል።               ❤ #ጥር ፩ (1) ቀን። ❤ እንኳን #ለሊቀ_ዲያቆናት_ለቀዳሜ_ሰማዕት #ለቅዱስ_እስጢፋኖስ_ለልደቱና_ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓልና #ከሶርያ_አገር_ለሆነ በከሀዲው መክስምኖስ ዘመነ መንግስት ሰማዕትነት ለተበቀበለ #ለቅዱስ_ለውንድዮስ ለዕረፍት በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከእስክድርያ ስልሳ ዘጠነኛ ሊቀ ጳጳስ #ከአባ_መቃርስ ዕረፍት፣ #ከከበሩ_ከአክሚም_ሰማዕታት የምስክርነታቸውን ተጋድሎ ከፈጸሙ ስማቸው #ቅዱሳን_ዲዮስቆሮስና_ሰከላብዮስ ዕረፍት፣ በዲዮቅልጥያኖስ እጅ ሰማዕትነት ከተቀበሉ ቊጥራቸው #ከካህናት_ስምትት_መቶ፣ #ከዲያቆናት_መቶ_ሠላሳ_ከመምህራን_ኃምሳ፣ #ከሦስት_ከቤተ_ክርስቲያን_ሹማምንት_ከሰማንያ_መሳፍንት_ከሠላሳ_ሁለት_ንፍቅ_ዲያቆናትና_ከመቶ_ኃምሳ_ሕዝባውያን ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                                                                                     ✝ ✝ ✝ ❤ #ቀዳሜ_ሰማዕታት_ቅዱስ_እስጢፋኖስ፦ ለዚህም ለከበረ እስጢፋኖስ እግዚአብሔር ኃይልን ጸጋ የተመላ ሰው እንደነበረና በሕዝቡም መካከል ታላላቅ ተአምራትንና ድንቅ ሥራን ይሠራ እንደነበረ የሐዋርያት ሥራ የተባለ መጽሐፍ ስለርሱ ምስክር ሆነ። ከዚህም በኋላ አይሁድ ቀኑበት የሐሰት ምስክሮች የሚሆኑ ሰዎችንም አስነሡበት "ይህን ሰው በሙሴና በእግዚአብሔር  ላይ የስድብ ቃልን ሲናገር ሰምተነዋል እንዲሉ ሐሰትን አስተማሩአቸው። ሕዝቡንና ሽማግሌዎችን ጸሐፊዎችንም አነሣሡአቸው አዳርሱን ብለው ከበው እየጐተቱ ወደ ሸንጎ ወሰዱት። ❤ የሐሰት ምስክሮችንም አቆሙበት እነርሱ ይህ ሰው በቤተ መቅደስ ላይ በኦሪትም ላይ ስድብን ሲናገር ተው ብንለው እምቢ አለ። "የናዝሬቱ ኢየሱስ ቤተ መቅደሳችሁን ያፈርሰዋል ሙሴ የሰጣችሁን ኦሪታችሁንም ይሽራል" ሲል ሰምተነዋል አሉ። በአደባባይ ተቀምጠው የነበሩት ሁሉ ተመለከቱት ፊቱም የእግዚአብሔርን መልአክ ፊት ሁኖ አዩት። ሊቀ ካህናቱም "እውነት ነውና እንዲህ አልክ" አለው። እርሱም እንዲህ አለ "ወንድሞቻችንና አባቶቻችን ስሙ ወደ ካራን ከመምጣቱ አስቀድሞ በሶርያ ወንዞች መካከል ሳለ ለአባታችን ለአብርሃም የክብር ባለቤት እግዚአብሔር ተገለጠለት። ካአገርህ ውጣ ከዘመዶችህም ተለይ እኔ ወደማሳይህ አገርም ና" አለው። ❤ "ከዚህም በኋላ ከከላውዴዎን ወጥቶ በካራን ተቀመጠ አባቱም ከሞተ በኋላ ዛሬ እናንተ ወደ አላችሁባት ወደዚች አገር አመጣው። ከዚህም በኋላ የግዝረትን ሥርዓት ሰጠው ይስሐቅም በወለደው ጊዜ በስምንተኛው ቀን ገዘረው እንዲሁ ይስሐቅም ያዕቆብን ገዘረው ያዕቆብም ዐሥራ ሁለቱን ነገድ አባቶች ገዘረ። የቀድሙ አባቶቻችንም በዮሴፍ ላይ ቀንተው ወደ ግብጽ አገር ሸጡት እግዚአብሔር ግን አክብሮት ነበር። ከመከራው ሁሉ አዳነው በግብጽ ንጉሥ በፈርዖን ፊትም ዕውቀትን መወደድን ሰጠው በግብጽ አገር ሁሉና በቤቱ ሁሉ ላይ ሾመው"። ነገርም በማስረዘም በሰሎሞን እጅ እስከተሠራችው ቤተ መቅደስ ያለውን ተረከላቸው። ❤ ከዚህም በኋላ ድምፁን ከፍ ከፍ አድርጎ "እናንተም እንደአባቶቻችሁ ዘወትር መንፈስ ቅዱስን የምታሳዝኑት ዐይነ ልቡናችሁ የታወረ ዕዝነ ልቡናችሁ የደነቈረ አንገተ ደንዳኖች" አላቸው። "አባቶቻችሁ ከነቢያት ያላሳደዱት ያልገደሉት ማን አለ እናንተ ክዳችሁ የገደላችሁትን ገደላችኋቸው። በመላእክት ሥርዓት ኦሪት ተቀብላችሁ አልጠበቃችሁም"። ❤ ይህንንም ሰምተው ተበሳጩ ልባቸውም ተናደደ ተነሠሣ ጥርሳቸውንም አፋጩበት። በቅዱስ እስጢፋኖስም መንፈስ ቅዱስ አደረበት ሰማይም ተከፍቶ ኢየሱስ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀምጦ የእግዚአብሔርን ክብር አየ። "እነሆ ሰማይ ተከፍቶ የሰው ልጅም በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀምጦ አያለሁ" አለ። ❤ ዶሮአቸውን ይዘው በታላቅ ድምፅ ጮኹ በአንድነትም ከበው ጐተቱት። እየጐተቱም ከከተማ ወደ ውጭ አውጥተው በደንጊያ ወግረው ገደሉት የገድሉትም ሰዎች ልብሳቸውን ሳውል ለሚባል ጐልማሳ ልጅ ያስጠብቁ ነበር። "ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ነፍሴን ተቀበል" እያለ ሲጸልይ እስጢፋኖስን በደንጊያ ወገሩት። ❤ ዘለፍለፍ ባለ ጊዜም ድምፁን ከፍ አድርጎ "አቤቱ ይህን ኃጢአታቸውን ይቅር በላቸው በደልም አታድርግባቸው" ይህንንም ብሎ ዐረፈ። ደጋግ ሰዎችም መጥተው የቅዱስ እስጢፋኖስን ሥጋ ወስደው ቀበሩት ታላቅ ልቅሶም አለቀሱለት። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም ሐዋርያና ሰማዕት በሆነ በቅዱስ እስጢፋኖስ  አማላጅነት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #ሰማዕቱ_ቅዱስ_ለውንድዮስ፦ የዚህም ቅዱስ ዜና እግዚአብሔርን የሚያመልክ ተጋዳይ እንደሆነ ንጉሥ መክስምያኖስ በሰማ ጊዜ ልኮ ወደርሱ አስመጣው ሃይማኖቱንም ትቶ አማልክቶቹን ያመልክለት ዘንድ ብዙ ገንዘብ አቀረበለትና ይሸነግለው ጀመረ የከበረ ቅዱስ ለውንድዮስ ግን ዘበተበት ስጦታውንም  በማቃለል ክብሩን አጐሳቈለ የረከሱ አማልክቶቹንም ረገመ። ❤ ያን ጊዜ እጅግ ተቆጥቶ በመንኰራኵር ውስጥ ሰቅለው ጽኑዕ የሆነ ሥቃይን እንዲ አሠቃዩት አዘዘ። ንጉሥ እንዳዘዘ አደረጉበት የክብር ባለቤት ጌታችን ግን ያለ ጥፋት በጤና አወጣው። ዳግመኛም በብረት ዘንጎች ይደበድቡት ዘንድ ቅባትና ስብንም በታላቅ ድስት አፍልተው ቅዱስ ለውንድዮስን ከውስጡ ይጨምሩት ዘንድ አዘዘ ይህን ሁሉ ሥቃይንም አሠቃዩት የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያጸናውና ያስታግሠው ያለ ጉዳትም በጤና ያስነሣው ነበር። ❤ ማሠቃየቱንም በደከመው ጊዜ ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ የሰማዕትነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ። ከሥጋውም ድንቆች የሆኑ ብዙዎች ተአምራቶች ተገለጹ ዜናውም በሶርያ አገር ሁሉ ተሰማ አብያተ ክርስቲያናትና ገዳማት ተሠሩለት ከገዳማቱም በአንዲቱ የአንጾኪያ ሊቀ ጳጳሳት የሆነው የከበረ ሳዊሮስ በሕፃንነቱ ተጠመቀባት። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ለውንድዮስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #የከበሩ_የአክሚም_ሰማዕታት_ቅዱሳን_ዲዮስቆሮስና_ሰከላብዮስ፦ እክሚም በሚባል አገር ሹም የሆነ አንድ ሰው ነበር በወርቅ በብር ባለጸጋ ነው ስሙም አልሰመማልዮስ ይባላል ስማቸው ዲዮስቆሮስና ሰከላብዮስ የሚባል ሁለት ልጆቹን ወለደ እነርሱም ከመጾምና ከመጸለይ ጋር እግዚአብሔርን በመፈራት አደጉ። አባታቸው በሞተ ጊዜ ምንኵስናን ተመኙ የእግዚአብሔርም መልአክ ተገልጦላቸው ወደ ገዳማዊ አባ ሙሴ ገዳም እንደመሔዱ አዘዛቸው ሒደውም በዚያ መነኰሱ ድንቆች ተአምራቶችንም እያደረጉ በብዙ ተጋድሎ ኖሩ። ከጥቂት ወራትም በኋላም ዲዮስቆሮስ ቅስና ሰከላብዮስም ዲቁና ተሾሙ። ዲዮቅልጥያኖስም የክብር ባለቤት ክርስቶስን በካደው ጊዜ ለጣዖታት የማይሰግዱ ክርስቲያኖችን ሁሉ ይገድል ዘንድ የእንዴናው ገዥ አርያኖስን አዘዘው።

❤ በሆሣዕና ዕለት ወደ አበ ምኔቱ ሒዶ ወደ ኢየሩሳሌም ለመሔድ ፈቃድ ለመነው ፈቀደለትም በማግሥቱም ፊታቸው የሚያበራ ሦስት ሰዎች ሲጠብቁት አብሮዋቸው ሔደ። ከዚህም በኋላ አበ ምኔቱ የአባ ዘካርያስን ቤት ሊጐበኝ ሔደ ሦስት ታላላቅ ዘንዶዎች በምድር ላይ ሲርመሰመሱ አግኝቶ በአያቸው ጊዜ ፈራቸው እነርሱም በስሙ ጠሩት ወደነርሱም ዘወር ሲል "አባት ሆይ ሲመግበን የነበረው ጌታችን ዘካርያስ ከዚህ ወደየት ሔደ"  ብለው በሰው አንደበት ተናገሩት። አበ ምኔቱም ሰምቶ አደነቀ መብልንም ሰጣቸው። አባ ዘካርያስም ወደ መኖሪያው ተመልሶ በብዙ ተጋድሎ ኖረ። ከዚህም በኋላ ታኅሣሥ30 ቀን በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ዘካርያስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የታኅሣሥ 30 ስንክሳር።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "የሐዩ ወይሁብዎ እምወርቅ ዓረብ። ወዘልፈ ይጼልዩ በእንቲአሁ። ወኵሎ አሚረ ይድኅርዎ"። መዝ 71፥15 ወይም መዝ 78፥10-11። የሚነበቡት መልዕክታት ፊሊ 3፥15-ፍ.ም፣ 1ኛ ጴጥ 2፥12-21 እና የሐዋ ሥራ 19፥8-19። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 2፥1-13። የሚቀደሰው ቅዳሴ የእመቤታችን የማርያም ቅዳሴ ነው። መልካም የብርሃነ ልደቱ በዓል ሰሞን። ለሁላችንም ይሁንልን።                 

❤ "በስመ አብ  ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤            ❤ #ታኅሣሥ ፴ (30) ቀን። ❤ እንኳን #ለታላቁ_አባት ለተመሰገኑ አባት አርባ ዓመት ሙሉ የሴቶች ፊት ሳያይ ለኖረ #ለአቡነ_ዮሐንስ ለዕረፍት በዓል፣ በአባ መቃርስ ገዳም በአስቄጥስ ገዳም አበ ምኔት ለሆነ ለከበረ አባት #ለአቡነ_ዮሐንስ ለዕረፍት በዓል፣ ከመኰንኑ ከአርያኖስ የጥፍሮቹ ታላላቆች #ለቅዱሳን_ለኮርዮንና_ፊልሞና ከእናርሳቸው ጋር ካሉ #ከአርባ_ወታደሮች ጋር ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው በዓልና ተጋድይ ለሆነ #ለአባ_ዘካርያስ ዕረፍትና በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ከሚታሰቡ፦ ኄሮድስ ከገደላቸው #ከከበሩና_ከነጹ_ሕፃናት ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                                                                 ✝ ✝ ✝ ❤ #አባ_ዮሐንስ፦ ይህም ተጋዳይ የምንኵስና ልብስን ከለበሰ ጀምሮ የትንቢትና በሽተኞችን የመፈወስ ሀብት ተሰጠው ዜናውም በአገሩ ሁሉ ተሰማ። ይህም አባ ዮሐንስ ሁል ጊዜ የሚጐበኘው አንድ መኰንን ነበረ የመኰንኑም ሚስት ወደ አባ ዮሐንስ ዘንድ እንዲወስዳት ባሏን ታምለውና ታስገድደው ነበር እርሱም "የከበረ አባ ዮሐንስ ከአርባ ዓመት ጀምሮ የሴቶችን ፊት አላየም" አላት።  ከዚህም በኋላ መኰንኑ ሒዶ ሚስቱ ያለችውን ለአባ ዮሐንስ ነገረው አባ ዮሐንስም "በእግዚአብሔር ፈቃድ የፈለገችውን እፈጽምለሠታለሁ" አለው። ❤ በዚያችም ሌሊት የከበረ ዮሐንስ ለዚያች ሴት በሕልም ተገልጾ እንዲህ አላት "ጻድቅ ያልሆንኩ ወይም ነቢይ የኔን ፊት ታዪ ዘንድ የምትሺ አንቺ ሴት ከእኔ ምን አለሽ እኔስ ካንቺ ምን አለኝ እንግዲህስ ፊቴን ማየት አትሺ" ይህንንም ብሎ በላይዋ ጸልዮ ባረካት። በማግሥቱም የከበረ አባ ዮሐንስ በመንፈስ እንደታያት ለባሏ ነገረችው። መልኩንና አምሳያውን አመለከተችው ከዚያም በኋላ ከብዙ ሙገሳና ምስጋና ጋር ባሏን ወደ አባ ዮሐንስ ላከችው። ❤ የከበረ ዮሐንስም ባሏን በአየው ጊዜ ፈገግ ብሎ "የሚስትህ ምኞቷ የተፈጸመላት አይደለምን በዚች ዕለት በእግዚአብሔር ፈቃድ አግኝታኛለችና" አለው መኰንኑም ሰምቶ ከትሩፋቱና ከደግነቱ የተነሣ እጅግ አደነቀ። ይህም አባ ዮሐንስ ጭንቅ በሆነ ተጋድሎ ዘጠና ዓመት ያህል ኖረ ከዚህም በኋላ ታኅሣሥ30 ቀን በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ዮሐንስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ❤ የአስቄጥ ገዳም አበ ምኔት አባ ዮሐንስ፦ ይህም አባት በተሾም ጊዜ ቤተ ክርስቲያን በራች ለብዙ ቅዱሳንም አባት ሆነ ከእርሳቸው ውስጥ ታላላቅ ከዋክብት የሆኑ አባ ገዐርጊና አባ አብርሃም የአገረ ተሙዝ ኤጲስቆጶስ አባ ሚናስ የአገረ ስሐ አባ ዘካርያስ ለብዙ ሰዎች ነፍሳት ወደብ የሆኑ እነርሱን የመሰሉ ሌሎች ብዙዎች አሉ። ለሕዝቡ ቅዱስ ቊርባንን በሚያቈርብ ጊዜ ኃጢአተኞውና ጻድቁ ይገለጥለታና ከቅዱሳን መላእክቶቹ ጋር ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስንም በመሠዊያው ላይ ብዙ ጊዜ አየው። ❤ በአንዲትም ዕለት ሥራው የከፋ አንዱን ቄስ ወደ ቤተክርስቲያን ሲመጠሠ አየው ከእርሱም ጋር ያሉ ብዙዎች ርኩሳን የረቀቁ አጋንንት ከበውት አፉ ውስጥ ልጓም አድርገዋል ወደ ቤተ ክርስቲያንም ከመግባቱ በፊት የእግዚአብሔር መልአክ ከመሠዊያው ወጥቶ በእሳት ሰይፍ ከእርሱ ከቄሱ መናፍስትን አሳደዳቸው ቄሱም ወደ መቅደስ በገባ ጊዜ መቀደሻውን የክህነት ልብስ ለበሰ ሁለመናውም እንደ እሳት ሆነ ቀድሶም ለሕዝቡ ሥጋውና ደሙን አቀበላቸው። ልብሰ ተክህኖውንና የመቀደሻውን ሽልማት ከላዩ አውልቆ ወደ ውጭ በወጣ ጊዜ እነዚያ የጠቆሩ መናፍስት ርኩሳን ተቀብለው እንደቀድሞው አደረጉበት። አባ ዮሐንስም ይህን ነገር ለመነኰሳቱ ሲያስረዳ እንዲህ አላቸው "በቅዳሴ አገልግሎት ጊዜ ለኃጢአተኛውና ለጻድቁ ቄስ ልዩነት የለም ስለ ሕዝቡ እምነት ያ ኅብስት ተለውጦ የክርስቲያን ሥጋ ይሆናልና ወይኑም የከበረ ደሙን ይሆናልና"። ❤ ዳግመኛም በምሳሌ እንዲህ አላቸው "በብረት በወርቅና በብር ላይ እንደሚቀረጽ እንደ ንጉሥ ማኅተም ነው። ማኅተሙም አይለወጥም እንዲሁ ከካህናትም የክህነት ጸጋ አይለወጥም እርሱ እግዚአብሔር በጊዜው ጊዜ ለሁሉም ለየአንዳዱ እንደሠራው ይከፍለዋል እንጂ"። ይህንም የከበረ ዮሐንስ ታላቅ መከራ ደርሶበታል አረማውያን በርበር ማርከው ወደ አገራቸው ወስደውታልና እያሠቃዩትም በእነርሱ ዘንድ ብዙ ዘመን ታሥሮ ኖረ ከዚህም በኋላ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ገዳሙ መለሰው። ❤ ከመሞቱ በፊት የሚሞትበት ጊዜ አውቆ መነኰሳቱን ሰበሰባቸውና የወንጌልን ትዕዛዝ ይጠብቁ ዘንድ በሰማያዊ መንግሥት በጎ ዕድልን ርስትንም ከእርሳቸው ጋር ይቀበሉ ዘንድ እንደ ቅዱሳን አባቶች አካሄድ እንዲጓዙ አዘዛቸው። ❤ ከዚህም በኋላ ጥቂት ታመመ ነፍሱን ሊቀበሉ የቅዱሳንን አንድነት ሲመጡ አያቸውና ፈጽሞ ደስ አለው ነፍሱንም በእግዚአብሔር እጅ ሰጠ መነኰሳቱ ወደ ከበረች ቤተ ክርስቲያን ተሸክመው ወስደው በመዘመርና በታላቅ ምስጋና ገንዘው ቀበሩት እርሱንም ከመውደዳቸው የተነሣ ከተገነዘበት ልብስ ቆርጠው በእነርሱ ዘንድ አኖሩት ለሚታመም ሁሉ የሚፈውስ ሆነ የዚህም አባት ዕድሜ ዘጠና ዓመት ሆነ በግቢግ የሚልዋት መኖሪያው እስከ ዛሬ አለች። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ዮሐንስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                                ✝ ✝ ✝ ❤ #ቅዱሳን_ሰማዕታት_ኮርዮንና_ፊልሞና_አርባ_ወታደሮች፦ የሰማዕትነታቸውም ምክንያት የአክሚም ታላላቆች ከሆኑ ከሰማዕታት ዲዮስቆሮስ፣ ከሰከላብዮስና ከብኑድያስ የተደረገውን ተአምራት በአዩ ጊዜ የወታደርነት የማዕርግ ሽልማታቸውን ጣሉ በመኰንኑ አርያኖስም ፊት ቁመው "እኛ በእውነተኛ አምላክ በክርስቶስ የምናምን በግልጥ ክርስቲያን ነን ብለው ጮኹ። መኰንኑም ከእሳት ማንደጃ ውስጥ ይጥሏቸው ዘንድ አዘዘ ራሳቸውንም ሲወረውሩ ብዙዎች አዩአቸው ገድላቸውንም እንዲህ ፈጸሙ።                              ✝ ✝ ✝ ❤ #ተጋዳይ_አባት_ቅዱስ_ዘካርያስ፦ ይንም ቅዱስ ከመመንኰሱ በፊት በጐዳና ሲጓዝ አረማውያን በርበር ተነሡበትና ያዙት ሊያርዱትም ወደዱ በእግዚአብሔርም ፍቃድ የገዳሙ አለቃ በዚያች ጐዳና ሲያልፍ በላያቸው ጮኸ እነርሱም ሠራዊት እንደደረሰባቸው ተጠራጠሩ ፈርተውም ሸሹ ሲሸሹም ከባሕር ገብተው ሰጠሙ። ቅዱስ ዘካርያስም ከመገደል በዳነ ጊዜ ይሸጥ ዘንድ ገንዘባቸውን ይዞ ወደ ከተማ ገባ የአገሩም ገዥ ያዘው ሌባ እንደ ሆነ አስቦ ሊገለው ወደደ ግን ሥራውን በአወቀ ጊዜ ተወው። ❤ ከዚህም በኋላ ወደ አባ ጳኲሚስ ገዳም ሒዶ የምንኵስና ልብስ ለበሰ ሰይጣንም እስከ ቀናበት ድረስ በጾምና በጸሎት ተጠመደ ከዚህም በኋላ በአባቱ ተመስሎ በሕልም ታየውና "መሞቻዬ ጊዜ ደርሷልና ትቀብረኝ ዘንድ ና" አለው ቅዱሱም እውነት እንደሆነ አስቦ ወደ አባቱ ሔደ ግን በጤንነት አገኘው። የሰይጣን ተንኰልም እንደሆነ አውቆ ወደ መኖሪያው ተመለሰ ሰይጣንንም ድል እስአደረገው ድረስ በሩን ዘግቶ እየተጋደለ ኖረ።