uk
Feedback
🗞 ዹ አቡጁነይድ መልዕክቶቜ Abujunaid posts

🗞 ዹ አቡጁነይድ መልዕክቶቜ Abujunaid posts

ВіЎкрОтО в Telegram

ይህ በአቡ ጁነይድ ሳላህ አህመድ ዚቀሚቡ ዚድምፅና ዹፅሁፍ መልዕክቶቜ ዚሚሰበሰቡበት ቻነል ነው። አላህ ጠቃሚ እውቀትን ኚመልካም ስራ ጋር ያግራልን! You can contact me here @salehom100

ППказатО більше
2 217
ПіЎпОсМОкО
НеЌає ЎаМОх24 гПЎОМО
-57 ЎМів
-3330 ЎеМь
Архів ЎПпОсів
ኡድሂያ ለማሚድ ካቀዱ ኚወዲሁ ጥፍርና ጾጉርዎን ኚመቁሚጥ ይቆጠቡ! ------------------- ☞ እንድ ሙስሊም ሀጅ ዚማያደርግ ኹሆነና በዒድ አል አድሀ እለት ኡድሂያን ለማሚድ ካሰበ ዹዙልሂጃ ወ
ኡድሂያ ለማሚድ ካቀዱ ኚወዲሁ ጥፍርና ጾጉርዎን ኚመቁሚጥ ይቆጠቡ! ------------------- ☞ እንድ ሙስሊም ሀጅ ዚማያደርግ ኹሆነና በዒድ አል አድሀ እለት ኡድሂያን ለማሚድ ካሰበ ዹዙልሂጃ ወር ኚገባበት ዚምጀመሪያዉ ቀን ጀምሮ ጥፍሩንና ጞጉሩን አይቆርጥምፀ ቆዳውንም አይቀርፍም። ይህም ተኚታዩን ዚኡሙሰለማ ሀዲስ መሰሚት ያደሚገ ነው። عن أم سلمة رضي الله عنها أن النؚي صلى الله عليه وسلّم قال : " إذا رأيتم هلال ذي الحجة ، وفي لف؞ : "إذا دخلت الع؎ر وأراد أحدكم أن يضحي فليمسك عن ؎عره وأ؞فاره ". رواه أحمد ومسلم ، وفي لف؞ : " فلا يأخذ من ؎عره وأ؞فاره ؎ي؊اً حتى يضحي ". وفي لف؞ : "فلا يمس من ؎عره ولا ؚ؎ره ؎ي؊اً ". ኚኡሙ ሰለማ በተላለፈ ሀዲስ ዹአላህ መልእክተኛ እንዲህ ብለዋልፀ «ዚዙልሂጃ ወርን ጹሹቃ ካያቜሁና ኹናንተ መካኚል አንዱ ኡድሂያ ለማሚድን ካቀደፀ ፀጉሩንና ጥፍሩን ኚመቁሚጥ ይቆጠብ» አል ኢማም አህመድ ዘግበውታል። በሌላም ዘገባም «ኡድሂያውን እስኪያርድ ድሚስ ኚፀጉሩና ኚጥፍሩ ምንንም አይቁሚጥ» ብለዋል። እንደዚሁፀ «ኚሰውነቱ ቆዳ ወይም ኚፀጉሩ ምንንም አይቁሚጥ» ብለዋል። ይህ ማንኛውም ሙስሊም እራሱን በሀጅ ላይ ካሉ ሰዎቜ ጋር ዚሚያመሳስልበት እና ዹተወሰኑ ዚኢህራም ክልኚላዎቜን ኚነሱ ጋር ዚሚጋራበት ዲናዊ ስርአትና ነብያዊ ትዕዛዝ ነው። ☞ ጾጉርንና ጥፍርን ኚመቁሚጥ ዹሚኹለኹለው ለራሱ ወይም ለሰው በራሱ ገንዘብ ዚሚያርድ ሰው ብቻ ነው። ህጉ ዹሚመለኹተው ዚሚያርደዉን ሰው ብቻ ነው ሲባልፀ በወኪልነት ለሌላ ስው ዚሚያርድን ሰው አይጚምርም። ☞ እያወቀ ጥፍሩን ወይም ጞጉሩን ዹቆሹጠ ወንጀል ፈጜሟልና ወደ አላህ በተውበት ሊመለስ ይገባዋልፀ ኡድሂያው ግን አይበላሜም ማካካሻ ኚፋራም ዚለበትም። አንዳንዶቜ እንደሚያስቡት ሳይሆን ወንጀሉን ቢፈፅምም ኡድሂያ ማሚዱን መተው ዚለበትም። ☞ በስህተት ወይም በመርሳት ፀጉሩን ወይም ጥፍሩን ዹቆሹጠ ሰው ምንም ወንጀል ዚለበትም። በተመሳሳይ መልኩ በጣም አስፈላጊ ሲሆን ቢቆርጥ ቜግር ዚለውም። ለምሳሌ ዚተጎዳን ዚሰውነት ቆዳ ለማኹም ወይም ዹተሰበሹ ጥፍሩን ለማስተካኚል መቁሚጥ ይፈቀድለታል። ፠ ስለ ኡድሂያ ጥቂት ተጚማሪ ነጥቊቜ 1 - በዙልሂጃ አስር ቀናት ኚተወደዱ ተግባሮቜ መካኚል ኡድሂያን በማሚድ ወደ አላህ መቃሚብ አንዱ ነው። 2- ኡድሂያ በጣም ኚጠነኚሩ ዚነብዩ صلى الله عليه وسلم ሱናዎቜ መካኚል ነው። ኡድሂያ ዚነብዩ ኢብራሂምን ሱና ህያው ኚማድሚግ በተጚማሪ ለድሆቜ እና ቜግሚኞቜ መድሚስ ነው። 3- ኡድሂያን በተመለኹተ አላህ ኹኛ ዹሚፈልገው ለእርሱ ያለንን ፍራቻ ተቅዋና ታዛዥነት ግልጜ ማድሚጋቜንን ብቻ ነው። አላህ እንዲህ ብሏልፀ {ﻟَﻊ ﻳَﻚَﺎﻝَ اﻟﻠَّﻪَ ﻟُﺀُﻮﻣُﻬَﺎ ﻭَﻻَ ﺩِﻣَﺎﺅُﻫَﺎ ﻭَﻟَٰﻜِﻊ ﻳَﻚَﺎﻟُﻪُ اﻟﺘَّﻘْﻮَﻯٰ ﻣِﻚﻜُﻢْ ۚ ﻛَﺬَٰﻟِﻚَ ﺳَﺚَّﺮَﻫَﺎ ﻟَﻜُﻢْ ﻟِﺘُﻜَﺒِّﺮُﻭا اﻟﻠَّﻪَ ﻋَﻠَﻰٰ ﻣَﺎ ﻫَﺪَاﻛُﻢْ ۗ ﻭَﺑَﺞِّﺮِ اﻟْﻀُﺀْﺎِﻚِﻎﻊَ} الحج 37 አላህን ሥጋዎቿም ደሞቿም ፈጜሞ አይደርሰውም፡፡ ግን ኚእናንተ ዹሆነው ፍራቻ ይደርሰዋል፡፡ እንደዚሁ አላህን በመራቜሁ ላይ ልታኚብሩት ለእናንተ ገራት፡፡ በጎ ሠሪዎቜንም አብስር፡፡» አል ሐጅ 37 4- ኡድሂያ ዚሚታሚደው ኚዒድ ሰላት በኋላ ነው። ዹአላህ መልዕክተኛ صلى الله عليه وسلم ኚኢድ ሰላት በፊት ያሚደ ሰው እንዲደግም አዘዋል። 5- ሚዛን በሚደፋው ዚኡለማዎቜ አቋም መሰሚት ዚዒድ ሰላት ኚተጠናቀቀበት ጊዜ ጀምሮ ዚሶስተኛው ቀን ጾሀይ እስክትጠልቅ ድሚስ ኡድሂያን ማሚድ ይቻላል። 6- ወንድም ይሁን ሎት ግመል፣ ዚቀንድ ኚብቶቜ፣ በግና ፍዹል ለኡድሂያ ይታሚዱሉ። 7- ዹአላህ መልዕክተኛ صلى الله عليه وسلم እንኚን ያለባ቞ውን እንስሳት እንዳናርድ ኚልክለዋል። አንድ አይኑ ዚታወሚ፣ ስብራት ያለበት፣ ዚኚሳና ዹደኹመ ወይም ዚታመመ እንስሳ ለኡድሂያ አይሆንም። 8- ኡድሂያን ለብቻ ማሚድ እንደሚቻለው ሁሉ ለሰባት ሆኖ አንድን ወይፈን ወይም በሬ መጋራትም ይቻላል። 9- አንድ ሰው ኡድሂያ ሲያርድ ለራሱ እና በህይወት ላሉም ይሁን በህይወት ለሌሉ ቀተሰቊቹ አስቊ ሊያርድ ይቜላል። 10- ዚኡድሂያውን ስጋ፣ ለቀት፣ ለስጊታ እና ለሰደቃ አድርጎ ሶስት ቊታ መኹፋፈሉ ሱና ነው። ይህ ማለት ግን እንደ አስፈላጊነቱ ለሶስቱም ያውለዋል ማለት እንጂ ሶስት እኩል ቊታዎቜ ይኹፋፍለዋል ማለት አይደለም። አቡጁነይድ Http://www.t.me/abujunaidposts

🗞 ኚዱንያ ቀናት ሁሉ ብልጫ ያላ቞ው አስርቱ ዹዙልሂጃ ቀናት ✍ ዝግጅትፊ አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ ህዳር 2004 🔗 ዹፅሁፉ ሊንክ https://d1.islamhouse.com/data/am/ih_articles/single/am_Virtues_of_the_Ten_Days_of_Dhul_Hijjah.pdf 🔗 telegram Share Link https://t.me/abujunaidposts/374 ---------------- 📮ዚአቡጁነይድ መልዕክቶቜ @abujunaidposts

አሰላሙዓለይኩም ዚመዲና ኢስላላዊ ዩኒቚርሲቲ ኚተለያዩ ዹአለም ሀገራት ለመማርና ማህበሚሰባ቞ውን ለማገልገል ዹሚፈልጉ ተማሪዎቜ ኹ May 1 እስኚ july 14 / 2025 ብቻ ኹ በ "study in Sa
አሰላሙዓለይኩም ዚመዲና ኢስላላዊ ዩኒቚርሲቲ ኚተለያዩ ዹአለም ሀገራት ለመማርና ማህበሚሰባ቞ውን ለማገልገል ዹሚፈልጉ ተማሪዎቜ ኹ May 1 እስኚ july 14 / 2025 ብቻ ኹ በ "study in Saudi" በሚባለው ዚማመልኚቻ መቀበያ ድሚገፅ በኩል እንዲያመለክቱ ይጋብዛል። ሊንክ https://studyinsaudi.moe.gov.sa وفقكم الله

🔎 እውነትን ፍለጋ! 🌎 ዹሰልማን አልፋሪሲይ ዚመስለም ታሪክ 🎙አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ 📆 እሁድ ዚካቲት 12/2015 🕌 በአቃቂ ዑመር መስጂድ ዹቀሹበ ሙሀደራ 🔗 Telegram Link https://t.me/abujunaidposts/581 ---------------- 📮ዚአቡጁነይድ መልዕክቶቜ @abujunaidposts

🔎 እውነትን ፍለጋ! 🌎ዚሰልማን አልፋሪሲይ ዚመስለም ታሪክ 🎙አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ 📆 እሁድ ዚካቲት 12/2015 🕌 በአቃቂ ዑመር መስጂድ ዹቀሹበ ሙሀደራ 🔗 Telegram Link https://t.me/abujunaidposts/579 ---------------- 📮ዚአቡጁነይድ መልዕክቶቜ @abujunaidposts

🔎 እውነትን ፍለጋ! 🌎ዚሰልማን አልፋሪሲይ ዚመስለም ታሪክ 🎙አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ 📆 እሁድ ዚካቲት 12/2015 🕌 በአቃቂ ዑመር መስጂድ ዹቀሹበ ሙሀደራ 🔗 Telegram Link https://t.me/abujunaidposts/578 ---------------- 📮ዚአቡጁነይድ መልዕክቶቜ @abujunaidposts

🔎 እውነትን ፍለጋ! 🌎ዚሰልማን አልፋሪሲይ ዚመስለም ታሪክ 🎙አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ 📆 እሁድ ዚካቲት 12/2015 🕌 በአቃቂ ዑመር መስጂድ ዹቀሹበ ሙሀደራ 🔗 Telegram Link https://t.me/abujunaidposts/578 ---------------- 📮ዚአቡጁነይድ መልዕክቶቜ @abujunaidposts

🏷 ኢስላማዊ ማንነት 🎙አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ ⏱ እሁድ 3:00 ሚያዝያ 3/2013 🕌 በአባጅፋር መስጂድ ዹቀሹበ 🔗 Telegram Link https://t.me/abujunaidposts/391 ---------------- 📮ዚአቡጁነይድ መልዕክቶቜ @abujunaidposts

🏷 ኢስላማዊ ማንነት 🎙አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ 🎙አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ ⏱ እሁድ 3:00 ሚያዝያ 3/2013 🕌 በአባጅፋር መስጂድ ዹቀሹበ 🔗 Telegram Link https://t.me/abujunaidposts/391 ---------------- 📮ዚአቡጁነይድ መልዕክቶቜ @abujunaidposts

ዚአዳዲስ ሰለም቎ዎቜ መመሪያ New muslim guide.pdf https://newmuslimguide.com/am

🔖 ዚእምነት ፈተና እና ዚኢማሙ አሕመድ ፅናት 🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ ⌚ 38:12 ደቂቃ 🍂 ዚአህሉሱና ኢማም አህመድ ኢብኑ ሀንበል በንጉሶቜ በታገዙ ጀህሚያዎቜ ዚደሚሰባ቞ውን ኚባድ ግፍና ፈተና ካለፉበት ፅናት ዚሚወሰዱ ትምህርቶቜ https://t.me/abujunaidposts/92 ---------------- 📮ዚአቡጁነይድ መልዕክቶቜ @abujunaidposts

በሚመዳን ወር ቎ልቪዥን እና ቪዲዮ መመልኚት ፆምን ያጓድላልን?  áˆ˜áˆáˆµ - አንድ ሠው ዚሚያዳምጠው ወይም ዹሚመለኹተው ነገር ኚተፈቀዱ ነገሮቜ (ሙባሀት) ኹሆነ ምንም ቜግር ዹለውም ፆምመአ ላይ እንኚን አይሆንም፡፡ ሆኖም ግን ፆመኛ ሰው ጊዜውን ወደ አላህ ሊያቃርበው በሚቜል ነገር ብቻ ነው ማሳለፍ ያለበት፡፡ ቁርዓንን ያነባል አላህን ያወድሳል ወዘተ...  áŠ áˆ‹áˆ… ሀራም ያደሚገውን ነገር ማዳመጥ ወይም መመልኚት ግን ፆምን እንደሚያጓድል ምንም ጥርጥር ዚለውም፡፡ ዹዚህም ምክንያት ፆም ዚተደነገገበት አላማ ዹአላህን ፍራቻ (ተቅዋን) መላበስ ነው፡፡  Ù‚ال تعالى{يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُواْ كُتَِؚ عَلَيْكُمُ الصِّيَامُ كَمَا كُتَِؚ عَلَى الَّذِينَ مِن قَؚْلِكُمْ لَعَلَّكُمْ تَتَّقُونَ} الؚقرة : 183  Â«áŠ¥áŠ“áŠ•á‰° ያመናቜሁ ሆይ ጟም በነዚያ ኹናንተ በፊት በነበሩት (ሕዝቊቜ) ላይ እንደተደነገገ ሁሉ በናንተም ላይ ተደነገገ። ልትጠነቀቁ ይኚጀላልና፡፡»አልበቀራህ 183  áŠ áˆ‹áˆ… በዚህ አንቀፅ ፆም በግዎታነት ዚተደነገገበት አላማ ተቅዋ መሆኑን ገልፆዋል፡፡  Ø¹Ù† أؚي هريرة رضي الله عنه قال قال رسول الله صلى الله عليه وسلم: (من لم يدع قول الزور والعمل ØšÙ‡ فليس لله حاجة في أن يدع طعامه و؎راؚه) صحيح الؚخارى  á‹šáŠ áˆ‹áˆ… መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል ‹‹መጥፎ ንግግርን እና መሀይምነትን ያልተወ ሰው አላህ ዘንድ ምግብና መጠጥ መተው ቊታ ዹለውም (ቡኻሪ ዘግበውታል)  á‰ á‹šáˆ… መሠሚት ማንኛውም ፆመኛ ዚሚሠራው ሀጢዓት ፆሙ ላይ ተፅዕኖ አለው፡፡  áŠšá‹šáˆ…áˆ ውስጥ አንዳንድ ሠዎቜ እንደሚያደርጉት ኚምግብ ኚመጠጥና ኚስጋዊ ተራክቊ ይቆጠቡና በአላህ ላይ ያምፃሉ፡፡ አንዳንዱ ሱሁር ኹበላ በኋላ ይተኛና ዹፈጅርን ሠላት ያሣልፋል ዚሚነሣው ፀሃይ ኚወጣቜ በኋላ ነው፡፡ ሌላው ደግሞ ዚዓስርን ሠላት ሣይሰግድ ይተኛና በኢፍጣር ሰዓት ተነስቶ አራት ጊዜ ጎንበስ ቀና ይላል፡፡ ጥቂትን እንዲ አላህን አያድስም፡፡ አንዳንድ ሠዎቜ ደግሞ ሠዎቜን ያማሉ በንግድ ወቅት ያጭበሚብራሉ ብዙ ወንጀሎቜንም ይፈፅማሉ፡፡ ይህን ሁሌ ዚሚያደርጉት ፆመኛ ሆነው ነው፡፡ እነዚህ ሁሉ ዹሚፈፅሙን ሀራም ተግባር ዹፆማቾውን ምንዳ እንደሚቀንሠው ጥርጥር ዚለውም፡፡ ምናልባትም ምንዳውና ሀጢአቱ እኩል ይሆኑና ዹፆሙን ምንዳ ያጣሉ፡፡  áˆˆáˆ™áˆµáˆˆáˆŠáˆ ወንድሞቜ እና እህቶቜ ዚማስተላልፈው ምክርፀ አላህ በእነርሱ ላይ እርም ካደሚጋ቞ው ነገሮቜ እና ተግባሮቜ ፆማቾውን እንዲጠብቁ እና ይህን ዚተባሚኚ ወር አላህን በመታዘዝ እንዲያሳልፉት ነው፡፡ እርም ነገሮቜን ኹመተው እና ግዎታዎቜን ኹመፈፀም ሚገድ ራሳ቞ውን ዚሚያንፁበት ታላቅ እድል ነው፡፡ ወቢላሂ ተውፊቅ!  áˆžá‹­áŠœ ሙሀመድ ቢን ሷሊህ አል-ኡሰይሚን @abujunaidposts

🔖 ዒባዳን ለመገንዘብ! 🎙አቡ ጁነይድ ሳላሕ አሕመድ 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/209 ---------------- 📮ዚአቡጁነይድ መልዕክቶቜ @abujunaidposts

وَقَالُوا۟ ٱتَّخَذَ ٱلرَّحۡمَـٰنُ وَلَدࣰا * لَّقَدۡ جِ؊ۡتُمۡ ؎َیۡـًٔا إِدࣰّا *  تَكَادُ ٱلسَّمَـٰوَ ٰ⁠تُ یَتَفَطَّرۡنَ مِنۡهُ وَتَن؎َقُّ ٱلۡأَرۡضُ وَتَخِرُّ ٱلۡجَِؚالُ هَدًّا *  أَن دَعَوۡا۟ لِلرَّحۡمَـٰنِ وَلَدࣰا *  وَمَا یَنَؚۢغِی لِلرَّحۡمَـٰنِ أَن یَتَّخِذَ وَلَدًا *  إِن كُلُّ مَن فِی ٱلسَّمَـٰوَ ٰ⁠تِ وَٱلۡأَرۡضِ إِلَّاۀ ءَاتِی ٱلرَّحۡمَـٰنِ عَؚۡدࣰا *  لَّقَدۡ أَحۡصَىٰهُمۡ وَعَدَّهُمۡ عَدࣰّا *  وَكُلُّهُمۡ ءَاتِیهِ یَوۡمَ ٱلۡقِیَـٰمَةِ فَرۡدًا «አልሚሕማንም ልጅን ያዘ (ወለደ)» አሉ፡፡ ኚባድ መጥፎን ነገር በእርግጥ አመጣቜሁ፡፡ በእርሱ (በንግግራ቞ው ምክንያት) ሰማያት ሊቀደዱ፣ ምድርም ልትሰነጠቅ፣ ጋራዎቜም ተንደው ሊወድቁ ይቃሚባሉ፡፡ ለአልሹሕማን ልጅ አለው ስለአሉ፡፡ ለአልሹሕማን ልጅን መያዝ አይገባውም!! በሰማያትና በምድር ያለው ሁሉ (በትንሣኀ ቀን) ለአልራሕማን ባሪያ ኟነው ዚሚመጡ እንጂ ሌላ አይደሉም Surah Maryam 88 - 95 @abujunaidposts

{ قَالَ أَتَعُؚۡدُونَ مَا تَنۡحِتُونَ * وَٱللَّهُ خَلَقَكُمۡ وَمَا تَعۡمَلُونَ } «አላህ እናንተንም ዚምትሠሩትንም ዹፈጠሹ ሲኟንፀ ዚምትጠርቡትን ትገዛላ
{ قَالَ أَتَعُؚۡدُونَ مَا تَنۡحِتُونَ * وَٱللَّهُ خَلَقَكُمۡ وَمَا تَعۡمَلُونَ } «አላህ እናንተንም ዚምትሠሩትንም ዹፈጠሹ ሲኟንፀ ዚምትጠርቡትን ትገዛላቜሁን?» አላ቞ው። Surah Aá¹£-Ṣāffāt: 95-96

🀝 ዚሙስሊሞቜ አንድነት 🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ ⌚ ዹ 44 ደቂቃ መልዕክት 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/132 ---------------- 📮ዚአቡጁነይድ መልዕክቶቜ @abujunaidposts

📌 ንፁሕ ልብ ♡ 🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/137 ---------------- 📮ዚአቡጁነይድ መልዕክቶቜ @abujunaidposts

በካፊሮቜ በዓል እንኳን አደሚሳቜሁ ማለት ይፈቀዳልን? በበአላት ሰሞን በተደጋጋሚ እገሌና እገሌ ላይክ አድርገውታል ኹሚለን ፖስቶቜ መካኚል ኚፊሎቹ ዚእንኳን አደሚሳቜሁ መልእክቶቜ ና቞ው። ለጌታ መወለድ፣ ለጌታ መሰቀል፣ ለጌታ ሞቶ መነሳት (ትንሳኀና) መሰል ክስተቶቜ እንኳን አደሚሳቜሁ ሲባል ሌር ወይም ላይክ ዚሚያደርጉ ብዙ እህትና ወንድሞቜን አስተውያለው። አንዳንዎ በስህተት ሌላ ግዜም ነገሩን እንደቀላል በመውሰድ ዹሚፈፀም ሊሆን ይቜላል። ሆኖም እጅግ ኚባድና በአኌራ ዋጋ ዚሚያስኚፍል መዘናጋት ነው!! በካፊሮቜ በአልፀ እንኳን አደሚሳቜሁ... እንኳን ደስ አላቜሁ... እንኳን አብሮ አደሹሰን ማለት እነሱን ለማስደሰትም ይሁን ለመመሳሰል ኹአላህ ዲን መንሞራተት እና ዚካፊሮቜን ኩፍር ዹመናገር ስነልቊና መካብ ስለሆነ ክልክል ነው። መኚባበር እና አብሮነትን ለማሳዚት ኚእምነታቜን መንሞራተት አይጠበቅብንም። ዲን ኹምንም በላይ ነውና ሞሪዓን መተላለፍ ፍፁም ጥፋት ነው!! ፈጣሪ ወለደ ተወለደ ዹሚለው አስተምህሮ ዚጥፋትነቱ ክብደት ሰማያትንና ምድርን ሊሰነጥቅ እንደሚቀርብ ቁርአን ይነግሚናል። አላህን ዚሚያስቆጣ ተግባር በመፈፀማቾው እንኳን ደስ ያላቜሁ ማለት ኚሙስሊም አይጠበቅም!! (وَقَالُوا۟ ٱتَّخَذَ ٱلرَّحۡمَـٰنُ وَلَدࣰا * لَّقَدۡ جِ؊ۡتُمۡ ؎َیۡـًٔا إِدࣰّا *  تَكَادُ ٱلسَّمَـٰوَ ٰ⁠تُ یَتَفَطَّرۡنَ مِنۡهُ وَتَن؎َقُّ ٱلۡأَرۡضُ وَتَخِرُّ ٱلۡجَِؚالُ هَدًّا *  أَن دَعَوۡا۟ لِلرَّحۡمَـٰنِ وَلَدࣰا *  وَمَا یَنَؚۢغِی لِلرَّحۡمَـٰنِ أَن یَتَّخِذَ وَلَدًا *  إِن كُلُّ مَن فِی ٱلسَّمَـٰوَ ٰ⁠تِ وَٱلۡأَرۡضِ إِلَّاۀ ءَاتِی ٱلرَّحۡمَـٰنِ عَؚۡدࣰا *  لَّقَدۡ أَحۡصَىٰهُمۡ وَعَدَّهُمۡ عَدࣰّا *  وَكُلُّهُمۡ ءَاتِیهِ یَوۡمَ ٱلۡقِیَـٰمَةِ فَرۡدًا) [«አልሚሕማንም ልጅን ያዘ (ወለደ)» አሉ፡፡ ኚባድ መጥፎን ነገር በእርግጥ አመጣቜሁ፡፡ በእርሱ (በንግግራ቞ው ምክንያት) ሰማያት ሊቀደዱ፣ ምድርም ልትሰነጠቅ፣ ጋራዎቜም ተንደው ሊወድቁ ይቃሚባሉ፡፡ ለአልሹሕማን ልጅ አለው ስለአሉ፡፡ ለአልሹሕማን ልጅን መያዝ አይገባውም!! በሰማያትና በምድር ያለው ሁሉ (በትንሣኀ ቀን) ለአልራሕማን ባሪያ ኟነው ዚሚመጡ እንጂ ሌላ አይደሉም] Surah Maryam 88 - 95 ለመሆኑ አንድን ካፊር ለሀይማኖታዊ በአል እንኳን አደሹሰህ ስትለውፀ ምን ማለት እንደሆነ ግልፅ አይደለምን? እንኳን አደሹሰህ... ጌታ ተወልዶ ተሰቅሎ ሞቷል ብለህ ለማወጅ፣ ለመስቀል ለመስገድና  ዚፈጣሪን ክብር ዚሚነኩ ንግግሮቜን ለመናገር እንኳን በቃህ! እንኳን አደሹሰህ... ማርያም ፈጣሪዋን ወለደቜውፀ በመጠቅለያም ጠቀለለቜው እያልክ ለመዘመር እንኳን በቃህ! ዚኩፍር ተግባርን ለመኹወን ኹሆነ ዹደሹሰው ለምንስ እንኳን አብሮ አደሹሰን እንላለን? እውቁ አሊም ኢብኑል ቀይም ሹሂመሁላህ ይህ ተግባር ዹተኹለኹለ ስለመሆኑ ዚኡለማዎቜ ዚጋራ አቋም መሆኑን በመጠቆም እንዲህ ብለዋልፀ «ኩፍርን ብቻ በሚያንፀባርቁ ዚሀይማኖታ቞ው መገለጫዎቜ እንኳን አደሚሳቜሁ...እንኳን ደስ ያለቜሁ ማለት ሀራም መሆኑ ዹሁሉም ሊቃውንት ስምምነት ያለበት ነው። ለምሳሌ አንድ ሙስሊም በነሱ በዓላትና ፆም ጊዜፀ «በአሉን ዚተባሚኚ ያድርግልህ» ወይም «መልካም ዚደስታ በአል ያድርግልህ» እና መሰል ዚደስታ መግለጫዎቜን ቢያስተላልፍፀ ተናጋሪው ኚኩፍር ቢድን እንኳ ኚባድ ወንጀል ነው ዚፈፀመው። ይህምፀ ልክ «እንኳን ለመስቀል ሰገድክ» ብሎ ደስታን እንደመግለፅ ነው! ይህ እንደውምፀ አንድ ሰው ነብስ በማጥፋቱ፣ አልኮል በመጠጣቱ፣ ዝሙት በመፈፀሙና በመሰል ተግባራት እንኳን ደስ ያለህ ኚማለት በወንጀልነት ዹኹበደ እና አስቀያሚ ነው። ለኢስላማዊ ድንጋጌዎቜ ተገቢዉን ክብር ዚማይሰጡ ብዙ ሰዎቜ ይህንን ይፈፅማሉ።  ምን ያክል ዚሚያስጠላ ዚግባር እንደፈፀሙም አያስተውሉም። ቢድአ፣ ኩፍር እና ወንጀሎቜ በመፈፀማቾው እንኳን አደሚሰህ፣ እንኳን ደስ ያለህ እና መሰል ዚደስታ መግለጫዎቜን ያስተላለፈፀ እራሱን ለአላህ ቁጣና ጥላቻ ዚተገባ እንዲሆን ዚሚያደርግ ምክኒያት ፈፅሟል»  አህካም አህሉዚማህ ዚዘመናቜን ፈቂህ ሞይኜ ኡሰይሚን ሹሂመሁላህ እንዲህ አሉ «ካፊሮቜን እንኳን አደሚሳቜሁ ማለት ኢብኑል ቀይም እንዳለው ዹዚህን ያክል ኚባድ ዚሆነበት ምክኒያት እነርሱ ዹሚፈፅሟቾውን ዚኩፍር መገለጫዎቜ ማፅደቅ ስለሆነ ነው። ምንም እንኳን ለራሱ ይህንን ኩፍር መፈፀምን ባይወድም እነሱ መፈፀማቾውን ወዷልና። ሙስሊም ደግሞ ዚኩፍር መገለጫዎቜን መውደድም ይሁን ሌሎቜን እንኳን ደስ ያላቜሁ ማለት አይፈቀድለትም።» መጅሙዑ ፈታዋ ወሚሳኢል አሞይኜ ኢብኑ ኡሰይሚን 3/44  በተመሳሳይ መልኩፀ ክሪስማስም ሆነ ሌሎቜ በአላት ላይ ስጊታ ወይም ፓስት ካርዶቜን መለዋወጥፀ እንዲሁም ማንኛውም ደስታን መግለጫ ዹሆኑ ነገሮቜን መፈፀም በአሉን መካፈል ስለሆነ ዹተኹለኹለ ነው!! በዚህ ፅሁፍ መጠቆም ዚፈለኩት ምንም አይነት ማህበራዊ ግንኙነት ሀራም ነው ዹሚል መልእክት አይደለም። በተለይም ኚክርስቲያን እና አይሁዶቜ ጋር ባለን ማህበራዊ ግንኙነቶቜ ላይ ዚተፈቀዱ ብዙ በመልካም ዹመኗኗር እሎቶቜ አሉን።  ሆኖም ሀይማኖታዊ ወሰኖቜ ዹሉም ማለት አይደለም። ዹተፈቀደውን ስንተገብር እንደ ያልተፈቀደ ጋብቻ፣ በአላት ላይ መሳተፍ፣ ለሞቱት ዹአላህን ማርታ መለመንና ባጠቃላይ በዲን መመሳሰልን ግን በፍፁም አንፈፅምም። ይህንን ዚእምነትና ዚሀይማኖት ወሰን መናድ አይቻልም። ማንነታቜንን ማክበር፣ ግንኙነታቜንን በዲናዊ ገደቊቜ ማጠር ብሎም አለመሟሟት ለሌሎቜ ሞራል ዲንና ማንነት ኹመጹነቅ ይቀድማል። ዲን ኹምንም በላይ ነውና ኹመሾማቀቅ እንውጣ። ይህ  ዚዲናቜን መገለጫ እንጂ እንደ ማክሹርና ፅንፈኝነት ዚሚታይ አይደለም። በነገራቜን ላይ ዚአንድ እምነት ተኚታይ ኚሌሎቜ ለመቀራሚብ ብሎ ኚራሱ እምነት ጋር ዚሚጣላበት ሁኔታ ድሮ ቀርቷል። ሌሎቹም ቢሆኑ ይህ በኛ ሀይማኖት አልፈቀድም እና ይቅርታ ይሉሀል። (فَلَا تُطِعِ ٱلۡمُكَذِؚِّینَ * وَدُّوا۟ لَوۡ تُدۡهِنُ فَیُدۡهِنُونَ * وَلَا تُطِعۡ كُلَّ حَلَّافࣲ مَّهِینٍ) አስተባባዮቜንም አትታዝዙ፡፡ ብትመሳሰላ቞ውና ቢመሳሰሉህ ተመኙ፡፡ [Surah Al-Qalam 8 - 10] ወላሁ አዕለም አላህ ኚጥፋት ሁሉ ይጠብቀን! https://t.me/abujunaidposts/141 ____ አቡጁነይድ ሚጀብ 24/1437 ዓ.ሒ / ሜይ 1/ 2016

አልሀበሺ እውነታውን ሲያምን!! #መውሊድ መውሊድን ዹማክበር ሀሳብ ኚክርስቲያኖቜ ዹገና በአል ተኮርጆ ዚመጣ መሆኑን ላለመቀበል ሀሰን ታጁ እና መሰሎቹ ቢሞግቱም አብደላህ አልሀበሺ በተቃራኒው እውነታው
አልሀበሺ እውነታውን ሲያምን!! #መውሊድ መውሊድን ዹማክበር ሀሳብ ኚክርስቲያኖቜ ዹገና በአል ተኮርጆ ዚመጣ መሆኑን ላለመቀበል ሀሰን ታጁ እና መሰሎቹ ቢሞግቱም አብደላህ አልሀበሺ በተቃራኒው እውነታውን አምኗልፀ ☞ ዹ ‘ኢዝሀሩል አቂደቲሱኒያህ’ ዚድምፅ ማብራሪያ ካሎት ቁ.9 ዚመጀመሪያው ክፍል ላይ ዚመውሊድን አጀማመር አስመልክቶፀ መውሊድን ለመጀመሪያ ጊዜ ያኚበሚው ዚኢርቢሉ ንጉስ ሙዘፈር እንደሆነ እና አጀማመሩም ክርስቲያኖቜ ዚመሲህን ልደት ሲያኚብሩ አይቶ ሙሀመድ ï·º በዚህ አለም ብቅ በማለታ቞ው አላህን ሊያመሰግን እንደሆነ ያብራራል። ★እኛም እውነታዉን በማመኑ እያመሰገነው ተኚታዮቹን ነጥቊቜ እንጠቁማለንፀ 1) መውሊድን በዓል አድርጎ ማክበር መልእክተኛው ï·º ወደዚህ አለም በመምጣታ቞ው ለአላህ ምስጋና ዚማቅሚቢያና ውዎታንም ዚመግለጫ መንገድ ኹሆነ ኚሰሀቊቜና ታቢዒዮቜ ዘመን ጀምሮ ዚኖሩ ምርጥ ዚኢስላም ልጆቜ ሳያውቁት በ630 ዓ.ሒ ዹሞተው ንጉስ ተገለጠለትን? 2) በላጭ ትውልዶቜ ዚተባሉት ቀደምቶቹ ሰለፎቜ ይህንን መውሊድ ያላኚበሩትፀ ክርስቲያኖቜና አህባሟቜ ዚደሚሱበትን መውሊድ አላህን ዚማመስገኛ መንገድ ዹመሆኑን እውነታ ማወቅ ተስኗ቞ው ነውን? ይህንን ካላቜሁ ጥመታቜሁ ግልፅ ወጣ አለያ ወደነሱ መንገድ ተመለሱ!! 3) ይህ ዚተምታታ ግንዛቀ መነሻ ያደሚገውን ሀሳብ ስንመለለትፀ ክርስቲያኖቜ ዚኢሳን ልደት በማክበራ቞ው አላህን በማመስገን ኚምርጊቹ ዚሰለፎቜ ትውልዶቜ መቅደማቾውን ያመላክታል። ይህ ደግሞ ባጢል ነው!! 4) አልሐበሺ እና ተኚታዮቹ ክርስቲያኖቜን በመኹተል ልደት ሲያኚብሩ መልእክተኛው ï·º በብዙ ሀዲሶቜፀ በኢስላማዊ እንድንኮራ ማዘዛቾውና አይሁዶቜና ክርስቲያኖቜን አርአያ እንዳናደርግ አበክሹው መምኚራ቞ውን ለምን ዘነጉ? ሙስሊም ኚካፈር ጋር መመሳሰል እንደሌለበት አያውቁምን?? መልዕክተኛው ï·º እንዲህ ብለዋልፀ عَنْ أَؚِي سَعِيدٍ الْخُدْرِيّ، قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللّهِ صلى الله عليه وسلم "لَتَتؚِّعُنّ سَنَنَ الّذِينَ مِنْ قَؚْلِكُمْ. ؎ِؚْراً ؚِ؎ِؚْرٍ، وَذِرَاعاً ؚِذِرَاعٍ. حَتّىَ لَوْ دَخَلُوا فِي جُحْرِ ضََؚ لاَتَؚّعْتُمُوهُمْ" قُلْنَا: يَا رَسُولَ اللّهِ آلْيَهُودُ وَالنّصَارَىَ؟ قَالَ "فَمَنْ؟". [رواه الؚخارى ومسلم ]. አቢ ሰዒድ አልኹድሪይ ሚዲዚላሁ ዐንሁ እንዲህ አሉፀ ዹአላህ መልዕክተኛ ï·º እንዲህ አሉፀ «ኚናንተ በስተፊት ዚነበሩትን (ህዝቊቜ) ፈለግ ስንዝር በስንዝር እርምጃ በእርምጃ ትኚተላላቜሁ። ዚተሳቢ እንስሳ ጉድጓድ እንኳ ቢገቡ ትኚተሏ቞ዋላቜሁ!» ዹአላህ መልዕክተኛ ï·º ሆይ ይሁዶቜንና ነሳራዎቜን ነው ? «ሌላ ማንን ነው!» (እነሱን ነው እንጂ) አሉ። ይህንን ነብያዊ ትንቢት ባንሰማ ኖሮ በሙዘፈር ድርጊት ተገርመን አናበቃም ነበር። 5) አላህ ዲናቜንን ዹተሟላ አድርጎት ሳለፀ ክርስቲያኖቜ ሰሩት ብለን በዲናቜን ዹሌለን ነገር እንፈፅማለን?? (ٱلْيَوْمَ أَكْمَلْتُ لَكُمْ دِينَكُمْ وَأَتْمَمْتُ عَلَيْكُمْ نِعْمَتِى وَرَضِيتُ لَكُمُ ٱلْإِسْلَـٰمَ دِينًۭا ۚ فَمَنِ ٱضْطُرَّ فِى مَخْمَصَةٍ غَيْرَ مُتَجَانِفٍۢ لِّإِثْمٍۢ ۙ فَإِنَّ ٱللَّهَ غَفُورٌۭ رَّحِيمٌۭ) الما؊دة 3 «ዛሬ ሃይማኖታቜሁን ለእናተ ሞላሁላቜሁ። ጞጋዬንም በናንተ ላይ ፈጞምኩ። ለእናንተም ኢስላምን ኚሃይማኖት በኩል ወደድኩ» አልማኢዳህ 3 በእውነትም ዹዛኔ ዲን ያልነበሚ አሁን ዲን ሊሆን አይቜልም!! አኹኩም አቡጁነይድ ሚቢኡልአወል 9 /1436 ዓ.ሒ https://t.me/abujunaidposts