uk
Feedback
ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ

ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ

Відкрити в Telegram

ይህ በግራር ደ/አባይ ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ ፍኖተ ብርሀን ሰንበት ት/ቤት የተዘጋጀ :- ለምዕመናን : ትምህርትን , ዝማሬዎችን , ኪናዊ ዝግጅቶችን, የቤተ ክርስቲያንን ወቅታዊ ዜናዎችንና በአላትን(ንግስ, ልዮ ልዮ የሰርክ ጉባኤያት ..ወዘተ) በምን መልኩ እንደተከበሩ ለምዕመናን ተዘጋጅቶ የሚተላለፍበት ገፅ ነው።

Показати більше
637
Підписники
Немає даних24 години
-37 днів
-1230 день
Архів дописів
ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ቆሪል ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን።                           ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የአክሚም_ቅዱሳን_ሰማዕታት፦ እነርሱም በከበረ የልደት በዓል በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የቊርባን ቅዳሴ አድርገው ተሰብስበው ሳሉ እነሆ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በመሠዊያው ላይ ሥጋውንና ደሙን ለሕዝቡ ሲያቀብላቸው አዩት። በዚህም ታላቅ ደስታ ውስጥ እያሉ መኰንኑ አርያኖስ መጥቶ ከበባቸው ወደ ቤተ ክርስቲያንም ገብቶ ስማቸው በሕዋፋና ወኒን የሚባል ሁለቱን የሀገር አለቆች ይዞ ራሳቸውን በሰይፍ ቆረጠ። ❤ ከዚህም በኋላ ቀሳውስትን ዲያቆናትን ንፍቀ ዲያቆናትን መምህራንን የቤተ ክርስቲያንን ሹማምንት ገደለ ደማቸው ከቤተ ክርስቲያኑ ደጃፍ ወጥቶ ሃያ ክንድ ያህል እስቲጎርፍ ወንዶችን ሴቶችንና ልጆችንም ምንም ሳያስቀር አሳረዳቸው። ኤጲስቆጶሱን አባ ብኑድያኖስን ዲዮስቆሮስን ሰከላብዮስን ከኤጲስቆጶሱ ጋር ያሉ መነኰሳትንም እነርሱን እንደታሠሩ አርያኖስ ከእርሱ ጋር ወሰዳቸው እነሆ የዕረፍታቸው መታሰቢያ ጥር አንድ ቀን ተፅፎአል። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳን ሰማዕታት ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ትኑር ዘለዓለሙ አሜን። ምንጭ፦ የታኅሣሥ29 ስንክሳር።                                       ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ነገሥተ ተርሴስ ወደሰያት አምኃ ያበውዑ። ነገሥተ ሳባ ወዓረብ ጋዳ ያመጽኡ። ወይሰግዱ ሎቱ ኵሎሙ ነገሥተ ምድር"። መዝ71፥10-11። የሚነበበው ወንጌል ማቴ1፥1-18።                            ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "የሐዩ ወይሁብዎ እምወርቅ ዓረብ። ወዘልፈ ይጼልዩ በእንቲአሁ። ወኵሎ አሚረ ይድኅርዎ"። መዝ 71፥15። የሚነበቡት መልዕክታት ገላ 4፥4-12፣ 1ኛ ዮሐ 4፥9-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 13፥16-22። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ2፥1-21። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ጎርጎርዮስ ካልእ ነው። መልካም የብርሃነ ልደቱ በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።                 

❤ ቤዛ ይስሐቅ በግዕ ከኅቱም ዕፀ ሳቤቅ እንደገኘ በእስራኤል በበርሃ ውስጥ ከኅቱም ዐለት ውኃ እንደ ፈለቀ የደረቀች የአሮን በትርም እንደለመለመችና እንደአፈራች። በሶምሶንም እጅ ወስጥ ከአህያ መንጋጋ ዐጥንት ውኃ እንደፈሰሰ። እንዲሁ የጌታችን ልደት በህቱም ድንግልና ሆነ። በዕፀ ጳጦስ ውስጥ እሳት እንደነደደች እጺቱም እንዳልተቃጠለች እንዲሁም የመለኮት እሳት ድንግልን አላቃጠላትም። ለርሱም ከቸር አባቱ ከማሕየዊ መንፈስ ቅዱስ ጋር ጌትነት ክብር ምስጋና ሰጊድ ከርሱ ጋር በትክክል ይገባል ለዘላለሙ አሜን።                          ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #ቅዱስ_ኢያሱ_ነቢይ፦እርሱም ከኤፍሬም ወገን  ለእስራኤል ልጆች ከጠላት ሰልፍ መድኃኒት ሁኖ ያዳናቸው ነው። የጌታችንም መወለድ ለአዳምና ለልጆቹ መድኃኒት ሆናቸው። የርሱም የቀድሞ ስሙ ሆሴዕ ነበረ እስራኤልን ከአማሌቅ ጦርነት በራፌድ በአዳናቸው ጊዜ ኢያሱ ተብሎ ተጠራ ይህም አዳኝ ማለት ነው። ❤ ሙሴም ከሞተ በኋላ እግዚአብሔር መረጠውና ለእስራኤል መስፍን አድርጎ ሾመው ልዩ ከሆኑ አሕዛብም ጦርነት አዳናቸው ርስታቸውንም አወረሳቸው ከዚህም በኋላ በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን ለዘለዓለሙ አሜን።                           ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #ጻድቅ_ቅዱስ_አቃርዮስ፦ የርሱም ግዛቱ በሶርያ አገር ሰርሜን በምትባል ክፍል ነው እርሷም ሮሀ ናት። ❤ ጣዖትን የሚያመልክ ሆኖ ኖረ መፃጉዕም ነበረ ለባለ መድኃኒቶችም ገንዘቡን ሁሉ ሰጥቶ ሊአድኑት አልቻሉም። የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሽተኞችን በማዳን አጋንንትን በማስወጣት የዕውሮችን ዐይኖች በመግለጥ ሙታንን በማስነሣት የሚሠራውን ድንቅ ተአምራቱን በሰማ ጊዜ እንዲህ ሲል ወደርሱ ላከ። "የሰውን ሥጋ ለብሰህ በኢየሩሳሌም የተገለጥክ የእግዚአብሔር ልጅ ምስጋና ይድረስህ ከእርሱ ሳትለይ ወደታች ለላከህ ለቸር አባትህም ምስጋና ይድረሰው አንተ የምትስተካከለው ክርስቶስ እንደሆንክ በሕሊናየ ለገለጠልኝ መንፈስ ቅዱስም ምስጋና ይሁን። ያለወንድ ዘር በድንግልና ለወለደችህም እናትህ ምስጋና ይሁን ለሚያምኑብህ ሁሉ ሰላምታ ይድረሳቸው። እኔም በአንተ አምኜ ከንቱ ጣዖትን ከማምለክ አንተን ወደ ማምለክ ተመለስኩ በኔ ላይም ንጉሥ ትሆን ዘንድ ሀገሬንም ትባርክ ዘንድ ከበሽታዬም ታድነኝ ዘንድ ከኃጢአቴም ታነጻኝ ዘንድ ወደኔ ና ጌታዬ ሆይ የከበረ ስምህን አይሁድ ሲጠሉ ለአንተ በኢየሩሳሌም መኖር ምን ያደርግልሃል። በከንቱ ለምን ትደክማለህ መካር ያጡ ወገኖች ናቸውና በቀድሞ ዘመንም ድንቆች ተአምራቶችን በማድረግ ከግብጽ አገር በአወጣኻቸው ጊዜ አላመኑብህም በበረሀም አርባ ዓመት መናውን በመገብካቸው ጊዜ ተቆጥተህ ለጥፋት እስከ አደረስካቸው በአንተ ላይ ምን ያህል አጒረመረሙብህ በሚራብና በሚጠማ ምድራዊ ሥጋማ ሲያዩህ እንዴት ነዋ ኀሳባቸው ከዚህ የተለየ ይመስልሃልን አንተ ከጥንት ጀምሮ የተሠወረውን ታውቃለህና ። ይኸንንና ይህን የመሰለውን ጽፎ ደብዳቤ ወደርሱ ላከ። ❤ የንጉሥ መልክተኞችም ወደ ጌታችን በደረሱ ጊዜ ሳይነግሩት የመጡለትን መልእክት አውቆ ነጭ ልብስ አንሥቶ ፊቱን አሸበት የፊቱም መልክ ወደ ልብሱ ገባ ከደቀ መዝሙሩ ከታዴዎስ ጋር እንዲህ ብሎ ላከለት ይህን የኔ መልክ የሆነውን ሥዕል ተቀበል እርሱም የምትሻውን ሁሉ ይፈጽምልሃል ከበሽታህም ይፈውስሃል ሀገርህንም ይባርካል መንግሥትህንም ያጸናል ይህ ሥዕል እኔን ነውና ይለወጥ እንደሆነ በውኃ በእሳት ፈትነው። መልክተኞችም ወደ ንጉሥ አቃርዮስ በደረሱ ጊዜ ያንን ሥዕል ሰጡት በእሳትና በውኃም ፈተነውና ምንም ምን ጥፋት አልደረሰበትም የሮሀ አገር ሰዎችም ከንጉሣቸው ጋር በጌታችን የመለኮት ሥልጣን አመኑ ይህ ሥዕል ቊጥር የሌለው ብዙ ድንቅ ተአምራትን አደረገ ንጉሡንም ከበሽታው ፈወሰው ከዚህም በኋላ ዕድሜውን ሲፈጽም በዚች ዕለት ዐረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን አሜን።                         ✝️✝️✝️ ❤ #ቅዱስ_ቆሪል_ገመላዊ፦ እርሱም በጾም በጸሎት ተወስኖ የሚኖር ነው እግዚአብሔርም የተሰወሩ ምሥጢራት ማወቅን ሰጠው የሚገለገልባቸው ከማሳም ተልባ የሚጭንባቸው ሦስት ግመሎች አሉት። ❤ ፈራጉን በሚባል አገር ለእመቤታችን ማርያም ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ካህናት የሆነ አንድ ሰው ነበረ ቤተ ክርስቲያኒቱም ነገሥታትና መኳንንት በየጊዜው የሰጧት ብዙ ገንዘብ አላት በሊቀ ካህናቱም ዘንድ የዕቃው ሣጥን በሥውር ይኖር ነበር የዚያንም ዕቃ ቊጥር ኤጲስቆጶሱ ያውቃል ያ ሊቀ ካህናት በእርሱ ሥልጣን ሥር ነበርና ከዚህም በኋላ የዕቃው ሣጥን ያለበትን ለልጁ ሳይነግር ያ ሊቀ ካህናት በድንገት ሞተ። ❤ ኤጲስቆጶሱም የሊቀ ካህናቱን ሞት በሰማ ጊዜ ወደዚያች ቤተ ክርስቲያን መጥቶ ከልጁ ገንዘቧን ፈለገ ያም ልጅ አባቴ በድንገተኛ ሞት ስለተነጠቀና ስለ አልነገረኝም ዕቃው ያለበትን አላወቅሁም አለው። ኤጲስቆጶሱም ሰምቶ ተቆጣ ሊአሠቃየውም ፈለገ ያም ልጅ ኤጲስቆጶሱን ዕቃው ያለበትን ቦታ እስከምፈልግ ድረስ ቆየኝ ባላገኘሁትም ጊዜ የወደድከውን ታደርግብኛለህ ብሎ ለመነው እርሱም ጊዜ ሰጠው። ወደ ቤቱም በገባ ጊዜ ችግሩን ሁሉ ለሚስቱ ነገራት። እርሷም በእግዚአብሔር ታምነህ በአባ መቃርስ ገዳም ወዳሉ አባቶች መነኰሳት ወደ ጎረቤቶቻቸውም ሒድ እነርሱ ይነግሩሃልና አለችው። ወደዚያም ሲደርስ ችግሩን ይፈጽሙለት ዘንድ ለመነኰሳቱ ነገራቸው የሚነግረውም አጥቶ ተስፋ ቆረጠ። አንድ ባሕታዊም ጠቀሰውና እንዲህ አለው "ሰምኑድ ወደሚሉት አገር ሒደህ ስለ ባለ ግመሉ ቆሪል ጠይቅ በእርሱም ዘንድ እደር እርሱም ይነግርሃል" አለው። ❤ ወደ ሰምኑድ መንደርም ደርሶ ስለርሱ ስለቆሪል ጠየቀ ሰዎችም ነገሩት ያለበትንም አመለከቱት በሔደ ጊዜም ከመኖሪያው አገኘው ሦስቱ ግመሎቹም ከእርሱ ጋር ነበሩ አባ ቆሪልም ፍላጎቱን በመንፈስ ቅዱስ አውቆ ወደ ማደሪያው አስገብቶ መብልን አቀረበለት "አባቴ ሆይ ችግሬን ሳትፈጽምልኝ እኔ አልበላም" አለው ቆሪልም "ችግርህ በጊዜው ጊዜ ይፈጸማልና አሁን ብላ" አለው። ከራትም በኋላ በየመኝታቸው ተኙ የሌሊቱም እኩሌታ ሲሆን ያ ሰው ቆሪልን ከግመሎቹ ጋር ቁሞ አየው ሲሰግድ ይሰግዳሉ ሲቆምም ይቆማሉ። በነጋ ጊዜም ተልባ ይጭንባቸው ዘንድ ወደ ማሳ ወሰዳቸው ያም ሰው ሊራዳው አብሮ ሔደ ወደ ማሳውም በደረሱ ጊዜ ቆሪል በግመል ላይ መጫን ጀመረ ያም ሰው ሁለተኛውን ገመል ወስዶ ያለ አቅሙ ሸክሙን አክብዶ ጫነው ገመሉም መንቀሳቀስ ተሳነው ሊመታው ፈልጎ በትር አነሣ።ገመሉም "አባቴ ቆሪል ሆይ በላዬ ጉዳት እንዳያደርስ ይህን ሰው አታሰናብተውም እርሱ ያለ ችሎታዬ አሸክሞኛልና" ብሎ በሰው አንደበት ጮኸ ቆሪልም መጥቶ ሸክሙን አቀለለለት ያንንም ሰው "ልጄ ሆይ በማይችለው መጠን ለምን አሸከምከው አንተ የምትአዝነው ልትሸከመው የማትችለውን ሸክም በላይህ ስለ አመጡብህ አይደለምን" አለው። ❤ ወደ ቤትም በገቡ ጊዜ ያ ሰው ስለ ችግሩ የዕቃውን ቦታ ይገለጥለት ዘንድ አባ ቆሪልን ለመነው እርሱም ለሌላ እንዳይናገር ከአማለው በኋላ ገለጠለት እንዲህም አለው "በዚያች ቤተ ክርስቲያን በስተ ምሥራቅ ታናሽ ዋሻ አለ ዕቃውም በዚያ አለ"። ወደ ቤቱም በተመለሰ ጊዜ ለሚስቱ ነገራት በአንድነትም ወደዚያ ቦታ ሔዱ ከነገሥታት መዛግብት እንኳ የሚመስለው የሌለ መዝገብን አገኙ ከዚህም በኋላ ለኤጲስቆጶስ ነገረው ኤጲስቆጶሱም ይጠብቅ ዘንድ ለርሱ ስጠው። ይህም ጻድቅ ሰው ቆሪል ብዙ ተጋድሎን ከተጋደለ በኋላ በመልካም ሽምግልና ዐረፈ። ለእግዚአብሔር

❤ "በስመ አብ  ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤          ❤ #ታኅሣሥ ፳፱ (29) ቀን። ❤ እንኳን #ለጌታችን_ለአምላካችን_ለመድኃኒታችን #ለኢየሱስ_ክርስቶስ ከእናቱ #ከእመቤታች_ከቅድስት_ድንግል_ማርያም_በሥጋ_ለተወለደበት የበዐላት ሁሉ ራስ ለሆነች #ለብርሃነ_ልደቱ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በእዚህች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከኤፍሬም ወገን ከመስፋኑ #ከቅዱስ_ኢያሱ_ልደት፣ #ከከበሩ_ከያዕቆብ_ከፈሊስ ከሌላው ሰማዕት፣ #ከቴዎድሮስ ከመታሰቢያቸው፣ #ከሮሀ_ንጉሥ_ከአቃርዮስ ዕረፍት፣ ሰምኑድ ከሚባል አገር ከሆነ ከገመላዊው #ከቅዱስ_ቆሪል ዕረፍትና #ከአክሚም_ሰማዕታት ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                                                                                                                   ✝️ ✝️ ✝️ ❤ በዚች ቀን የከበረና የተመሰገነ #ታላቅ_የልደት_በዓል_ሆነ_የጌታችንና_የመድኃኒታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ_ከእመቤታችን_ከከበረች_ድንግል_ማርያም_የተወለደባት ዕለት ከበዓላት ሁሉ ተለይታ ከፍ ከፍ ያለች ናት። ❤ የቤተ ክርስቲያን መምህራን አባቶቻችን የከበረ የልደትን በዓል በሁለት ቀኖች ያከብሩ ዘንድ በምክራቸው ተስማሙ ከወደኋላ ባለ በሃያ ስምንት ሌሊቱ የልደት በዓል ነው በሃያ ዘጠኝ መዓልቱ ጳጒሜን ስድስት በሆነ ጊዜ በዚያች ዓመት የልደት በዓል በሃያ ስምንት ከሆነ ግን በሃያ ዘጠኝ ይሆናል ስለዚህ የበዓላት ሁሉ ራስ የሆነ የከበረ የልደት በዓል በሁለት ቀኖች እንዲከበር አዘዙ ወሠኑ። ❤ የበዓላት ራስ ስለሆነ ስለ ከበረ የልደት በዓል የከበረ ወንጌል እንዲህ አለ "በንጉሥ በኄሮድስ ዘመን በይሁዳ ዕፃ በቤተልሔም ጌታ ኢየሱስ በተወለደ ጊዜ እነሆ የፍልስፍና ሰዎች ከምሥራቅ መጥተው ወደ ኢየሩሳሌም ደረሱ። ኮከብን በምሥራቅ አይተን እንሰግድለት ዘንድ መጥተናልና የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ ወዴት ነው እያሉ። እሊህ ፈላስፎች ከበለዓም ወገን ናቸው እነርሱም በከዋክብት የሚፈላሰፉ ናቸው በመጽሐፋቸው በበለዓም መጽሐፍም የአይሁድ ንጉሥ ሊወለድ እንዳለው ተጽፎአል እርሱ በለዓም ከያዕቆብ ኮከብ ይወጣል ከእስራኤልም ንጉሥ ብሎ ነበርና። ❤ ይቅር ባይ እግዚአብሔር በረቀቀ ጥበቡ አለበማቸው በሚያምኑበትም ሳባቸው እነርሱ ከዋክብትን በመጠባበቅ የሚፈላሰፉ ናቸውና ይህንንም ኮከብ ገለጠላቸው በአዩትም ጊዜ ደስ አላቸው መልኩ በብዙ አይነት ልውጥ ነውና። ሕፃን የታቀፈች ድንግል ብላቴናን ይመስላል እርሱም በቀን ይጓዛል በሌሊትም ይሠወራል ከሰውም ሲገናኙ ይሠወርና ሲቆሙ በሌላ አንጻር ይገለጥላቸዋል። ❤ እነርሱም ወደ ኢየሩሳሌም ሲደርሱ ያ ኮከብ ተሠወራቸው እጅግ አዘኑ የሚያድረጉትንም አላወቁም ከዚህም በኋላ ወደ ኢየሩሳሌም ከተማ ገብተው ስለተወለደው ንጉሥ ጠየቁ። የእሊህም ሰዎች ቊጥራቸው ሠላሳ ሽህ ነው ነገሥታቱ ሦስት ናቸው ለእያንዳንዳንዱ ንጉሥ ዐሥር ዐሥር ሺህ ሠራዊት አለው። ንጉሡ ኄሮድስም በሰማ ጊዜ ደነገጠ ኢየሩሳሌምም በመላዋ ከእርሱ ጋር ደነገጠች። የካህናት አለቆችና የሕዝቡን ጸሐፊዎች ሁሉ ሰብስቦ "ክርስቶስ በየት ይወለዳል?" ብሎ ጠየቃቸው። "በይሁዳ ዕፃ በቤተልሔም ነው" አሉት በነቢይ እንዲህ ተብሎ ተጽፏልና። "የኤፍራታ ዕፃ ቤተ ልሔም አንቺም ከይሁዳ ነገሥታት አታንሺም ወገኖቼ እስራኤልን የሚጠብቅ ንጉሥ ካንቺ ይወለዳልና"። ❤ ከዚህም በኋላ  ኄሮድስ ሰብአ ሰገልን በጭልታ ጠርቶ ኮከቡ የታየበትን ዘመን ከነሱ ተረዳ። "ሔዳችሁ የዚያን ሕፃን ነገር እርግጡን መርምሩ ያገኛችሁትም እንደሆነ እኔም መጥቼ እሰግደለት ዘንድ በኔ በኩል ተመልሳችሁ ንገሩኝ" ብሎ ወደ ቤተልሔም ሰደዳቸው የነገራቸውንም ሰምተው ከንጉሡ ሔዱ እነሆ በምሥራቅ ያዩት ኮከብ ወደ ቤተልሔም እስኪያደርሳቸው ይመራቸው ነበር ሕፃኑ ካለበትም ዋሻ ላይ ደርሶ ቆመ። ኮከቡንም ባዩ ጊዜ እጅግ ደስ አላቸው ወደ ቤትም በገቡ ጊዜ ሕፃኑን ከእናቱ ከድንግል ማርያም ጋር አገኙት ወድቀውም ሰገዱለት ሣጥናቸውንም ከፍተው ወርቅ ከርቤ ዕጣን እጅ መንሻ አቀረቡለት። ❤ በእግዚአብሔርም ፈቃድ ዮሴፍ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሕፃኑ ጌታ ኢየሱስ በዚያች ዕለት ወደ ቤተልሔም መጡ ስለዚህም ሰብአ ሰገል አገኙአቸው የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያለ ናዝሬት በሌላ ቦታ አላደገምና ከተወለደም ዕድሜው ሁለት ዓመት ሁኖት ነበር። አምላክ ነውና ስለ መንግሥቱ ወርቅን ገበሩለት ክህነትም ገንዘቡ ነውና ዕጣንን ገበሩለት ማሕያዊ ለሆ ሞቱ ምልክትም ከርቤን ገበሩለት። ወደ ኄሮድስም እንዳይመለሱ በሕልም ነገራቸው በሌላ መንገድም ወደ አገራቸው ተመልሰው ገቡ። አምላክ በሥጋ ስለመገለጡ ዓዋጅ ነጋሪዎችና ሰባኪዎች ሆኑ። ❤ ይችም ዕለት ነቢዩ ኢሳይያስ ትንቢት ስለርሷ የተናገረላት ናት እንዲህ ብሎ "እነሆ ድንግል ፀንሳ ወንድ ልጅን ትወልዳለች ስሙንም አማኑኤል ትለዋለች ትርጓሜውም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ማለት ነው"። ስለዚችም የከበረች ድንግል ነቢይ ሕዝቅኤል እንዲህ ብሎ ትንቢት ተናገረ "እግዚአብሔርም አለኝ ይህች በር ተዘግታ ትኖራለች አትከፈትም የሚገባበትም የለም የእስራኤል ፈጣሪ እግዚአብሔር እንደተዘጋች ይገባባታልና ተዘግታ ትኑር" አለ። ❤ ነቢዩ ዳንኤልም አለ "ሌሊት በራእይ አየሁ እነሆ ታላቁ እንደ ሰው ልጅ በሰማይ ደመና መጣ ዘመኑን ወደ ሚያስረጅ ደረሰ ከፊቱም አቀረቡት የዘላለም አገዛዝ ጌትነት መንግሥት ተሰጠው ሕዝቡና አሕዛቡ ሁሉ መንደር መንድረው የሚኖሩትና ነገዱም ነገሥታቱም ሁሉ ይገዙለታል አገዛዙም የዘላለም አገዛዝ ነው መንግሥቱም የማያልፍ የማይጠፋ ነው። ❤ ዳግመኛም ኢሳይያስ "እግዚአብሔር እንደእኔ የሥጋ መጋረጃ በመጋረድ ተገለጸልኝ" አለ። "አሁኑም ደግሞ አዲስ ሰማይ አዲስ ምድር እሠራ ዘንድ አለኝ" አለ ሁለተኛም "ከዕሴይ ሥር በትር ትወጣለች ከእርሷም ጽጌ አበባ ይወጣል" አለ። ዳግመኛም "ሕፃን ተወልዶልናልና ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና ይኸውም ሥልጣን በጫንቃው የሆነ ክርስቶስ ነው። ስሙም ድንቅ መካር የዘላዓለም አባት የሰላም አለቃ ይባላል" አለ። ❤ ኤርምያስም አለ "እግዚአብሔር እንዲህ አለ ለዳዊት ብርሃንን አወጣለሁ በምድር የቀና ፍርድ ያደርጋል እግዚአብሔር ያመኑበትን ያድናቸዋል"። ኤልሳዕም እንዲህ አለ "እግዚአብሔር ከሰማ ይወርዳል በእስራኤል ልጆች አደባባይም በመመላለስ ለሕዝቡ እውነትን ያስተምራቸዋል ከአብርሃም ልጅነት ልዩ ከሆነች ወገኖቹ በቀር አሕዛብ ሁሉ ይታዘዙለታል"። ናሆም ነቢይም እንዲህ አለ "እግዚአብሔር በእኔ አርአያ ይመጣል ልብሱም እንደ ልብሴ ነው"። ❤ ነቢዩ ኢዩኤልም እንዲህ ተናገረ የእግዚአብሔር ዙፋን የሆነች ብላቴና ድንግልን አየሁ እርሷም እንደ እሳት ያልባት ነበር ስለርሷም ይቺ ማናት ብዬ ኪሩብን ጠየቅሁት ከአዳም ልጆች የተመረጠች የእግዚአብሔር ዙፋን ይች ድንግል ናት በርሷም የተጎሳቈሉ ይድናሉ ለአመነባትም ረድኤትና መጠጊያ ናት። ❤ ዳዊትም በመዝሙሩ እንዲህ አለ "እግዚአብሔር አንተ ልጄ ነህ በተዋሕዶም ወለድኩህ አለኝ። ለምን አሕዛብን ርስት አድርጌ እሰጥሃለሁ ግዛትህም በመላው ዓለም ነው"። ዳግመኛ "አብ አለ ቀዳማዊ ወልድ በኃይል ቀን ከአንተ ጋር ሳለሁ ከአጥብያ ኮከብ በፊት ከሆድ ወለድኩህ እንደ መልከጼዴቅ አንተ የዓለም አገልጋይ ካህን ነህ ብሎ እግዚአብሔር ማለ ከማለም አይፀፀትም"።

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤         ❤ #ታኅሣሥ ፳፰ (28) ቀን። ❤ እንኳን #ለቅዱስ_አማኑኤል_ለልደቱ (ለጌና) መታሰቢያ ዓመታዊ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ #ከእንዴናው_አገር_ሰዎች ከሆኑ በሰማዕትነት ካዐረፉ #ከመቶ_ሃምሳ_ወንዶችና #ከሃያ_አራት_ሴቶች፣ ከአባቶቻች #ከአብርሃም_ከይስሐቅና_ከያዕቆብ ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                                                                                       ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #በዚች_ዕለት_የጌና_በዓል_ሆነ፦ ይኸውም የልደት በዓል ነው”።  ይህም እንዲህ ነው በአምላካችን በረቀቀ ጥበቡ ሰዎች ሁሉ ይቈጠሩ ዘንድ ስማቸውንም ይጻፋና ይመዘገቡ ዘንድ ከንጉሥ ቄሣር ትእዛዝ መጣ። ስለዚህም ከእመቤታችን ከከበረች ድንግል ማርያም ጋር ሊቆጠር ዮሴፍ ከናዝሬት ወደ ቤተልሔም የርሱንና የቡርክት ድንግል ማርያምን ስም ሊስመዘግብ ወጣ እርሱ ከይሁዳ ነገድ ከዳዊት ወገን ነውና ቤተልሔምሜ የዳዊት ቦታው ናትና። ❤ የከበረ ወንጌል እንደተናገረ ከዚህም በኋላ ከዚያ ሳሉ የምትወልድበት ቀን ደረሰ የበኵር ልጇንም ወለደች አውራ ጣቱንም አሠረችው በጨርቅም ጠቅልላ በበረት አስተኛችው ለማደሪያቸውም ቦታ አልነበራቸውምና። በዚያ ሰፈር እረኞች ነበሩ ሌሊትም በየተራቸው ተግተው መንጋቸውን ይጠብቁ ነበር። እነሆ የእግዚአብሔር መልአክ አጠገባቸው ቆመ የእግዚአብሔርም ብርሃን በላያቸው በራ ታላቅ ፍርሀትም ፈሩ መልአኩም "ለእናንተና ለመላው ዓለም ደስታ የሚሆን ታላቅ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ" አላቸው። ❤ "እነሆ ዛሬ በዳዊት አገር መድኅን የሆነ ጌታ ክርስቶስ ተወልዶላችኋልና። ለእናንተም ምልክት እንዲህ ነው ሕፃኑ አውራ ጣቱን ታሥሮ በጨርቅ ተጠቅልሎ በበረት ውስጥ ተኝቶ ታገኙታላችሁ" አላቸው። ድንገትም ከዚያ መልአክ ጋር ብዙ የሰማይ ሠራዊት እግዚአብሔርን እያመሰገኑ "በሰማይ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን በምድርም ሰላም በሰው በጎ ፈቃድ እያለ መጡ። ❤ ከዚህም በኋላ መላእክት ከእነርሱ ዘንድ ባረጉ ጊዜ እነዚህ እረኞች ሰዎች እርስበርሳቸው "ኑ ወደ ቤተ ልሔም ሔደን ይህን እግዚአብሔር የገለጠውንን ነገር እንወቅ" አሉ። ፈጥነውም ሔዱ ማርያምንና ዮሴፍን ሕፃኑንም በበረት ውስጥ ተኝተ አገኟቸው። አይተውም የነገሩዋቸው ስለዚህ ሕፃን እንደሆነ አወቁ እረኞች የነገሩዋቸውን የሰሙ ሁሉ አደነቁ። እረኞችም ለሕፃኑ ሰግደው እግዚአብሔርን እያመሰገኑ ወደ ቦታቸውም ተመለሱ። ከወገኖችን ሰው ሁኖ ለጐበኘንና ይቅር ላለን እግዚአብሔር ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የታኅሣሥ 28 ስንክሳር።                          ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #ከእንዴናው_አገር_ሰዎች_የሆኑ #መቶ_ሃምሳ_ወንዶች_ሃያ_አራት_ሴቶች_በሰማዕትነት፦ እሊህም ቀድሞ ከሀዲያን ነበሩ የእንዴናው መኰንን የከበረ ሶርያዊ ጳውሎስን በሚያሠቃየው ጊዜ ከዚያ ነበሩ ሲአሠቃየውም ይመለከቱ ነበር መኰንኑም ችንካሮችን በእሳት አግለው ዐይኖቹን እንዲአወልቁ አዘዘ። ይህንንም ባደረጉበት ጊዜ ዐይኖቹ ወለቁ ከወህኒ ቤትም ጣሉት። በማግሥቱም እሊህ ሰዎች ሊያዩት በሔዱ ጊዜ ያለ ምንም ጉዳት ድኖ ጤነኛ ሁኖ አገኙት የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አድኖታልና ። ❤ ይህንንም ድንቅ ተአምር አይተው እጅግ አደነቁ ጣዖቶቻቸውም ምንም መሥራት እንደማይችሉ አስተዋሉ። የክርስቲያኖች አምላክ እርሱ እውነተኛ አምላክ እንደ ሆነ አወቁ ወደከበረ ጳውሎስ ሒደው ሰገዱለት እንዲጸልይላቸውም ለመኑት እርሱም ባረካቸው እግዚአብሔር እምነታችሁን ተቀብሎ ከሰማዕታት ጋር ይቊጠራችሁ አላቸው ። ❤ ከዚህም በኋላ ወደ መኰንኑ ቀርበው በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመኑ መኰንኑም ራሶቻቸውን ቊረጡ ብሎ አዘዘና ቈረጧቸው በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበሉ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በሰማዕታት ጸሎት ይማረን ለዘላለሙ አሜን።                           ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ምስሌከ ቀዳማዊ በዕለ ኃይል። ወብርሃኖሙ ለቅዱሳን። ወለድኩከ እምከርሥ እምቅድመ ኮከበ ጽባሕ"። መዝ109፥3።የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 1፥26-57።                            ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "የሐዩ ወይሁብዎ እምወርቅ ዓረብ። ወዘልፈ ይጼልዩ በእንቲአሁ። ወኵሎ አሚረ ይድኅርዎ"። መዝ 71፥15። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 8፥3-18፣ 1ኛ ዮሐ 4፥1-9 የሐዋ ሥራ 3፥22-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ማቴ1፥1-18። የሚቀደሰው ቅዳሴ የእመቤታችን የማርያም ቅዳሴ ነው። መልካም የቅዱስ አማኑኤል በዓልና የገሐድ ጾም። ለሁላችንም ይሁንልን።               

❤ "በስመ አብ  ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤          ❤ #ታኅሣሥ ፳፯ (27) ቀን። ❤ እንኳን #ለኤጲስ_ቆጶስ_ለአባ_አብሳዴ ለዕረፍት በዓልና #ለቸሩ_መድኃኔዓለም_ለስቅለቱ_መታሰቢያ ወራዊ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ #ከአባ_ፊልጶስና ከሰማዕታት ፍጻሜ ከሆነ #ከኖላዊ ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                                                                                ✝ ✝ ✝ ❤ #አባ_አብሳዲና_አባ_አላኒቆስ፦ ያን ጊዜ ታላላቆች የሆኑ የላይኛው ግብጽ ኤጲስቆጶሳት አባ አብሳዲና አባ አላኒቆስ የክብር ባለቤት የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሆነች በቀናች ሃይማኖት ሕዝቡን እንደሚያጸኑአቸው የአማልክትንም አምልኮ እንደሚሽሩ ዜናቸውን ዲዮቅልጥያኖስ በሰማ ጊዜ መልክተኞችን ልኮ ወደርሱ አስመጥቶ ታላቅ ሥቃይን አሠቃያቸው። የከበረ አባ አብሳዲ ግን አንዲት ቀን እንዲታገሡት መልክተኞችን ለመናቸውና የቊርባን መሥዋዕትን አዘጋጅቶ ቅዳሴ ቀድሶ ለሕዝቡ ሥጋውንና ደሙን አቀበላቸው። በቀናች ሃይማኖትም እንዲጸኑ አስተማራቸው ከዚህም በኋላ በሰላምታ ተሰናብቷቸው ከእርሳቸው ዘንድ ወጣ ሰውነቱንም በእግዚአብሔር ላይ ጥሎ ከመልክተኞች ጋር ሔደ ወደ እንዴናው ገዥ ወደ አርያኖስ ወሰዱት። ❤ መኰንኑም የአባ አብሳዲን ገጽ በአየ ጊዜ ከአርያውና ከግርማው የተነሣ አደነቀ ራራለትም እንዲህም አለው "አንተ የከበርክና የምታስፈራ ሰው ለነፍስህ እዘን የንጉሥንም ቃል ስማ"። አባ አብሳዲም እንዲህ ብሎ መለሰ "እኔ የንጉሥን ቃል ሰምቼ በዚህ በኃላፊው ዓለም ሕይወት መንግሥት ሰማያትን አልለውጥም" በመካከላቸውም ብዙ የነገር ምልልስ ሆነ ከበጎ ምክሪ ባልተመለሰ ጊዜ በመንኰራኵር ያሠቃዩትና ከእሳት ማንደጃ ውስጥም ይጨምሩት ዘንድ መኰንኑ አዘዘ ይህን ሁሉ ታገሠ እግዚአብሔርም ያለ ጉዳት በጤና አስነሣው። ❤ ከዚህም በኋላ ራሱን ይቆርጡት ዘንድ አዘዘ አባ አብሳዲም ሰምቶ ደስ አለው ልብሰ ተክህኖ ለብሶ እጆቹንም ዘርግቶ አንገቱን ለሰይፍ ሰጠ የከበረች ራሱንም ቆረጡት የሰማዕትነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ አብሳዲ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የታኅሣሥ 27 ስንክሳር።                                                    ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "መላእክትኒ ተጋብኡ ምስሌሆሙ ኅብረ። ላዕለ እግዚአብሔር ወላዕለ መሲሑ። ንበትክ እምኔነ ማዕሠሪሆሙ"። መዝ 2፥2-3። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 16፥21-ፍ.ም።                              ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "አንሥእ ኃይለከ ወነዓ አድኅነነ። አምላክ ኃያላን ሚጠነ። አብርህ ገጸከ ላዕሌነ ወንድኃን"። መዝ 79፥2-3። የሚነበቡት መልዕክታት 16፥16-ፍ.ም፣ 1ኛ ጴጥ 2፥21-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 20፥28-31። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 10፥17-22። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ቅዳሴ ነው። መልካም የአቡነ በግዑ የዕረፍት በዓልና የነቢያት (የገና) ለሁላችንም ይሁንልን።           

❤ "በስመ አብ  ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤          ❤ #ታኅሣሥ ፳፮ (26) ቀን። ❤ እንኳን #ከሮሜ_አገር_ለሆነች_ለከበረች_ለቅድስት_አንስጣስያ ሰማዕትነት ለተቀበለችበት ለዕረፍቷ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከከበረች ከሰማዕት #ከቅድስት_ዮልያና ከመታሰቢያዋና #ከጻድቁ_ከቅዱስ_አቦሊ ከመታሰቢያው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #ቅድስት_አንስጣስያ፦ የዚችም ቅድስት አባቷ ጣዖትን የሚያመልክ ነው እናቷ ግን ክርስቲያን ናት ይቺንም ቅድስት በወለደቻት ጊዜ አባቷ ሳያውቅ የክርስትና ጥምቀትን በሥውር አጠመቀቻት አውቆ ቢሆን ማጥመቅ ባልተቻላትም ነበር። ከዚህም በኋላ በበጎ አስተዳደግ አሳደገቻት በቀናች ሃይማኖት እስከ አጸናቻት ድረስ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት አስተማረቻት ጠባይዋን መለወጥ ለማንም አልተቻለውም። ❤ አድጋም አካለ መጠን በአደረሰችም ጊዜ አባቷ እንደርሱ ላለ ከሀዲ ሰው አጋባት እርሷ ግን እጅግ ጠላችው ልትገናኘውም አልፈለገችም በሴቶች ላይ በሚሆነው ግዳጅና አንዳንድ ጊዜም በደዌ የምታመካኝ ሆነች እንዲጠላትና ከእርሷ እንዲለይ ያደፈና የቆሸሸ የተጐሳቈለ ልብስ ትለብስ ነበር። ባሏም ወደ ሥራው ወጥቶ በተሰማራ ጊዜ እርሷም ስለ ቀናች ሃይማኖት የታሠሩ እስረኞችን ትጐበኝ ዘንድ ትሰማራለች ታገለግላቸውና የሚሹትን ትሰጣቸዋለች። ባሏም ይህን የምትሠራውን በአወቀ ጊዜ ወደ ውጭ እንዳትወጣ በቤት ውስጥ ዘጋባት እርሷም ከእጁ ያወጣት ዘንድ አዘውትራ በመረረ ልቅሶ ወደ እግዚአብሔር የምትለምን ሆነች ጌታችንም ልመናዋን ሰምቶ ያንን ሰው አጠፋው። እርሷም በሞቱ ደስ አላት ከዚህም በኋላ ለድኆችና ለምስኪኖች ስለ ቀናች ሃይማኖትም በመታመን ለታሠሩ እሥረኞች ገንዘቧን ሁሉ ሰጠች። ❤ የሮሜ አገር ገዢም ዜናዋን በሰማ ጊዜ መልእክተኞችን ልኮ ወደርሱ አስመጣት ስለ ሃይማኖቷም ጠየቃት ክርስቲያን እንደሆነች በፊቱ ታመነች ቃል ኪዳን በመግባትም ተናገራት ከበጎ ምክርዋ አውጥቶ ወደ ክህደት ሊያዘነብላት አልቻለም። በዚያንም ጊዜ በብዙ በተለያየ ሥቃይ አሠቃያት። ❤ ከዚህም በኋላ ወደ ባሕር ያሠጥሟት ዘንድ አዘዘ ባሕሩም በሕይወቷ ተፋት ዳግመኛም በአራት ካስማ መካከል አስተኝተው ዘርግተው አሥረው ታላቅና ጽኑዕ የሆነ ግርፋትን ይገርፋዋት ዘንድ አዘዘ መኰንኑም እንዳዘዘ አደረጉባት ግን ምንም ምን ጉዳት አልደረሰባትም። ከዚህም በኋላ ወደ አዘጋጁላት የእሳት ማንደጃ ውስጥ ይጨምርዋት ዘንድ አዘዘ በጨመርዋትም ጊዜ ነፍሷን በእግዚአብሔር እጅ ሰጠች በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊል ተቀበለች። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅድስት አንስጣስያ ጸሎት ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋር ይኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የታኅሣሥ  26 ስንክሳር።                             ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_ለአንስጣስያ_ጣዖታ_አቡሃ_መኒና። እንተ ተለወት ፍጹመ ሃይማኖተ እማ ክርስትና። እስከ መኰንን ዕልው በዋዕየ እሳት አርሰና። ወሰላም ካዕበ #ለብፅዕት_ዮልያና። ዘተሳተፈት ክብረ ሰማዕት አሐደ ከዊና"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የታኅሣሥ_26።                 

❤ "በስመ አብ  ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤          ❤ #ታኅሣሥ ፳፮ (26) ቀን። ❤ እንኳን #ለታላቁ_አባት_ለሐዲስ_ሐዋርያ ለኢትዮጵያ ብርሃኗ ለሆኑት #ለአቡነ_ተክለሃይማኖት #በተወለዱ_በሦስት_ቀናቸው_ቅድስት_ሥላሴ ላመሰገኑበት ዓመታዊ ክብረ በዐል እግዚአብሔር በሰላምና በጤና አደረሰን። በዐሉ የታላቁ ገዳም የደብረ ሊባኖስ አባቶችን ወደ ኢቲሳ ደብረ ጽላሽ ወርደው በየዓመቱ በታላቅ ድምቀት ይከበራል።                           ✝ ✝ ✝ ❤ #አባታችን_አቡነ_ተክለ_ሃይማኖት በተወለዱ በሦስተኛው ቀን ቅድስት ሥላሴ እንዳመሰገኑ፦ ...   "ይህም እግዚአብሔር የመረጠው ልጅ በተወለደ በሦስተኛው ቀን ይህችውም የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤው ቀን በዕለተ ሰንበት ማለት ነው። ከቀኑ በሦስት ሰዓት ይህ ብላቴና እጆቹን አንሥቶ ወደ ሰማይ ተመልክቶ እግዚአብሔርን በማመስገን እንዲህ ብሎ አሰምቶ ተናገረ "ከወልድ ከመንፈስ ቅዱስ ጋራ በባሕርይ በህልውና አንድ የሚሆን አብ በአካል በስም ልዩ ነው። ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በባህሪይ በሕልውና አንድ የሚሆን ወልድ በአካል በስም ልዩ ነው። ከአብ ከወልድ ጋር በባህርይ በሕልውና አንድ የሚሆን መንፈስ ቅዱስ በአካል በስም ልዩ ነው ብሎ አመሰገነ። ❤ በሦስት ሰዓት በቅዳሴ ጊዜ መንፈስ ቅዱስ ወደ ወደደበት ስለሚወርድ ሕፃኑም መንፈስ ቅዱስ ሲወርድ አይቶ እሱ እንዳስተማረው ለፈጣሪው እየተገዛ ይህን ሦስት የምስጋና ቃል አቀረበ። እናቱም ከተመረጠ ልጇ ይህን ልዩ ምስጋና ሰምታ በልቡናዋ እያደነቀች "ልጄ ፍሥሐ ጽዮን ምን ትላለህ ይህ ቃል የአባትህ ሥራ ነው። ላንተ ግን የሚገባህ ጡት መጥባት ነውና"። ባሏ ጸጋ ዘአብ ተመልሶ ወደ ቤቱ በገባ ጊዜ ልጁ የተናገረውን ነገር ሁሉ ነገረች። ጸጋ ዘአብም ነገሩን ሰምቶ አደነቀና "ልጄ እግዚአብሔር ያሳድግህ ብዙ ዘመን ያኑርህ። በቤተ እግዚአብሔርም እንዲህ እያልክ ስትቀድስ አይህ ዘንድ እመኛለሁ" አለ። ❤ ይህንም ብላቴና መላእክት ክንፋቸውን እየጋረዱ ዘወትር ይመግቡታል። እርሱም ክንፋቸውን ሲጋርዱት ባያቸው ጊዜ ከእነሱ ጋራ ይጫወት ነበር። ሁል ጊዜ ይስቅ ነበር እንጂ ሕፃናት እንደ ሚያለቅሱ አያለቅስም ነበር ቅኖች ሰዎች ዘወትር ደስ ይላችዋልና። ምንጭ፦ ገድለ አቡነ ተክለ ሃይማኖት።                

❤ "በስመ አብ  ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ እንኳን #ለጌታችን_ለአምላካችን_ለመድኃኒታችን_ለኢየሱስ_ክርስቶስ ለንዑስ በዓል ለአንዱ #ለኖላዊ  መታሰቢያ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                           ✝ ✝ ✝ ❤ የዚህ ሳምንት መዝሙር፦ ሃሌ ሃሌ ሉያ በ፪ "#ኖላዊ_ዘመጽአ_ውስተ_ዓለም ወልዱ ወቃሉ #ለእግዚአብሔር፤ ዘወረደ እምላዕሉ በአቅሙ #ክርስቶስ፤ እስመ ውእቱ #እግዚአ_ለሰንበት፤ ይቤሎ #አብ_ለወልዱ_ወልድየ_ንበር_በየማንየ። ትርጉም፦ ወደ ዓለም የመጣው #እረኛ_የእግዚአብሔር_አብ ቃሉና ልጁ ነው ከላይ የወረደውም #ክርስቶስ ተብሎ ይጠራ ዘንድ ነው። (ፍጹመ አካል ፍጹመ ክብር ነው) #የሰንበት_ጌታ እሱ ነውና #አብ_ልጁን_ልጄ_በቀኜ_ተቀመጥ_አለው። #ሊቁ_ቅዱስ_ያሬድ_በድጓው_ላይ።                                        ❤ " #ኖላዊ_ኄር " ❤ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ታኅሣሥ 21 ይህችን ዕለት "ኖላዊ ሔር" ብላ ታከብራለች። ይሕንንም ለሳምንት ያህል ታዘክራለች (ከታኅሣሥ 21-27)። በነዚህ ቀናች እሑድ የዋለበት ቀን ማኅሌት ተቆሞ ኖላዊ ተብሎ ይከበራል። መሠረታዊ መነሻዋም (ዮሐ. 10፥1) ነው። "ኖላዊ" ማለት በቁሙ "እረኛ" ማለት ሲሆን "ሔር" ደግሞ "ቸር-ርሕሩሕ-አዛኝ" እንደ ማለት ነው። ❤ ገጥመን ብንተረጉመው ደግሞ "ቸር እረኛ" የሚል ትርጉምን ይሰጠናል። ከአባታችን አዳም ስህተት በኋላ ተፈጥረው ከነበሩ ችግሮች አንዱ ቸር እረኛ ማጣት ነው። እግዚአብሔር አዳምን ፈጥሮ። ቸር እረኛ ሆኖ በገነት አሰማርቶት ነበር። ❤ ኤዶም ገነት የለመለመች። ፈሳሾች የሞሉባት መልካም መስክ ናትና። አባታችን ቅዱስ አዳም ደግሞ እንደ አቅሙ የጸጋ እረኝነት ተሰጥቶት ነበር። ድቀት ካገኘው በሁዋላ ግን ከነፍስ እረኛው ጋር ተጣልቶ ከመልካሟ መስክ ገነት ወጣ። ❤ እርሷንና የነፍሱን እረኛ ሲሻም አለቀሰ። ተስፋ ድኅነት ሲሰጠውም ለልጆቹ ነገራቸው። ከዚያም በመንጋው ላይ በአዳም ሴት ተተካ። ከሴ፣ ኄኖስ፣ ከኄኖስ፣ ቃይናን . . . እያለ ከኖኅ ደረሰ። ❤ ከኖኅም በሴም ከአብርሃም፣ ከአብርሃምም በይስሐቅና በያዕቆብ ወርዶ ከሙሴ ደረሰ። ከሙሴም በኢያሱ አልፎ ከነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊት ደረሰ። እነዚህ ሁሉ እረኞች ምንም እንኩዋ ለእግዚአብሔር ሕዝብ በትጋት ቢሠሩም ሕዝቡን ከሲዖል ማዳን አልቻሉም። ❤ ከሲዖል የሚያድን የነፍስ እረኛ ነውና ያን ጊዜ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት የራሱን የአባቶቹንና የልጆቹን ጩኸት ባንድ አድርጐ ጮኸላቸው። "ኖላዊሆሙ ለእሥራኤል አጽምዕ - የእሥራኤል እረኛ ሆይ ስማን!" አለ። (መዝ. 79:1) ❤ ጩኸቱም ቅድመ እግዚአብሔር ደረሰ። ይህንን የሰማ ጌታም በጊዜው ከድንግል ማርያም ተወለደ። በየጥቂቱ አድጐ ቸር እረኝነቱን ገለጠ። መድኃኒታችን እንዳስተማረን እርሱ ቸር እረኛ ነው። ❤ ከእርሱ በፊት የተነሱት ቴዎዳስ ዘግብጽና ይሁዳ ዘገሊላ (ሐዋ. 5፥36, ዮሐ. 10፥8) ሐሰተኛ እረኞች ነበሩ። እርሱ ግን እውነተኛው የበጐች በር ነውና (ዮሐ 10፥7) በእርሱ የሚገቡ ሁሉ የዘለዓለም ሕይወትን ያገኛሉ። ❤ እርሱ እውነተኛ እረኛ ነውና (ዮሐ 10፥11) ለመንጋው ራሱን አሳልፎ ይሰጣል። በእሥራኤል ባሕል እረኞች ከፊት መንጋው (በጐቹ) ከኋላ ሆነው ይሔዳሉና ገዳይ ቢመጣ መጀመሪያ የሚገድለው እረኛውን ነው። ❤ መድኃኒታችን ክርስቶስ በሞቱ ሕይወትን፤ በመራቆቱ የጸጋ ልብስን፤ በውርደቱ ክብርን: በድካሙ ኃይልን ይሰጠን ዘንድ ስለ እኛ ራሱን አሳልፎ ሰጠ። የማይሞት ንጉሥ ስለ መንጋው ሞተ። ሰማይን ከነግሡ ምድርንም ከነልብሱ የፈጠረ ጌታ (ዘፍ 1፥1, ዮሐ. 1፥2) ስለ በጐቹ ይህንን ሁሉ ታግሦ ከሲዖል አዳነን። ❤ በሚያርግ ጊዜም በእርሱ ፈንታ ባለ ሙሉ ስልጣን እረኞችን፤ ሐዋርያትን (ዮሐ 21፥15) ሊቃነ ዻዻሳትን (ሐዋ 20፥28) ካህናትን (ማቴ 18፥18) ሾመልን። እነርሱን እረኞች አሰኝቶ እርሱ "ሊቀ ኖሎት-የእረኞች አለቃ" ተባለ። እነርሱም እስከ ዓለም ፍጻም የክርስቶስን መንጋ ሊጠብቁ ስልጣኑም፤ ኃላፊነቱም አለባቸው። (ማቴ 28፥19) ምንጭ፦ ከዲያቆን ዮርዳኖስ አበበ ፔጅ።                              ✝ ✝ ✝ ❤ #የዚህ_ሳምንት_ምስባክ፦ "ኖላዊሆሙ ለእስራኤል አጽምዕ። ዘይርዕዮሙ ከመ አባግዐ ዮሴፍ። ዘይነብር ላዕለ ኪሩቤል አስተርአየ"። መዝ 79፥1። የሚነበቡት መልዕክታት ዕብ 13፥16-ፍ.ም፣ 1ኛ ጴጥ 2፥21-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 11፥22-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 10፥1-22። የሚቀደሰው ቅዳሴ ቅዳሴ እግዚእነ ነው። መልካም የኖላዊ በዓል፣ ዕለተ ሰንበትና የነቢያት (የገና) የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።               

የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ ስም በጠራ ጊዜና በንጽሕና ሆኖ የክርስቶስ ሥጋና ደምን በሚቀበል ሰው ላይ ለማደር ሥልጣን የለኝም" አለው፡፡ ከዚህም በኋላ የሚያስትበትን ሁሉ በዝርዝር ነገረው፡፡ ሊቀ ጳጳሳትን፣ ጳጳሳትን፣ መነኮሳትን፣ መእመናንን፣ ባለትዳሮችን፣ አዛውንቶችን፣ ወጣቶችና ሕፃናትን…ሁሉንም ነገር እያንዳንዱን በምን በምን እንደሚያስት ሁሉንም ነገር በዝርዝር ነገረው፡፡ ወዲያውም የሰይጣን መልኩ ተለውጦ እንደ እሳት ነበልባል ሲሆን አባ ጳውሊ ተመልክቶ እጅግ ደነገጠ፡፡ በዚያም ቅጽበት የታዘዘ መልአክ መጥቶ አባ ጳውሊን አበረታው፡፡ ❤ በዚያችም ሌሊት መቅሰፍት ወርዶ በዝሙት ቤት ያሉትን አጠፋቸው፡፡ ከ5 ወንዶችና ከ5 ሴቶች በቀር የተረፈ የለም፡፡ አባ ጳውሊም "ይህን ለምን ታደርጋላችሁ?" ቢላቸው "በየወሩ አንዲት ቀን ወደ ውሽባ ቤት እየገባን በሩን ዘግተን መብራት አጥፍተን ከእጃችን የገባችዋን ሴት ይዘን አንተኛለን" አሉት፡፡ "ከእናንተ ውስጥ እኅቱን ወይም ልጁን እንዴት ያውቃል?" አላቸው፡፡ "እንደ እንስሳ በመሆን እንጃ ማወቅ የለም" አሉት፡፡ ከዚህም በኋላ አባታችን የክርስቶስን ወንጌል ሰበከላቸውና አሳምኖ አጠመቃቸው፡፡ ሥጋ ወደሙንም አቀበላቸው፡፡ በሃይማኖት ካጸናቸው በኋላ ወደ በዓቱ ተመልሶ ገድሉን ፈጽሞ ታኅሣሥ 24 ቀን በሰላም ዐረፈ፡፡ ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ጳውለመ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                              ✝ ✝ ✝ ❤ #አባ_ፊሎንጎስ፡- ይኽም ቅዱስ አስቀድሞ ሚስት አግብቶ አንዲት ልጅ ወለደ፡፡ ከዚህም በኋላ ሚስቱ ሞተች፡፡ እርሱም ከዚህ በኋላ የምንኩስና ልብስ ለብሶ ታላቅ ተጋድሎን እየተጋደለ ኖረ፡፡ ስለ መልካም ተጋድሎውትና ስለ ትሩፋቱ በአገልግሎትም ስለመጠመዱ በአንጾኪያ አገር ላይ ሊቀ ጳጳሳት እንዲሆን እግዚአብሔር መረጠው፡፡ በተሾመም ጊዜ የክርስቶስን መንጋዮች ምእመናንን በመልካም አጠባበቅ ጠበቃቸው፡፡ ከአርዮሳውያን ከመቅዶንዮስና ከሰባልዮስ ነጣቂ ተኩላዎች በሚገባ ጠበቃቸው፡፡ በሊቀ ጵጵስናውም የሹመት ወቅት አኗኗሩን እንደ መላእክት አደረገ፡፡ መልካም የሆነ ገድሉንም ፈጽሞ በዚህች ዕለት በሰላም ዐረፈ፡፡ ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የታኅሣሥ24 ስንክሳር።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "አድኅነኒ እምደም እግዚአብሔር አምላክ መድኃኒትየ። ይትፌሣሕ ልሳንየ በጽድቀ ዚአከ እግዚኦ። ትከሥት ከናፍርየ ወአፉየ ያየድዓ ስብሓቲከ። መዝ50፥14-15። የሚነበበው ወንጌል ማቴ11፥25-ፍ.ም።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "እምአፈ ደቂቅ ወሕፃናት አስተዳሎከ ስብሐተ። በእንተ ጸላኢ። ከመ ትንሥቶ ለጸላኢ ወለገፋዒ"። መዝ 8፥2። የሚነበቡት መልዕክታት ኤፌ 4፥11-17፣ 1ኛ ጴጥ 1፥13-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 19፥11-21። የሚነበበው ወንጌል ማቴ18፥1-12። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱሳን ሐዋርያት ቅዳሴ ነው። መልካም የአቡነ ተክለ ሃይማኖት የልደት በዓል፣ የቅዱስ አግናጥዮስ ምጥው ለአንበሳ የዕረፍቱና የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።              

❤ በዚያንም ጊዜ ንጉሥ ተቆጣ ከሥጋው ምንም ምን ሳያስቀሩ ይበሉት ዘንድ ሁለት የተራቡ አንበሶችን በላዩ እንዲሰዱ አዘዘ። የከበረ አግናጥዮስም አንበሶች ወደርሱ ሲቀርቡ በአያቸው ጊዜ ድምፁን ከፍ አድርጎ ሕዝብን እንዲህ አላቸው "ከዚህ የተሰበሰባችሁ እናንተ የሮሜ ሰዎች ቃሌን ስሙ እወቁም እኔ ይህን ሥቃይ የታገሥኩት በትዕቢትና በትምክህት አይደለም የክብር ባለቤት በሆነ በጌታዬና በፈጣሪዬ ኢየሱስ ክርስቶስ  ፍቅር እንጂ። አሁንም እኒህ አንበሶች እንደ ሥንዴ ይፈጩኝ ዘንድ ነፍሴ ወደደች የክብር ባለቤት ወደ ሆነ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ልትሔድ ነፍሴ ሽታለችና"። ❤ ንጉሡም ቃሉን ሰምቶ አደነቀ ድንጋጠረም አድሮበት እንዲህ አለ "የክርስቲያኖች ትዕግሥታቸው ምን ይብዛ ስለ አምልኮት ከአረማውያን በእንዲህ ያለ ሥቃይ ላይ የሚታገሥ ማን ነው" አለ። እነዚያ አንበሶችም ወደ ቅዱሱ ቀረብ ብለው ደንግጠው ቆሙ። ከዚህም በኋላ አንዱ አንበሳ እጁን ዘርግቶ አንገቱን ያዘው በዚያንም ጊዜ ደስ ብሎት ነፍሱን በፈጣሪው ክርስቶስ እጅ ሰጠ ልመናውንም ፈጸመለት። ❤ ለእነዚያ አንበሶችም ሥጋውን ይዳስሡት ዘንድ አልተቻላቸውም የክብር ባለቤት ክርስቶስ ዳግመኛ እስከ ሚመጣ የተጠበቀ ሆነ እንጂ ከዚህም በኋላ በክብር በምስጋና ከከተማ ውጭ ቀበሩት እንደዚህም በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም በመልካም ተጋድሎ ምስክርነቱን ፈጸመ ለምእመናንም ጠቃሚ ይሆን ዘንድ ገድሉን ጻፉ የበዓሉንም መታሰቢያ አደረጉለት። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ሐዋርያ በቅዱስ አግናጥዮስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #የአሚናዳብ_ልጅ_ቅድስት_አስቴር፡- የአይሁድ ወገን የሚሆን ስሙ መርዶክዮስ የሚባል የኢያኤሩ ልጅ ከብንያም ወገን የተወለደ የቄስዩ ልጅ አንድ ሰው በሱሳ አገር ነበረ፡፡ ከኢሩሳሌምም በባቢሎን ንጉሥ በናቡከደነጾር እጅ የተማረከ ነው፡፡ ያሳደጋት ልጅ ነበረችው፡፡ እርሷም የአባቱ ወንድም የአሚናዳብ ልጅ አስቴር ናት፡፡ ከዘመዶቿ ተለይታ በወጣች ጊዜ ልጅ ትሆነው ዘንድ አሳደጋት፡፡ እርሷም እጅግ መልከ መልካም ነበረች፡፡ በአንዲትም ዕለት ንጉሥ አርጢክስስ ብዙ ተድላ ደስታ አድርጎ መኳንንቶቹን ሁሉ ጠራ፡፡ የመኳንንቶቹንም አለቃ አማሌቃዊውን ሐማንንም ጠራው፡፡ እርሱ ከሁሉም መኳንንት የከበረ ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ ንጉሥ 7ቱን ባለሟሎቹን ጠርቶ ንግሥቲቱን አስጢንን አምጥተው የእቴጌነት ዘውድ ያቀዳጇት ዘንድ እርሷ መልከ መልካም ናትና ለአሕዛብም አለቆች ሁሉ መልኳንና ውበቷን ያሳዩ ዘንድ አዘዛቸው፡፡ ንግሥቲቱ አስጢን ግን የንጉሡን ትእዛዝ ባለመቀበል እምቢ አለች፡፡ ከባለሟሎቿም ጋር ትመጣ ዘንድ ባለወደደች ጊዜ ንጉሡ እጅግ ተናዶ ከንግሥትነቷ ሻራት፡፡ ከዚህም በኋላ 127 ከሚሆኑ ከሚገዘቸው አገሮች አንድ ሺህ ቆነጃጅቶችን ይመርጡለት ዘንድ ንጉሡ አዘዘ፡፡ ከሺህ መቶ፣ ከመቶ ዓሥር፣ ከዓሥር ሦስት መረጡ፡፡ ከሁሉም በመልክ፣ በውበት፣ በደም ግባትም አንደኛ ሆና አስቴር ተመረጠች፡፡ ንጉሡም አስቴርን አነገሣት፡፡        ❤ ንጉሡም አስቴርን እጅግ አድርጎ ወደዳት፣ በሴቶቹም ሁሉ ላይ የበላይ አድርጎ ሾማት፡፡ ከዚህም አስቀድሞ መርዶክዮስ አገሩንና አደባባዩን ከሚጠብቁት ከንጉሡ ባለሟሎች ጋር በአደባባይ ኖረ፡፡ እነርሱም ስማቸው ታራ እና ገቦታ ይባላል፡፡ እርሱም እነዚህ ሁለቱ በንጉሡ ላይ ያሰቡትን ተንኮላቸውን ሰማ፡፡ ንጉሥ አርጤክስስን ይገድሉት ዘንድ ወንጀልን እንዳዘጋጁ ባወቀ ጊዜ መርዶክዮስ ሄዶ ለንጉሡ ነገረው፡፡ ንጉሡም ነገራቸውን መርምሮ ቀጣቸውና ይህን ነገር ታሪክና ወግ በሚጻፍበት ላይ ጻፈው፡፡ ሐማ ግን አማሌቃዊ ነበረና መርዶክዮስንና እስራኤላውያንን ይጠላቸው እጅግ ነበርና የአይሁድን ወገን ሁሉ ለማጥፋት ተነሣ፡፡ መርዶክዮስም ይህንን በሰማ ጊዜ ልብሱን ቀዶ ማቅ ለበሰ፡፡ መርዶክዮስም የሀዘኑን መርዶ ለአስቴር እንዲደርሳት አደረገ፡፡ አስቴርም "እስከ ሦስት ቀን ጹሙ ጸልዩ እኔም ደንገጡሮቼም እንጾማለን" ብላ ላከችለት፡፡ ሱባኤዋንም እንደጨረሰች የማቅ ልብሷን አውልቃ ጥላ ወደ ንጉሡ አዳራሽ በገባች ጊዜ "እስከ መንግሥቴም እኩሌታ ቢሆን እሰጥሻለሁና የሆንሽውን ንገሪኝ" አላት፡፡ በዓልንም አደረገና ሐማንና መኳንንቱን ሁሉ ጠራ፡፡ በበዓሉም ላይ ድጋሚ "ላደርግልሽ ፈቅጂውን ንገሪኝ" አላት፡፡ ❤ ንጉሡም ለመርዶክዮስ ውለታ ያደረገለትን ሲያስብ ምንም እንዳላደረገለት ዐወቀ፡፡ ወዲያውም ሐማ መርዶክዮስን በመስቀል ላይ ሰቅሎ ሊገድለው እንደሆነ ተነገረ፡፡ ንጉሡም ሐማን "ንጉሥ የወደደውን ሰው ምን ያደርግለት ዘንድ ይገባል?" አለው፡፡ ሐማም "ይህስ ለእኔ ነው" ብሎ "በክብር ይሾም ዘንድ ሹመቱም አዋጅ ይነገርለት ዘንድ ይገባዋል" አለ፡፡ ንጉሡም ለሐማ ይህን ጊዜ "መልካም ተናግረሃል፣ ለመርዶክዮስ እንዲሁ ይደረግለታል" አለው፡፡ ሐማም የንጉሡን ትእዛዝ ተቀብሎ መርዶክዮስን በፈረስ አስቀምጦ በከተማው በማዞር በክብር መሾሙን በአዋጅ አስነገረለት፡፡ ❤ ከዚህም በኋላ ንጉሡና አስቴር ለማዕድ አብረው በተቀመጡ ጊዜ ንጉሡ "ጉዳይሽን የማትነግሪኝ ለምንድነው?" አላት፡፡ እሷም ይህን ጊዜ "ንጉሥ ሆይ ዝም ባልኩ በወደድኩ ነበር ነግር ግን ወገኖቼና እኔ ለሞት ተላልፈን ተሰጥተናል" በማለት ሐማ እስራኤላውያንን በአዋጅ ሊያጠፋ መሆኑን ነገረችው፡፡ ንጉሡም "ማነው ይህን በማድረግ የደፈረኝ?" አላት፡፡ እሷም ሐማ መሆኑን ነገረችው፡፡ ንጉሡም ሐማ መርዶክዮስን ለመስቀል ባዘጋጀው መስቀል ላይ ራሱ ሐማን እንዲሰቅሉት አዘዘ፡፡ ሐማም ተሰቅሎ ሞተ፡፡ የእስራኤል ወገኖችም ሁሉ በጻድቂቱ አስቴር መዳናቸው በእርሷ ተደርጓልና ሁሉም አመሰገኗት፡፡ ምስጉን የሆነ እግዚአብሔርን አመሰገኑት፡፡  የእስራኤል ወገኖች ሁሉ ድኅነታቸው በእርሷ ተደርጓልና ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #አቡነ_ጳውሊ_ዘሀገረ_ሰሎንቅያ፡- ሰሎንቅያ በምትባል በምስር አገር ሰይጣንን ገዝተው በግልጽ ያነጋገሩትና ብዙ ምሥጢርን እንዲናገር ያደረጉት ታላቅ አባት ናቸው፡፡ የሰሎንቅያ አገር ሰዎች የሄሮድስ ወገን የሆኑ ክፉዎች ናቸው፡፡ ከዱሮ ጀምረው ሴቶችና ወንዶች ሆነው በጋራ በአንድነት ወደ አንድ ክፍል ገብተው እንስሳዊ ግብራቸውን ይፈጽማሉ፡፡ ብዙ ሆነው ገብተው በሩን ዘግተው መብራት አጥፍተው በእጃቸው የገባውን ይዘው ያድራሉ፡፡ እኅቱም ትሁን ልጁ ወደዚያ ቤት የገባ ሰው ሌላውን አይለየውም፡፡ ይህም ሰይጣናዊ ተግባራቸው ባሕላቸው ሆኖ በወር አንድ ጊዜ ያደርጉታል፡፡ ❤ አባ ጳውሊም ይህን ባየ ጊዜ ስለ ኃጢአታቸው በጣም አዝኖ "ለምን እንዲህ ታደርጋላችሁ?" ቢላቸው እነርሱም "አባቶቻችን ያዘዙን ትእዛዝና ባሕላችን ነው" አሉት፡፡ አባ ጳውሊም ወደዚያ ቤት ሲገቡ አይቶ እጅግ በማዘን ወደ ጌታችን ጸለየ፡፡ ጸሎቱንም እንደፈጸመ አንድ ጥቁር ሰው ከዝሙት ቤቱ ዕራቁቱን ሆኖ የእሳት ሰይፍ ተሸክሞ መጣ፡፡ አባ ጳውሊም ካማተበበት በኋላ "አንተ ማነህ? ማንንስ ትሻለህ?" አሉት፡፡ ጥቁሩም ሰው "እኔ ሰይጣን ነኝ፣ አንተ ወደ ጌታህ በለመንህ ጊዜ ላከኝ" አለው፡፡ አባ ጳውሊም "የምታስትበትን ነገር ሁሉ ትነግረኝ ዘንድ እጠይቅሃለሁ" አለው፡፡ ሰይጣንም "የምትሻውን ጠይቀኝ" አለው፡፡ አባም "ያለ እግዚአብሔር ፈቃድ በሰው ላይ ታድር ዘንድ ምክንያት እንዴት ታገኛለህ?" አለው፡፡ ሰይጣንም "ሰው በእግዚአብሔር ሕግ ጸንቶ ሳለ

ከንቱ የሆነ ጣዖትን ከማምለክ ሰዎችን ስለሳብኳቸውና ሰማይና ምድርን ወደ ፈጠረ ወደ ክርስቶስ አምልኮት ስለአስገባኋቸው በእኔ ላይ ትቆጣለህን ለረከሱ ጣዖቶችህስ እንድሠዋ ታዘኛለህን እኔ ግን ቃልህን ተቀብዬ ለሰይጣናት አልሠዋም ለእውነተኛ አምላክ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ እሠዋለሁ እንጂ" አለው። ❤ በዚያንም ጊዜ ንጉሥ ተቆጣ ከሥጋው ምንም ምን ሳያስቀሩ ይበሉት ዘንድ ሁለት የተራቡ አንበሶችን በላዩ እንዲሰዱ አዘዘ። የከበረ አግናጥዮስም አንበሶች ወደርሱ ሲቀርቡ በአያቸው ጊዜ ድምፁን ከፍ አድርጎ ሕዝብን እንዲህ አላቸው "ከዚህ የተሰበሰባችሁ እናንተ የሮሜ ሰዎች ቃሌን ስሙ እወቁም እኔ ይህን ሥቃይ የታገሥኩት በትዕቢትና በትምክህት አይደለም የክብር ባለቤት በሆነ በጌታዬና በፈጣሪዬ ኢየሱስ ክርስቶስ  ፍቅር እንጂ። አሁንም እኒህ አንበሶች እንደ ሥንዴ ይፈጩኝ ዘንድ ነፍሴ ወደደች የክብር ባለቤት ወደ ሆነ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ልትሔድ ነፍሴ ሽታለችና"። ❤ ንጉሡም ቃሉን ሰምቶ አደነቀ ድንጋጠረም አድሮበት እንዲህ አለ "የክርስቲያኖች ትዕግሥታቸው ምን ይብዛ ስለ አምልኮት ከአረማውያን በእንዲህ ያለ ሥቃይ ላይ የሚታገሥ ማን ነው" አለ። እነዚያ አንበሶችም ወደ ቅዱሱ ቀረብ ብለው ደንግጠው ቆሙ። ከዚህም በኋላ አንዱ አንበሳ እጁን ዘርግቶ አንገቱን ያዘው በዚያንም ጊዜ ደስ ብሎት ነፍሱን በፈጣሪው ክርስቶስ እጅ ሰጠ ልመናውንም ፈጸመለት። ❤ ለእነዚያ አንበሶችም ሥጋውን ይዳስሡት ዘንድ አልተቻላቸውም የክብር ባለቤት ክርስቶስ ዳግመኛ እስከ ሚመጣ የተጠበቀ ሆነ እንጂ ከዚህም በኋላ በክብር በምስጋና ከከተማ ውጭ ቀበሩት እንደዚህም በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም በመልካም ተጋድሎ ምስክርነቱን ፈጸመ ለምእመናንም ጠቃሚ ይሆን ዘንድ ገድሉን ጻፉ የበዓሉንም መታሰቢያ አደረጉለት። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ሐዋርያ በቅዱስ አግናጥዮስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #የአሚናዳብ_ልጅ_ቅድስት_አስቴር፡- የአይሁድ ወገን የሚሆን ስሙ መርዶክዮስ የሚባል የኢያኤሩ ልጅ ከብንያም ወገን የተወለደ የቄስዩ ልጅ አንድ ሰው በሱሳ አገር ነበረ፡፡ ከኢሩሳሌምም በባቢሎን ንጉሥ በናቡከደነጾር እጅ የተማረከ ነው፡፡ ያሳደጋት ልጅ ነበረችው፡፡ እርሷም የአባቱ ወንድም የአሚናዳብ ልጅ አስቴር ናት፡፡ ከዘመዶቿ ተለይታ በወጣች ጊዜ ልጅ ትሆነው ዘንድ አሳደጋት፡፡ እርሷም እጅግ መልከ መልካም ነበረች፡፡ በአንዲትም ዕለት ንጉሥ አርጢክስስ ብዙ ተድላ ደስታ አድርጎ መኳንንቶቹን ሁሉ ጠራ፡፡ የመኳንንቶቹንም አለቃ አማሌቃዊውን ሐማንንም ጠራው፡፡ እርሱ ከሁሉም መኳንንት የከበረ ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ ንጉሥ 7ቱን ባለሟሎቹን ጠርቶ ንግሥቲቱን አስጢንን አምጥተው የእቴጌነት ዘውድ ያቀዳጇት ዘንድ እርሷ መልከ መልካም ናትና ለአሕዛብም አለቆች ሁሉ መልኳንና ውበቷን ያሳዩ ዘንድ አዘዛቸው፡፡ ንግሥቲቱ አስጢን ግን የንጉሡን ትእዛዝ ባለመቀበል እምቢ አለች፡፡ ከባለሟሎቿም ጋር ትመጣ ዘንድ ባለወደደች ጊዜ ንጉሡ እጅግ ተናዶ ከንግሥትነቷ ሻራት፡፡ ከዚህም በኋላ 127 ከሚሆኑ ከሚገዘቸው አገሮች አንድ ሺህ ቆነጃጅቶችን ይመርጡለት ዘንድ ንጉሡ አዘዘ፡፡ ከሺህ መቶ፣ ከመቶ ዓሥር፣ ከዓሥር ሦስት መረጡ፡፡ ከሁሉም በመልክ፣ በውበት፣ በደም ግባትም አንደኛ ሆና አስቴር ተመረጠች፡፡ ንጉሡም አስቴርን አነገሣት፡፡        ❤ ንጉሡም አስቴርን እጅግ አድርጎ ወደዳት፣ በሴቶቹም ሁሉ ላይ የበላይ አድርጎ ሾማት፡፡ ከዚህም አስቀድሞ መርዶክዮስ አገሩንና አደባባዩን ከሚጠብቁት ከንጉሡ ባለሟሎች ጋር በአደባባይ ኖረ፡፡ እነርሱም ስማቸው ታራ እና ገቦታ ይባላል፡፡ እርሱም እነዚህ ሁለቱ በንጉሡ ላይ ያሰቡትን ተንኮላቸውን ሰማ፡፡ ንጉሥ አርጤክስስን ይገድሉት ዘንድ ወንጀልን እንዳዘጋጁ ባወቀ ጊዜ መርዶክዮስ ሄዶ ለንጉሡ ነገረው፡፡ ንጉሡም ነገራቸውን መርምሮ ቀጣቸውና ይህን ነገር ታሪክና ወግ በሚጻፍበት ላይ ጻፈው፡፡ ሐማ ግን አማሌቃዊ ነበረና መርዶክዮስንና እስራኤላውያንን ይጠላቸው እጅግ ነበርና የአይሁድን ወገን ሁሉ ለማጥፋት ተነሣ፡፡ መርዶክዮስም ይህንን በሰማ ጊዜ ልብሱን ቀዶ ማቅ ለበሰ፡፡ መርዶክዮስም የሀዘኑን መርዶ ለአስቴር እንዲደርሳት አደረገ፡፡ አስቴርም "እስከ ሦስት ቀን ጹሙ ጸልዩ እኔም ደንገጡሮቼም እንጾማለን" ብላ ላከችለት፡፡ ሱባኤዋንም እንደጨረሰች የማቅ ልብሷን አውልቃ ጥላ ወደ ንጉሡ አዳራሽ በገባች ጊዜ "እስከ መንግሥቴም እኩሌታ ቢሆን እሰጥሻለሁና የሆንሽውን ንገሪኝ" አላት፡፡ በዓልንም አደረገና ሐማንና መኳንንቱን ሁሉ ጠራ፡፡ በበዓሉም ላይ ድጋሚ "ላደርግልሽ ፈቅጂውን ንገሪኝ" አላት፡፡ ❤ ንጉሡም ለመርዶክዮስ ውለታ ያደረገለትን ሲያስብ ምንም እንዳላደረገለት ዐወቀ፡፡ ወዲያውም ሐማ መርዶክዮስን በመስቀል ላይ ሰቅሎ ሊገድለው እንደሆነ ተነገረ፡፡ ንጉሡም ሐማን "ንጉሥ የወደደውን ሰው ምን ያደርግለት ዘንድ ይገባል?" አለው፡፡ ሐማም "ይህስ ለእኔ ነው" ብሎ "በክብር ይሾም ዘንድ ሹመቱም አዋጅ ይነገርለት ዘንድ ይገባዋል" አለ፡፡ ንጉሡም ለሐማ ይህን ጊዜ "መልካም ተናግረሃል፣ ለመርዶክዮስ እንዲሁ ይደረግለታል" አለው፡፡ ሐማም የንጉሡን ትእዛዝ ተቀብሎ መርዶክዮስን በፈረስ አስቀምጦ በከተማው በማዞር በክብር መሾሙን በአዋጅ አስነገረለት፡፡ ❤ ከዚህም በኋላ ንጉሡና አስቴር ለማዕድ አብረው በተቀመጡ ጊዜ ንጉሡ "ጉዳይሽን የማትነግሪኝ ለምንድነው?" አላት፡፡ እሷም ይህን ጊዜ "ንጉሥ ሆይ ዝም ባልኩ በወደድኩ ነበር ነግር ግን ወገኖቼና እኔ ለሞት ተላልፈን ተሰጥተናል" በማለት ሐማ እስራኤላውያንን በአዋጅ ሊያጠፋ መሆኑን ነገረችው፡፡ ንጉሡም "ማነው ይህን በማድረግ የደፈረኝ?" አላት፡፡ እሷም ሐማ መሆኑን ነገረችው፡፡ ንጉሡም ሐማ መርዶክዮስን ለመስቀል ባዘጋጀው መስቀል ላይ ራሱ ሐማን እንዲሰቅሉት አዘዘ፡፡ ሐማም ተሰቅሎ ሞተ፡፡ የእስራኤል ወገኖችም ሁሉ በጻድቂቱ አስቴር መዳናቸው በእርሷ ተደርጓልና ሁሉም አመሰገኗት፡፡ ምስጉን የሆነ እግዚአብሔርን አመሰገኑት፡፡  የእስራኤል ወገኖች ሁሉ ድኅነታቸው በእርሷ ተደርጓልና ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን።                           ✝ ✝ ✝ ❤ #አቡነ_ጳውሊ_ዘሀገረ_ሰሎንቅያ፡- ሰሎንቅያ በምትባል በምስር አገር ሰይጣንን ገዝተው በግልጽ ያነጋገሩትና ብዙ ምሥጢርን እንዲናገር ያደረጉት ታላቅ አባት ናቸው፡፡ የሰሎንቅያ አገር ሰዎች የሄሮድስ ወገን የሆኑ ክፉዎች ናቸው፡፡ ከዱሮ ጀምረው ሴቶችና ወንዶች ሆነው በጋራ በአንድነት ወደ አንድ ክፍል ገብተው እንስሳዊ ግብራቸውን ይፈጽማሉ፡፡ ብዙ ሆነው ገብተው በሩን ዘግተው መብራት አጥፍተው በእጃቸው የገባውን ይዘው ያድራሉ፡፡ እኅቱም ትሁን ልጁ ወደዚያ ቤት የገባ ሰው ሌላውን አይለየውም፡፡ ይህም ሰይጣናዊ ተግባራቸው ባሕላቸው ሆኖ በወር አንድ ጊዜ ያደርጉታል፡፡ ከንቱ የሆነ ጣዖትን ከማምለክ ሰዎችን ስለሳብኳቸውና ሰማይና ምድርን ወደ ፈጠረ ወደ ክርስቶስ አምልኮት ስለአስገባኋቸው በእኔ ላይ ትቆጣለህን ለረከሱ ጣዖቶችህስ እንድሠዋ ታዘኛለህን እኔ ግን ቃልህን ተቀብዬ ለሰይጣናት አልሠዋም ለእውነተኛ አምላክ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ እሠዋለሁ እንጂ" አለው።

❤ "በስመ አብ  ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤          ❤ #ታኅሣሥ ፳፬ (24) ቀን። ❤ እንኳን #ለታላቁ_አባት_ለሐዲስ_ሐዋርያ ለኢትዮጵያ ብርሃኗ ለሆኑት #ለአቡነ_ተክለ_ሃይማኖት ለልደት በዓል፣ ለአንጾኪያ ሊቀ ጳጳስ ለከበረና ለተመሰገነ #ለሐዋርያው_ቅዱስ_አግናጥዮስ ምጥው ለአንበሳ ለዕረፍቱ መታሰቢያ በዓል፣ ሰሎንቅያ በምትባል በምስ አገር ለሆኑ ሰይጣንን ገዝተው በግልጽ ላነጋገሩ ለታላቁ አባት #ለአባ_ጳውሊ ለዕረፍት በዓል፣ #ለአሚናዳብ_ልጅ_ለጻድቂቱ_ለቅድስት_አስቴር ለዕረፍቷ መታሰቢያና ለታላቁ አባት #ለአቡነ_ቴዎድሮስ_ኃይለ_መነኰስ ለዕረፍታቸው መታሰቢያ እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከአንጾክያ አገር ሊቀ ጳጳስ ከከበረ #ከአባት_ፊሎንጎስ ዕረፍት፣ የእግዚአብሔር መልአክ ከነገራቸው #በከዲህ_ከአሉ_ጻድቃን በአንዲት ቀን ዕረፍታቸው ከሆነና #ከአዝቂርም ከመታሰቢያው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                                                        ✝ ✝ ✝ ❤ #የአባታችን_የአቡነ_ተክለ_ሃይማኖት_ልደት፦ ... ከዚህም ቀጥሎ ከዘጠኝ ወር በኋላ በታኅሣሥ በሃያ አራት ቀን ፍስሐ ጽዮን ተወለደ። በዚያችም ቀን በጸጋ ዘአብ ቤት ታላቅ ደስታ ተደረገ መካን የነበረች ሚስቱ እግዚእ ኃረያ ወንድ ልጅ ወልዳለችና። መልኩ እጅግ ድንቅ ነው እንደ ብርሌ እንደ መስታወት የሚያንጸባርቅ ነው። ቅላቱም እንደ ጽጌ ረዳ ነው ለነዳያንም ግብዣ አድርገው ዋሉ። ለአገራቸውም ሰዎች እንደየማዕርጋቸው ምሳ አደረጉላቸው። ❤ በዓሉንም ካከበሩ በኋላ ለእግዚእ ኃረያና ለጸጋ ዘአብ እግዚአብሔር ያደረገላቸውን በጐ ሥራውን ሁሉ እያደነቁ ወደ የቤታቸው ተመልሰው ገቡ። ይህም እግዚአብሔር የመረጠው ልጅ በተወለደ በሦስተኛው ቀን ይህችውም የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤው ቀን በዕለተ ሰንበት ማለት ነው። ከቀኑ በሦስት ሰዓት ይህ ብላቴና እጆቹን አንሥቶ ወደ ሰማይ ተመልክቶ እግዚአብሔርን በማመስገን እንዲህ ብሎ አሰምቶ ተናገረ "ከወልድ ከመንፈስ ቅዱስ ጋራ በባሕርይ በህልውና አንድ የሚሆን አብ በአካል በስም ልዩ ነው። ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በባህሪይ በሕልውና አንድ የሚሆን ወልድ በአካል በስም ልዩ ነው። ከአብ ከወልድ ጋር በባህርይ በሕልውና አንድ የሚሆን መንፈስ ቅዱስ በአካል በስም ልዩ ነው ብሎ አመሰገነ። ❤ በሦስት ሰዓት በቅዳሴ ጊዜ መንፈስ ቅዱስ ወደ ወደደበት ስለሚወርድ ሕፃኑም መንፈስ ቅዱስ ሲወርድ አይቶ እሱ እንዳስተማረው ለፈጣሪው እየተገዛ ይህን ሦስት የምስጋና ቃል አቀረበ። እናቱም ከተመረጠ ልጇ ይህን ልዩ ምስጋና ሰምታ በልቡናዋ እያደነቀች "ልጄ ፍሥሐ ጽዮን ምን ትላለህ ይህ ቃል የአባትህ ሥራ ነው። ላንተ ግን የሚገባህ ጡት መጥባት ነውና"። ባሏ ጸጋ ዘአብ ተመልሶ ወደ ቤቱ በገባ ጊዜ ልጁ የተናገረውን ነገር ሁሉ ነገረች። ጸጋ ዘአብም ነገሩን ሰምቶ አደነቀና "ልጄ እግዚአብሔር ያሳድግህ ብዙ ዘመን ያኑርህ። በቤተ እግዚአብሔርም እንዲህ እያልክ ስትቀድስ አይህ ዘንድ እመኛለሁ" አለ። ❤ ይህንም ብላቴና መላእክት ክንፋቸውን እየጋረዱ ዘወትር ይመግቡታል። እርሱም ክንፋቸውን ሲጋርዱት ባያቸው ጊዜ ከእነሱ ጋራ ይጫወት ነበር። ሁል ጊዜ ይስቅ ነበር እንጂ ሕፃናት እንደ ሚያለቅሱ አያለቅስም ነበር ቅኖች ሰዎች ዘወትር ደስ ይላችዋልና። ምንጭ፦ ገድለ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ም16።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #አቡነ_ቴዎድሮስ_ኃያል_መነኰስ፦ አገራቸው ሮም ሲሆን በ27 ዓመታቸው በአባ ጳውሊ እጅ መነኰሱ። የታላቁ አባት ጳኲሚስ ረዳት የነበሩ ሲሆን መጽሐፍ ሊቀ ጳጳሳትም ይላቸዋል። የመነኰሳት ቁጥር ከጀመሠሪው ከአባ እንጦስ እስከ ቴዎድሮስን ያለው ትውልድ ይባላል። በድንቅ ተአምረሠታቸው ዓለምን ያደነቃቸው ተሰዓቱ ቅዱሳን የተነሱት በዚህ ጻድቅ መናኝ ጊዜ ስለነበር ከፊሎቹንም ያመነኰሷቸው እሳቸው ናቸው። ይለብሱት የነበረው የብረት ልብስ ነበር። ❤ እንጦስ በሊቀ መላእክት በቅዱስ ሚካኤል እጀሰ መነኰሱ፤ እንጦንስም መቃርስን አመነኰሱ፤ መቃርስም ጳኲሚስን አመነኰሱ፤ ጳኲሚስም እኚህን ታላቅ መነኰስ ቴዎድሮስን አመነኰሱ። እርሳቸውም እነ አቡነ አረጋወመንና ሌሎቹንመሰ ቅዱሳን አመነኰሰዋል። ❤ በዐፄ ገላውዲዮስና በዐፄ ልብነ ድንግል ዘመን ወደ አገራችን የገባውን ቅዱስ ገድላቸውን ፊልክሲዮስ፣ ገብረ ክርስቶስ፣ አረጋዊና መንፈሳዊና ማር ይስሐቅ ናቸው የተረጐሙት።ጻድቁ የተወለዱባትን ሮምን በከሃዲነቷ በእጅጉ ይጠሏት ነበር። ሮም የእነ ልዮንን የኑፋቄ ትምህርተሰ ተከትላ ሁለት ባሕሪይ በማለቷ ከሌሎች ሊቃውንት ጋር ሆነው አውግዘዋል። በስማቸው የተሠሩ ቤተ ክርስቲያኖች በጎንደር በትግራይ ሁለት አሉ። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳንና ቅዱሳት በዓላት።                               ✝ ✝ ✝ ❤ #ቅዱስ_አግናጥዮስ_ምጥው_ለአንበሳ፦ ይህም ቅዱስ የወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ ደቀ መዝሙሩ ነው። በስብከተ ወንጌልም በማገልገል ከእርሱ ጋር ብዙ አገሮችን ዙሮ አስተምሮአል ከዚህም በኋላ በአንጾኪያ አገር ላይ ሊቀ ጵጵስና ሾመው በውስጥዋመሰ ሕይወተሰ የሆነ የወንጌልን ትምህርት አስተማረ ብዙዎችንም እግዚአብሔርን ወደ ማወቅ መለሳቸው የክርስትና ጥምቀትንም አጠመቃቸው በትምህርቱም ልቡናቸውን አበራላቸው። ❤ ከዚህም በኋላ ጣዖትን ለሚያመልኩ ስሕተቻተውን በገለጠላቸው ጊዜ ተቆጡ። ወደ ከሀዲው ንጉሥ ወደ ጠራብዮስ ሔደው ከሰሱት እንዲህም አሉት "አግናጥዮስ የአማልክቶችህን አምልከሸ ይሽራል እኮን ሰዎችንም እያስተማረ ክርስቶስን ወደ ማመን ያስገባቸዋል"። በዚያንም ጊዜ ወታደሮች ልኮ ወደርሱ አስመጣውና "አግናጥዮስ ሆይ ለምን ይህን አደረግህ የአማልክቶቼን አምልኮስ ለምን ሻርክ ሰዎችን ሁሉ እግዚአብሔርን ወደ ማምለክ አስገብተሃቸዋልና" አለው። አግናጥዮስም "ንጉሥ ሆይ ቢቻለኝስ ያክብር ባለቤት ወደሆነ ወደ ክርስቶስ አምልኮት ባስገባሁህ ነበር" አለው ንጉሡም "ይህን ነገር ትተህ ለአማልክቶቼ ሠዋ አለዚያ በታላቅ ሥቃይ አሠቃይሃለሁ" አለው። "በእኔ ላይ የምትሻውን አድርግ እኔ ግን ለረከሱ አማልክቶችህ አልሠዋም ሥቃይህንም እሳትም ቢሆን አንበሳንም ቢሆን አልፈራም ከሕያው ንጉሥ ከክርስቶስ ፍቅር ልትለየኝ አትችልም" አለው። ይህንንም ሲሰማ ንጉሡ ተቆጣ ያሠቃዩትም ዘንድ አዘዘ በተለያዩ በብዙ ሥቃዮችም አሠቀሠዩት በእጆቹም ውስጥ እሳት አድርገው ከእጆቹ ጋር በጉጠት ይዘው አቃጠሉት። ❤ ከዚህም በኋላ በዲንና በቅባት እያነደዱ ጎኖቹን አቃጠሉ በሾተሎችም ሥጋውን ሠነጠቁ። ከማሠቃየትም በደከሙ ጊዜ የሚያደርጉበትን እስከመክሩ ድረስ ከወህኒ ቤት ጨመሩት ብዙ ቀኖችም በዚያ ኖረ። ❤ ከዚህም በኋላ አስታውሱት ከወህኒቤትም አውጥተው በንጉሡ ፊት አቆሙት ንጉሡም "አግናጥዮስ ሆይ አማልክቶቼን ብታያቸው ውበታቸው ባማረህ ነበር" አለው። ቅዱሱም "ንጉሥ ሆይ አንተ በክብር ባለቤት ክርስቶስ ብታምን ሙታኖችን የምታሥነሣቸው በሽተኞችንም የምትፈውሳቸው ባደረገህ ነበር"። ንጉሡም "ለፀሐይ ከመስገድ የተሻለ የለም" አለ የከበረ አግናጥዮስም "መንግሥቱ የማያልቀውን ፈጣሪ ትተህ ለተፈጠረ ፀሐይ ትሰግዳለህን?" ብሎ መለሰ ንጉሡም "ለራስህ መልካም አልክ ግን በመተላለፍ የአንጾኪያና የሶርያን ሰዎች ስበሕ ወደ ክርስቶስ አምልኮት አስገባሃቸው እንጂ" አለው። የከበረ አግናጥዮስም ተቆጥቶ "ንጉሥ ሆይ

                            ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ለስሒት መኑ ይብልዋ። እምኅቡአትየ አንጽሐኒ። ወእምነኪር መሀኮ ለገብርከ"። መዝ 18፥12-13 ወይም መዝ 88፥19-20። የሚነበቡት መልዕክታት 2ኛ ጢሞ 2፥8-19፣ 1ኛ ጴጥ 5፥2-8 እና የሐዋ ሥራ 13፥30-44። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 22፥31-46። የሚቀደሰው ቅዳሴ የሠለስቱ ምዕት ቅዳሴ ነው። መልካም የቅዱስ ዳዊት የዕረፍት በዓልና የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።               

❤ ቅዱስ ዳዊትም እጁን ወደ ድጉ ሰዶ አንዲት ደንጊያ አውጥቶ ወነጨፋት ያንንም ኢሎፍላዊ ግንባሩን ገመሰው ያቺም ደንጊያ  ከግንባሩ ገብታ ናላውን በጠበጠችው በምድር ላይም በግንባሩ ተደፋ። ዳዊትም ሩጦ የገዛ ሰይፉን አንሥቶ ራሱን ቆረጠው ከእስራኤልም ልጀጆች ስድብን አራቀ። ቅዱስ ዳዊትም መላው ዕድሜው ሰባ ነው መንግሥትን ሳይዝ ሠላሳ ዓመት ኖረ ከያዘ በኋላ አርባ ዓመት ኖረ። የክብር ባለቤት ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ ከመምጣቱ በፊት በሽህ አንድ መቶ ሃያ ዓመት ውስጥ ትንቢት የተናገረበት ዘመን ነው በሰላምም ዐረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በልበ አምላክ በቅዱስ ዳዊት በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                              ✝ ✝ ✝ ❤ #የከበሩ_ቅዱሳን_አባቶቻችን_አባ ሳሙኤል_አባ_ስምዖንና_አባ_ገብርኤል፡- አባ ሳሙኤል የተባለው ይኽም ቅዱስ ባሕታዊ ሆኖ ቀርጣሚን በምትባል አገር የሚኖር ነው፡፡ በዚያም አቅራፎስ የሚባል ሰማዕት ዐፅም ስለነበር ከእርሱ በረከትን እየተቀበለ እየተሳለመ ይኖር ነበር፡፡ ሰሊባ የሚባል አንድ መኮንን ነበር፡፡ እርሱም ስምዖን የሚባል ልጅ አለው፡፡ ልጁም ለሞት በሚያበቃ ጽኑ ሕማም ታመመ፡፡ መኮንኑ በልጁ ላይ ይጸልይ ዘንድ ወደ አባ ሳሜኤል ላከ፡፡ ነገር ግን አባ ሳሙኤል ሲደርስ ልጁ ሞቶ አገኘው፡፡ አባ ሳሙኤልም በጸሎቱ ከሞት አስነሣው፡፡ ልጁ ስምዖንም ከሞት ከተነሣ በኋላ የአባ ሳሙኤል ደቀመዝሙሩ ሆነ፡፡ ሁለቱም በጋራ በተጋድሎ አብረው ኖሩ፡፡ ❤ ቅዱስ ስምዖን ውኃ ሊቀዳ ሲሄድ ሰይጣን እንስራውን ሰበረበት፡፡ አባቱም ሌላ መቅጃ ቢሰጠው እርሱንም ሰበረበት፡፡ የታዘዘ መልአክ ተገለጠላቸውና ወደ ሌላ ቦታ ሄደው ቤተ ክርስቲያን እንዲሠሩ አዘዛቸው፡፡ ንጉሥ አንስጣስዮስም ቤተ ክርስቲያኑን ሠራላቸው፡፡ እነርሱም ለመነኮሳትና ለነዳያን መኖሪያ 500 መኖሪያ ቤቶችን ሠሩ፡፡ አባ ሳሙኤልም ባረፈ ጊዜ መነኮሳት ልጆቹን ለአባ ስምዖን አስረክቦ በሰላም ዐረፈ፡፡ መነኮሳቱም 12 ሺህ እስኪሆኑ ድረስ በዙ፡፡ አባ ስምዖንም በሚገባ ይመራቸው ነበር፡፡ በዘመኑም "ትንሣኤ ሙታን የለም" የሚል ሰይጣን በልቡ ያደረ አንድ መናፍቅ ተነሣ፡፡ አባ ስምዖንም ቢመክረውና ቢያስተምረው የማይለስ ሆነ፡፡ አባ ስምዖንም በሞተ ሰው ላይ ጸልዮ ያንን ሙት አስነሥቶ እንዲመሰክርለት ቢያደርገው አላምን አለው፡፡ ከዚህም በኋላ አባ ስምዖን ወደ እግዚአብሔር ቢጸልይ እሳት ከሰማይ ወርዶ ያንን መናፍቅ አቃጠለውና ክፉ አሟሟት ሞተ፡፡ አባ ስምዖንም አገልግሎቱን ፈጽሞ በዚህች ዕለት በሰላም ዐረፈ፡፡ ❤ ከአባ ስምዖንም በኋላ አባ ገብርኤል ተሹሞ መለኮሳቱን የሚጠብቅ እረኛ ሆነ፡፡ እርሱም ምግባሩ ያማረ ሃይማኖቱ የሰመረ በትሩፋት በተጋደሎ ያጌጠ ነው፡፡ ብዙ አስደናቂ ተአምራትንም የሚያደርግ ሆነ፡፡ ከዕለታም በአንደኛው ቀን መነኮሳቱ ለእንጀራ ማቡኪያ የሚሆን እጅግ ትልቅ የሆነ የድንጋይ ገንዳ ወደ ገዳሙ ሊያስገቡ ቢሉ ከክብደቱ የተነሣ እምቢ አላቸው፡፡ አባ ገብርኤልም በዚህ ጊዜ በገዳሙ ያሉት ሁሉ ወጥተው እንዲራዱ በቃላቸው ባዘዙ ጊዜ 10 ሺህ ሰዎች ከሙታን ተነሡ፡፡ አባ ገብርኤልም ይህን አይቶ "እናንተን ያልኩ አይደለም በሕይወት ያሉትን ነው እንጂ" አሏቸውና ወዲያው ወደ መቃብራቸው ተመለሱ፡፡ ❤ ከዕለታትም በአንደኛው ቀን አንድ ሰው ብዙ የሆነ ወርቁን ከአንዱ መነኩሴ ዘንድ በአደራ አስቀምጦ ወደ ሩቅ አገር ሄደ፡፡ ሰውየውም በተመለሰ ጊዜ መነኩሴው ለማንም ሳይናገር በሞት ዐርፎ አገኘው፡፡ የመነኩሴውም ረድእ አባቱ ያስቀመጠበትን ቦታ እንዳልነገረው አስረዳ፡፡ ከዚህም በኋላ አባ ገብርኤል ወደሟቹ መነኩሴ መቃብር ሄዶ መቃብሩን ስለዚያ ወርቅ ጠየቀው፡፡ ሟቹም መነኮሴ ወርቁን ያኖረበትን ቦታ ለአባ ገብርኤል ነገረውና ወስዶ ለባለቤቱ ሰጠው፡፡ ባለወርቁም እጅግ እያደነቀ ወርቁን ተቀብሎ በሰላም ሄደ፡፡                              ✝ ✝ ✝ ❤ #አባ_ጢሞቴዎስ፡- ደጋግ የሆኑ ወላጆቹ የቤተ ክርስቲያንን ትምህት እያስተማሩ አሳደጉት፡፡ በደገም ጊዜ ዓለምን ንቆ መንሶ ገዳም በመግባት በተጋድሎ መኖር ጀመረ፡፡ መጻተኞችንና ጦም አዳሪዎችን ይመግባቸው ዘንድ ከገዳሙ አቅራቢያ መኖሪያን አበጀ፡፡ ነዳያንንም እየመገበ በመንፈሳዊ ተጋድሎው እየጸና 5 ዓመት ያህል ከኖረ በኋላ የበጎ ነገር ጠላት የሆነ ሰይጣን በቅናት ተነሣበትና የእጅ ሥራውን ትገዛ ዘንድ አንዲት ጋለሞታን ወደ እርሱ አመጣበት፡፡ ❤ እርሷም ወደ አባ ጢሞቴዎስ ከመመላለሷ የተነሣ የኃጢአት ፍቅር አድሮባቸው በመብል ጊዜ አብረው የሚመገቡ ሆኑ፡፡ ከዚህም በኋላ ከእርሷ ጋር በኃጢአት ወደቀና በኃጢአት ሥራ ውስጥ 7 ወር ያህል ኖረ፡፡ እግዚአብሔር ሁለቱንም አልጣላቸውምና በዕለተ ምፅዓት በፊቱ የሚቆሙ መሆናቸውን አሳሰባቸው፡፡ ከዚህም በኋላ አባ ጢሞቴዎስ ተነሥቶ ጥቅጥቅ ወዳለ ጫካ ገብቶ በዚያ እየታደለ ብዙ ዘመን ኖረ፡፡ እግዚአብሔርም ጣፋጭ የሆነች የውኃ ምንጭንና ቴምርን አዘጋጀለት፡፡ እርሷን እየተመገበ በተጋድሎ ሲኖር ሰይጣን ዳግመኛ በቅናት ተነሣበትና አስጨናቂ የሆድ ሕማም አመጣበት፡፡ አባ ጢሞቴዎስ ከሕማሙ ጽናት የተነሣ በግንባሩ ምድር ላይ የወደቀ ሆኖ ቀረ፡፡ በዚህም ጊዜ ነፍሱን ‹‹ነፍሴ ሆይ ይህ የሠራሽው የኃጢአትሽ ፍሬ ነውና በዚህ ደዌሽ ታገሺ›› ይላት ነበር፡፡ በዚህም አስጨናቂ ሕማም ውስጥ ሆኖ 4 ዓመት ኖረ፡፡ ❤ ከ4 ዓመትም በኋላ መሐሪና ይቅር ባይ የሆነ እግዚአብሔር ለአባ ጢሞቴዎስ መልአኩን ላከለት፡፡ መልአኩም የአባ ጢሞቴዎስን ሆድ በእጁ አሸው፡፡ ጎኑንም በጣቱ ሰነጠቀና ጨንጓራውንና አንጀቱን አፀዳለት፡፡ በኋላም ወደቦታው መልሶ እንደቀድሞው አያይዞ አዳነውና "እነሆ እንግዲህ ጤነኛ ሆንክ፣ ዳግመኛ አትበድል ከዚህ የከፋ እንዳይደርስብህ" አለው፡፡ አባ ጢሞቴዎስም በበረሃ እየተጋደለ 40 ዓመት ኖረ፡፡ ከዚያ በፊት በገዳም 17 ዓመት በዋሻ 10 ዓመት ኖሯል፡፡ በእነዚህም ዘመናቱ ከልብስ ተራቁቶ ኖረ፡፡ የራሱም ፀጉር ከፊትና ከኋላ ሸፍኖት ነበር፡፡ ስለ አገልግሎቱ፣ ስለ ተጋድሎውና ስለ አምልኮቱ የዱር አራዊት እስኪደግዱለትና የእግሩን ትቢያ እስኪልሱለት ድረስ እግዚአብሔር ትልቅ ጸጋን ሰጠው፡፡ አገልግሎቱንም ፈጽሞ ታኅሣሥ23  በሰላም ዐረፈ፡፡ ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእሊህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የታኅሣሥ 23 ስንክሳር።                             ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_ለዳዊት_ትሕትናሁ_ሶበ_ርእየ። ወየውሀቶ ፍጹም ዘአልቦ እከየ። #እግዚአብሔር ይቤ እንዘ ይነብብ ሰደየ። እምነ ሕዝብየ አልዓልኩ ኅሩይየ። ወረከብክዎ #ለዳዊት_ገብርየ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የታኅሣሥ_23።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ወአልዐልኩ ኅሩይየ እምሕዝቡ። ወረከብክዎ ለዳዊት ገብርየ። ወቀባዕክሙ ቅብዐ ቅዱስ"። መዝ 88፥19-20። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 6፥19-ፍ.ም።