uk
Feedback
🗞 የ አቡጁነይድ መልዕክቶች Abujunaid posts

🗞 የ አቡጁነይድ መልዕክቶች Abujunaid posts

Відкрити в Telegram

ይህ በአቡ ጁነይድ ሳላህ አህመድ የቀረቡ የድምፅና የፅሁፍ መልዕክቶች የሚሰበሰቡበት ቻነል ነው። አላህ ጠቃሚ እውቀትን ከመልካም ስራ ጋር ያግራልን! You can contact me here @salehom100

Показати більше
2 212
Підписники
-224 години
-67 днів
-3430 день
Архів дописів
ኡድሂያ ለማረድ ካቀዱ ከወዲሁ ጥፍርና ጸጉርዎን ከመቁረጥ ይቆጠቡ! ------------------- ☞ እንድ ሙስሊም ሀጅ የማያደርግ ከሆነና በዒድ አል አድሀ እለት ኡድሂያን ለማረድ ካሰበ የዙልሂጃ ወር ከገባበት የምጀመሪያዉ ቀን ጀምሮ ጥፍሩንና ጸጉሩን አይቆርጥም፤ ቆዳውንም አይቀርፍም። ይህም ተከታዩን የኡሙሰለማ ሀዲስ መሰረት ያደረገ ነው። عن أم سلمة رضي الله عنها أن النبي صلى الله عليه وسلّم قال : " إذا رأيتم هلال ذي الحجة ، وفي لفظ : "إذا دخلت العشر وأراد أحدكم أن يضحي فليمسك عن شعره وأظفاره ". رواه أحمد ومسلم ، وفي لفظ : " فلا يأخذ من شعره وأظفاره شيئاً حتى يضحي ". وفي لفظ : "فلا يمس من شعره ولا بشره شيئاً ". ከኡሙ ሰለማ በተላለፈ ሀዲስ የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ብለዋል፤ «የዙልሂጃ ወርን ጨረቃ ካያችሁና ከናንተ መካከል አንዱ ኡድሂያ ለማረድን ካቀደ፤ ፀጉሩንና ጥፍሩን ከመቁረጥ ይቆጠብ» አል ኢማም አህመድ ዘግበውታል። በሌላም ዘገባም «ኡድሂያውን እስኪያርድ ድረስ ከፀጉሩና ከጥፍሩ ምንንም አይቁረጥ» ብለዋል። እንደዚሁ፤ «ከሰውነቱ ቆዳ ወይም ከፀጉሩ ምንንም አይቁረጥ» ብለዋል። ይህ ማንኛውም ሙስሊም እራሱን በሀጅ ላይ ካሉ ሰዎች ጋር የሚያመሳስልበት እና የተወሰኑ የኢህራም ክልከላዎችን ከነሱ ጋር የሚጋራበት ዲናዊ ስርአትና ነብያዊ ትዕዛዝ ነው። ☞ ጸጉርንና ጥፍርን ከመቁረጥ የሚከለከለው ለራሱ ወይም ለሰው በራሱ ገንዘብ የሚያርድ ሰው ብቻ ነው። ህጉ የሚመለከተው የሚያርደዉን ሰው ብቻ ነው ሲባል፤ በወኪልነት ለሌላ ስው የሚያርድን ሰው አይጨምርም። ☞ እያወቀ ጥፍሩን ወይም ጸጉሩን የቆረጠ ወንጀል ፈጽሟልና ወደ አላህ በተውበት ሊመለስ ይገባዋል፤ ኡድሂያው ግን አይበላሽም ማካካሻ ከፋራም የለበትም። አንዳንዶች እንደሚያስቡት ሳይሆን ወንጀሉን ቢፈፅምም ኡድሂያ ማረዱን መተው የለበትም። ☞ በስህተት ወይም በመርሳት ፀጉሩን ወይም ጥፍሩን የቆረጠ ሰው ምንም ወንጀል የለበትም። በተመሳሳይ መልኩ በጣም አስፈላጊ ሲሆን ቢቆርጥ ችግር የለውም። ለምሳሌ የተጎዳን የሰውነት ቆዳ ለማከም ወይም የተሰበረ ጥፍሩን ለማስተካከል መቁረጥ ይፈቀድለታል። ፠ ስለ ኡድሂያ ጥቂት ተጨማሪ ነጥቦች 1 - በዙልሂጃ አስር ቀናት ከተወደዱ ተግባሮች መካከል ኡድሂያን በማረድ ወደ አላህ መቃረብ አንዱ ነው። 2- ኡድሂያ በጣም ከጠነከሩ የነብዩ صلى الله عليه وسلم ሱናዎች መካከል ነው። ኡድሂያ የነብዩ ኢብራሂምን ሱና ህያው ከማድረግ በተጨማሪ ለድሆች እና ችግረኞች መድረስ ነው። 3- ኡድሂያን በተመለከተ አላህ ከኛ የሚፈልገው ለእርሱ ያለንን ፍራቻ ተቅዋና ታዛዥነት ግልጽ ማድረጋችንን ብቻ ነው። አላህ እንዲህ ብሏል፤ {ﻟَﻦ ﻳَﻨَﺎﻝَ اﻟﻠَّﻪَ ﻟُﺤُﻮﻣُﻬَﺎ ﻭَﻻَ ﺩِﻣَﺎﺅُﻫَﺎ ﻭَﻟَٰﻜِﻦ ﻳَﻨَﺎﻟُﻪُ اﻟﺘَّﻘْﻮَﻯٰ ﻣِﻨﻜُﻢْ ۚ ﻛَﺬَٰﻟِﻚَ ﺳَﺨَّﺮَﻫَﺎ ﻟَﻜُﻢْ ﻟِﺘُﻜَﺒِّﺮُﻭا اﻟﻠَّﻪَ ﻋَﻠَﻰٰ ﻣَﺎ ﻫَﺪَاﻛُﻢْ ۗ ﻭَﺑَﺸِّﺮِ اﻟْﻤُﺤْﺴِﻨِﻴﻦَ} الحج 37 አላህን ሥጋዎቿም ደሞቿም ፈጽሞ አይደርሰውም፡፡ ግን ከእናንተ የሆነው ፍራቻ ይደርሰዋል፡፡ እንደዚሁ አላህን በመራችሁ ላይ ልታከብሩት ለእናንተ ገራት፡፡ በጎ ሠሪዎችንም አብስር፡፡» አል ሐጅ 37 4- ኡድሂያ የሚታረደው ከዒድ ሰላት በኋላ ነው። የአላህ መልዕክተኛ صلى الله عليه وسلم ከኢድ ሰላት በፊት ያረደ ሰው እንዲደግም አዘዋል። 5- ሚዛን በሚደፋው የኡለማዎች አቋም መሰረት የዒድ ሰላት ከተጠናቀቀበት ጊዜ ጀምሮ የሶስተኛው ቀን ጸሀይ እስክትጠልቅ ድረስ ኡድሂያን ማረድ ይቻላል። 6- ወንድም ይሁን ሴት ግመል፣ የቀንድ ከብቶች፣ በግና ፍየል ለኡድሂያ ይታረዱሉ። 7- የአላህ መልዕክተኛ صلى الله عليه وسلم እንከን ያለባቸውን እንስሳት እንዳናርድ ከልክለዋል። አንድ አይኑ የታወረ፣ ስብራት ያለበት፣ የከሳና የደከመ ወይም የታመመ እንስሳ ለኡድሂያ አይሆንም። 8- ኡድሂያን ለብቻ ማረድ እንደሚቻለው ሁሉ ለሰባት ሆኖ አንድን ወይፈን ወይም በሬ መጋራትም ይቻላል። 9- አንድ ሰው ኡድሂያ ሲያርድ ለራሱ እና በህይወት ላሉም ይሁን በህይወት ለሌሉ ቤተሰቦቹ አስቦ ሊያርድ ይችላል። 10- የኡድሂያውን ስጋ፣ ለቤት፣ ለስጦታ እና ለሰደቃ አድርጎ ሶስት ቦታ መከፋፈሉ ሱና ነው። ይህ ማለት ግን እንደ አስፈላጊነቱ ለሶስቱም ያውለዋል ማለት እንጂ ሶስት እኩል ቦታዎች ይከፋፍለዋል ማለት አይደለም። አቡጁነይድ Http://www.t.me/abujunaidposts

🗞 ከዱንያ ቀናት ሁሉ ብልጫ ያላቸው አስርቱ የዙልሂጃ ቀናት ምስጋና ለአላህ የተገባ ነው፡፡ የአላህ ሰላምና እዝነት በታላቁ ነብይ በሙሀመድ በባልደረቦቻቸው እና በቤተሰቦቻቻው ሁሉ ላይ ይሁን፡፡ ከተከበሩት ወራት መካከል አንዱ የሀጅ ወር ዙልሂጃ ነው። ከቀናት ሁሉ አላህ ዘንድ የተወደዱት ደግሞ አስሩ የዙልሂጃ ቀናት ናቸው። እንደዉም ከዱንያ ቀናት ሁሉ ብልጫ ያላቸው እነኝህ ቀናት ናቸው። የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል፦ عن جَابِرِ بْنِ عَبْدِ اللهِ رَضِيَ الله عَنْهُ قَالَ: قَالَ رَسُولَ اللهِ صَلَّى الله عَلَيْهِ وَسَلَّمَ: "أَفْضَلُ أَيَّامِ الْدُّنْيَا أَيَّامُ الْعَشْرِ، يَعْنِي عَشْرُ ذِي الحْجَّةِ". صحيح الجامع ، رقم 1133 ጃቢር ኢብኑ ዓብዲላህ ባስተላለፉት ሀዲስ የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል «ከዱንያ ቀናት ሁሉ ብልጫ ያላቸው፤ አስርቱ ቀናት ናቸው። ማለትም አስሩ የዙልሂጃ ቀናት» አልባኒ ሰሂሁል ጃሚዕ 1133 ላይ አስፍረውታል عن ابن عباس رضي الله عنهما، عن النبي صلى الله عليه وسلم قال: "ما من أيام العمل الصالح فيهن أحب إلى الله منه في هذه الأيام العشر. قالوا ولا الجهاد في سبيل الله !! قال : ولا الجهاد في سبيل الله، إلا رجل خرج بنفسه وماله ولم يرجع من ذلك بشيء" أخرجه البخاري ከኢብኑ ዓባስ በተዘገበ ሀዲስ የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል:‐ «በነዚህ አስር ቀናቶች ውስጥ ከሚፈጸሙ መልካም ስራዎች በበለጠ ስራዎች አላህ ዘንድ የተወደዱ የሚሆኑባቸው ቀናት የሉም፤ “በአላህ መንገድ ላይ የሚደረግ ጂሀድም ጭምር?” ተባሉ። እርሳቸውም፤ “ራሱንና ንብረቱን ይዞ ወጥቶ ምንም ያልተመለሰለት ሰው ሲቀር ጂሀድም ከዚህ አይበልጥም” አሉ።» ቡኻሪ ዘግበውታል በነዚህ ቀናቶች ትኩረት ልንሰጣቸው ከሚገቡ የዒባዳ አይነቶች መካከል:‐ 1. ጾም፦ ጾም ከስራዎች ሁሉ በላጭ ነውና በእነዚህ ቀናት መጾም እጅግ የተወደደ ነው። የአላህ መልዕክተኛ ዘጠኙን የዙልሂጃ ቀናት ይጾሙ እንደነበር ተዘግቧል። (አስረኛው ቀን ግን ዒድ ስለሆነ አይጾምም) 2. ዚክሮችን ማብዛት፦ አላህን ማመስገን (አልሀምዱሊላህ) ፣ ተክቢር፣ ተስቢህ(ሱብሀነላህ) እና ተህሊል (ላ ኢላሀ ኢለላህ)፤ ኢባዳዉን ለማስታወስና የአላህን ስም ከፍ ለማድረግ በተለያዩ አጋጣሚዎች ድምጽን ከፍ አድርጎ እነዚህን ዚክሮች ማድረግ ይወደዳል። عن عبد الله بن عمر رضي الله عنهما عن النبي صلى الله عليه وسلم قال : "ما من أيام أعظم عند الله ولا أحب إليه العمل فيهن من هذه الأيام العشر فأكثروا فيهن من التهليل والتكبير والتحميد" أخرجه احمد 7/224 وصحّح إسناده أحمد شاكر ዓብዱላህ ኢብኑ ዑመር ባስተላለፉት ሀዲስ ነብዩ እንዲህ ብለዋል፤ «ከነዚህ አስር ቀናት በበለጠ አላህ ዘንድ ታላቅ የሆኑና መልካም ስራ እጅግ የተወደደባቸው ቀናት የሉም፤ ተህሊል ተክቢር እና ተህሚድ አብዙ» አል ኢማም አህመድ ዘግበውታል አህመድ ሻኪርም ሰሂህነቱን አረጋግጠዋል። ከተክቢር አደራረግ መካከል፤ الله أكبر ، الله أكبر لا إله إلا الله ، والله أكبر ولله الحمد “አላሁ አክበር፤ አላሁ አክበር፤ ላ ኢላሀ ኢለላህ ወላሁ አክበር ወሊላሂልሀምድ” የሚለው ዋነኛው ሲሆን ሌሎችም ይዘቶች አሉት። በእነዚህ ቀናት ውስጥ ሊደረግ የሚገባው ይህ ተክቢር ብዙ ሰዎች ስለማይፈጽሙት እየተረሱ ካሉ ሱናዎች መካከል ነው። ሰዎችን ለማስታወስ እና ሱናን ህያው ለማድረግ ድምጽን ከፍ አድርጎ ተክቢር ማድረግ ያስፈልጋል። ዓብዱላህ ኢብኑ ኡመር እና አቡሁረይራህ በነዚህ አስር ቀናት ገበያ ወጥተው ተክቢራ ሲያደርጉ ሰዎችም እያስታወሱ ተክቢራ ያደርጉ እንደነበር ተዘግቧል። ይህም፤ ሁሉም ሰው የራሱን ዚክር ያደርጋል ማለት ነው እንጂ ሰዎች እየተሰባሰቡ በአንድ ድምጽ ተክቢራ ያድርጉ ማለት አይደለም። ይህ መረጃ ያልተገኘለት የተሳሳተ አፈፃፀም ነው። 3. ሐጅና ዑምራ፦ በነዚህ ቀናት ውስጥ ከሚፈጸሙ መልካም ስራዎች መካከል ሐጅ ማድረግ ይገኝበታል፤ በነዚህ አስር ቀናት የሐጅ ዒባዳ ላይ ተገኝቶ በተገቢው መልኩ ከፈጸመው በአላህ ፍቃድ ከተከታዩ የአላህ መልዕክተኛ ብስራት ድርሻ ይኖረዋል፤ عن أبي هريرة رضي الله عنه قال: سمعته يقول: "الحج المبرور ليس له جزاء إلا الجنة" متفق عليه. ከአቡ ሁረይራ በተላለፈ ሀዲስ የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል፤ «ከወንጀል የራቀና ተቀባይነት ያለው ሐጅ (አል-ሐጅ አል-መብሩር) ምንዳው ጀነት እንጂ ሌላ አይደለም፡፡» ቡኻሪና ሙስሊም ተስማምተውበታል 4. ኡድሂያ፦ በነዚህ አስር ቀናት ከተወደዱ ተግባሮች መካከል ኡድሂያን በማረድ ወደአላህ መቃረብ ነው። የሚከተሉት ነጥቦች አጠር ያለ ግንዘቤን ይሰጣሉ፤ - ኡድሂያ በጣም ከጠነከሩ የነብዩ ሱናዎች መካከል ነው። የነብዩ ኢብራሂምን ሱና ህያው ከማድረጉ በተጨማሪ ለድሆች እና ችግረኞች መድረስ ነው። - ኡድሂያን በተመለከተ አላህ ከኛ የሚፈልገው ለእርሱ ያለንን ፍራቻ (ተቅዋ) ነው። - ኡድሂያ የሚታረደው ከዒድ ሰላት በኋላ ነው። የአላህ መልዕክተኛ ከኢድ ሰላት በፊት ያረደ ሰው እንዲደግም አዘዋል። - ሚዛን በሚደፋው የኡለማዎች አቋም መሰረት የዒድ ሰላት ከተጠናቀቀበት ጊዜ ጀምሮ የሶስተኛው ቀን ጸሀይ እስክትጠልቅ ድረስ ኡድሂያን ማረድ ይቻላል። - ግመል፣ የቀንድ ከብቶች፣ በግና ፍየል ለኡድሂያ ይታረዱሉ። - የአላህ መልዕክተኛ እንከን ያለባቸውን እንስሳት እንዳናርድ ከልክለዋል። አንድ አይኑ የታወረ፣ ስብራት ያለበት፣ የከሳና የደከመ፣ የታመመ እንስሳ ለኡድሂያ አይሆንም። - ኡድሂያን ለብቻ ማረድ እንደሚቻለው ሁሉ ለሰባት ሆኖ አንድን ወይፈን ወይም በሬ መጋርትም ይቻላል። - አንድ ሰው ኡድሂያ ሲያርድ ለራሱ እና በህይወት ላሉም ይሁን በህይወት ለሌሉ ለቤተሰቦቹ አስቦ ሊያርድ ይችላል። - ኡድሂያውን ለራሱ፣ ለስጦታ እና ለሰደቃ አድርጎ መከፋፈሉ ሱና ነው። ይህ ማለት ግን እንደ አስፈላጊነቱ ለሶስቱም ያውለዋል ማለት እንጂ ሶስት እኩል ቦታዎች ይከፋፍለዋል ማለት አይደለም። - በዒድ ቀን ኡድሂያን ለማረድ አስቦ የዙልሂጃ ወር ከገባ ጥፍሩንና ጸጉሩን አይቆርጥም። ቆዳውንም አይቀርፍም። ይህ በሀጅ ላይ ያሉ ሰዎችን የሚመሳሰልበት ነብያዊ ትዕዛዝ ነው። ሆኖም ይህ የሚመለከተው የሚያርደዉን ሰው ብቻ ነው። እያወቀ ጥፍሩን ወይም ጸጉሩን የቆረጠ ወንጀል ፈጽሟልና ወደ አላህ በተውበት ሊመለስ ይገባዋል፤ ኡድሂያው ግን አይበላሽም። የመልካም ስራ በሮች ብዙ ናቸውና የቻልነዉን ሁሉ በመፈጸም ወደ አላህ መቃረብ ይገባል፤ የታሰረን ወይም የታመመን ሰው መጠየቅ፣ ዝምድናን መቀጠል፣ ሰደቃ ማብዛት፣ ሱና ሰላቶችን ማብዛት፣ ቁርዓን መቅራት፣ ዚክር ማብዛት፣ ዱዓን ማብዛት…ወዘተ ያስፈልጋል። አላህ በነዚህ ወርቃማ ጊዜያት ከሚጠቀሙና አላህ ዘንድ መልካም ምንዳን ከሚያገኙ ጠንካራና ብልህ የአላህ ባሮች ያድርገን። ✍ አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ ህዳር 23/ 2004 ዓ.ል ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

🗞 ከዱንያ ቀናት ሁሉ ብልጫ ያላቸው አስርቱ የዙልሂጃ ቀናት ✍ አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ ህዳር 23/ 2004 ዓ.ል 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/220 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

🔖 ተውሒድ እና የሐጅ ፍሬዎች 🎙 አቡጁነይድ እና ጣሀ አህመድ በ 2002 በጃሊያ አዳራሽ የቀረበ 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/219 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

🔖 ከሱረቱል ፋቲሀ ቁምነገሮች Arabic/Amharic 🎙ዶክተር ሙሀመድ በኺት አልሁጀይሊይ ሀፊዘሁላህ 💾 የ1424 የፓልቶክ ሙሐደራ ከአማርኛ ትርጉም ጋር በአቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/217 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

ልዩ ዕድል ለኢልም ፈላጊዎች በታላቁ መስጂደነበዊ የሙቱኖች ሂፍዝ ፕሮግራም ባሉበት ሆነው በርቀት በመሳተፍ ቋሚ የሀረም ተማሪዎች የሚያገኙትን የብቃት ኢጃዛና የምስክር ወረቀት ማግኘት ይችላሉ። ፕሮግራሙ በእውቁ ኢማም ሸይኽ አብዱልሙህሲን አልቃሲም አስተባባሪነት የሚካሄድ ሲሆን፤ ለተማሪዎች የብቃት ማረጋገጫ ኢጃዛውንም የሚሰጡት እራሳቸው ናቸው። ማሳሰቢያ፦ ይህ ፕሮግራም የሚመለከው ወንዶችን ብቻ ነው! ______ ✔ በተማሪነት ለመመዝገብ የዋትሳብ ግሩፑን ይቀላቀሉ https://chat.whatsapp.com/GzlyXFiUPjgCEfbPUAom3c ✔ በጉግል Meet የቀጥታ ስብሰባ በኩል ለመሳተፍ https://meet.google.com/zzh-oadj-jbr ✔ ለበለጠ መረጃ የኢትዮጵያ ተማሪዎች አስተማሪ ሸይኽ ሙሀመድ ሰዒድን በቀጥታ ማግኘት ይችላሉ +966558142209 ✔ ለጀማሪዎች በተሰናዳው የተምሂዲ ፕሮግራም እና በቀጣይ እርከኖች የሚተሀፈዙትን ኪታቦች በተከታዩ ሊንክ ማግኘት ትችላላችሁ https://a-alqasim.com/books-cats/mutoon/ ________ 📮 የአቡጁነይድ መልችክቶች @abujunaidposts

🔖 ሙሀመድ ኢብኑ ዓብዲል ወሓብ ማን ናቸው? 🎙አቡ ጁነይድ ሳላሕ አሕመድ 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/212 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

ሙሀመድ ኢብኑ ዓብዲል ወሓብ ማናቸው.mp38.24 MB

السلام عليكم الآن يمكنكم المشاركة في برنامج حفظ المتون بالمسجد النبوي مع محفّظ الطلبة الإثيوبيين أخونا الشيخ محمد سعيد الحبشي حفظه الله. تمنح الشهادات من المسجد النبوي بتوقيع الشيخ عبد المحسن القاسم. تنبيه:- البرنامج للرجال فقط! كما يمكنكم الانضمام إلى المجموعة في الواتساب للتسميع مباشرة: https://chat.whatsapp.com/GzlyXFiUPjgCEfbPUAom3c رقم الشيخ للتسجيل والترتيب +966 55 814 2209 *رابط الاجتماع* https://meet.google.com/zzh-oadj-jbr *فيديو شرح البرنامج* https://youtu.be/nW6INJmK6MU *تحميل برنامج Google Meet* http://onelink.to/dac8a4 *مواقيت الصلاة بالمدينة المنورة* http://bit.ly/Mawaqit @abujunaidposts

ሰዎች አራት አይነት ናቸው! ከየትኛው ነን? ራሳችንን እንገምግም! ከኢብኑ ተይሚያህ አልሀራኒ ምርጥ ገለፃዎች (በአጭሩ የቀረበ) قال تعالى: {تِلْكَ الدَّارُ الْآخِرَةُ نَجْعَلُهَا لِلَّذِينَ لَا يُرِيدُونَ عُلُوًّا فِي الْأَرْضِ وَلَا فَسَادًا وَالْعَاقِبَةُ لِلْمُتَّقِينَ} [القصص: 83]. «የመጨረሻይቱም ሀገር (አኺራ) ለነዚያ በምድር ላይ ኩራትንና በአላህ ትእዛዛት ላይ ማመፅን ለማይፈልጉት እናደርጋታለን፤ መልካም መጨረሻም አላህን ለሚፈሩት ጥንቁቆች ነው።» አል ቀሰስ 83 1) በሰዎች ላይ አምባገነንነትን ማሳየት የሚፈልጉ፣ የአመፀኝነትን መስፋፋትና የአላህ ትእዛዝ መጣሱን የሚወዱ ናቸው። እነዚህም እንደ ፊርአውን እና መሰሎቹ ያሉት መሪዎች ሲሆኑ ከፍጥረታት ሁሉ መጥፎዎች ናቸው። ከነዚህ በምድር ላይ ጥፋትን የሚያስፋፉ ሰዎች መገለጫዎች መካከል ኩራት ዋነኛው ሲሆን እርሱም ራስን ከሀቅ በላይ ማድረግና አለመቀበል እንዲሁም ሰዎችን መናቅና ማጣጣል ነው። 2) የሰዎችን ንብረት እንደሚሰርቁ ሰዎች፤ እራሳቸውን ከሰዎች በላይ ማድረግን ባይፈልጉም በአላህ ትእዛዛት ላይ ማመፅን የሚተገብሩ ሲሆኑ እነዚህም የማህበረሰቡ ዝቃጭ ናቸው። 3) እንደ አንዳንድ ዲን ያላቸው ሰዎች፤ በአላህ ትእዛዛት ላይ ማመፅን የማይወዱ ነገር ግን ዲኑን በመጠቀም እራሳቸውን ከሰዎች በላይ የሚያደርጉ ሰዎች። 4) የመጨረሻዎቹ ክፍሎች የጀነት ሰዎች ሲሆኑ፤ እነርሱም፦ አላህ እንዳለው፤ قَالَ اللَّهُ تَعَالَى : { وَلَا تَهِنُوا وَلَا تَحْزَنُوا وَأَنْتُمُ الْأَعْلَوْنَ إنْ كُنْتُمْ مُؤْمِنِينَ } آل عمران 139 «አትሥነፉ፣ አትዘኑም፤ ምእምናን እስከሆናችሁ እናንተ የበላዮች ናችሁ» አል ኢምራን 139 በኑሯቸው ከሰዎች በላይ ሊሆኑ ይችላሉ፤ ነገር ግን፤ እራሳቸውን ከሰዎች በላይ ማድረግን እና በአላህ ትእዛዛት ላይ ማመፅን የማይፈልጉ ናቸው። ከሰዎች ሁሉ የበላይ መሆንን እየፈለገ ወደ ታች የሚወርድ ስንቱ ነው!! የበላይነትን ሳይመኝ አምባገነን ሳይሆን አላህ ከፍ የሚያደርገውስ ስንቱ ነው!! አልፈታዋ አል ኢራቂያህ 2/972 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

🔖 ዒባዳን ለመገንዘብ! 🎙አቡ ጁነይድ ሳላሕ አሕመድ 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/209 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

🔊 የይለፍ መታወቂያ አለዎትን? 🎙አቡ ጁነይድ ሳላሕ አሕመድ 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/208 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

🍂 يا نَفسُ أَنّى تُؤفَكينا حَتّى مَتى لا تَرعَوينا 🍂 حَتّى مَتى لا تَعقِلي نَ وَتَسمَعينَ وَتُبصِرينا 🍂 أَصبَحتِ أَطوَلَ مَن مَضى أَمَلاً وَأَضعَفَهُم يَقينا 🍂 وَلِيَأتِيَنَّ عَلَيكِ ما أَفنى القُرونَ الأَوَّلينا 🍂 يا نَفسُ طالَ تَمَسُّكي بِعُرى المُنى حيناً فَحينا 🍂 يا نَفسُ إِلّا تَصلُحي فَتَشَبَّهي بِالصالِحينا 🍂 وَتَفَكَّري فيما أَقو لُ لَعَلَّ قَلبَكِ أَن يَلينا 🍂 أَينَ الأُلى جَمَعوا وَكا نوا لِلحَوادِثِ آمِنينا 🍂 أَينَ الأُلى جَمَعوا وَكا نوا لِلحَوادِثِ آمِنينا 🍂 أَفناهُمُ الأَجَلُ المُطِل لُ عَلى الخَلائِقِ أَجمَعينا 🍂 فَإِذا مَساكِنُهُم وَما جَمَعوا لِقَومٍ آخَرينا 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/207 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

የሸዋልን ፆም ለጀመሩ እህቶች አምስት አስፈላጊ ጥቆማዎች الحمد لله والصلاة والسلام على رسول الله وعلى آله وصحبه، أما بعـد: ከሸዋል ፆም ጋር በተያያዘ ብዙ እህቶች ከሚጠይቋቸው ጥያቄዎች በመነሳት አምስት ጥቆማዎች ይኖሩኛል፤ 1) ቀዳ ያለባት ሴት ከቀዳና ከሸዋል ሱና የትኛውን ታስቀድም? ☞ በሀይድ ወይም በወሊድ ደም ምክኒያት ረመዳንን አሟልታ ያልፆመች ሴት፤ ከሸዋል ስድስት ቀናት መፆምን አስመለክቶ በሀዲስ የተጠቀሰውን የአንድ አመት ፆም ምንዳ ለማግኘት አጅሩን እንደሚያገኝ ቃል የተገባለት ረመዳንን ካሟላ በኋላ የፆመው ሰው ስለሆነ፤ ቅድሚያ ረመዳንን መፆም ግድ ስለሚል በተቻላት መጠን ከሸዋል ሱና በፊት የረመዳንን ቀዷ ለማጠናቀቅ መሞከር ይኖርባታል። 📚 የሳውዲ ቋሚ የፈትዋ ኮሚቴ ይህንን በማስመልከት እንዲህ ብሏል፤ ¹ «ከረመዳን የተወሰኑ ቀናት ያሉበት ሰው በቅድሚያ እነሱን ሊፆምና ከዛ በኃላ ከሸዋል ወር ስድስት ቀናትን ሊፆም ይገባል፤ ምክኒያቱም ረመዳንን አስከትሎ ከሸዋል ስድስት ቀን ሊፆም የሚችለው ረመዳንን አሟልቶ ከፆመ ነው።» ፈታወለጅናህ 10/392 ይህንን መተግበር ሴቶች ያለባችውን ቀዷ በጊዜ መክፈል ይችሉ ዘንድ ያበረታቸዋል። 2) የረመዳንን ወር በሙሉ ካልፆመችስ? 📚 ሸይኽ ኡሰይሚን እንደገለፁት² በወሊድ ወይም በተለያዩ በሽታዎች ምክኒያት ረመዳንን ሙሉዉን መፆም ያልቻለች ሴት ሸዋልን ቀዳ በማውጣት ከጨረሰችና ስድስቱን የሱና ቀናት መፆም የምትችልበት ጊዜ ሸዋል ውስጥ ካላገኘች የዘገየችው ከአቅም በላይ በሆነ ምክኒያት (ደሩራ) ስለሆነ ቀጣዩ የዙልቂእዳ ወር ከገባ በኃላም ቢሆን በሸዋል ሱና ነይታ ፆሟን ብታሟላው ኢን ሻ አላህ አጅሩን ታገኛለች። ይህንን መልእክት ያዘለውን የሸይኽ ኡሰይሚን ፈትዋ በመጅሙኡል ፈታዋ 20/19 ያገኙታል 3) ቀዳና የሸዋል ሱናን በአንድ ኒያ መፆም 📚 ሸይኽ ኢብኑ ባዝ ረሂመሁላህ (ኑሩን አለደርብ)² የጥያቄና መልስ ፕሮግራም ላይ ተጠይቀው ሲያብራሩ እንዲህ ብለዋል፤ «የስድስቱን ቀናት ፆም ከፈለገች በቅድሚያ ቀዳ አውጥታ በመቀጠል ሱናውን ፆም ትፁም። በሸዋል ወር ቀዳ አውጥታ ስድስቱን ቀናትም ከፆመች ትልቅ ኸይር ነው። የስድስቱን የሸዋል ቀናት ፆም ከቀዳ ጋር በአንድ ኒያ ብትፆም ግን የስድስቱን ቀናት አጅር ታገኛለች ብዬ አላስብም። የሸዋል ፆም የሚፆመው በተገደበ ጊዜ ሲሆን እራሱን የቻለ ኒያ ይፈልጋል።» ስለዚህም ሁለቱን በአንድ ላይ መፆም ሳይሆን ቅድሚያ ረመዳንን አሟልቶ ሱናውን ፆም መጀመር ተገቢ ነው። 4) የሸዋል ወር ሳያልቅ የመጀመሪያዎቹ ስድስት ቀናት ቢያልፉስ? ☞ ብዙ ሴቶች የሸዋል ፆም የሚባለው ወሩ እንደገባ ያሉት ስድስት ቀናት ብቻ ይመስሏቸዋል። ይህ ስህተት ነው። በሀዲሱ የተጠቀሰው ምንዳ ከሸዋል ወር ስድስት ቀናት የፆመን ሰው ሁሉ ይመለከታል። ይህ ደግሞ መጀመሪያም መጨረሻም በመካከልም ሊሆን ይችላል። 5) የሸዋልን ፆም አከታትሎ መፆም ☞ ሸዋል እንደገባ ብዙ ሰዎች አከታትለው በመፆም ይጨርሳሉ። ይህም ስንፍናን ለማስወገድና በረመዳን ያካበቱትን የመፆም ብቃት ላለማጣት ከማሰብ ነው። ነገር ግን በተቃራኒው ሰኞና ሀሙስ እንዲሁም አያመልቢድ በመፆም ሱና ፆም የመፆምን ልምድ ማዳበርም መልካም ነው። አንዳንድ ሴቶች አከታትለው መፆማቸው ግዴታ ስለሚመስላቸው ከመፆም ይሳነፋሉ። ይህ ሊታረም የሚገባው ግንዛቤ ነው። አላህ ፆማችንን ይቀበለን ዘንድ እማፀነዋለሁ! አቡጁነይድ ሸዋል 4/10/1436 ————// ———— ¹ (...والذي ينبغي لمن كان علي شيء من أيام رمضان أن يصومها أولا ثم يصوم ستة أيام من شوال ؛ لأنه لا يتحقق له اتباع صيام رمضان لست من شوال إلا إذا كان قد أكمل صيامه . وبالله التوفيق وصلى الله على نبينا محمد وآله وصحبه وسلم ) فتاوى الجنة الدائمة 10/392 ² سئل الشيخ ابن عثيمين رحمه الله تعالى عما إذا كان على المرأة دين من رمضان فهل يجوز أن تقدم الست على الدين أم الدين على الست ؟ فأجاب بقوله : "إذا كان على المرأة قضاء من رمضان فإنها لا تصوم الستة أيام من شوال إلا بعد القضاء ، ذلك لأن النبي صلى الله عليه وسلم يقول : ( من صام رمضان ثم أتبعه ستا من شوال ) ومن عليها قضاء من رمضان لم تكن صامت رمضان فلا يحصل لها ثواب الأيام الست إلا بعد أن تنتهي من القضاء ، فلو فرض أن القضاء استوعب جميع شوال ، مثل أن تكون امرأة نفساء ولم تصم يوما من رمضان ، ثم شرعت في قضاء الصوم في شوال ولم تنته إلا بعد دخول شهر ذي القعدة فإنها تصوم الأيام الستة ، ويكون لها أجر من صامها في شوال ، لأن تأخيرها هنا للضرورة وهو ( أي صيامها للست في شوال) متعذر، فصار لها الأجر" انتهى مجموع الفتاوى 20/19 ³ سئل الشيخ ابن باز رحمه الله هل يجوز للمرأة الجمع بين صيام ستة أيام من شوال وقضاء ما عليها من رمضان في هذه الأيام الستة بنية القضاء والأجر معاً، أم لا بد من القضاء أولاً ثم صيام ستة أيام من شوال؟ نعم، تبدأ بالقضاء، ثم تصوم الست إذا أرادت، الست نافلة، فإذا قضت في شوال ما عليها ثم صامت الست من شوال فهذا خير عظيم، وأما أن تصوم الست بنية القضاء والست فلا يظهر لنا أنه يحصل لها بذلك أجر الست، الست تحتاج إلى نية خاصة في أيام مخصوصة. http://www.binbaz.org.sa/node/13470 والله تعالى المسؤول أن يوفقنا لما يحب ويرضى t.me/abujunaidposts

قال ابن تيمية : "الرد على أهل البدع من الرافضة وغيرهم إن لم يُقْصَد فيه بيان الحق وهدى الخلق ورحمتُهم والإحسان إليهم لم يكن عمله صالحًا" منهاج السنة 5/239 "ለራፊዷ እና መሰል የቢድዓ ሰዎች የሚሰጥ ምላሽ (ረድ) አላማው፤ ሀቅን ማብራራት፣ ለሰዎች በማዘን መልካም ውለታን መዋልና ቅኑን መንገድ ማሳየት ካልሆነ ይህ መልካም ተግባር አይሆንም" ሚንሐጁሱና 5/234 @abujunaidposts

ኢድ ሙባረክ መንድም እህቶቼ! تقبل الله منا ومنكم صالح الأعمال አላህ የደስታ ኢድ ያድርግልን፤ ሙስሊሞች ላይ የተጋረጡ ችግሮችን ያንሳልን። መጪው ግዜ ቁድስ ነፃ የሚሆንበት የኡመተ
ኢድ ሙባረክ መንድም እህቶቼ! تقبل الله منا ومنكم صالح الأعمال አላህ የደስታ ኢድ ያድርግልን፤ ሙስሊሞች ላይ የተጋረጡ ችግሮችን ያንሳልን። መጪው ግዜ ቁድስ ነፃ የሚሆንበት የኡመተል ኢስላም የከፍታ ዘመን እንዲሆን እመኛለው። አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ

የእናቶች ቀን... ሙስሊሞች እንዴት ያዩታል? እኛ ሙስሊሞች፤ እናትን በመታዘዝ፣ ለእናት መልካም በመዋልና አሷን በማስደሰት ታዘናል። እናትን ከመበደልና በሷ ላይ ከማመፅ በእጅጉ ተከልክለናል። ለእናት ክብር እንሰጥ ዘንድ በእርግዝና ወቅት ምን ያክል ድካምና እንግልት እንደሚገጥማት ቁርአን ያሳስበናል። (ﻭَﻭَﺻَّﻴْﻨَﺎ اﻹِْﻧﺴَﺎﻥَ ﺑِﻮَاﻟِﺪَﻳْﻪِ ﺣَﻤَﻠَﺘْﻪُ ﺃُﻣُّﻪُ ﻭَﻫْﻨًﺎ ﻋَﻠَﻰٰ ﻭَﻫْﻦٍ ﻭَﻓِﺼَﺎﻟُﻪُ ﻓِﻲ ﻋَﺎﻣَﻴْﻦِ ﺃَﻥِ اﺷْﻜُﺮْ ﻟِﻲ ﻭَﻟِﻮَاﻟِﺪَﻳْﻚَ ﺇِﻟَﻲَّ اﻟْﻤَﺼِﻴﺮُ) لقمان 14 «ሰውንም በወላጆቹ (በጎ እንዲያደርግ) በጥብቅ አዘዝነው፡፡ እናቱ ከድካም በላይ በሆነ ድካም አረገዘችው፡፡ ጡት መጣያውም በሁለት ዓመት ውስጥ ነው፡፡ ለእኔም ለወላጆችህም አመስግን በማለት አዘዝነው፡፡ መመለሻውም ወደኔ ነው፡፡» ሉቅማን 31:14 እኛ ዘንድ እናትን ማገልገል በህይወት ዘመኗ ብቻ ሳይሆን ከሞተችም በኃላ ይቀጥላል። አንድ ሙስሊም ለእናቱ ያለውን ክብር ከሚገልፅባቸው ተግባራት መካከል፤ የእናትን ኑዛዜ ተግባራዊ ማድረግ፣ ዱዓ ማድግ፣ ከአላህ ማርታን መጠየቅ፣ ቤተሰቧንና ጓደኞቿን ማክበር ይገኝበታል። በጥቅሉ እናትን ማስደሰት ለጀነት ከሚያበቁ ታላላቅ መልካም ስራዎች ይመደባል። በኢስላማዊ ሸሪዓ ለእናት የተሰጠውን ክብር በየትኛውም ምድራዊ ህግ ወይም ሀይማኖት አናገኘውም። እናትን አስመለክቶ የተጣለብን ሀላፊነት ከአባት የበለጠ መሆኑም ተገልፆልናል። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُ قَالَ : [جَاءَ رَجُلٌ إِلَى رَسُولِ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ فَقَالَ : يَا رَسُولَ اللَّهِ ، مَنْ أَحَقُّ النَّاسِ بِحُسْنِ صَحَابَتِي ؟ قَالَ : أُمُّكَ . قَالَ : ثُمَّ مَنْ ؟ قَالَ : ثُمَّ أُمُّكَ . قَالَ : ثُمَّ مَنْ ؟ قَالَ : ثُمَّ أُمُّكَ . قَالَ : ثُمَّ مَنْ ؟ قَالَ : ثُمَّ أَبُوكَ] رواه البخاري ومسلم አቡ ሁረይራ እንዲህ ብለዋል፤ «አንድ ሰው የአላህ መልእክተኛ ﷺ ዘንድ መጣና እንዲህ አላቸው፤ የአላህ መልእክተኛ ሆይ! ከማንም በላይ መልካም ልውልለት የሚገባ ሰው ማነው? በማለት ጠየቀ። "እናትህ" አሉት። ቀጥሎስ? አላቸው። "እናትህ" አሉት። ቀጥሎስ? አላቸው። "እናትህ" አሉት። ቀጥሎስ? አላቸው። "አባትህ" አሉት» ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል የእናቶች ቀንን ማክበር እንዴት ይታያል? ኢስላም ለእናት ታላቅ ክብርን አጎናፅፏል። ይሁንና "የእናቶች ቀን" በማለት በአመት አንድ ቀን ብቻ እንድትከበር አላዘዘም። ይህንንም ለማብራራት፤ 1) የእናቶችን ቀን በዓል አድርጎ ማክበር በዲናችን ያልነበረ እንግዳ ተግባር ነውና በዲን ውስጥ እንደተጨመረ ቢድዓ እንጂ እንደመልካም ስራ አይታይም። መልእክተኛው፤ እንዲሁም ሰሀቦችም ይሁኑ የዚህ ኡማ ታላላቅ መሪዎች ሁሉ አልፈፀሙትም። መልእክተኛው ﷺ ከቢድዓ ሲያስጠነቅቁ እንዲህ ብለዋል፤ وشَرُّ الْأُمُورِ مُحْدَثَاتُهَا ، وَكُلُّ بِدْعَةٍ ضَلَالَةٌ رواه مسلم والنسائي وزاد:وَكُلُّ ضَلَالَةٍ فِي النَّارِ. «የነገሮች ሁሉ ክፉ፤ (በዲን ውስጥ) አዳዲስ ፈጠራዎች ናቸው፤ ቢድዓ ሁሉ ጥመት ነው!» ሙስሊም ዘግበውታል። በነሳኢ ዘገባ ደግሞ «ጥመት ሁሉ ደግሞ የእሳት ነው» የሚለውን ጭማሪ እናገኛለን። ሆኖም፤ ቢድዓ በዲን ውስጥ መጨመር ነው። ይህ ተግባር ኢባዳ አይደለም በአሉም እንዲሁ ነውና ታዲያ ለምን ቢድአ ይሆናል የሚል ጥያቄ የሚያነሱ አሉ። በቅድሚያ፤ ለጉዳዩ ያለንን እይታ ሙስሊም ያልሆኑ ሰዎች ዘንድ ባለው መልካም ስራ የመስራት ግንዛቤ ሳይሆን እንደ ኢስላም የመልካም ተግባራት ትርጓሜ ልናጤነው ይገባል። እንደ ኢስላም የሚታዩም ይሁን ልባዊ መልካም ስራዎች ሁሉ ኢባዳ ናቸው። እናትን ማስደሰት በአኼራ ታላቅ ደረጃን የሚያስገኝ የፅድቅ ዲናዊ ተግባር ኢባዳ መሆኑ ግልፅ ነው። አመታዊ በአሉም ቢሆን እንደሙስሊም ካሰብነው ለእናት መልካም በመዋል አጅር ለማግኘት ዲናዊ ስራ የሚሰራበት ቀን ነው። በዓል ማለት፤ በየአመቱ በሆነ ቀን በቋሚነት የሚደጋገምና ሰዎች በአልነቱን አስበውት የሚውሉት ቀን ነው። ቀናት ሁሉ የአላህ ናቸውና ለሆነ መልካም ስራ የሆነን ቀን በመምረጥ ቋሚ እና አመታዊ በአል አድርገን ስንደነግገው ከዲን ጋር የሚጋጭ ተግባር ይሆናል። በአል ማድረግ የምንችለው በዲናችን የታወቁትን አላህ የደነገጋቸውን የዒድ አልፊጥር እና የኢድ አል አድሐ በአላት ብቻ ነው። ከዚህ ውጭ ያሉ በአላት ወይ ከሌላ እምነቶች የተወሰዱ ወይም ደግሞ በዲን ውስጥ መሰረት የሌላቸው ፈጠራዎች ናቸውና አይፈቀዱም። ስለዚህም ታላላቅ ኡለማዎችን ያቀፈው ቋሚ የፈትዋ ኮሚቴ የእናቶች ቀንን ማክበር እንደማይፈቀድ ብይን ሰጥቷል (ፈታዋለጅናህ ቅፅ 3 ገፅ 86) 2) የእናቶች ቀን የተቀዳው ቤተሰባዊና ማህበራዊ ትስስራቸው በእጅጉ ከተጎዳ ካፊር ማህበረሰቦች ተግባር ስለሆነ ቢድዓ ከመሆኑ በተጨማሪ ከካፊሮች ጋር መመሳሰል ነው። ሙስሊም በማንነቱ ሊኮራና ምርጥ የሙስሊም ትውልዶችን አርአያ ሊያደርግ እንጂ የሌሎች ጭራ ሊሆን አይገባም። የሚገርመው ይህ በአል የመጣብን የወላጆች ክብር ከጠፋባቸውና በደል ከተንሰራፋባቸው ማህበረሰቦች መሆኑ ነው። ወላጆቻቸውን የአዛውንቶች መጦርያ ጥለው በአመት እንኳ ለመጠየቅ ፍቃደኛ የማይሆኑ ሰዎች ከበዙባቸው ሀገራት ነው። እነሱ ዘንድ ወላጆችን ማስከፋትና መበደል እጅጉን ተንሰራፍቷል። ይህም ስለሆነ እናታቸውን የሚያስታውሱበትን ቀን መመደባቸው አይገርምም። አለዚያማ ከብዙ አመታት መማፀን በኃላ ልጆቻቸው ሳያዩዋቸው የሚሞቱ ወላጆች በርካታ መሆናቸውን በነዚህ ሀገራት የሚኖሩ ወዳጆቻችን ያጫውቱናል። ለነሱ በእናቶች ቀን የሚፈፅሙት ዚያራና መልካም ስራ አመቱን ሙሉ ያሳዩትን ጉድለት የሚያካክስ ይመስላቸዋል። እኛ ሙስሊሞች ዘንድ ግን ሁኔታው ይለያል። አመቱን ሙሉ የእናትን ፍቅር ስናገኝና ስናገለግል ብንኖር ውለታዋን እንደማንመልስ ዲናችን ያስተምረናል። ታዲያ በአመት አንድ ቀን መርጦ እናት እናት ማለት እና ማሟሟቅ ምንም ትርጉም አይኖረውም። ሸይኽ ኡሰይሚን እንዲህ ብለዋል፤ «እናት፤ በአመት አንድ ቀን ብቻ ትኩረትን ከመቸሯ የበለጠ ሀቅ አላት። እንደውም ልጆች እናታቸውን የመንከባከብ ግዴታ አለባቸው። እንደዚሁ፤ ከአላህ ትእዛዝ ጋር እስካልተጋጨ ድረስ እናትን በማንኛውም ጊዜና ቦታ መታዘዝ ግዴታ ነው» መጅሙዑል ፈታዋ 2/301 እዝነትና መልካምነትን ያቀፈ ነውና ይህንን ታላቅ ዲን ጠንክረን እንያዝ! ከአዳዲስ ድንጋጌዎችም በርሱ እንብቃቃ፤ ስርአትና ድንጋጌዎቹንም እንተግብር። ምስጋና ለአላህ የተገባ ነው! ወንድማቸሁ አቡጁነይድ ግንቦት 3/2007 --------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

የአይሁድ መንግስት በመስጂደል አቅሳ እየፈፀመው ያለው ግፍ በእጅጉ ያሳምማል። ኢባዳ በሚያደርጉበት እና ለኢድ በሚዘጋጁበት ወቅት እንዲሀ እንዲህ ያለ ጭካኔ አይገባም ነበር። በጋዛም ከበድ ያለ ጭፍጨፋ በማድረግ ላይ ነው። አቅም ኖሮን ልንረዳቸው ባለመቻላችን ብንቆጭም ዱአ ብርቱ መሳሪያ መሆኑን ግን መርሳት የለብንም። በቻልነው አቅም ዱአ እናድርግላቸው! اللهم إنا نشكو إليك ضعف قوَّتنا، وقلَّة حِيلتنا، وهواننا على الناس، اللهم أنت ربُّ المستضعفين وأنت ربنا، لا إله إلا أنت، إلى من تكِلنا، إلى قريبٍ يتجهمنا، أم إلى عدوٍ ملكته أمرنا، إن لم يكن بك سخطٌ علينا فلا نبالي، غير أن عافيتك هي أوسع لنا! اللهم انصر إخواننا في فلسطين ضد اليهود الغاصبين @abujunaidposts