fa
Feedback
🗞 የ አቡጁነይድ መልዕክቶች Abujunaid posts

🗞 የ አቡጁነይድ መልዕክቶች Abujunaid posts

رفتن به کانال در Telegram

ይህ በአቡ ጁነይድ ሳላህ አህመድ የቀረቡ የድምፅና የፅሁፍ መልዕክቶች የሚሰበሰቡበት ቻነል ነው። አላህ ጠቃሚ እውቀትን ከመልካም ስራ ጋር ያግራልን! You can contact me here @salehom100

نمایش بیشتر
2 219
مشترکین
-124 ساعت
-77 روز
-3530 روز
آرشیو پست ها
ኡድሂያ ለማረድ ካቀዱ ከወዲሁ ጥፍርና ጸጉርዎን ከመቁረጥ ይቆጠቡ! ------------------- ☞ እንድ ሙስሊም ሀጅ የማያደርግ ከሆነና በዒድ አል አድሀ እለት ኡድሂያን ለማረድ ካሰበ የዙልሂጃ ወ
ኡድሂያ ለማረድ ካቀዱ ከወዲሁ ጥፍርና ጸጉርዎን ከመቁረጥ ይቆጠቡ! ------------------- ☞ እንድ ሙስሊም ሀጅ የማያደርግ ከሆነና በዒድ አል አድሀ እለት ኡድሂያን ለማረድ ካሰበ የዙልሂጃ ወር ከገባበት የምጀመሪያዉ ቀን ጀምሮ ጥፍሩንና ጸጉሩን አይቆርጥም፤ ቆዳውንም አይቀርፍም። ይህም ተከታዩን የኡሙሰለማ ሀዲስ መሰረት ያደረገ ነው። عن أم سلمة رضي الله عنها أن النبي صلى الله عليه وسلّم قال : " إذا رأيتم هلال ذي الحجة ، وفي لفظ : "إذا دخلت العشر وأراد أحدكم أن يضحي فليمسك عن شعره وأظفاره ". رواه أحمد ومسلم ، وفي لفظ : " فلا يأخذ من شعره وأظفاره شيئاً حتى يضحي ". وفي لفظ : "فلا يمس من شعره ولا بشره شيئاً ". ከኡሙ ሰለማ በተላለፈ ሀዲስ የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ብለዋል፤ «የዙልሂጃ ወርን ጨረቃ ካያችሁና ከናንተ መካከል አንዱ ኡድሂያ ለማረድን ካቀደ፤ ፀጉሩንና ጥፍሩን ከመቁረጥ ይቆጠብ» አል ኢማም አህመድ ዘግበውታል። በሌላም ዘገባም «ኡድሂያውን እስኪያርድ ድረስ ከፀጉሩና ከጥፍሩ ምንንም አይቁረጥ» ብለዋል። እንደዚሁ፤ «ከሰውነቱ ቆዳ ወይም ከፀጉሩ ምንንም አይቁረጥ» ብለዋል። ይህ ማንኛውም ሙስሊም እራሱን በሀጅ ላይ ካሉ ሰዎች ጋር የሚያመሳስልበት እና የተወሰኑ የኢህራም ክልከላዎችን ከነሱ ጋር የሚጋራበት ዲናዊ ስርአትና ነብያዊ ትዕዛዝ ነው። ☞ ጸጉርንና ጥፍርን ከመቁረጥ የሚከለከለው ለራሱ ወይም ለሰው በራሱ ገንዘብ የሚያርድ ሰው ብቻ ነው። ህጉ የሚመለከተው የሚያርደዉን ሰው ብቻ ነው ሲባል፤ በወኪልነት ለሌላ ስው የሚያርድን ሰው አይጨምርም። ☞ እያወቀ ጥፍሩን ወይም ጸጉሩን የቆረጠ ወንጀል ፈጽሟልና ወደ አላህ በተውበት ሊመለስ ይገባዋል፤ ኡድሂያው ግን አይበላሽም ማካካሻ ከፋራም የለበትም። አንዳንዶች እንደሚያስቡት ሳይሆን ወንጀሉን ቢፈፅምም ኡድሂያ ማረዱን መተው የለበትም። ☞ በስህተት ወይም በመርሳት ፀጉሩን ወይም ጥፍሩን የቆረጠ ሰው ምንም ወንጀል የለበትም። በተመሳሳይ መልኩ በጣም አስፈላጊ ሲሆን ቢቆርጥ ችግር የለውም። ለምሳሌ የተጎዳን የሰውነት ቆዳ ለማከም ወይም የተሰበረ ጥፍሩን ለማስተካከል መቁረጥ ይፈቀድለታል። ፠ ስለ ኡድሂያ ጥቂት ተጨማሪ ነጥቦች 1 - በዙልሂጃ አስር ቀናት ከተወደዱ ተግባሮች መካከል ኡድሂያን በማረድ ወደ አላህ መቃረብ አንዱ ነው። 2- ኡድሂያ በጣም ከጠነከሩ የነብዩ صلى الله عليه وسلم ሱናዎች መካከል ነው። ኡድሂያ የነብዩ ኢብራሂምን ሱና ህያው ከማድረግ በተጨማሪ ለድሆች እና ችግረኞች መድረስ ነው። 3- ኡድሂያን በተመለከተ አላህ ከኛ የሚፈልገው ለእርሱ ያለንን ፍራቻ ተቅዋና ታዛዥነት ግልጽ ማድረጋችንን ብቻ ነው። አላህ እንዲህ ብሏል፤ {ﻟَﻦ ﻳَﻨَﺎﻝَ اﻟﻠَّﻪَ ﻟُﺤُﻮﻣُﻬَﺎ ﻭَﻻَ ﺩِﻣَﺎﺅُﻫَﺎ ﻭَﻟَٰﻜِﻦ ﻳَﻨَﺎﻟُﻪُ اﻟﺘَّﻘْﻮَﻯٰ ﻣِﻨﻜُﻢْ ۚ ﻛَﺬَٰﻟِﻚَ ﺳَﺨَّﺮَﻫَﺎ ﻟَﻜُﻢْ ﻟِﺘُﻜَﺒِّﺮُﻭا اﻟﻠَّﻪَ ﻋَﻠَﻰٰ ﻣَﺎ ﻫَﺪَاﻛُﻢْ ۗ ﻭَﺑَﺸِّﺮِ اﻟْﻤُﺤْﺴِﻨِﻴﻦَ} الحج 37 አላህን ሥጋዎቿም ደሞቿም ፈጽሞ አይደርሰውም፡፡ ግን ከእናንተ የሆነው ፍራቻ ይደርሰዋል፡፡ እንደዚሁ አላህን በመራችሁ ላይ ልታከብሩት ለእናንተ ገራት፡፡ በጎ ሠሪዎችንም አብስር፡፡» አል ሐጅ 37 4- ኡድሂያ የሚታረደው ከዒድ ሰላት በኋላ ነው። የአላህ መልዕክተኛ صلى الله عليه وسلم ከኢድ ሰላት በፊት ያረደ ሰው እንዲደግም አዘዋል። 5- ሚዛን በሚደፋው የኡለማዎች አቋም መሰረት የዒድ ሰላት ከተጠናቀቀበት ጊዜ ጀምሮ የሶስተኛው ቀን ጸሀይ እስክትጠልቅ ድረስ ኡድሂያን ማረድ ይቻላል። 6- ወንድም ይሁን ሴት ግመል፣ የቀንድ ከብቶች፣ በግና ፍየል ለኡድሂያ ይታረዱሉ። 7- የአላህ መልዕክተኛ صلى الله عليه وسلم እንከን ያለባቸውን እንስሳት እንዳናርድ ከልክለዋል። አንድ አይኑ የታወረ፣ ስብራት ያለበት፣ የከሳና የደከመ ወይም የታመመ እንስሳ ለኡድሂያ አይሆንም። 8- ኡድሂያን ለብቻ ማረድ እንደሚቻለው ሁሉ ለሰባት ሆኖ አንድን ወይፈን ወይም በሬ መጋራትም ይቻላል። 9- አንድ ሰው ኡድሂያ ሲያርድ ለራሱ እና በህይወት ላሉም ይሁን በህይወት ለሌሉ ቤተሰቦቹ አስቦ ሊያርድ ይችላል። 10- የኡድሂያውን ስጋ፣ ለቤት፣ ለስጦታ እና ለሰደቃ አድርጎ ሶስት ቦታ መከፋፈሉ ሱና ነው። ይህ ማለት ግን እንደ አስፈላጊነቱ ለሶስቱም ያውለዋል ማለት እንጂ ሶስት እኩል ቦታዎች ይከፋፍለዋል ማለት አይደለም። አቡጁነይድ Http://www.t.me/abujunaidposts

🗞 ከዱንያ ቀናት ሁሉ ብልጫ ያላቸው አስርቱ የዙልሂጃ ቀናት ✍ ዝግጅት፦ አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ ህዳር 2004 🔗 የፅሁፉ ሊንክ https://d1.islamhouse.com/data/am/ih_articles/single/am_Virtues_of_the_Ten_Days_of_Dhul_Hijjah.pdf 🔗 telegram Share Link https://t.me/abujunaidposts/374 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

አሰላሙዓለይኩም የመዲና ኢስላላዊ ዩኒቨርሲቲ ከተለያዩ የአለም ሀገራት ለመማርና ማህበረሰባቸውን ለማገልገል የሚፈልጉ ተማሪዎች ከ May 1 እስከ july 14 / 2025 ብቻ ከ በ "study in Sa
አሰላሙዓለይኩም የመዲና ኢስላላዊ ዩኒቨርሲቲ ከተለያዩ የአለም ሀገራት ለመማርና ማህበረሰባቸውን ለማገልገል የሚፈልጉ ተማሪዎች ከ May 1 እስከ july 14 / 2025 ብቻ ከ በ "study in Saudi" በሚባለው የማመልከቻ መቀበያ ድረገፅ በኩል እንዲያመለክቱ ይጋብዛል። ሊንክ https://studyinsaudi.moe.gov.sa وفقكم الله

🔎 እውነትን ፍለጋ! 🌴 የሰልማን አልፋሪሲይ የመስለም ታሪክ 🎙አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ 📆 እሁድ የካቲት 12/2015 🕌 በአቃቂ ዑመር መስጂድ የቀረበ ሙሀደራ 🔗 Telegram Link https://t.me/abujunaidposts/581 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

🔎 እውነትን ፍለጋ! 🌴የሰልማን አልፋሪሲይ የመስለም ታሪክ 🎙አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ 📆 እሁድ የካቲት 12/2015 🕌 በአቃቂ ዑመር መስጂድ የቀረበ ሙሀደራ 🔗 Telegram Link https://t.me/abujunaidposts/579 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

🔎 እውነትን ፍለጋ! 🌴የሰልማን አልፋሪሲይ የመስለም ታሪክ 🎙አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ 📆 እሁድ የካቲት 12/2015 🕌 በአቃቂ ዑመር መስጂድ የቀረበ ሙሀደራ 🔗 Telegram Link https://t.me/abujunaidposts/578 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

🔎 እውነትን ፍለጋ! 🌴የሰልማን አልፋሪሲይ የመስለም ታሪክ 🎙አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ 📆 እሁድ የካቲት 12/2015 🕌 በአቃቂ ዑመር መስጂድ የቀረበ ሙሀደራ 🔗 Telegram Link https://t.me/abujunaidposts/578 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

🏷 ኢስላማዊ ማንነት 🎙አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ ⏱ እሁድ 3:00 ሚያዝያ 3/2013 🕌 በአባጅፋር መስጂድ የቀረበ 🔗 Telegram Link https://t.me/abujunaidposts/391 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

🏷 ኢስላማዊ ማንነት 🎙አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ 🎙አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ ⏱ እሁድ 3:00 ሚያዝያ 3/2013 🕌 በአባጅፋር መስጂድ የቀረበ 🔗 Telegram Link https://t.me/abujunaidposts/391 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

የአዳዲስ ሰለምቴዎች መመሪያ New muslim guide.pdf https://newmuslimguide.com/am

🔖 የእምነት ፈተና እና የኢማሙ አሕመድ ፅናት 🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ ⌚️ 38:12 ደቂቃ 🍂 የአህሉሱና ኢማም አህመድ ኢብኑ ሀንበል በንጉሶች በታገዙ ጀህሚያዎች የደረሰባቸውን ከባድ ግፍና ፈተና ካለፉበት ፅናት የሚወሰዱ ትምህርቶች https://t.me/abujunaidposts/92 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

በረመዳን ወር ቴልቪዥን እና ቪዲዮ መመልከት ፆምን ያጓድላልን?  መልስ - አንድ ሠው የሚያዳምጠው ወይም የሚመለከተው ነገር ከተፈቀዱ ነገሮች (ሙባሀት) ከሆነ ምንም ችግር የለውም ፆምመአ ላይ እንከን አይሆንም፡፡ ሆኖም ግን ፆመኛ ሰው ጊዜውን ወደ አላህ ሊያቃርበው በሚችል ነገር ብቻ ነው ማሳለፍ ያለበት፡፡ ቁርዓንን ያነባል አላህን ያወድሳል ወዘተ...  አላህ ሀራም ያደረገውን ነገር ማዳመጥ ወይም መመልከት ግን ፆምን እንደሚያጓድል ምንም ጥርጥር የለውም፡፡ የዚህም ምክንያት ፆም የተደነገገበት አላማ የአላህን ፍራቻ (ተቅዋን) መላበስ ነው፡፡  قال تعالى{يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُواْ كُتِبَ عَلَيْكُمُ الصِّيَامُ كَمَا كُتِبَ عَلَى الَّذِينَ مِن قَبْلِكُمْ لَعَلَّكُمْ تَتَّقُونَ} البقرة : 183  «እናንተ ያመናችሁ ሆይ ጾም በነዚያ ከናንተ በፊት በነበሩት (ሕዝቦች) ላይ እንደተደነገገ ሁሉ በናንተም ላይ ተደነገገ። ልትጠነቀቁ ይከጀላልና፡፡»አልበቀራህ 183  አላህ በዚህ አንቀፅ ፆም በግዴታነት የተደነገገበት አላማ ተቅዋ መሆኑን ገልፆዋል፡፡  عن أبي هريرة رضي الله عنه قال قال رسول الله صلى الله عليه وسلم: (من لم يدع قول الزور والعمل به فليس لله حاجة في أن يدع طعامه وشرابه) صحيح البخارى  የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል ‹‹መጥፎ ንግግርን እና መሀይምነትን ያልተወ ሰው አላህ ዘንድ ምግብና መጠጥ መተው ቦታ የለውም (ቡኻሪ ዘግበውታል)  በዚህ መሠረት ማንኛውም ፆመኛ የሚሠራው ሀጢዓት ፆሙ ላይ ተፅዕኖ አለው፡፡  ከዚህም ውስጥ አንዳንድ ሠዎች እንደሚያደርጉት ከምግብ ከመጠጥና ከስጋዊ ተራክቦ ይቆጠቡና በአላህ ላይ ያምፃሉ፡፡ አንዳንዱ ሱሁር ከበላ በኋላ ይተኛና የፈጅርን ሠላት ያሣልፋል የሚነሣው ፀሃይ ከወጣች በኋላ ነው፡፡ ሌላው ደግሞ የዓስርን ሠላት ሣይሰግድ ይተኛና በኢፍጣር ሰዓት ተነስቶ አራት ጊዜ ጎንበስ ቀና ይላል፡፡ ጥቂትን እንዲ አላህን አያድስም፡፡ አንዳንድ ሠዎች ደግሞ ሠዎችን ያማሉ በንግድ ወቅት ያጭበረብራሉ ብዙ ወንጀሎችንም ይፈፅማሉ፡፡ ይህን ሁሌ የሚያደርጉት ፆመኛ ሆነው ነው፡፡ እነዚህ ሁሉ የሚፈፅሙን ሀራም ተግባር የፆማቸውን ምንዳ እንደሚቀንሠው ጥርጥር የለውም፡፡ ምናልባትም ምንዳውና ሀጢአቱ እኩል ይሆኑና የፆሙን ምንዳ ያጣሉ፡፡  ለሙስለሊም ወንድሞች እና እህቶች የማስተላልፈው ምክር፤ አላህ በእነርሱ ላይ እርም ካደረጋቸው ነገሮች እና ተግባሮች ፆማቸውን እንዲጠብቁ እና ይህን የተባረከ ወር አላህን በመታዘዝ እንዲያሳልፉት ነው፡፡ እርም ነገሮችን ከመተው እና ግዴታዎችን ከመፈፀም ረገድ ራሳቸውን የሚያንፁበት ታላቅ እድል ነው፡፡ ወቢላሂ ተውፊቅ!  ሸይኽ ሙሀመድ ቢን ሷሊህ አል-ኡሰይሚን @abujunaidposts

🔖 ዒባዳን ለመገንዘብ! 🎙አቡ ጁነይድ ሳላሕ አሕመድ 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/209 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

وَقَالُوا۟ ٱتَّخَذَ ٱلرَّحۡمَـٰنُ وَلَدࣰا * لَّقَدۡ جِئۡتُمۡ شَیۡـًٔا إِدࣰّا *  تَكَادُ ٱلسَّمَـٰوَ ٰ⁠تُ یَتَفَطَّرۡنَ مِنۡهُ وَتَنشَقُّ ٱلۡأَرۡضُ وَتَخِرُّ ٱلۡجِبَالُ هَدًّا *  أَن دَعَوۡا۟ لِلرَّحۡمَـٰنِ وَلَدࣰا *  وَمَا یَنۢبَغِی لِلرَّحۡمَـٰنِ أَن یَتَّخِذَ وَلَدًا *  إِن كُلُّ مَن فِی ٱلسَّمَـٰوَ ٰ⁠تِ وَٱلۡأَرۡضِ إِلَّاۤ ءَاتِی ٱلرَّحۡمَـٰنِ عَبۡدࣰا *  لَّقَدۡ أَحۡصَىٰهُمۡ وَعَدَّهُمۡ عَدࣰّا *  وَكُلُّهُمۡ ءَاتِیهِ یَوۡمَ ٱلۡقِیَـٰمَةِ فَرۡدًا «አልረሕማንም ልጅን ያዘ (ወለደ)» አሉ፡፡ ከባድ መጥፎን ነገር በእርግጥ አመጣችሁ፡፡ በእርሱ (በንግግራቸው ምክንያት) ሰማያት ሊቀደዱ፣ ምድርም ልትሰነጠቅ፣ ጋራዎችም ተንደው ሊወድቁ ይቃረባሉ፡፡ ለአልረሕማን ልጅ አለው ስለአሉ፡፡ ለአልረሕማን ልጅን መያዝ አይገባውም!! በሰማያትና በምድር ያለው ሁሉ (በትንሣኤ ቀን) ለአልራሕማን ባሪያ ኾነው የሚመጡ እንጂ ሌላ አይደሉም Surah Maryam 88 - 95 @abujunaidposts

{ قَالَ أَتَعۡبُدُونَ مَا تَنۡحِتُونَ * وَٱللَّهُ خَلَقَكُمۡ وَمَا تَعۡمَلُونَ } «አላህ እናንተንም የምትሠሩትንም የፈጠረ ሲኾን፤ የምትጠርቡትን ትገዛላ
{ قَالَ أَتَعۡبُدُونَ مَا تَنۡحِتُونَ * وَٱللَّهُ خَلَقَكُمۡ وَمَا تَعۡمَلُونَ } «አላህ እናንተንም የምትሠሩትንም የፈጠረ ሲኾን፤ የምትጠርቡትን ትገዛላችሁን?» አላቸው። Surah Aṣ-Ṣāffāt: 95-96

🤝 የሙስሊሞች አንድነት 🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ ⌚️ የ 44 ደቂቃ መልዕክት 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/132 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

📌 ንፁሕ ልብ ♡ 🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/137 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

በካፊሮች በዓል እንኳን አደረሳችሁ ማለት ይፈቀዳልን? በበአላት ሰሞን በተደጋጋሚ እገሌና እገሌ ላይክ አድርገውታል ከሚለን ፖስቶች መካከል ከፊሎቹ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክቶች ናቸው። ለጌታ መወለድ፣ ለጌታ መሰቀል፣ ለጌታ ሞቶ መነሳት (ትንሳኤና) መሰል ክስተቶች እንኳን አደረሳችሁ ሲባል ሼር ወይም ላይክ የሚያደርጉ ብዙ እህትና ወንድሞችን አስተውያለው። አንዳንዴ በስህተት ሌላ ግዜም ነገሩን እንደቀላል በመውሰድ የሚፈፀም ሊሆን ይችላል። ሆኖም እጅግ ከባድና በአኼራ ዋጋ የሚያስከፍል መዘናጋት ነው!! በካፊሮች በአል፤ እንኳን አደረሳችሁ... እንኳን ደስ አላችሁ... እንኳን አብሮ አደረሰን ማለት እነሱን ለማስደሰትም ይሁን ለመመሳሰል ከአላህ ዲን መንሸራተት እና የካፊሮችን ኩፍር የመናገር ስነልቦና መካብ ስለሆነ ክልክል ነው። መከባበር እና አብሮነትን ለማሳየት ከእምነታችን መንሸራተት አይጠበቅብንም። ዲን ከምንም በላይ ነውና ሸሪዓን መተላለፍ ፍፁም ጥፋት ነው!! ፈጣሪ ወለደ ተወለደ የሚለው አስተምህሮ የጥፋትነቱ ክብደት ሰማያትንና ምድርን ሊሰነጥቅ እንደሚቀርብ ቁርአን ይነግረናል። አላህን የሚያስቆጣ ተግባር በመፈፀማቸው እንኳን ደስ ያላችሁ ማለት ከሙስሊም አይጠበቅም!! (وَقَالُوا۟ ٱتَّخَذَ ٱلرَّحۡمَـٰنُ وَلَدࣰا * لَّقَدۡ جِئۡتُمۡ شَیۡـًٔا إِدࣰّا *  تَكَادُ ٱلسَّمَـٰوَ ٰ⁠تُ یَتَفَطَّرۡنَ مِنۡهُ وَتَنشَقُّ ٱلۡأَرۡضُ وَتَخِرُّ ٱلۡجِبَالُ هَدًّا *  أَن دَعَوۡا۟ لِلرَّحۡمَـٰنِ وَلَدࣰا *  وَمَا یَنۢبَغِی لِلرَّحۡمَـٰنِ أَن یَتَّخِذَ وَلَدًا *  إِن كُلُّ مَن فِی ٱلسَّمَـٰوَ ٰ⁠تِ وَٱلۡأَرۡضِ إِلَّاۤ ءَاتِی ٱلرَّحۡمَـٰنِ عَبۡدࣰا *  لَّقَدۡ أَحۡصَىٰهُمۡ وَعَدَّهُمۡ عَدࣰّا *  وَكُلُّهُمۡ ءَاتِیهِ یَوۡمَ ٱلۡقِیَـٰمَةِ فَرۡدًا) [«አልረሕማንም ልጅን ያዘ (ወለደ)» አሉ፡፡ ከባድ መጥፎን ነገር በእርግጥ አመጣችሁ፡፡ በእርሱ (በንግግራቸው ምክንያት) ሰማያት ሊቀደዱ፣ ምድርም ልትሰነጠቅ፣ ጋራዎችም ተንደው ሊወድቁ ይቃረባሉ፡፡ ለአልረሕማን ልጅ አለው ስለአሉ፡፡ ለአልረሕማን ልጅን መያዝ አይገባውም!! በሰማያትና በምድር ያለው ሁሉ (በትንሣኤ ቀን) ለአልራሕማን ባሪያ ኾነው የሚመጡ እንጂ ሌላ አይደሉም] Surah Maryam 88 - 95 ለመሆኑ አንድን ካፊር ለሀይማኖታዊ በአል እንኳን አደረሰህ ስትለው፤ ምን ማለት እንደሆነ ግልፅ አይደለምን? እንኳን አደረሰህ... ጌታ ተወልዶ ተሰቅሎ ሞቷል ብለህ ለማወጅ፣ ለመስቀል ለመስገድና  የፈጣሪን ክብር የሚነኩ ንግግሮችን ለመናገር እንኳን በቃህ! እንኳን አደረሰህ... ማርያም ፈጣሪዋን ወለደችው፤ በመጠቅለያም ጠቀለለችው እያልክ ለመዘመር እንኳን በቃህ! የኩፍር ተግባርን ለመከወን ከሆነ የደረሰው ለምንስ እንኳን አብሮ አደረሰን እንላለን? እውቁ አሊም ኢብኑል ቀይም ረሂመሁላህ ይህ ተግባር የተከለከለ ስለመሆኑ የኡለማዎች የጋራ አቋም መሆኑን በመጠቆም እንዲህ ብለዋል፤ «ኩፍርን ብቻ በሚያንፀባርቁ የሀይማኖታቸው መገለጫዎች እንኳን አደረሳችሁ...እንኳን ደስ ያለችሁ ማለት ሀራም መሆኑ የሁሉም ሊቃውንት ስምምነት ያለበት ነው። ለምሳሌ አንድ ሙስሊም በነሱ በዓላትና ፆም ጊዜ፤ «በአሉን የተባረከ ያድርግልህ» ወይም «መልካም የደስታ በአል ያድርግልህ» እና መሰል የደስታ መግለጫዎችን ቢያስተላልፍ፤ ተናጋሪው ከኩፍር ቢድን እንኳ ከባድ ወንጀል ነው የፈፀመው። ይህም፤ ልክ «እንኳን ለመስቀል ሰገድክ» ብሎ ደስታን እንደመግለፅ ነው! ይህ እንደውም፤ አንድ ሰው ነብስ በማጥፋቱ፣ አልኮል በመጠጣቱ፣ ዝሙት በመፈፀሙና በመሰል ተግባራት እንኳን ደስ ያለህ ከማለት በወንጀልነት የከበደ እና አስቀያሚ ነው። ለኢስላማዊ ድንጋጌዎች ተገቢዉን ክብር የማይሰጡ ብዙ ሰዎች ይህንን ይፈፅማሉ።  ምን ያክል የሚያስጠላ የግባር እንደፈፀሙም አያስተውሉም። ቢድአ፣ ኩፍር እና ወንጀሎች በመፈፀማቸው እንኳን አደረሰህ፣ እንኳን ደስ ያለህ እና መሰል የደስታ መግለጫዎችን ያስተላለፈ፤ እራሱን ለአላህ ቁጣና ጥላቻ የተገባ እንዲሆን የሚያደርግ ምክኒያት ፈፅሟል»  አህካም አህሉዚማህ የዘመናችን ፈቂህ ሸይኽ ኡሰይሚን ረሂመሁላህ እንዲህ አሉ «ካፊሮችን እንኳን አደረሳችሁ ማለት ኢብኑል ቀይም እንዳለው የዚህን ያክል ከባድ የሆነበት ምክኒያት እነርሱ የሚፈፅሟቸውን የኩፍር መገለጫዎች ማፅደቅ ስለሆነ ነው። ምንም እንኳን ለራሱ ይህንን ኩፍር መፈፀምን ባይወድም እነሱ መፈፀማቸውን ወዷልና። ሙስሊም ደግሞ የኩፍር መገለጫዎችን መውደድም ይሁን ሌሎችን እንኳን ደስ ያላችሁ ማለት አይፈቀድለትም።» መጅሙዑ ፈታዋ ወረሳኢል አሸይኽ ኢብኑ ኡሰይሚን 3/44  በተመሳሳይ መልኩ፤ ክሪስማስም ሆነ ሌሎች በአላት ላይ ስጦታ ወይም ፓስት ካርዶችን መለዋወጥ፤ እንዲሁም ማንኛውም ደስታን መግለጫ የሆኑ ነገሮችን መፈፀም በአሉን መካፈል ስለሆነ የተከለከለ ነው!! በዚህ ፅሁፍ መጠቆም የፈለኩት ምንም አይነት ማህበራዊ ግንኙነት ሀራም ነው የሚል መልእክት አይደለም። በተለይም ከክርስቲያን እና አይሁዶች ጋር ባለን ማህበራዊ ግንኙነቶች ላይ የተፈቀዱ ብዙ በመልካም የመኗኗር እሴቶች አሉን።  ሆኖም ሀይማኖታዊ ወሰኖች የሉም ማለት አይደለም። የተፈቀደውን ስንተገብር እንደ ያልተፈቀደ ጋብቻ፣ በአላት ላይ መሳተፍ፣ ለሞቱት የአላህን ማርታ መለመንና ባጠቃላይ በዲን መመሳሰልን ግን በፍፁም አንፈፅምም። ይህንን የእምነትና የሀይማኖት ወሰን መናድ አይቻልም። ማንነታችንን ማክበር፣ ግንኙነታችንን በዲናዊ ገደቦች ማጠር ብሎም አለመሟሟት ለሌሎች ሞራል ዲንና ማንነት ከመጨነቅ ይቀድማል። ዲን ከምንም በላይ ነውና ከመሸማቀቅ እንውጣ። ይህ  የዲናችን መገለጫ እንጂ እንደ ማክረርና ፅንፈኝነት የሚታይ አይደለም። በነገራችን ላይ የአንድ እምነት ተከታይ ከሌሎች ለመቀራረብ ብሎ ከራሱ እምነት ጋር የሚጣላበት ሁኔታ ድሮ ቀርቷል። ሌሎቹም ቢሆኑ ይህ በኛ ሀይማኖት አልፈቀድም እና ይቅርታ ይሉሀል። (فَلَا تُطِعِ ٱلۡمُكَذِّبِینَ * وَدُّوا۟ لَوۡ تُدۡهِنُ فَیُدۡهِنُونَ * وَلَا تُطِعۡ كُلَّ حَلَّافࣲ مَّهِینٍ) አስተባባዮችንም አትታዝዙ፡፡ ብትመሳሰላቸውና ቢመሳሰሉህ ተመኙ፡፡ [Surah Al-Qalam 8 - 10] ወላሁ አዕለም አላህ ከጥፋት ሁሉ ይጠብቀን! https://t.me/abujunaidposts/141 ____ አቡጁነይድ ረጀብ 24/1437 ዓ.ሒ / ሜይ 1/ 2016

አልሀበሺ እውነታውን ሲያምን!! #መውሊድ መውሊድን የማክበር ሀሳብ ከክርስቲያኖች የገና በአል ተኮርጆ የመጣ መሆኑን ላለመቀበል ሀሰን ታጁ እና መሰሎቹ ቢሞግቱም አብደላህ አልሀበሺ በተቃራኒው እውነታው
አልሀበሺ እውነታውን ሲያምን!! #መውሊድ መውሊድን የማክበር ሀሳብ ከክርስቲያኖች የገና በአል ተኮርጆ የመጣ መሆኑን ላለመቀበል ሀሰን ታጁ እና መሰሎቹ ቢሞግቱም አብደላህ አልሀበሺ በተቃራኒው እውነታውን አምኗል፤ ☞ የ ‘ኢዝሀሩል አቂደቲሱኒያህ’ የድምፅ ማብራሪያ ካሴት ቁ.9 የመጀመሪያው ክፍል ላይ የመውሊድን አጀማመር አስመልክቶ፤ መውሊድን ለመጀመሪያ ጊዜ ያከበረው የኢርቢሉ ንጉስ ሙዘፈር እንደሆነ እና አጀማመሩም ክርስቲያኖች የመሲህን ልደት ሲያከብሩ አይቶ ሙሀመድ ﷺ በዚህ አለም ብቅ በማለታቸው አላህን ሊያመሰግን እንደሆነ ያብራራል። ★እኛም እውነታዉን በማመኑ እያመሰገነው ተከታዮቹን ነጥቦች እንጠቁማለን፤ 1) መውሊድን በዓል አድርጎ ማክበር መልእክተኛው ﷺ ወደዚህ አለም በመምጣታቸው ለአላህ ምስጋና የማቅረቢያና ውዴታንም የመግለጫ መንገድ ከሆነ ከሰሀቦችና ታቢዒዮች ዘመን ጀምሮ የኖሩ ምርጥ የኢስላም ልጆች ሳያውቁት በ630 ዓ.ሒ የሞተው ንጉስ ተገለጠለትን? 2) በላጭ ትውልዶች የተባሉት ቀደምቶቹ ሰለፎች ይህንን መውሊድ ያላከበሩት፤ ክርስቲያኖችና አህባሾች የደረሱበትን መውሊድ አላህን የማመስገኛ መንገድ የመሆኑን እውነታ ማወቅ ተስኗቸው ነውን? ይህንን ካላችሁ ጥመታችሁ ግልፅ ወጣ አለያ ወደነሱ መንገድ ተመለሱ!! 3) ይህ የተምታታ ግንዛቤ መነሻ ያደረገውን ሀሳብ ስንመለለት፤ ክርስቲያኖች የኢሳን ልደት በማክበራቸው አላህን በማመስገን ከምርጦቹ የሰለፎች ትውልዶች መቅደማቸውን ያመላክታል። ይህ ደግሞ ባጢል ነው!! 4) አልሐበሺ እና ተከታዮቹ ክርስቲያኖችን በመከተል ልደት ሲያከብሩ መልእክተኛው ﷺ በብዙ ሀዲሶች፤ በኢስላማዊ እንድንኮራ ማዘዛቸውና አይሁዶችና ክርስቲያኖችን አርአያ እንዳናደርግ አበክረው መምከራቸውን ለምን ዘነጉ? ሙስሊም ከካፈር ጋር መመሳሰል እንደሌለበት አያውቁምን?? መልዕክተኛው ﷺ እንዲህ ብለዋል፤ عَنْ أَبِي سَعِيدٍ الْخُدْرِيّ، قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللّهِ صلى الله عليه وسلم "لَتَتّبِعُنّ سَنَنَ الّذِينَ مِنْ قَبْلِكُمْ. شِبْراً بِشِبْرٍ، وَذِرَاعاً بِذِرَاعٍ. حَتّىَ لَوْ دَخَلُوا فِي جُحْرِ ضَبَ لاَتّبَعْتُمُوهُمْ" قُلْنَا: يَا رَسُولَ اللّهِ آلْيَهُودُ وَالنّصَارَىَ؟ قَالَ "فَمَنْ؟". [رواه البخارى ومسلم ]. አቢ ሰዒድ አልኹድሪይ ረዲየላሁ ዐንሁ እንዲህ አሉ፤ የአላህ መልዕክተኛ ﷺ እንዲህ አሉ፤ «ከናንተ በስተፊት የነበሩትን (ህዝቦች) ፈለግ ስንዝር በስንዝር እርምጃ በእርምጃ ትከተላላችሁ። የተሳቢ እንስሳ ጉድጓድ እንኳ ቢገቡ ትከተሏቸዋላችሁ!» የአላህ መልዕክተኛ ﷺ ሆይ ይሁዶችንና ነሳራዎችን ነው ? «ሌላ ማንን ነው!» (እነሱን ነው እንጂ) አሉ። ይህንን ነብያዊ ትንቢት ባንሰማ ኖሮ በሙዘፈር ድርጊት ተገርመን አናበቃም ነበር። 5) አላህ ዲናችንን የተሟላ አድርጎት ሳለ፤ ክርስቲያኖች ሰሩት ብለን በዲናችን የሌለን ነገር እንፈፅማለን?? (ٱلْيَوْمَ أَكْمَلْتُ لَكُمْ دِينَكُمْ وَأَتْمَمْتُ عَلَيْكُمْ نِعْمَتِى وَرَضِيتُ لَكُمُ ٱلْإِسْلَـٰمَ دِينًۭا ۚ فَمَنِ ٱضْطُرَّ فِى مَخْمَصَةٍ غَيْرَ مُتَجَانِفٍۢ لِّإِثْمٍۢ ۙ فَإِنَّ ٱللَّهَ غَفُورٌۭ رَّحِيمٌۭ) المائدة 3 «ዛሬ ሃይማኖታችሁን ለእናተ ሞላሁላችሁ። ጸጋዬንም በናንተ ላይ ፈጸምኩ። ለእናንተም ኢስላምን ከሃይማኖት በኩል ወደድኩ» አልማኢዳህ 3 በእውነትም የዛኔ ዲን ያልነበረ አሁን ዲን ሊሆን አይችልም!! አኹኩም አቡጁነይድ ረቢኡልአወል 9 /1436 ዓ.ሒ https://t.me/abujunaidposts