ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ
Відкрити в Telegram
ይህ በግራር ደ/አባይ ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ ፍኖተ ብርሀን ሰንበት ት/ቤት የተዘጋጀ :- ለምዕመናን : ትምህርትን , ዝማሬዎችን , ኪናዊ ዝግጅቶችን, የቤተ ክርስቲያንን ወቅታዊ ዜናዎችንና በአላትን(ንግስ, ልዮ ልዮ የሰርክ ጉባኤያት ..ወዘተ) በምን መልኩ እንደተከበሩ ለምዕመናን ተዘጋጅቶ የሚተላለፍበት ገፅ ነው።
Показати більше637
Підписники
Немає даних24 години
-37 днів
-1230 день
Архів дописів
❤ ከዚህም በኋላ ተነሥተው በአንድነት ሔዱ ወደ መኰንኑ ወደ ቊልቊልያኖስም ደረሱ መሰንቆና እንዚራ እያስመታ ለጣዖታቱ በዓልን ሲያከብር አገኙት ያንጊዜ ወታደሮቹ ይዘው በመኰንኑ ፊት አቆሙት ሚስቱም ተከተለችው መኰንኑም ለጣዖት መስገድን እያግባባ በርኅራኄ ቃል ተናገረው ቅዱስ ግን እርሱንና የረከሰች ሃይማኖቱን ሰደበ ስለዚህም መኰንኑ ተቆጥቶ ከሚስቱ ጋር ወደ ወህኒ ቤት እንዲአስገቡት አዘዘ።
❤ ከጥቂት ቀኖች በኋላም ከሚስቱ ጋር አውጥተው ደማቸው እንደ ውኃ እስቲፈሰሰ በአለንጋዎች እንዲገረፋአቸው አዘዘ ያለ ርኅራኄም ገረፋአቸው ሚስቱም በዚህ ሥቃይ ምስክርነቷን ፈጸመች። ዳግመኛም ለጣዖታት መስገድን እሺ ይለው ዘንድ ቅዱስ ጢሞቴዎስን ማባበል ጀመረ እምቢ ባለውም ጊዜ የነዳጅ ድፍድፍ ሥጋውን ቀብተው ከእሳት ማንደጃ ውስጥ እንዲጨምሩት አዘዘ በጨመሩትም ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ወርዶ ከዚህ ቃጠሎ አዳነው።
❤ ከዚህም በኋላ ሁለተኛ ወደወህኒ ቤት መለሱት ተአምራትንም የሚያደርግ ሆነ በአንዲት ዕለትም በዚያ ሲጸልይ ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደርሱ መጥቶ ቃል ኪዳንን ገባለት ሰላምታንም ሰጠው። በማግሥቱም ከእሥር ቤት አውጥተው ወደ በንሑር ከተማ ወስደው ቅድስት ራሱን ቆረጡ ያን ጊዜ ንውጽውጽታ ሆነ አየርም መላእክትን ተመላች አማንያን ሰዎችም መጥተው ሥጋውን ወስደው በመልካም አገናነዝ ገንዘው ቀበሩት። የመከራውም ዘመን በአለፈ ጊዜ ቤተ ክርስቲያን ሠሩለት ሰኔ ሃያ ሰባት ቀንም አከበርዋት ሥጋውንም በውስጥዋ አኖሩ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በሰማዕቱ በቅዱስ ጢሞቴዎስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የኅዳር27 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_እብል_ለልሳንከ ዘተውህበ። መዓርዒረ ቃል ወመአድመ ንባበ። ኀቤከ ይብጻሕ ዘተዝካርየ ክታበ። #ፈኑ_ሊተ_ፊልሞና እስመ ራሰይኩከ አበ። ሀገረ ልድያ ቀዳሚ ዘፈኖከ ርግብ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የኅዳር_27።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ለምንት አንገለጉ አሕዛብ። ወሕዝብኒ ነበቡ ከንቶ። ወተንሥኡ ነገሥተ ምድር። መዝ 2፥3-4 ወይም ። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 27፥57-ፍ.ም።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ጸኒሐ ጸናሕክዎ ለእግዚአብሔር። ሰምዓኒ ወተመይጠኒ። ወሰምዓኒ ቃለ ስእለትየ"። መዝ 39፥1-2 ወይም መዝ 73፥12-13። የሚነበቡት መልዕክታት ፊሊ 1፥1-ፍ.ም፣ 1ኛ ጴጥ 5፥9-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 11፥25-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 10፥1-12። የቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ወይም የሠለስቱ ምዕት ቅዳሴ ነው። መልካም የአቡነ ተክለ ሐዋርያት የዕረፍት በዓልና የነቢያት (የገና) የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ኅዳር ፳፯ (27) ቀን።
❤ እንኳን #ከሰባ_ሁለቱ_አርድእት ለአንዱ #ለቅዱስ_ፊልሞና ለመታሰቢያው በዓል፣ ለፋርስ ንጉሥ ለሳፎር ልጅ ለንጉሥ ሰክራድ ከጭፍሮች ውስጥ ለሆነ ሕዋሳቱን የተቆራረጠ #ለቅዱስ_ያዕቆብ ዘግሙድ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓልና በንሑር ከሚባል አገር ለሆነ #ለቅዱስ_ጢሞቴዎስ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከመድኃኒታችን #ከመድኃኔዓለም ከስቅለቱ መታሰቢያ፣ ከገርማው #ከአባ_ገብረ_ዮሐንስ፣ ከደብረ ቊንጽል #ከአባ_ሊቃኖስ ከመታሰቢያቸውና ዘርቦች ከምትባል አገር #ከደብረ_ጒይ_ከሰማዕት_ቀሌምንጦስ ከመታሰቢያው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
❤ በዚችም ዕለት ከሰባ ሁለቱ አርድእት የአንዱ #የቅዱስ_ፊልሞና መታሰቢያው ነው። የቅዱስ ፊልሞና በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #ያዕቆብ_ዘግሙድ፦ ይህ ለሳፎር ልጅ ለንጉሥ ሰክራድ ከጭፍሮቸሐ ውስጥ የሆነ ነው። ንጉሥ ሰክራድ እጅግ ይወደው ነበር ስለ መንግሥቱ ሥራ ሁሉ ከእርሱ ጋር ይማክር ነበርና ስለዚህም የቅዱስ ያዕቆብን ልቡና አዘንብሎ ፀሐይንና እሳትን እንዲአመልክ አደረገው። በሃይማኖቱም ከንጉሡ ጋር እንደተስማማ የተቀደሱ እናቱ ሚስቱንና እኅቱ በሰሙ ጊዜ እንዲህ ብለው ጽፈው ወደርሱ ላኩ "የቀናች የጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን ሃይማኖት ትተህ የፍጡራንን ጠባይ ለምን ተከተልክ እሊህም ፀሐይ ጨረቃ ከዋክብት እሳት ናቸው ዕወቅ ከዛሬ ጀምሮ በንጉሥ ሃይማኖት ከኖርክ እኛ ከአንተ የተለየን ነን"። የመልክታቸውንም ጽሑፍ በአነበበ ጊዜ መሪር ልቅሶን አለቀሰ "በዚህም የጥፋት ምክር ጸንቼ ብኖር ከቤተሰቦቼና ከወገኖቹ የተለየሁ መሆኔ ነው። ደግሞስ በጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ፊት እንዴት እቆማለሁ" አለ።
❤ ከዚህም በኋላ የቤተ ክርስቲያንን መጻሕፍቶች ማንበብ ጀምረ የንጉሡን አግልግሎትም ተወ ለንጉሡም "ወዳጅህ ያዕቆብ እነሆ አገልግሎትህን አማልክቶችህም ማምለክ ተወ" ብለው ነገሩት። ንጉሡም ልኮ ወደርሱ አስቀርቦ "አገልግሎትህን ለምን ተወክ?" አለው ቅዱስ ያዕቆብም እንዲህ አለ "ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በከበረ ወንጌል በሰው ፊት ያመነብኝን ሁሉ እኔም በሰማያዊ አባቴ ፊት አምነዋለሁ በሰው ፊት የካደኝንም በአባቴ ፊትና በመላእክት ፊት እክደዋለሁ ብሏልና ስለዚህ አገልግሎትህን ፍቅርህን አማልክቶችህንም ማምለክ ትቼ ሰማይና ምድርን ፀሐይን ጨረቃን ከዋክብትን የሚታየውንና የማይታየውን ለፈጠረ ለሕያው እግዚአብሔር ልጅ ለጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ የምሰግድ ሆንኩ"።
❤ ንጉሡም ይህን በሰማ ጊዜ ደሙ እንደ ውኃ በዝቶ እስቲፈስ ታላቅ ግርፋትን እንዲገርፉት አዘዘ እርሱ ግን ከበጎ ምክሩ አልተመለሰም ዳግመኛም ሕዋሳቱነሰ በየዕለቱ እንዲቆርጡ አዘዘ የእጆቹንና የእግሮቹን ጣቶች ሃያውን ቆረጡ ክንዶቹንና እግሮቹን እስከ ጭኖቹ ድረስ ወደ አርባ ሁለት ቊራጭ በየጥቂቱ ቆረጡት። በሚቆርጡትም ጊዜ ሁሉ "ጌታዬና ንጉሤ ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ዕንጨት ቅርንጫፍ ሰውነቴን በይቅርታህ ገናናነት ተቀበል የወይን አታክልት ያለው በሦስት ዓጽቅ ሲቆርጡለት ዓጽቆቹ በዝተው ይበቅላሉ ይሰፋሉ በሚያዝያ ወር አብቦ ያፈራልና" እያለ የሚዘምርና የሚያመሰግን ሆነ። ደረቱና አካሉ እንደ ግንድ ድብልብል ሁኖ በቀረ ጊዜ ነፍሱን ለመስጠት እንደ ደረሰ አውቆ በዚያን ጊዜ በዓለም ውስጥ ያሉትን ሰዎች ሁሉንም ይመራቸው ዘንድ እግዚአብሔርን ለመነው እንዲህም አለ "ለእኔ ግን ወደ አንተ የማነሣው አካል አልቀረኝም ሕዋሳቶቼ ተቆርጠው በፊቴ የወደቁ ስለሆነ አሁንም ነፍሴን ተቀበላት" አለ።
❤ በዚያንም ጊዜ ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገልጾ አረጋጋው አጸናውም ያን ጊዜ ነፍሱ ደስ አላት ነፍሱንም ከመስጠቱ በፊት ወታደሩ በፍጥነት መጥቶ የከበረች ራሱን በሰይፍ ቆረጠ የሰማዕትነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ ሥጋውንም ምእመናን ሰዎች ወስደው በመልካም አገናነዝ ገነዙትና በንጹሕ ቦታ አኖሩት። እናቱ ሚስቱና እኅቱ በሰማዕትነት እንደ ሞተ በሰሙ ጊዜ አጅግ ደስ አላቸው ወደ ቅዱስ ያዕቆብም ሥጋ መጥተው ተሳለሙት አለቀሱለትም የከበሩ ልብሶችንም በላዩ አኖሩ ጣፋጮች የሆኑ ሽቱዎችንም ረጩበት።
❤ በደጋጎች ነገሥታት በአኖሬዎስና በአርቃዴዎስ በሌሎችም ዘመን አብያተ ክርስቲያን ታነፁ ገዳማትና አድባራትም ተሠሩ የሰማዕታትንም ሥጋ በውስጣቸው አኖሩ ታላላቆቸሰ ድንቆች ተአምራትም ከእሳቸው የሚታዩ ሆኑ። የፋርስ ንጉሥም ሰምቶ በቦታው ሁሉ የሰማዕታትን ሥጋ ያቃጥሉ ዘንድ አዘዘ በሚገዛውም አገር ውስጥ ምንም ምን እንዳይተው አማንያን ሰዎችም መጥተው የቅዱስ ያዕቆብን ሥጋ ወደ ኢየሩሳሌም ወሰዱት በዚያም ወደ አገረ ሮሀ ከአገረ ሮሀም የከበረ ኤጲስቆጶስ ጴጥሮስ ወደ ግብጽ አገር ወደ ብሕንሳ ከተማ ወሰደው። በዚያም ጥቂት ጊዜ ኖረ ከርሱ ጋርም መነኰሳት ነበሩ ከቀኑ እኵሎታም ሲጸልዩ ቅዱስ ያዕቆብ ሥጋ ከብዙ የፋርስ ሰማዕታት ሥጋ ጋር በአለበት ሰማዕታት አብረዋቸው ዘመሩ ባረኳቸውም ቅዱስ ያዕቆብም "እግዚአብሔር እንዳዘዘ ሥጋዬ በዚህ ይኑር" አለ ከዚያም በኋላ ተሠወሩ።
❤ ከዚህም በኋላ የከበረ ኤጲስቆጶስ ጴጥሮስ ወደ አገሩ ሊመለስ በወደደ ጊዜ ሥጋዬ በዚህ ቦታ ይኑር ያለውን የቅዱስ ያዕቆብን ቃል ተላለፎ የቅዱስ ያዕቆብን ሥጋ ወሰደ በዚያንም ጊዜ አስቀድሞ ወደ አመለከተው ቦታ ከእጆቻቸው መካከል ተመለሰ ከሥጋውም ታላላቅ የሆኑ ተአምራት ተገለጡ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ሰማዕት በቅዱስ ያዕቆብ ዘግሙድ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #ቅዱስ_ጢሞቴዎስ፦ ይህም ቅዱስ ከታናሽነቱ ጀምሮ እግዚአብሔርን የሚፈራ ሁል ጊዜ በጾም በጸሎት ተጠምዶ የሚኖር ነው ስሟ ሞራ የሚባል ሚስት አለችው እርሷም የአጎቱ ልጅ ናት በሥራዋ ሁሉ ደስ የምታሰኘው መልካም ሴት ናት። እንደዚህም በፍቅርና በስምምነት ሲኖሩ ከከሀዲ ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ዘንድ የጣዖታት ቤቶች ይከፈቱ ዘንድ አብያተ ክርስቲያናት እንዲዘጉ ትእዛዝ ወጣ። ቅዱስ ጢሞቴዎስም ይህን ሰምቶ እጅግ ደስ አለው። እርሱ ስለ ክርስቶስ ፍቅር ደሙን ያፈስ ዘንድ ይህን ዘመን ይጠብቀው ነበርና ለሚስቱም ሊሠራው ያሰበውን ነገራት እርሷም "የእግዚአብር ፈቃድ ይሁን" አለች።
❤ ከዚህም በኋላ መንገዱን ያቀናለት ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ ጌታችንም በዚያች ሌሊት በሕልሙ ተገልጾለት "ወዳጄ ጢሞቴዎስ ሆይ ሰላም ላንተ ይሁን እንሆ ከጻድቃኖቼ ቊጥር ውስጥ ቆጥሬሃለሁ አሁንም ተነሣ ሚስትህንም ይዘህ ወደ ብህንሳ ከተማ ሒዳችሁ ጣዖታትን በሚያመልኩ ሁሉ ሕዝብ ፊት በስሜ ታመኑ" አለው። በነቃ ጊዜም ለሚስቱ ነገራት እርሷም ይህንኑ የሚመስል ሕልሟን ነገረችው።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ኅዳር ፳፯ (27) ቀን።
❤ እንኳን #ለኢትዮጵያዊው_ጻድቅ ስለ ጌታችን ሥጋና ደም ክብር ሲሉ ቅዱስ ቊርባን የተቀበለ ሰው ያስታወከው የጠጡ ለታላቁ አባት #ለአቡነ_ተክለ_ሐዋርያት_ለዕረፍት በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #አቡነ_ተክለ_ሐዋርያት፦ አባታቸው የእናርዕት አገረ ገዥ የነበሩት እድርያስ ሲሆኑ እናታቸው ደግሞ እሌኒ ይባላሉ። የትውልድ አገራቸው ሸዋ ሲሆን በዚሁ የምትገኘውን ታላቋን ደብረ ጽሙናን ገዳም የመሠረቱ ሲሆን በዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ዘመን የነበሩ ታላቅ አባት ናቸው። ገና በእናታቸው ማኅፀን ሳሉ አጋንንትን እያቃጠሉ ያጠፏቸው ነበር። የቤተ ክርስቲያንንም ትምህርት ተምረው ከጨረሱ በኋላ ገና በድቁና እያገለገሉ ሳለ 40 ቀን በማክፈል ይጾሙና ይጸልዩ ነበር። አባታችን የመነኰሱትና ብዙ ተጋድሏቸውን ፈጽመው ወደ ሰማይ ተነጥቀው ሥላሴን እስከማየት የደረሱት በደብረ ሊባኖስ ነው። ያመነኰሷቸውም ሁሉን በስውር ያለውን የሚያውቁት አቡነ ዮሐንስ ከማ ናቸው። አባታችን ማታ ማታ ከባሕር ውስጥ ገብተው ሲጸልዩ እያደሩ በቀን 30 ፍሬ አተር ብቻ እየተመገቡ ይጾሙ ነበር።
❤ በአባ አትናቴዎስ መቃብር ላይ ሄደው አጥብቀው የጸለዩ ፯ አክሊል የወረደላቸው ጌታ ተገልጾ ከጊዮርጊስና ከዮሐንስ መጥምቁ ጋር ነው ክፍልህ ያላቸው ጻድቅ ናቸው። በዚህም ሙታን የተነሱላችሁ ብዙ ተዓምር ያደረጉ ብርሃን የወረደላቸው ታላቅ ጻድቅ ናቸው። ሲጸልዩ ነፍሴ ፫ (ሦስት) ነገርን ትፈልጋለች ይሉ ነበር።
➻ 1 ከዚህ ዓለም ሀሜት መራቅን ፤
➻ 2 ክፉ ነገር ከማየት መራቅን ፤
➻ 3 ከንቱ ነገር ከመስማት መራቅን እያሉ ይማጸኑ ነበር።
❤ እንዲህ እያሉ በሚጸልዩበትም ወቅት መልአኩ መጣና ወደ በረሃ ምንም ሰው ወዳሌለበት ሂድ አላቸው። እንዳላቸው ወደ ምድረ ሐጋይ በዝዋይ አድርገው አልፈው ከባሕር ውስጥ በሚገኝ ዋሻ ገቡ። ከዚያ ገብተው ይጸልዩ ጀመር። በዚያም ብርሃን ወርዶላቸው ነፍሴ ሰውነቴን ተጸየፈች እያሉ ይጸልዩ ጀመር። በዚያን ጊዜ ጌታ ተገልጾላቸው ቃል ኪዳን ገብቶላቸዋል።
❤ አባታችን አቡነ ተክለሐዋርያት ከሌሎች ፃድቃን ለየት የሚያደርጋቸዉ፦ አንድ ዓመት የታመመ ህመምተኛ ሥጋወደሙ ወስዶ (ተቀብሎ ) ከህመሙ የተነሳ አስመለሰዉ ዲያቆኑ ያስመለሰዉን በእቃ ተቀበለዉ ። ደምና መግል የተቀላቀለበት ነበር አባታችን አቡነ ተክለሐዋርያት ሰለ ስጋወ ደሙ ክብር በዕለተ ዓርብ ሃሞትና ሆምጣጤዉን እንደ አጠጡት የወልድን የመስቀሉን መከራ አስበዉ ፈጣሪአቸዉን ከመዉደዳቸዉ የተነሳ ያንን ያስመለሰውን ግጥም አደርገዉ ጠጡት በዘያን ጊዜ ጌታችን ወደሳቸዉ መጥቶ ወዳጄ ተክለሐዋርያት ሆይ በሰው ፊት እንዳከበርከኝ በሰማያዊ መላአክትና በምድራውያን ፃድቃን ሰማእታት ፊት አከብርሃለሁ ብሎ ጣቱን አንስቶ በጣቱ ፊታቸዉን በባረከዉ ጊዜ ፊታቸዉ እንደ ፀሐይ አበራ በፊቱም ላይ ያለዉ የፀሐይ ብርሃን በምድር ላይ ሁሉ ታየ ።
🐓አንድ ዶሮ በሰንበት ቀን ከባለቤቱ አምልጦ መጥቶ አስጥለኝ ብሎ ለመናቸዉ አሳቸዉ የዶሮውን ባለቤት ሰንበት ነው አትረደዉ ቢሉት አልሰማ ሰላላቸዉ ያላቸዉን ሸማ (ልብስ ) ሰጥተዉ ዶሮውን ከመታረድ አድነውታል በስዕሉ ላይ አንደሚታየዉ።
❤ በመጨረሻም አባታችን አቡነ ተክለ ሐዋርያት ሕዳር ፳፯ ቀን በክብር አርፈዋል። መላዕክትም ፭ ሆነው ወርደው ቀብረዋቸዋል። መጀመሪያ በደብረ ብርሃን ተቀብረው ከ፲፫ ዓመት በኋላ በምዕራብ ሸዋ አህጉረ ስብከት ስር በምትገኘው ወደ ደብረ ፅሙና አፅማቸው መጥቷል። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳንና የደብረ ሲና ቅዱስ እግዚአብሔር ዕፀ ጳጦስ ሰንበት ትምህርት ቤት።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_እብል_ለተክለ_ሐዋርያት በተአምኆ። ወለተአምሪከ እሴብሖ። ለምሳሐ ሰንበት ሶበ ፈቀደ ይጥብሖ። ተማሕፀንኩ በጸሎትከ እንዘ ይብል ከሊሖ። በልሳነ ሰብእ ነበበ ነቃዊ ዶርሖ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የኅዳር _27።
❤ ፍሬምናጦስም ወደ እስክንድሪያ ለመሄድ አስቦ ሳለ እንደተኛ እመቤታችን ድንግል ማርያም ተገልጣለት "ዲቁናና ቅስናን መቀበል ይገባሃል፣ ለጵጵስና ተዘጋጅ፣ እግዚአብሔር ይህችን ከፍ ያለችውን ማዕረግ ሰጥተሃልና የልጄ ወዳጅ ሆይ በጸሎትህና በልመናህ በስብከትህም የኢትዮጵያ ሰዎች ሁሉ ይድናሉ፣ በእጅህ ጥምቀትንና ሥጋ ወደሙን ይቀበላሉ" አለችው፡፡ ጌታችንም እንዲሁ ተገልጦለት "ወደ ሊቀ ጳጳሳት ወደ አትናቴዎስ ሄደህ ከፍ ያችውን ማዕረግ ተቀብለህ የኢትዮጵያን ሰዎች አጥምቅልኝ፣ ነቢዩ ዳዊት ስለ እነርሱ "ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች" ብሎ ተናግሯልና" አለው፡፡ ከዚህም በኋላ አቡነ ሰላማ ቅዱሳኑን ነገሥታት አብርሃንና አጽብሓን አግኝቶ ከእነርሱም ጋር ተማክሮ ወደ እስክንድሪያ ሄዶ በቅዱስ አትናቴዎስ እጅ በአገራችን ላይ የመጀመሪያው ሊቀ ጳጳስ ሆኖ ታኅሳስ 18 ቀን ተሾመ፡፡ ስሙንም ሰላማ ከሣቴ ብርሃን አለው፡፡ ሰላማ ማለት እግዚአብሔርንና ሰውን የሚያስታርቅ ማለት ነው፡፡ ከሣቴ ብርሃን ማለትም ሃይማኖትን ገልጦ የሚያስተምር ማለት ነው፡፡ ቅዱስ አትናቴዎስም ከሾመው በኋላ ታቦትና በጣም ብዙ ንዋያተ ቅድሳትንና መገልገያ ዕቃዎችን ሰጥቶ መርቆ በሰላም ወደ ኢትዮጵያ ላከው...፡፡ አቡነ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #አቡነ_ኢየሱስ_ሞዐ፦ አገራቸው ጎንደር ክፍለ ሀገር ስማዳ ወረዳ ሲና ዳኅና በሚባል ቦታ ነሐሴ 26 ቀን ተፀንሰው ግንቦት 26 ቀን 1210 ዓ.ም ከአባታቸው ከቅዱስ ዘክርስቶስና ከእናታቸው ከቅድስት እግዚእ ክብራ ተወለዱ፡፡ የተወለዱትም በቅዱስ ነአኲቶ ለአብ ዘመነ መንግሥት ነው፡፡
❤ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ የአቡነ ተክለ ሃይማኖት የቆብ አባት ሲሆኑ ታላቁን ሐይቅ ቅዱስ እስጢፋኖስን ገዳም የቆረቆሩ ደገኛ አባት ናቸው፡፡ ዕድሜያቸው 30 ዓመት እስከሚደርስ ድረስ ከቤተሰቦቻቸው ትምህርተ ሃይማኖትንና ግብረ ገብን ሲማሩ ከቆዩ በኋላ በ1240 ዓ.ም ይህንን ዓለም በመተው ወደ ደብረ ዳሞ ገዳም ገቡ፡፡ በደብረ ዳሞ ገዳም መነኰሳቱን እየረዱ፣ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት እያጠኑ፣ ቅዱሳት መጻሕፍትን እየገለበጡ ለሰባት ዓመታት ከቆዩ በኋላ የደብረ ዳሞ 3ኛ አበ ምኔት ከሆኑት ከአባ ዮሐኒ እጅ ምንኩስናን በ1247 ዓ.ም ተቀበሉ፡፡
❤ አንድ ቀን ሌሊት መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ወደርሳቸው መጥቶ "የስምህ መክበርያ ወደሆነው ሐይቅ ወደ ተባለው ሥፍራ ሂድ" አላቸው፡፡ አባታችንም "ቦታውን እንዴት ዐውቀዋለሁ?" በማለት መልአኩን ቢጠይቁት "ተነሥ! ጉዞህን ጀምር ቦታውን እኔ አሳይሃለሁ" አላቸው፡፡ አባ ኢየሱስ ሞዐ በመልአኩ እንደታዘዙት ከበዓታቸው ተነሥተው ተከተሉት፡፡ የብዙ ወራት መንገድ የሆነውን ጐዳናም በስድስት ሰዓት አደረሳቸው፡፡ በዚያን ወቅት ከሐይቅ ገዳም በስተ ሰሜን ወደነበረው የቅዱሳን ጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤተ ክርስቲያን ደረሱ፡፡ ወደ ሐይቅ እስጢፋኖስ ከመግባታቸው በፊት ለ6 ወራት ያህል በቅዱሳን በጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤተ ክርስቲያን አገልግለዋል፡፡ ያገለግሉበት በነበረው ቤተ ክርስቲያን ቀን ቀን ሕዝቡን ሲያስተምሩ በመዋል ሲመሽ ወደ ሐይቁ በመግባት ሲጸልዩ ያድሩ ነበር፡፡ በሐይቅ እስጢፋኖስና በዙርያው ለነበሩ አበው ማታ ማታ አንድ ብርሃን ወደ ሐይቁ ሲገባ ጠዋት ጠዋትም ሲወጣ ይታያቸው ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ አባታችን በገዳሙ አባቶች ልመናና በልዑል እግዚአብሔር ትዕዛዝ ወደ ሐይቅ ገዳም ገብተው አበምኔት ሆኑ፡፡
❤ ሐይቅ እስጢፋኖስ ገዳም ከደሴ 30 ኪሎ ሜትር ርቆ የሚገኝ ሲሆን የመሠረቱት ካልዕ ሰላማ የተባሉ ግብፃዊ ጻድቅ ናቸው፡፡ ሐይቅን አባ ሰላማ ካልዕና ዐፄ ድል ነአድ በ862 ዓ.ም ነው የቆረቆሩት። ገዳሙን ካቀኑት በኋላ "የማንን ታቦት እናስገባ?" ብለው ሲያስቡ ቶራ የምትባል እንስሳ ጭነት ተጭና ከመካከላቸው ተገኘች፤ ጭነቱን አውርደው ቢያዩት በሐር ጨርቅ የተጠቀለለ የቅዱስ እስጢፋኖስንና የቅዱስ ጊዮርጊስን ሁለት ታቦት አገኙ፡፡ በላዩም ላይ "ይህንን ታቦት በኢየሩሳሌም የሚኖሩ የተሰወሩ ቅዱሳን ከእግዚአብሔር ታዘው የላኩት ነው" የሚል ጽሑፍ አገኙ፡፡ ይህ ከሆነ ከ400 ዘመን በኋላ ነው አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ወደዚህ ቦታ የመጡት፡፡ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ለ52 ዓመት ቀን ቀን መንፈሳዊ ሥራቸውን እየሠሩ ሌሊት ሌሊት ሐይቁ ውስጥ ቆመው ሲጸልዩ ያድራሉ፡፡
❤ አባ ኢየሱስ ሞዐ በሐይቅ እስጢፋኖስ በአበ ምኔትነት በቆዩባቸው 45 ዓመታት ከየገዳማቱ ቅዱሳን መጻሕፍትን በመገልበጥና በማሰባሰብ የመጀመርያው ዘመናዊ የቤተ ክርስቲያን ቤተ መጻሕፍት በሐይቅ እስጢፋኖስ ገዳም እንዲቋቋም አድርገዋል፡፡ በዚሁ ገዳም ውስጥ የመጀመርያውን የቤተ ክርስቲያን ቋሚ ትምህርት ቤት በማቋቋም 800 መነኮሳትን በትምህርተ ሃይማኖት አሠልጥነው በንቡረ ዕድነት ማዕረግ ሾመው በመላ ሀገራችን እንዲሠማሩ አድርገዋቸዋል፡፡ ከእነዚህም ተማሪዎቻቸው መካከል አቡነ ተክለ ሃይማኖት (ደብረ ሊባኖስ)፣ አቡነ ኂሩተ አምላክ (ጣና ሐይቅ ዳጋ እስጢፋኖስ)፣ አቡነ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ (ቦረና)፣ አባ በጸሎተ ሚካኤል (ቦረና)፣ አቡነ ገብረ እንድርያስ (ቦረና)፣ አቡነ ሕዝቅያስ (ቦረና)፣ አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ (ዳውንት)፣ አቡነ አሮን (መቄት)፣ አቡነ ተክለ ኢየሱስ ሞዐ (ሐይቅ)፣ አቡነ አላኒቆስ (ትግራይ)፣ አቡነ በግዑ (ሐይቅ)፣ አቡነ ሠረቀ ብርሃን (ሐይቅ)፣ አቡነ ብስጣውሮስ (ሐይቅ)፣ አቡነ ዮሴፍ (ላስታ) ዋና ዋናዎቹና በጣም ጥቂቶቹ ናቸው፡፡ ጻደቁን ንጉሥ ዐፄ ይኩኖ አምላክንም በትምህርተ ሃይማኖት አንጸውና ኮትኩተው ያሳደጉት ጻድቁ አባታችን ናቸው፡፡
❤ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ወደ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ መጥተው በሐይቁ ዳር ቆመው ሳለ ቅዱስ ሚካኤል መጥቶ በእግሩ በውኃው ላይ እየሄደ እያሳያቸው ተከትለውት እንዲሄዱ ነገራቸው። አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖትም ሐይቁን በእግራቸው ጠቅጥቀው ተራምደው ተሻግረው አቡነ ኢየሱስ ሞዐን አገኟቸው፡፡ እርሳቸውም አቡነ ተክለ ሃይማኖት ወደ እርሳቸው እየመጡ እንደሆነ በመንፈስ ዐውቀው ነበርና ሲያገኟቸው በጣም ተደስተው ከተቀበሏቸው በኋላ አመነኵሰዋቸዋል፡፡ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ እጅግ በጣም ብዙ መነኰሳትን አፍርተዋል፡፡ የመጀመሪያው መነኩሴ አባ እንጦንስ ነው፡፡ እንጦንስ መቃርስን፣ መቃርስ ጳኵሚስን፣ ጳጉሚስ ቴዎድሮስን፣ አቡነ አረጋዊንና 8ቱን ቅዱሳን አመነኰሱ፡፡ አቡነ አረጋዊም ወደ ኢትዮጵያ በ460 ዓ.ም መጥተው ክርስቶስ ቤዛን፣ አባ ክርስቶስ ቤዛም መስቀለ ሞዐን፣ መስቀለ ሞዐም አባ ዮሐኒን፣ አባ ዮሐኒም አባ ኢየሱስ ሞዐን፣ አባ ኢየሱም ሞዐም አቡነ ተክለ ሃይማኖትን አመነኰሱ፡፡ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ምን ያህል ቀደምትና ባለ ታሪክ አባት እንደሆኑ ከዚህ መረዳት ይቻላል፡፡
❤ በዮዲት ጉዲት እጅጉን ተጐድታ የነበረችው አገራችን ዳግም የወንጌሉ ብርሃን እንዲበራባት ሊቃውንት፣ እንዳይታጡባት፣ ቅዱሳት መጻሕፍት እንዳይቆነጻጸሉ፣ መነኰሳት አባቶች ወደ ደቡብ ኢትዮጵያ ወርደው ገዳማትን እንዲያስፋፉ ያደረጉት አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ለቤተ ክርስቲያናችንና ለአገራችን ትልቅ ባለውለታ ናቸው፡፡ በተለይም በሐይቅ እስጢፋኖስ ያፈሯቸውን 800 ሊቃውንት በመላዋ ኢትዮጵያ በመሰማራታቸው ዛሬ የምናያቸውን አብዛኛዎቹን ገዳማትና ቅዱሳት መጻሕፍት አቆይተውልናል፡፡ አባታችን ለ45 ዓመታት ሐይቅ እስጢፋኖስ ገዳምን በአበ ምኔትነት እያስተዳደሩ ከቆዩ በኋላ ኅዳር 26 ቀን 1292 ዓ.ም በዕለተ እሑድ ዐርፈዋል፡፡ ከአባታችከኢየሱስ
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ኅዳር ፳፮ (26) ቀን።
❤ እንኳን #ለኢትዮጵያውያኑ_ጻድቃን ታላቁን ገዳም ሐይቅ እስጢፍኖስ ለመሰረቱት #ለአቡነ+ኢየሱስ_ሞዐና ለታላቁ አባት #ለአቡነ_ሀብተ_ማርያም_ለዕረፍታቸው_በዓል፣ ለኢትዮጵያ የመጀመርያው ሊቀ ጳጳስ ለነበሩት #ለአቡነ_ሰላማ_ከሣቴ_ብርሃን ለልደት በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #ስለ_አባታችን_አቡነ_ሀብተ_ማርያም_ዕረፍት፦ ... ከዚህም በኋላ ዕለተ ሞቱ በደረሰ ጊዜ ለሞቱ ምክንያት የሚሆን ቸነፈር ያዘው፤ መድኃኔዓለም አምላካችን በዐቢይ ምስጋና ወደ እርሱ መጥቶ "ሰላም ለአንተ ይሁን ወዳጄ ሀብተ ማርያም ሆይ ዛሬ ግን ወደ አንተ የመጣሁት ከድካም ወደ ዕረፍት እወስድህ ዘንድ ነው ሰባት የጽድቅ የክብር አክሊሎችን አዘጋጅቼለሃለሁ አንደኛው ስለ ንጹሕ ድንግልናህ፣ ሁለተኛው ዓለምንና በውስጡ ያለውን ንቀህ በመኖርህ፣ ሦስተኛው ስለ ፍጹም ምንኵስናህ፣ አራተኛው ዘወትር አራቱ ወንጌላትን በማንበብህ በመጸለይህ ስለ እኔ ምክንያት፣ አምስተኛው በረኃብህ፣ ስድስተኛው በጾም ስለ ተጋደልክ፣ ሰባተኛው በልብህ ቂምና ጥላቻን ትዕቢትን ትምክህትን ባለማሳደርህና በልብህ ውስጥ ባለማስቀመጥህ፣ ስለ ንጹሕ ተልዕኮ ክነትህ ስለ ምዑዝ ዕጣንህና ስለ ንጹሕ መሥዋዕትህ ነው፤ እኒህ ሰባት አክሊላትም እያንዳንዳቸው ባለ ዐሥራ አምስት ኅብርና ጌጥ ያላቸው ናቸው። አህጉረ ገነትም በውስጧ አምስት መቶ የወርቅ አምዶች ያለው ትገባበት ዘንድ አንተና እንዳንተ ላሉ ወዳጆችህ የሚገቡበት ቤት እሰጥሃለሁ በምሰጥህም ቤት መታሰቢያህን ያደረገ በጸሎቶህ የተማፀነ ይገባል የወርቅ ጫማን፤ የእሳት መስቀልን የብርሃን ልብስን ድብቅ መናን እሰጥሃለሁ" አለው።
❤ መድኃኔዓለምም ይህንን ቃል ኪዳን ሲሰጠው ዘጠና ዘጠኙ ነገደ መላእክት በየሥርዓታቸው መጥተው ቆሙ፣ "ወዳጃችን አባ ሀብተ ማርያም ሆይ ሰላም ለአንተ ይሁን ዛሬስ በዝማሬና በማኅሌት ከፀሐይና ከጨረቃ ከከዋክብትም ሰባት እጅ ወደ ምታበራ ወደ ሰማያዊት ሀገር እንወስድህ ዘንድ ደስ ይበልህ" አሉት፤ ቅዱስ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም "ለእግዚአብሔር በሰማያት ምስጋና ይሁን በምድርም የሰውን ልጅ ለወደደውና ላፈቀረው" ብሎ አመሰገነ። ይህንንም ባለ ጊዜ አምላክ በሦስትነቱ ተገልጾ ታየው፤ "ከዮሐንስ መጥምቅ ጎን ለጎን ቀጥላ ያለችውንና ከፀሐይ እልፍ እጅ የበለጠ የምታበራውን አገር እንድሰጥህ እንሆ በማይሻር ቃሌ ማልኩልህ" አለው፣
❤ "እውነት እውነት እልሃለሁ መታሰቢያህም ያደረገ ስምህንም የጠራ ለቤተ ክርስቲያንህም ዕጣን የሰጠ ወይም ዘቢብ የሰጠ ወይን መብራት የሰጠ ከአንተ ጋር ይኖራል አራቱ ወንጌልንም ታነብ ስለ ነበር ለእያንዳንዷም የወንጌል ቃል ፍሬህን አንድ ሺህ አንድ ሺህ አደረኩልህ ይህ ቃል ኪዳን ለአመኑ ልጆችህና መታሰቢያህን ለሚያደርጉ ሁሉ ማየ ጸሎቱን ለሚጠመቁ ለሚያነቡ ለሚያስነብቡ ይህን ቃለ ኪዳን ሰጥቻለሁ" አለው።
❤ ይህንንም ካለው በኋላ ጌታችን አፋን ሦስት ጊዜ ሳመው፤ ያን ጊዜም ከመድኃኔዓለም ጣዕም ፍቅር የተነሣ ነፍሱ ከሥጋው ተለየች፤ ጌታችንም ተቀብሎ አቀፋት ከእርሱም ጋር ወደ ሰማይ አሳረጋት ያን ጊዜም በቅዱሳን ሠራዊተ መላእክት ዘንድ ታላቅ እልልታና ብዙ ደስታ ሆነ በሰማያዊ መላእክት በምድራዊያን ስውራን ቅዱሳን ዘንድ ታላቅ ደስታ ሆነ በሐሳበ ዕብራውያን በናኢብሮስ ታስሪን ወርህ 22 ቀን በኢትዮጵያ ኅዳር26 ቀን በሰማዕታተ ናግራን በዓል በ6ሺ 9መቶ 99 ዓመተ ኩነኔ በኋላ 1ሺ 499 ዓ.ም በሆነ ዘመን ዕለት የአባታችን የአቡነ ሀብተ ማርያም ነፍሱ ከሥጋው ተለየች፤ ያን ጊዜም ከአባታችን ከአቡነ ሀብተ ማርያም የሕይወት መንፈሳቸው ከወጣች በኋላ ካህናት በመልካም ልብስ ገንዘው በዝማሬ በማኅሌት ከቅዱስ አባታችን ከአቡነ ተክለ ሃይማኖት አጽም ጋር በጻድቁ መቃብር ቀበሩት። ከአባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸውም ይማረን።
ምንጭ፦ ገድለ አቡነ ሀብተ ማርያም 18፥18-27።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #አቡነ_ሰላማ_ከሣቴ_ብርሃን፡- ቅዱስ አባታችን አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በኋላ በ245 ዓ.ም በቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም ኅዳር 26 ቀን ሲወለዱ ታላቅ ብርሃን ከሰማይ ወርዶ ለ7 ቀናት አብርቷል፡፡ ቅዱሳን መላእክትም ወደ ምድር ወርደው ጻደቁ በመወለዳቸው ታላቅ ደስታን አድርገዋል፡፡ አባታችን በተወለዱ ጊዜ "ለአብ ስግለት ለወልድ ስግደት ለመንፈስ ቅዱስ ስግደት ይገባል፣ ከጨለማ ወደ ብርሃን ለአወጡኝ ቅድመ ዓለም ለነበሩ ዛሬም ላሉ ዓለምን አሳልፈው ለሚኖሩ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይገባል" ብለው ዳግመኛም "አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ" ብለው ፈጣሪያቸውን በአንድነት በሦስትነት አመስግነዋል፡፡ ቅዱስ አባታችን በሌላኛው ስማቸው ፍሬምናጦስ እየተባሉ ይጠራሉ፡፡ በ40 ቀናቸው ጌታ በተጠመቀበት በዮርዳኖስ ያጠመቋቸውና ስመ ክርስትና የሰጧቸው ሊቀ ጳጳስ "ይህ ሕፃን ለኢትዮጵያውን ሁሉ ብርሃን ይሆንላቸዋል" በማለት ትንቢት ተናግረዋል፡፡
❤ አቡነ ሰላማ በሊቀ ጳጳሱ በቅዱስ አትናቴዎስ በሚገባ ተምረው ካደጉ በኋላ በ257 ዓ.ም ከኢየሩሳሌም ወደ ኢትዮጵያ ስሙ ሜርጵዮስ ከሚባል ከአንድ ነጋዴ ጋር መጡ፡፡ ከእነሱም ጋር አድስዮስ የሚባል ልጅ ነበር፡፡ ወደ ሀገራችንም ሊመጡ የቻሉት እንዴት ነው? ቢሉ መጀመሪያ ለሰባት ወር በአንድ ሌላ አገር ኖረው ወደ ኢየሩሳሌም ሊመለሱ ሲሉ የበረሃ ሽፍቶች ሜርጵዮስንና ሌሎች መንገደኞችን ገደሏቸውና ሁለቱን ልጆች ማርከው ወስደው ስሙ አልአሜዳ ለሚባል ለአክሱም ንጉሥ ሰጡት፡፡ እርሱም አድስዮስን የቤተክርስቲያን የአልባሳትና የዕቃ ቤት ጠባቂ አድርጎ ሲሾመው ፍሬምናጦስን ደግሞ የቤተ ክርስቲያንና የሕግ ጠባቂ አደረገው-የቤተ ክርስቲያንን ሥርዓቷንና አገልግሎቷን ጠንቅቆ ያውቅ ነበርና፡፡ እርሱም በአክሱምም በተጋድሎና በትጋት ኖረ፡፡ ቅዳሜና እሁድ የዛፍ ቅጠሎችን ከመመገብ በቀር ሌላ ምግብ አይቀምስም ነበር፡፡ በየቀኑም አምስት ሺህ ስግደትን ይሰግድ ነበር፡፡ በእርሱም የተጋድሎ ዘመን ደጋግ የሆኑ ነገሥታት አብርሃና አጽብሓ ነገሡ፡፡ እነርሱም ሆኑ የኢትዮጵያ ሕዝብ ፍሬምናጦስን በጣም ይወዱት ነበር፡፡
❤ አንድ ቀን ፍሬምናጦስ የአክሱሙን ኤጲስ ቆጶስ ቅዱስ ሚናስን "ግዝረትና እምነት በእናንተ ዘንድ አለ ነገር ግን ጥምቀትና ሥጋ ወደሙ መቀበል በእናንተ ዘንድ የለም" አለው፡፡ ቅዱስ ሚናስም "ግዝረትንስ አባቶቻችን ሌዋውያን አመጡ፣ በክርስቶስ ማመንን ሕንደኬ የተባለች የኢትዮጵያ ንግሥት ጃንደረባ አመጣልን፡፡ ስለ ጥምቀትና ሥጋ ወደሙ ሐዋርያ ወደ እኛ አልተላከም ነገር ግን ያልከውን ሁሉ የሚያደርግልን የሚባርከንና የሚቀድሰን ጳጳስን ታመጣልን ዘንድ ሊቀ ጳጳሱ ወዳለበት ወደ እስክንድሪያ አገር አንተ ሂድ" አለው፡፡ ጥምቀትስ በጃንደረባው በኩል አገራችን ገብቶ ነበር ነገር ግን ገና ስላልተጠናከና ብዙ ሕዝብም አልተጠመቀም ነበርና አባታችን ፍሬምናጦስ አጠናክሮ ያልተጠመቀውን ሁሉ አጥምቆአል፡፡
❤ ከዚያንም ጊዜ ንጉሥ መልክተኞችን ልኮ ቅዱስ መርቆሬዎስን ወደርሱ አስመጣው በመዘግየቱም አድንቅ "ለአማልክት ዕጣን ለማድረግ ከእኔ ጋር ያልወጣህ የእኔን ፍቅር እንዴት ተውህ" አለው። በዚያንም ጊዜ ትጥቁንና ልብሱን ወረወረለትና ንጉሡን እንዲህ አለው "እኔ ክብር ይግባውና ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስን አልክደውም ለረከሱ ጣዖታትም አልሰግድም"። ንጉሥ ዳኬዎስም ይህን በሰማ ጊዜ እጅግ ተቆጣ እርጥብ በሆኑ የሽመል በትሮች እንዲደበድቡት አዘዘ። ሁለተኛም ከላም ቆዳ በተሠራ ጅራፍ ይገርፋት ዘንድ አዘዘ ንጉሡ እንዳዘዘ ይህን ሁሉ አደረጉበት።
❤ በዚያንም ጊዜ የአገር ሰዎች ስለ ቅዱስ መርቆሬዎስ እንዳይነሡበት ፈርቶ የቀጰዶቅያና የእስያ ክፍል ወደ ሆነች ወደ ቂሣርያ በብረት ማሠርያ አሥሮ ላከው። በዚያም እንዲአሠቃዩት አዘዘ ከአሠቃዩትም በኋላ ንጉሥ ዳኬዎስ እንዳዘዘው ራሱን በሰይፍ ቆረጡትና ተጋድሎውን ፈጽሞ በመግሥተ ሰማያት የሕይወት አክሊልን ተቀበለ። የማይጠፋ ሰማያዊ አክሊልንም ተቀዳጅቶ ወደ ዘላለም ሕይወት ከገባ በኋላ በዓለሙ ሁሉ አብያተ ክርስቲያናት ታነፁለት እግዚአብሔርም ታላላቅ የሆኑ ድንቆች ተአምራትን በውስጣቸው ገለጠ።
❤ ከተአምራቱም አንዲቱ ዑልያኖስ በነገሠ ጊዜ ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ካደ በዚያንም ወራት ቅዱስ ባስልዮስ የቂሣርያ ሊቀ ጳጳሳት ነበረ ተአምራቱ በተጻፈበት መጽሐፍ እንደተጻፈ ምእመናን በጽኑዕ ሥቃይ ዑልያኖስ ባሠቃየ ጊዜ መክሮ አስተምሮ ከስሕተቱ ይመልሰው ዘንድ ቅዱስ ባስልዮስ ወደርሱ መጣ።
❤ ዑልያኖስም ቅዱስ ባስልዮስን በአየው ጊዜ ክብር ይግባውና ጌታችንን ሰደበ ቅዱስ ባስልዮስንም አሠረው በዚያ በእስር ቤትም የቅዱስ መርቆሬዎስን ሥዕል አይቶ በፊቱ ቅዱስ ባስልዮስ ጸለየ ሥዕሉም ከቦታው ታጣ። ያን ጊዜ ወደ ዑልያኖሰሰ ሒዷልና በጦርም ወግቶ ገደለውና ወዲያውኑ ወደቦታው ተመለሰ ከጦሩም አንደበት ደም ይንጠፈጠፍ ነበር። ቅዱስ ባስልዮስም ከሀዲ ዑልያኖስን እንደገደለው አውቆ እንዲህ ብሎ ተናገረ "የክርስቶስ ምስክር ሆይ የእውነት ፀር የሆነ ዑልያኖስን ገደልከውን?" ያን ጊዜ አዎን እንደሚል ሥዕሉ ራሱን ዘንበለሰ አደረገ ቅዱስ ባስልዮስም ደስ ብሎት እግዚአብሔር አመሰገነ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ መርቆሬዎስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ ገድለ መርቆሬዎስና የኅዳር 25 ስንክሳር።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ፍትሕ ወርትዕ ተድላ መንበርከ። ሣህል ወጽድቅ የሐውር ቅድመ ገጽከ። ብፁዕ ሕዝብ ዘየአምር የብቦ"። መዝ 88፥14-15። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 20፥20-24።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ልሳነ ከለባቲከ ላዕለ ጸላእቱ። አስተርአየ ፍናዊከ እግዚኦ። ፍናዊሁ ለአምላክነ ለንጉሥ ዘውስተ መቅደስ"። መዝ 67፥23-24። የሚነበቡት መልዕክት 2ኛ ቆሮ 7፥4-12፣ 1ኛ ቆሮ 4፥12-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 5፥11-17። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 10፥17-32። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ነው። መልካም የቅዱስ መርቆሬዎስ በዓልና የነቢያት (የገና) የጾም ጊዜ። ለሁላችን ይሁንልን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ኅዳር ፳፭ (25) ቀን።
❤ እንኳን #ለታላቁ_ሰማዕት_ለቅዱስ_መርቆሬዎስ (ፒሉፓዴር) በንጉሥ ዳኬዎስ እጅ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ መታሰቢያ ዓመታዊ በዓል እግዚአብሔር አምላከ በሰላምና ጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከእስላሞች ወገን ከነበረ #ቅዱስ-መርቆሬዎስ ተአምር አድርጎ ከመለሰው #ከቅዱስ_ዮሐንስ፣ #ከአቃርዎስና_ከሮማኖስ ከመታሰቢያቸወ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #ቅዱስ_መርቆሬዎስ፦ መርቆሬዎስ ማለት የአብ ወዳጅ ማለት ነው። በሁለተኛ ትርጓሜ የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ ማለት ነው። ይህም ቅዱስ አስሊጥ ከምትባል አገር ነው እርሷም የአባቱና የአያቱ አገር ናት እርሱ ግን ተወልዶ ያደገው በሮሜ ከተማ ነው።
❤ የአባቱና የአያቱ ሥራቸው አውሬ ማደን ነበር በአንዲት ዕለትም እንደልማዳቸው ለማደን ወጡ ከገጸ ከለባት ወገንም ሁለት ወንዶች ተገናኙአቸውና የቅዱስ መርቆሬዎስን አያት ስዲሮስ በሉት። ሁለተኛም አባቱን አሮስን ሊበሉት ፈለጉ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክም ከለከላቸው "ከእርሱ የሚወጣ መልካም ፍሬ ስለ አለ አትንኩት" አላቸው።
❤ ከዚህም በኋላ የእግዚአብሔር መልአክ ዙሪያቸውን በእሳት ከበባቸው በተቸገሩ ጊዜም ወደ ቅዱስ መርቆሬዎስ አባት አሮስ መጥተው ሰገዱለት በዚያንም ጊዜ እግዚአብሔር ፍጥረታቸውን ወደገራምነት ለወጠውና እንደ በጎች የዋሆች ሆኑ አብረውትም ወደ መንደር ገቡ።
❤ ከዚህም በኋላ ቅዱስ መርቆሬዎስ በተወለደ ጊዜ ስሙን ፒሉፓዴር ብለው ጠሩት የውሻ መልክ ያላቸው በእነርሱ ዘንድ ብዙ ዘመናት የሚኖሩ ሆኑ ከዚህም በኋላ ክርስቲያኖች ሆኑ የቅዱስ መርቆሬዎስ ወላጆች አስቀድሞ አረማውያን ነበሩና የክርስትና ጥምቀትንም ጸጋ በተቀበሩ ጊዜ የቅዱስ መርቆሬዎስን አባት ኖኅ ብለው ሰየሙት እናቱንም ታቦት አሏት ፒሉፓዴርንም መርቆሬዎስ ብለው ሰየሙት። የውሻ መልክ ያላቸው ግን የእግዚአብሔር መልአክ በተገለጸላቸው ጊዜ እንደ ነገራቸው ለቅዱስ መርቆሬዎስ አባት የሚታዘዙና የሚያገለግሉ ሆኑ።
❤ ንጉሡም የኖኅንና የውሻ መልክ ያላቸውን ዜና በሰማ ጊዜ ወደርሱ አስቀረባቸው በዚያንም ጊዜ እግዚአብሔር በንጉሡ ፊት የቀድሞ ፍጥረታቸውን መልሶላቸው የንጉሡ ያቀረባቸውን ሁሉንም አራዊት አጠፏቸው። ንጉሡም ይህን በአየ ጊዜ እጅግ ፈራ የአራዊትንም ተፈጥሮአቸውን ያርቅ ዘንድ ወደ እግዚአብሔር እንዲማልድ የቅዱስ መርቆሬዎስን አባት ለመነው። እርሱም በለመነ ጊዜ ክብር ይግባውና ጌታችን ተፈጥሮአቸውን መልሶላቸው ገራሞች ሆኑ።
❤ ከዚህም በኋላ የቅዱስ መርቆሬዎስን አባት ንጉሡ ወስዶ ገዥና የሠራዊት አለቃ አድርጎ ሾመው የውሻ አርያ ያላቸውም ይታዘዙለት ነበር ከእርሳቸውም የተነሣ ሁሉም ይፈሩ ነበር። ከዚህም በኋላ የቅዱስ መርቆሬዎስን አባት የሾመውን ንጉሥ ይወጋ ዘንድ ከሀዲ ንጉሥ ተነሣ ንጉሡም ከጦር አባት ወደ ጦርነት ላከው። ከሀዲው ንጉሥ ግን እነዚያን የውሻ አርያ ያላቸውን አባብለውና ሸንግለው ወደርሱ የመጧቸው ዘንድ ወታደሮችን ላከ በአመጧቸውም ጊዜ ሃይማኖታቸውን ይለውጡ ዘንድ አብዝቶ ሸነገላቸው ባልሰሙትም ጊዜ ሊአሠቃያቸው ጀመረ አንዱ አምልጦ ሸሽቶ ወደ ጌታው ሔደ ሁለተኛውም በሰማዕትነት ሞተ።
❤ ከጦር ሜዳ የቅዱስ መርቆሬዎስ አባት በመለሰ ጊዜ ሚስቱንና ልጁን ፈለጋቸው ግን አላገኛቸውም ንጉሡ የሱ ወገኖች ድል እንደሆኑ በሰማ ጊዜ የቅዱስ መርቆሬዎስ አባት መኰንኑ የሞተ መስሎት ነበርና የቅዱስ መርቆሬዎስን እናት ወስዶ ሊአገባት ፈለገ ከንጉሥ ወታደሮችም አንዱ ንጉሡ ያሰበውን በጽሞና ነገራት። እርሷም ይህንኑ ወታደር ከአገር ውስጥ በሥውር ያወጣት ዘንድ ለመነችውና ከልጇ ከብፁዕ መርቆሬዎስ ጋር ወጥታ ወደ ሌላ አገር ሔደች። ንጉሡም ከእርሱ የሆነውን የመኰንኑም የመርቆሬዎስን አባት ሚስቱን ለማግባት ማሰቡን እንዳይነግሩት አዘዘ የውሻ መልክኮች ያላቸው ከእርሱ ጋር እንዳሉ የተቆጣም እንደሆነ እንደሚአመጣቸውና አገሮችን ያጠፋሉ ብሎ ይጠራጠራልና ስለዚህ እጅግ ይፈራዋል።
❤ ከዚህም በኋላ ደግሞ በንጉሡ ላይ ጦርነት ተነሣ የቅዱስ መርቆሬዎስም አባት ወደ ጦርነት ወጣ በእግዚአብሔርም ፈቃድ ይዘው ማረኩት ወደ ሮሜውም ንጉሥ አቀረቡት ንጉሡም ክርስቲያን ነበርና የተማረከው መኰንን ክርስቲያን መሆኑን በአወቀ ጊዜ አልገደለውም በክብር አኖረው እንጂ እጅግም ወደደውና ከጥቂት ቀኖች በኋላ በመርዶሳውያን አገሮች ሁሉ ላይ ገዥ አድርጎ ሾመው።
❤ ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፈቃድ ሚስቱና ልጁ መርቆሬዎስ ወዳሉበት አገር ደረሰ ሚስቱም በቤተ ክርስቲያን ደጃፍ በአየችው ጊዜ ባሏ እንደሆነ አወቀችው እርሱ ግን አላወቃትም በአንዲትም ዕለት እርሱና ጭፍሮቹ ከእንግዳ ማረፊያ ቤት በወጡ ጊዜ ልጅዋን መርቆሬዎስን ወስዳ ያማሩ ልብሶችን አልብሳ ሒዶ ከመኰንኑ ፈረስ ላይ እንዲቀመጥ አዘዘችው እርሱም አባቱ ነው በተቀመጠም ጊዜም ጭፍሮች ይዘው ወደ መኰንኑ ፊት አቀረቡት መኰንኑም ልጁ እንደሆነ አላወቀምና በእርሱ ላይ ተቆጣ።
❤ የመርቆሬዎስ እናት መጥታ "ጌታዬ ሆይ እኛ መጻተኞች ነን አንተም መጻተኛ እንደሆንክ በአወቅሁ ጊዜ ልጅህ ሁኖ ልጄ ከአንተ ጋር እንዲሆን አሰብኩ" አለችው። እርሱም ጠየቃት እንዴት እንደተሰደደችም መረመራት እርሷም ሚስቱ እንደሆች ነገረችው በዚያንም ጊዜ አወቃት ልጁን መርቆሬዎስንም አወቀው አጅግም ደስ ብሏቸው እግዚአብሔር አመሰገኑት ያንንም የእንግዳ ማረፊያ ቤት ቤተ ክርስቲያን አደረጉት እግዚአብሔርም እያመሰገኑ በአንድነት ኖሩ።
❤ ከዚህም በኋላ አባቱና እናቱ በሞቱ ጊዜ ንጉሡ ቅዱስ መርቆሬዎስን ወስዶ በአባቱ ፈንታ በመርዶሳውያን አገር ላይ ሾመው ቅዱስ መርቆሬዎስም መኰንንነትን በተሾመ ጊዜ ያ ገጸ ከልቡ ከርሱ ጋር ነበር ወደ ጦርነትም አብሮት የሚወጣ ሆነ። ለመዋጋትም በሚሻ ጊዜ የቀድሞ የአራዊት የሆነ ተፈጥሮውን እግዚአብሔር ይመልስለት ነበር ማንም ሊቋቋመው የሚችል የለም። ለቅዱስ መርቆሬዎስም ታላቅ የድል አድራጊነት ኃይል ተሰጠው ዜናውም በሁሉ ቦታ ተሰማ ከቤተ መንግሥት ሰዎችም ከፍ ከፍ አለ።
❤ እንዲህም ሆነ ያን ጊዜ በዚያን ወራት በሮሜ አገር ጣዖትን የሚያመልክ ዳኬዎስ የሚባል ንጉሥ አለ። ጠላቶቹም የበርበር ሰዎች ተነሡበት እርሱም ከእርሳቸው ጋር ሊዋጋ ሠራዊቱን ሰብስቦ ወጣ እነርሱ ግን እንደ ባሕር አሸዋ ብዙ ነበሩ ብዛታቸውንም በአየ ጊዜ ደንግጦ እጅግ ፈራ ቅዱስ መርቆሬዎስም "እግዚአብሔር ያጠፋቸው ዘንድ በእጃችንም አሳልፎ ሊሰጣቸው አለውና አትፍራ" አለው።
❤ ከዚህም በኋላ ቅዱስ መርቆሬዎስ የእግዚአብሔርን መልአክ በውጊያው ውስጥ አየው የተሳለ ሰይፍም በእጁ ውስጥ አለ ያቺንም ሰይፍ ሰጠውና እንዲህ አለው "ጠላቶችህን ድል በአደረግህ ጊዜ ፈጣሪህ እግዚአብሔር አስበው"። ጠላቶቹንም ድል አድርጎ በሰላም ተመለሰ መልአኩም ዳግመኛ ተገልጦለት "ለምን ፈጣሪህን የእግዚአብሔርን ስም መጥራት ረሳህ" አለው።ጦርነቱም ከተፈጸመ በኋላ ንጉሥ ዳኬዎስ ለጣዖታቱ ዕጣን በማሳረግ በዓልን ሊያደርግ ወደደ ቅዱስ መርቆሬዎስም ለበዓል ማክበር አብሮት አልወጣም ወደ ቤቱ ሔደ እንጂ ሰዎችም ቅዱስ መርቆሬዎስ እንዳልመጣና ዕጣንን በማሳረግም እንዳልተባባረ አስረዱት።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ አሐዱ አምላክ አሜን። ❤
❤ #ኅዳር ፳፫ (23) ቀን።
❤ እንኳን #ከሰባ_ሁለቱ_አርድእት አንዱ ለሆነው በሐዋርያው #በቅዱስ_ጴጥሮስ_እጅ_ለተጠመቀ ለመቶ አለቃ ለነበረው #ለጻድቁ_ቅዱስ_ቆርኔሌዎስና የስሙ ትርጓሜ የእግዚአብሔር አገልጋይ ለሆነ #ለነቢዩ_ቅዱስ_አብድዩ_ለዕረፍታቸው_በዓል በሰላም አደረሰን። ከእነዚህ ቅዱሳን እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
❤ #መቶ_አለቃው_ጻድቁ_ቅዱስ_ቆርኔሌዎስ፡- ይህም ቅዱስ የፍልስጤም ክፍል በሆነች በቂሣርያ የመቶ አለቃ ሆኖ የተሾመ ነው፡፡ እርሱም አስቀድሞ ከዋክብትን ሲያመልክ የነበረ ነው፡፡ እንደርሱ ማንም ሊአደርግ የማይቻለውን የሚያመልካቸው አማልክቶቹም ቢሆኑ በሐዋርያት እጅ የሚደረገውን የተአምራታቸውና የስብከታቸውን ዜና በሰማጊዜ ወዲያውኑ ለአማልክት መስገድን አቆመና በጾም በጸሎት ተወስኖ ለድኆችና ለችግረኞች የሚመጸውት ሆነ፡፡ ሁል ጊዜም በጸሎቱም "አቤቱ እውነተኛው አምላክ ሆይ! እኔ አንተን ከማወቅ ጎደሎ ነኝና አንተ ግን የቀናውን መንገድ ምራኝ" እያለ ይለምን ነበር፡፡ ይቅር ባይ ቸር እግዚአብሔርም ቆርኔሌዎስን ይቅር ብሎት ልመናውን ተቀብሎት መልአኩን ላከለት፡፡ እርሱም መልአኩን ባየው ጊዜ ደነገጠ፡፡ መልአኩም "ቆርኔሌዎስ ሆይ! ጸሎት ልመናህ ምጽዋትህ መልካም መታሰቢያ ሆኖ ወደ እግዚአብሔር ዐርጓልና ደስ ይበልህ፡፡ አሁንም በጫማ ሰፊው በስምዖን ቤት የሚኖረውን ስምዖን ጴጥሮስን ይጠሩልህ ዘንድ ሰዎችን በባሕር አቅራቢያ ወዳለች ኢዮጴ ከተማ ላክ" አለው። ቆርኔሌዎስም መልአኩ እንደነገረው ቅዱስ ጴጥሮስን ከስመጣው በኋላ ከእግሩ በታች ሰገደለት፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስም አነሣውና "እኔም እንደ አንተ ሰው ነኝ" አለው፡፡ ወደ ቤትም በገቡ ጊዜ ቆርኔሌዎስም ቤት ብዙ ሰዎችን ተሰብስበው አገኘ፡፡ ቆርኔሌዎስም ቅዱስ ጴጥሮስን ያስጠራበትን ምክንያት መልአኩም ተገልጦለት የነገረውን ሁሉ በዝርዝር ከነገረው በኋላ "እግዚአብሔር ያዘዘህን ሁሉ ልንሰማ እነሆ ሁላችን በፊትህ አለን" አለው፡፡ ሐዋ10፥1-31፡፡
❤ ቅዱስ ጴጥሮስም አንደበቱን ገልጦ የጌታችንን ሰው የመሆኑን ምሥጢር መከራ መስቀሉን፣
ሞቱ፣ ትንሣኤውን ፣ዕርገቱንና ዳግመኛም ለፍርድ እንደሚመጣ በግልጽ አስተማራቸው፡፡ ቆርኔሌዎስም በዚህ ጊዜ ከነቤተሰቡ በጌታችን አምኖ ተጠመቀ፡፡ ከዚያ የነበሩ ብዙ አሕዛብም አምነው ተጠመቁ፡፡ ከዚህም በኋላ ቆርኔሌዎስ ይህን ዓለም ለመግዛት የተሾመውን ሹመቱን ትቶ የቅዱስ ጴጥሮስ ተከታይ ሆነ፡፡ ሐዋርያውም ቆርኔሌዎስን እጆቹን ጭኖ በእስክንድርያ አገር ላይ ኤጲስቆጶስነት ሾመው፡፡
❤ ቅዱስ ቆርኔሌዎስም በእስክንድርያ ወንጌልን እየሰበከ ብዙ ጣዖታት የሚያመልኩ ሰዎችን ወደ ቀናች ሃይማኖት መለሳቸው፡፡ እያስተማረ መኰንኑን ዲሜጥሮስን ጨምሮ ብዙዎችን አሕዛብ አጠመቃቸው። በፊታቸውም ብዙ ተአምራትን ያደርግ ነበር፡፡ እግዚአብሔርን ሲያገለግል ኖሮ በዚህች ዕለት በሰላም ዐረፈ፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ መጽሐፍ ቅዱስና ስንክሳር የኅዳር 23።
✝ ✝ ✝
❤ #ቅዱስ_አብድዩ፦ ይህም ቅዱስ ከጠፍ በረሀ አቅራቢያ ከአለች ሱሳም ከምትባል አገር ካሉ ሰዎች ወገን ነው። ለነቢይ ቅዱስ ኤልያስ ደቀ መዝሙሩ ሁኖ ብዙ መከራን በእርሱ ላይ መጣውን ታግሦ ከመከራውም በትዕግሥቱ ዳነ።
❤ ይህም ኤልያስን የተለማመጠና ኤልያስም አዝኖለት አብሮት ወደ ንጉሥ አክዓብ የሔደለት ሦስተኛው የሃምሣ አለቃ ነው። ከዚህም በኋላ ምድራዊ ንጉሥን ማገልገልን ትቶ ነቢይን ሆነ የትንቢቱንም ወራት አድርሶ በሰላም አረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በነቢዩ አብድዩ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ ስንክሳር የኅዳር23።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ለከ_ብእሴ_ሐዲስ_መርዓ። ቆርኔሌዎስ ዋሕድ እምነ አርድእት ፸ዓ። ኀቤከአ ከመ አስተበቊዐ። ይጠይቅ አርአያከ ወአምሳሊከ ኅቡአ። ኬንያ ሥዕልከ መዊቶ ተንሥአ"።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ለአብድዩ_መንፈስ_አእምሮ_ለባሲ። በውሣጤ በዓት ዘኅብአ ነቢያተ እስራኤል ይሴሲ። እንዘ ያጤይቅ ምጽአቶ በከዊነ አምላክ ወብእሲ። ይቤ በአፉሁ እግዚአብሔር ነጋሢ። ለእለ ተኀርዩ መድኃኒተ በጽዮን እሬሲ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የኅዳር_23።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ወበኀቤየሰ ፈድፋደ ክቡራን አዕርክቲከ እግዝኦ። ወፈድፋደ ፀንዑ እምቀደምቶሙ። እምኌቆሙ እምኆፃ ይበዝኁ"። መዝ 138፥17-18። የሚነበቡት መልዕክታት ዕብ 11፥32-ፍ.ም፣ 2ኛ ጴጥ 1፥19-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 10፥23፥34። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 10፥32-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ ቅዳሴ ነው። መልካም የቅዱስ ቆርኔሌዎስና የነቢዩ የቅዱስ አብድዩ የዕረፍታቸው በዓልና የነቢያት (የገና) የጾም ጊዜ። ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ኅዳር ፳፪ (22) ቀን።
❤ እንኳን በንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ እጅ ሰማዕትነት ለተቀበሉ በድዮማ ከተማ አረምያ ከምትባል አገር ለሆኑ #ለቅዱሳን_ለቆዝሞስና_ለድምያኖስ ለወንድሞቻቸው #ለአላድዮስ_ለአቢሞስ_ለአብራንዮስና ለእናታቸው #ለቅድስት_ቴውዳዳ_ለዕረፍታቸው_በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ #ከቅዱስ_ቆዝሞስ ማኅበር #ሰማዕታት_ከሁለት_መቶ_ስልሳ_ሁለት ወንዶችን፣ #ከአርባ_ዘጠኝ_ሴቶችና_ከቀሌምንጦስ ዕረፍት እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
❤ #ቅዱሳን_ቆዝሞስና_ድምያኖስ ወንድሞቻቸው #አንቲቆስ_ዮንዲኖስና_አብራንዮስ እናታቸው #ቅድስት_ቴዌዳዳ፦ እሊህም ድዮማ ከምትባል ከተማ ስለ እግዚአብሔር ልጅ የታነፀች ግምብ ከአለችበት አረምያ ከምትባል አገር ናቸው። እናታቸውም ቴዌዳዳ እግዚአብሔርን የምትፈራና የምትራራ መጻተኞችንና ድኆችን የምትወዳቸው የምትረዳቸው ናት አባታቸውም ከሞተ በኋላ ልጆቿን እያስተማረች አሳደገቻቸው። እሊህም ሁለቱ ቆዝሞስና ድምያኖስ የሕክምና ጥበብን ተምረው በሽተኞችን ያለ ዋጋ የሚፈውሱአቸው ይልቁንም ድኆችን አብዝተው የሚረዷቸው ሆኑ። ወንድሞቻቸው ሦስቱ ግን ወደ ገዳም ሒደው መነኰሱ በጾምና በጸሎትም ተጠመዱ።
❤ ከአባ አጋግዮስ አደራ በአስጠበቀው በንጉሠ ቊዝ ልጅ ምክንያት ዲዮቅልጥያኖስ ክዶ የረከሱ ጣዖታትን በአመለከ ጊዜ በምዕመናን ላይ መከራ ሆነ ገንዘብ ወዳጅ አጋግዮስ ብዙ ወርቅን ተቀብሎ የንጉሠ ቊዝን ልጅ ወደ አባቱ ልኮታልና ከዚህም በኋላ የንጉሠ ቊዝን ልጅ ዲዮቅልጥያኖስ ዳግመኛ ከጦር ሜዳ አግኝቶ ማረከው እርሱንም ንጉሡን ልጅ ሠውሮ አባ አጋግዮስን ጠራው ያንንም አደራ የሰጠውን የንጉሠ ቊዝን ልጅ እንዲአመጣ አዘዘው አጋግዮስም ሙቶ ተቀብሮአል ብሎ በሐሰት ተናገረ በዚያንም ጊዜ በመሠዊያው ፊት አማለው እሳትም ከሰማይ ወርዳ እንደምታቃጥለው ጠበቀ የእሳትም መውረድዋ በዘገየ ጊዜ ወርቅን በእሳት አቅልጦ አጠጣውና አቃጠለው ስለዚህም ከወርቅና ከብር የተሠሩ ጣዖታትን አመለከ።
❤ ቆዝሞስና ድምያኖስ በአገሩ ሁሉ ስለ ክርስቶስ እነርሱ እንደሚያስተምሩ ዲዮቅልጥያኖስ በሰማ ጊዜ ወደርሱ እንዲአቀርቧቸው አዘዘ በደረሱም ጊዜ ለአገረ ገዢው ለሉልዮስ እንዲአሠቃያቸው ሰጠው። እነርሱም በብዙ ሥቃዮች ማሠቃየትን ጀመረ በእሳት የሚያቃጥልበት ጊዜ አለ በግርፋት የሚገርፍበት ጊዜ አለ ሦስት ወንድሞችም እንዳሏቸው ሰምቶ እነርሱንም ወደርሱ አስመጣቸውና አምስቱንም በመንኰራኵር ውስጥ እንዲአሠቃዩአቸው አዘዘ። ከዚህም በኋላ ከእሳት ውስጥ ጨምሩዋቸው በውስጡም ሦስት ቀኖችና ሌሊቶች ኖሩ ያለ ጥፋትም በጤንነት ወጡ ዳግመኛም ከብረት አልጋ ላይ አስተኝተው ከበታቻቸው እሳቱን አነደዱ እግዚአብሔርም ያለ ጥፋት ጠበቃቸው።
❤ መኰንኑም እነርሱን ማሰቃየት በሰለቸው ጊዜ ወደ ንጉሥ መለሳቸው ንጉሡም ዳግመኛ ታላቅ ሥቃይን አሠቃያቸው ቴዎዳዳ እናታቸውም የምታስታግሣቸው ንጉሡንና የረከሱ ጣዖቶቹን የምትረግም ሆነች። በዚያንም ጊዜ አንገቷን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበለች ሥጋዋ ግን በምድር ላይ ወድቆ ነበር ቆዝሞስም እንዲህ ብለሸ ጮኸ "የዚች አገር ሰዎች ሆይ ይችን አሮጊት መበለት ሥጋዋን አፈር አልብሶ ይሠውራት ዘንድ ከውስጣችሁ ርኅራኄ በልቡ ያደረበት የለምን?" የህርማኖስ ልጅ ቅዱስ ፊቅጦርም በሰማ ጊዜ ተደፋፍሮ ሥጋዋን ገንዞ ቀበራት።
❤ ንጉሡም እነርሱን ማሠቃየት በሰለቸ ጊዜ ራሶቻቸውን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ የሰማዕትነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበሉ። ከመከራውም ዘመን በኋላ ቤተ ክርስቲያን ተሠርታላቸው ሥጋቸውን በውስጧ አኖሩ ከእርሳቸውም ድንቆች የሆኑ ብዙዎች ተአምራት ተገለጡ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በእሊህ በቅዱሳን ሰማዕታት ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ወይርአዩ አሕዛብ በቅድመ አዕይንቲነ። በቀለ ደሞሙ ለአግብርቲከ ዘተክዕወ። ይባዕ ቅድሜከ ዐሮሙ ለሙቁሓን"። መዝ 78፥10-11። የሚነበቡት መልዕክታት 2ኛ ቆሮ 7፥1-5፣ ያዕ 1፥2-17 እና የሐዋ ሥራ 17፥2-13 የሚነበበው ወንጌል ማቴ 10፥9-18። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ነው። መልካም የጾም ጊዜና በዓል።ለሁላችን ይሁንልን።
በአጫብር ስም በሰንበት ት/ቤቶች የሚሰጥ ስልጠናን እግድ እንዳልተነሳ የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጽ/ቤት አስታወቀ።
በ16 /3 /2018ዓ.ም በደብዳቤ ቁጥር 1/545/2018ዓ.ም ከመንበረ ፓትሪያሪክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የወጣውን ደብዳቤ መሠረት በማድረግ በአጫብር ስም በሰንበት ት/ቤቶች የሚደረግ ጥናቶችን በተመለከተ የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔ እንደተሻረ አድርገው አንድ አንድ ግለሰቦች በማህበራዊ ሚዲያ የሐሰት መረጃ እያሰራጩ መሆኑን ተመልክተናል።
የአንድነቱን ጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔ ተከትሎ መጋቤ ሃይማኖት ዲበኩሉ ኀየሰ ነሐሴ 26/2017ዓ.ም ለጠቅላይ ቤተክህነት ባሰገቡት ማመልከቻ መነሻነት በትምህርት እና ስልጠና ማሰልጠኛ መምሪያ በኩል የማጣራት ስራ ተከናውኗል ። በሂደቱም የትምህርት እና ማስልጠኛ መምሪያ ኃላፊዎች መጋቤ ሃይማኖት ዲበ ኩሉ፣ የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ኃላፊ ፣ የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ኃላፊ የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጽ/ቤት ተወካዮች እና ሌሎች በርዕሰ ጉዳዩን ለመከታተል የመጡ አባቶች በተገኙበት ሰፊ ውይይት ተካሂዷል።
በውይይቱ የተነሱ ጭብጦች በቅድስት ቤተክርስትያን አጫብርን እንዲያስተምሩ የተፈቀደላቸው መጋቢ ሃይማኖት ዲበኩሉ ኀየሰ በአዲስ አበባ አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ ሰንበት ት/ቤቶች ጥናት እንዲያቆሙ የተላለፈው ውሳኔ እሳቸውን ይመለከታል ወይስ አይመለከትም የሚል ሲሆን በውይይቱም አሁን ያለው በአጫብር ስም የሚደረገው ጥናት እና ትእይንት በከፍተኛ መልኩ ቤተክርስትያንን እያስተቸ የሚገኝ መሆኑ እና እግዱ ተገቢ መሆኑንን በውይይቱ ላይ የተሳተፋ አካላት በሙሉ የተስማሙበት ሲሆን በተለይም መጋቢ ሃይማኖት ዲበኩሉ ኅየሰ እኔም በማየው ነገር አዝናለሁ አጫብር እንዳስጠና ቅዱስ ሲኖዶስ የፈቀደው ለእኔ ብቻ ነው ። ከዛ ውጪ የሚደረገውን ጥናት እኔም እቃወማለሁ የኔ ጥያቄ ለምን መስመር የሳተው ነገር ታገደ አይደለም እኔ የተፈቀደልኝ ሆኖ እያለ ለማስጠናት ስላልቻልኩ እሱ እንዲስተካከልልኝ ነው በሚል በሰንበት ት/ቤቶችም ሆነ በሌሎች ባልተፈቀደላቸው አስጠኝዎች የሚደረገውን እቃወማለሁ ከሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጋርም በጋራ እሰራለሁ በሚል ሀሳባቸውን ገልጸዋል።
የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተወካዮች በኩል የጉዳዩ መስመር መልቀቅ እና ተጠያቂነት በሌለው መልኩ በየቦታው ምንም አይነት ፈቃድ ከቅዱስ ሲኖዶስ ሳይሰጣቸው በአጫብር ስም የሚደረጉ ጥናቶች የሚቀርቡ ወረቦች ቤተክርስትያንን በከፍተኛ መልኩ እያስተቹ መሆኑን አጽኖት ሰጥቶ ያቀረቡ ሲሆን በወቅቱም ሁሉም ተወያይ አካላት በጉዳዩ አሳሳቢነት ላይ የተስማማ ሲሆን ለቀጣይ መፍትሔ ጥናት እንደሚያስፈልግ ከስምምነት ላይ የተደርሷል።
መጋቢ ሃይማኖት ዲበኩሉኀየሰ የሚሰጡትን ጥናት በተመለከተ አንድነቱ በአጫብር ስም የሚደረግ እንጂ ቤተክርስትያን የፈቀደችላቸውን አባት አይመለከትም ፣ ነገር ግን አካሄድላይ በተመለከተ ሰንበት ት/ቤት ለማስጠናት የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ እና የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት በማያውቀው መልኩ ሁለተኛ አደረጃጀት መፍጠር ስህተት መሆኑን እና የትኛውንም ትክክለኛ ጥናት ከማደራጃው እና ከአንድነቱ ጋር ብቻ በመናበብ እንዲቀጥል በወቅቱ በነበረው ውይይት ከስምምነት ተደርሷል።
በዚህም መሰረት ከላይ በተጠቀሰው ደብዳቤ ለመጋቢ ሃይማኖት ዲበኩሉ ኀየሰ ማስጠናት የሚችሉ መሆኑን የሚገልጽ እና ይህንንም ሲፈጽሙ ከማደራጃ መምሪያው እና ከአዲስ ከሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጋር ተናበው መሆን እንዳለበት የሚገልጽ እንጂ በአጫብር ስም በሰንበት ት/ቤቶች የሚሰጥ ስልጠናን የሚመለከት አለመሆኑንን የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጽ/ቤት አሳውቋል።
አሁንም በጠቅላላጉባኤው ውሳኔ መሠረት ማንም ሰንበት ት/ቤት በአጫብር ስም የሚደረግ ስልጠና የተከለከለ ሲሆን በመጋቢ ሃይማኖት ዲበኩሉ ኀየሰ በኩል የሚሰጠው ስልጠና የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ እና የአዲስ አበባ ሰንበት ትቤቶች አንድነት ጋር በመመካከር ሲፈቀድ ብቻ መሆኑን እናሳውቃለን ሲል የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጽ/ቤት አስታውቋል።
❤ ከዚህም በኋላ አገሪቱን ማጥፋትን ስለ አባ ዮሐንስ ይተው ዘንድ መልሱን ለመኰንኑ ንጉሡ ጽፎ ደብዳቤዋን ወደ ደመናው ወረወራት የተሰበሰቡትም እያዩ እጅ ተቀበለችውና ወደ ደመናው ገባች ወዲያውኑ አባ ዮሐንስ በዚያች ደመና ወደበዓቱ ተመለሰና በማግሥቱ ያቺን ደብዳቤ ለመኰንኑ ሰጠው በላይዋም የንጉሡ ፊርማውና ማኅተሙ አለ በአያትና በአነበባት ጊዜ ደነገጠ አደነቀም ስለ አገሪቱ ድኅነትም እግዚአብሔርን እያመሰገነ ወደ አገሩ ተመለሰ። የንጉግሥ ዘመድ የሆነች የከበረች ሴት ዜናውን በሰማች ጊዜ ከደዌዋ ይፈውሳት ዘንድ ወደርሱ መጣች በጸሎቱም ተፈወሰች።
❤ ከዚህም በኋላ ንጉሥ ቴዎዶስዮስ በሞተ ጊዜ መናፍቁ መርቅያን ነገሠ። ቅዱስ አባ ዲዮስቆሮስንም አሠቃየው። የቀናች ሃይማኖትን ስለመለወጡ አባ ዮሐንስ እየዘለፈና እየረገመው ወደ ርሱ ደብዳቤ ላከ ከጥቂት ወራትም በኋላ እግዚአብሔር ቀሠፈው። ለእርሱም ዕድሜው መቶ ሃያ አምስት ዓመት ሲሆነው ዕረፍቱ እንደደረሰ አወቀ እየጸለየም ግምባሩን በምድር አስነክቶ ሰገደ ነፍሱንም በእግዚአብሔር እጅ ሰጠ ከመቃብሩም ቊጥር የሌላቸው ድንቆች የሆነ ብዙዎች ተአምራት ተገለጡ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ አባት ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የኅዳር 21 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ለኪ_ማርያም_እምነ። ዘሰመናይናኪ ጸወነ። ሶበ እምርኁቅ ርእየ ዘጽላሎትኪ ስነ። ለቢሶ ዳዊት ልብሰ ክብር ዘየሐይድ ዐይነ። ቅድመ ታቦተ ሕግ ኀለየ ወዓዲ ዘፈነ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የኅዳር _21።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ዕግትዋ ለጽዮን ወሕቀፍዋ። ወተናገሩ በውስተ ማኅፈዲሃ። ደዩ ልበክሙ ውስተ ኃይላ"። መዝ 47፥12። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 23፥1-ፍ.ም።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "እስመ ሐረያ እግዚአብሔር ለጽዮን። ወአብደራ ከመ ትኩኖ ማኅደሮ። ዛት ይዕቲ ምዕራፍየ ለዓለም"። መዝ 131፥13-14። የሚነበቡት መልዕክታት 2ኛ ቆሮ 6፥12-ፍ.ም፣ 1ኛ ጴጥ 2፥5-11 እና የሐዋ ሥራ 7፥44-59። የሚነበበው ወንጌል # ማቴ 21፥42-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ የእመቤታችን የማርያም ቅዳሴ ነው። መልካም የጽዮን ማርያም በዓልና የጾም ጊዜ ። ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ኅዳር ፳፩ (21) ቀን።
❤ እንኳን #ለእናታች_ለእመቤታችን_ለቅድስት_ድንግል_ማርያም_ታቦተ_ጽዮን የፊልስጥኤማውያን ጣዖት ዳጎንን ለሰባበረችበት (ታሪኩ በመጽሐፍ ቅዱስ # 1ኛሳሙ 5)፣ #ወደ_ኢትዮጵያ_ገብታ_አክሱም ለመጀመርያ ጊዜ ለከበረችበትና ታቦተ ጽዮን ከነበረችበት ድንኳን ወጥታ ማንም ካህን ሳይሸከማት #በተአምራት_አብርሃና_አጽብሓ ወዳሠሩላት ቤተ መቅደስ ራሷ በመንፈስ ቅዱስ ገብታ ለተገኘች ለዓመታዊ መታሰቢያ በዓልና ለኢትዮጽያዊው ጻድቅ #ለአቡነ_ተወልደ_መድኅን ለበዓላቸው መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከሮሜ አገር ከሆነ ተአምራት ከሚያደርግ (ከገባሬ መንክራት) #ከቅዱስ_ጎርጎርዮስ ዕረፍት፣ ከእስክድርያ ሃምሳ አራተኛ ሊቀ ጳጳስ #ከአባ_ቆዝሞስ ዕረፍት ከእስሙናይ አገር ሰማዕታት #ከእልፍዮስ_ከዘኬዎስ_ከሮማኖስ፣_ከዮሐንስ፣ #ከፊቅጦርና_ይስሐቅ ከመታሰቢያቸው፣ ከብርሌና ከብርጭቆ ሠሪዎች ልጅ ከሆነ ከአስዩጥ ሀገር #ከቅዱስ_አባት_ከአባ_ዮሐንስ_ዕረፍትና፣ ጫብሬ ከምትባል ከአገር ድልበት #ከቅድስት_ዲቦራ ዕረፍት እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
❤ በዚች ቀን #የእመቤታችን_የቅድስት_ድንግል_ማርያም_የበዓልዋ_መታሰቢ ነው። በጸሎቷ የሚገኝ በረከቷም ከሁላችን የክርስቲያን ወገኖች ጋር ይኑር ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #የሮሜ_አገር_የሆነ_ገባሬ_መንክራት #ቅዱስ_ጎርጎርዮስ፦ ይህም ቅዱስ ከታናሽነቱ ጀምሮ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት የቀናች ሃይማኖትንም ተምሮ እውነተኛ ክርስቲያን ሆነ። ከዚህም በኋላ የዚህን ዓለም ኃላፊነት የማታልፍ የመንግሥተ ሰማያትንም ኑሮ አሰበ ኀሳቡንም ሁሉ ስለ ነፍሱ ድኅነት አደረገ።
❤ የዚያችም አገር ኤጲስቆጶስ በኤጲስቆጶስነት ሥራ ይረዳው ዘንድ ለመነው እርሱ ግን አልፈቀደም ከውዳሴ ከንቱ የሚሸሽ ሁኗልና ወደ ገዳምም ገብቶ ጽኑዕ የሆነ ተጋድሎንም መጋደል ጀመረ። የዚችም አገር ኤጲስቆጶስ በዐረፈ ጊዜ ኤጲስቆጶስ የሚያደርጉት ፈልገው አጡ ስለዚህም ተሰብስበው ሳሉ የመለኮትንም ነገር የሚናገር ጎርጎርዮስ ከእርሳቸው ጋር ሳለ ገዳማዊ ጎርጎርዮስን ፈልጋችሁ በእናንተ ላይ ሹሙት የሚል ቃል ከሰማይ ወደ እነርሱ መጣ። በበረሀም ውስጥ በፈለጉት ጊዜ አላገኙትም እየፈለጉትም ብዙ ቀን ኖሩ እርሱ ግን በአቅራቢያቸው ይኖር ነበር። ባላገኙትም ጊዜ በአንድ ምክር ተስማምተው በሌለበት ወንጌል ይዘው በላያቸው ኤጲስቆጶስነት ሾሙት ስሙንም የመለኮትን ነገር በሚናገር በጎርጎርዮስ ስም ጎርጎርዮስ ብለው ሰየሙት።
❤ ከዚህም በኋላ የእግዚአብሔር መልአክ ለቅዱስ ጎርጎርዮስ ተገልጦ "ተነሥተህ ወደ እነርሱ ሒድ እነሆ በላያቸው ኤጲስቆጶስነት ሹመውልሃልና ይህም ከእግዚአብሔር የሆነ ነው" አለው። ያን ጊዜም ወደ እነርሱ ወረደ የአምላክን ትእዛዝ መተላለፍ ፈርቷልና በአዩትም ጊዜ ወጥተው በታላቅ ክብር ተቀበሉት የሹመቱንም ሥርዓት ፈጸሙ። እግዚአብሔርም ቊጥር የሌላቸው ብዙዎች ተአምራትን በእጆቹ ገለጠ ስለዚህ ገባሬ መንክራት ጎርጎርዮስ ተብሎ ተጠራ።
❤ ከብዙዎች ተአምራቱም አንዲቱ ሁለት ወንድማማቾች ነበሩ ከእርሷም ብዙ ዓሣዎችን የሚያጠምዱባት ታናሽ ባሕር ነበረቻቸው አንዱም አንዱ የኔ ናት በማለት እርስ በርሳቸው ተጣሉ ስለዚችም ባሕር በመካከላቸው ይፈርድ ዘንድ ወደ ቅዱስ ጎርጎርዮስ ለመሔድ ተስማሙ እርሱም ከሁለት ተካፈሉ ብሎ አዘዛቸው እንዳዘዛቸውም ባልተስማሙ ጊዜ ስለዚች ባሕር እግዚአብሔርን ለመነው በዚያንም ጊዜ ባሕሪቱ ደርቃ የምትታረስ ምድር ሆነች ስለሚደረጉ ድንቆች ተአምራቴ ዜናው በሁሉ አገር ተሰማ በጎ አገልግሎቱንም ከፈጸመ በኋላ በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ቅዱስ አባት በገባሬ መክራት ጎርጎርዮስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #የብርሌና_የብልጭቆ_ሠሪዎች_ልጅ #አባ_ዮሐንስ፦ ይህንም ቅዱስ በወለዱት ጊዜ በበጎ ተግሣጽ አሳደገውታል የጥርብ ሥራንም አስተማሩት ከጥቂት ዘመናትም በኋላ አባቱና እናቱ ዐረፉ። ያን ጊዜ ወደ ቅዱስ ኢስድሮስና ወደ አባ ባይሞን ዘንድ ሒዶ መነኰሰ በጾምና በጸሎት በገድል ሁሉ ተጠምዶ ተጋደለ ዜናውም በራቀ ገዳማት ሁሉ ተሰማ።
❤ ከዚህም በኋላ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ ተገለጠለት ወደ አገሩ ሒዶ ወገኖቹን የጽድቅን ጎዳና ይመራቸው ዘንድ አዘዘው። ቅዱስ ቊርባንንም ሳይቀበል ከበዓቱ የማይወጣ ሆነ። በአንዲት ዕለትም ሁለት ቅዱሳን አረጋውያን አባ አብዢልና አባ ብሶይ ወደርሱ መጡ ገና ወደርሱ ሳይቀርቡ ከሩቅ ሳለ ስማቸውን በመጥራት ሳያውቃቸው አባቶቼ ለመምጣታችሁ ሰላምታ ይገባል ብሎ ተናገረ እጅግም አደነቁት አባ ሲኖዳም ከግብጽ አገር እየመጣ ብዙ ጊዜ ይጎበኘው ነበር።
❤ የከዳተኞችም ጠብ በግብጽ አገር ላይ በተነሳ ጊዜ ንጉሥ ቴዎዶስዮስ የላከው የጦር መኰንን ወደ ቅዱስ ዮሐንስ መጣ። በጸሎቱም ይረዳው ዘንድ ለመነው ቅዱስ ዮሐንስም መስቀሉን አንሥቶ መኰንኑን "አይዞህ አትዘን አንተ ጠላቶችህን ድል ታደርጋለህና"፧ አለው እንደ ቃሉም ሆነ። ዳግመኛም በንጉሥ ቴዎዶስዮስ ላይ ጠላት በተነሣበት ጊዜ ወደ ቅዱስ ዮሐንስ ላከ እርሱም "አትዘን ጠላትህን ታሸንፋለህ" አለው ያን ጊዜም ጠላቶቹን አሸነፈ።
❤ ከዚህም በኋላ በእነዚያ ወራት ንጉሥ ቴዎዶስዮስ የርኵሰትን ሥራ ስለ ሠሩ የአስዩጥን ሰዎች እንዲገድላቸው ሀገራቸውንም እንዲአጠፉ አዘዘ። ንጉሡም የላከው መኰንን ሳይደርስ የእግዚአብሔር መልአክ ይህን ነገር ለአባ ዮሐንስ አሳወቀው የአገርም ሰዎች የንጉሡን ትእዛዝ በሰሙ ጊዜ ወደ አባ ዮሐንስ ገዳም ወጥተው ስለ መጥፋታቸው በፊቱ አለቀሱ አባ ዮሐንስም "አትጨነቁ አይዟችሁ እግዚአብሔር ያድናችኋላና" አላቸው። መኰንኑም በመጣ ጊዜ ከእርሱ በረከትን ይቀበል ዘንድ ወደ አባ ዮሐንስ ደረሰ አባ ዮሐንስም ንጉሡ ያዘወውን ሁሉ ነገረው መኰንኑም ሰምቶ ደነገጠ ለቅድስናውም ተገዢ ሆነ ለመኰንኑም ርኵስ መንፈስ ያደረበት የዐሥራ ሁለት ዓመት ልጅ ነበረው ያድንለት ዘንድ ቅዱስ ዮሐንስን ለመነው በዚያንም ጊዜ ዘይትን ቀብቶ አዳነው።
❤ ከዚህም በኋላ የአስዩጥ ሰዎችን መገደላቸውን እንዲተው ወደ ንጉሥ ይጽፍለት ዘንድ መኰንኑን አባ ዮሐንስ ለመነው መኰንኑም ጽፎ ለአባ ዮሐንስ ሰጠው አባ ዮሐንስም ተቀብሎ ወደ ዋሻው ገባ ወደ ጌታችንም ጸለየ ብርህት ደመናም መጣች ተሸክማም ወደ ንጉሡ አደሰገችው ያን ጊዜም ንጉሥ ከማዕድ ላይ ነበረ ያንንም ደብዳቤ ከወደላይ ጣለለት ንጉሡም አንሥቶ በአነበበው ጊዜ ከመኰንኑ የተጻፈ እንደሆነ በመካከላቸው በአለ ምልክት ተሸፎ አገኘው የተጻፈውም ቃሉ ስለ አባ ዮሐንስ ልመና ሀገሪቱን ማጥፋትን እንዲተው የሚል ነበር ቀና ባለ ጊዜም ደመና አየ ንጉሡም አደነቀ።
