uk
Feedback
Bisrat pre-primary; primary and middle school in Ethiopia.

Bisrat pre-primary; primary and middle school in Ethiopia.

Відкрити в Telegram
1 290
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
Немає даних30 днів
Архів дописів
                   23/05/2016 ዓ.ም "የፈጣሪ ፈቃድ ይሁን ብለን ዝም አልን"! እጅግ ለማከብራችሁና በጣም ለምወዳችሁ ውድ የብስራት ቅድመ አንደኛ፣አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህራን፣አስተዳደር ሠራተኞች፣ወ.ተ.መ.ህ፣ተማሪዎች፣ወላጆች፣አሳዳጊዎች፣ሱፐርቫይዘሮቻችን፣የወረዳ 12 ትምህርት ጽ/ቤት ሀላፊ አት ጀባ ሹብሴና  ባለሙያዎች ፣የተማሪ መጋቢ እናቶች፣ የአጎራባች ትምህርት ቤቶች ርዕሳነ መምህራን፣የአዲስ ከተማ ትምህርት ፅህፈት ቤት ሀላፊዎች እንደየ ማዕረጋችሁ እና የአካባቢው ወጣቶች እና እኔን የምታውቁ ማሃበረሰቦች በሙሉ! ዛሬ ፈጣሪ ያለው ቀን ደረሰና እነሆ በስራ መለያየታችን እውን ሆኗል! ወደዚህ ተቋም በመምህርነት ከመጣሁበት ከ2003  ዓ.ም ከ2009 ዓ.ም እስከዚህ እለት ድረስ  በምክትልና በዋና ርዕሰ መምህርነት ሙያ ላይ  ከናንተ ጋር የነበረኝ ቆይታ እጅግ መልካምና በፍቅርና በስኬት የታጀበ ነበር ብዬ አምናለሁ፡፡ቢሆንም ግን ስጋ ለባሽ ደካማ ፍጡር ነኝና ከሥራዎችና አሰራሮች ጋር ተያይዞ ላስቀየምኳችሁ ሁሉ በፈጣሪ ስም ከልቤ ይቅርታ መጠየቅ እፈልጋለሁ፡፡   ሌላው ባለፉት አመታት ከባልደረቦቼ ጋር በመቀናጀት ለተከታታይ አመታት በተማሪ ውጤትና ስነ ምግባር በክፍለ ከተማና በአዲስ አበባ ውጤታማና ተሸላሚ ሞዴል ተቋማት ውስጥ ቀዳሚውን ደረጃ የያዘ ተቋም  ማድረግ ችለናል።ለዚህ ማሳያውም ያለፉት 3 አመታት ስራዎቻችን በኢንስፔክሽን ተመዝና በክፍለ ከተማና በአዲስ አበባ ካሉ መሰል ትምህርት ቤቶች መካከል አሸናፊ በመሆን የ2 ዋንጫ ተሸላሚ መሆን ችለናል። ታዲያ ይህ ውጤት እንዲመጣ መጠኑ ይለያይ እንጂ ሁሉም የትምህርት ማህበረሰብ አይተኬ ሚና ተጫውታችኋል። ሌላው ቅን፣ታታሪና ብትሰሩ ብትሰሩ የማይታክታችሁ የማነጅመንት አካላት ምክትል ርዕሰ መምህራን ወንድሜ እንድርያስ ወልደመድህን፣ወንድም እስጢፋኖስ ደሜ እና እህት ውቢት ልደቱ እንዲሁም እናቶቼ ወ/ሮ መሰረት ይነሱና ወ/ሮ ሰላማዊት ሽፈራው ለነበራችሁ የስራ ትጋት ሁሉ አመሰግናችኋለሁ፤ ሁሌም በልቤ ትኖራላችሁ። በመጨረሻም፦ እኛን ተክታችሁ ወደ ብስራት የተቀላቀላችሁ ርዕሰ መምህራን እንኳን ደህና መጣችሁ እያልኩ መልካም የስኬት የስራ ዘመን እንዲሆንላችሁ እየተመኘሁ መምህራኖቻችን፣አስተዳደር ሰራተኞች አደራ የምላችሁ ነገር ቢኖር ሁላችሁም የተሠጣችሁን የሥራ ኃላፊነት በከፍተኛ ተነሳሽነትና ሙያዊ ሥነ ምግባር እንድትከውኑ፣ከአዳዲሶቹ  ርዕሳነ መምህራን ጎን እንድትሰለፉና ዜጋን የሚጠቅም ውጤታማ ስራ እንድትሰሩ ስል መልእክቴን ማስተላለፍ እወዳለሁ። በስተመጨረሻም ትምህርታዊና አስተዳደራዊ ሥራዎች በአኩሪ ተግባራት ታጅበው በስኬት የሚጠናቀቅበት ዘመን እንዲሆንላችሁ አብዝቼ እመኝላችኋለው!ፈጣሪ ከናንተ ጋር ይሁን! ስለያችሁ በጥልቅ ሀዘንና በዕንባ ነው! ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝባችንን አብዝቶ ይባርክ! ወንድማችሁ ደስታ ሻረው ንጉሴ!👋

ለትምህርት ቤታችን መመምህራን በመሉ BSC ምዘና ነገ በ23/05/2016 ዓ.ም ጠዋት 2:30 ሰዓት ላይ ትምህርት ቤት ተገኝታችሁ እንድትመዘኑ እያሳሰብን በጊዜው ተገኝታችሁ ካልተመዘናችሁ በኋላ ለሚፈጠርባችሁ መስተጓጐል ሀላፊነቱን ትወስዳላችሁ።

በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ መምህራን ማህበር ስር ለሚገኙ መሰረታዊ መምህራን ማህበር አመራሮች በሙሉ ሰሞኑን ከቤት መደራጀት ጋር ተያይዞ የሚታዩ ክፍተቶችን ግንዛቤ መስጠትን ይመለከታል፡፡ መምህራንን በእነዚህ ሶስት ነጥቦች ላይ ግንዛቤ እንድትፈጥሩልን እና ስራዎችን እንድታቀላጥፉልን እንጠይቃለን፡፡ 1. ከ2009 ዓ.ም ላይ የተመለሱ ቤቶች ሁሉም መምህራን ርዕሰ መምህራን በእጣው ተሳታፊ ይሆናሉ፡፡ (ምክንያቱም 30% መክፈል የምንችል እጣ ውስጥ አንገባም የሚል ብዥታ ስለተፈጠረ ነው፡፡ ባለፈው የተመዘገቡት 28450 መምህራን ተሳታፊ ይሆናሉ) 2. አሁን ለስራ ቅደም ተከተል ሲባል በቅድሚ 30% ብር በእጃችሁ ያላችሁ መምህራ፣ርዕሰ መምህራንእና ሱፐርቫይዘሮችን ቅድሚያ ተደራጅተው አሰራሩን ተከትለው (ከሊዝ ነጻ የሆ መሬት፣ዲዛይን እና የግንባታ ፍቃድ )ተሰጥቷቸው የቤት ባለቤት የሚሆኑበት መንገድ ሲሆን 3. ሶስተኛው ደግሞ መምህራን አሁን 30% ቅድመ ክፍያው በእጃቸው ያላዙት በቀጣይ ተደራጅተው እንዲቆጥቡና እየቆጠቡ ያለው የገንዘብ መጠን የግንባታውን ብሩ 30% ሲደርስላቸው እንደሌሎቹ መሬትና ዲዛይን እንዲሁም የግንባታ ፍቃድ የሚሰጣቸውና የቤት ባለቤት የሚሆኑበት መንገድ ይመቻቻል፡፡ ማሳሰቢያ፡- በስማቸው ወይም በትዳር አጋራቸው ስም የተመዘገበ ቤት ካለ እንዲሁም በተለያየ መንገድ ቤት የደረሳቸውና የሸጡ በዚህ መርሃ ግብር መሳተፍ አይችሉም ተሳትፈው ቢገኙ ኃላፊነቱን የሚወስዱት ራሳቸው ናቸው፡፡

30 ፐረርሰነንተት ቀቁጠ (7).docx0.21 KB

ሰላም በያላችሁበት ይሁን ውድ መምህራን የመኖርያ ቤት በ30% ቅድመ ክፍያ ቁጠባ ማሟላት የምትችሉ መምህራን ቀጥሎ በተዘረዘሩት አማራጮች እስከ ነገ ማለትም 20/05/2016 ዓም እስከ 3:00 ሠዓት ድረስ ብቻ የትምህርት ቤታችን መምህራን ማህበር ሰብሳቢ የሆኑት መምህር አስማማው ጋር በመቅረብ እንድትመዘገቡ እናሳውቃለን ይህ መረጃ ለላልደረሳቸውም መልእክቱን አስተላልፉ

WPS Office: Complete office suite with PDF editor Here's the link to the file: https://eu.docworkspace.com/d/sIETBqaXlAeSa0q0G Shared from WPS Office: https://kso.page.link/wps

ለስም ጠሪ መምህራን በሙሉ ሮስተር በኮምፒውተር እንደሚሰራ ይታወቃል፡፡ ስለሆነ ከሰኞ ማለትም 06/05/2016 ዓ.ም ጀምሮ ሁሉም ስም ጠሪ መምህር የራሱን ክፍል soft copy ICT በመሄድ ሮስተር ላይ የተማሪዎችን ስም ዝርዝር እንድታስገቡ ለማሳሰብ እንወዳለን፡፡ በእጅ የሚሰራ ሮስተር ተቀባይነት የሌለው መሆኑን አውቃቹ ለስራ ጥራት ሲባል ት/ቤቱ ባዘጋጀው የሮስተር ፎርማት ብቻ እንድትሰሩ እናሳስባለን፡፡ ከሠላምታ ጋር ት/ቤቱ

2016 first result analysis form.xlsx1.07 KB

Grade 8 General Science Worksheet From Unit 1 - 4 Contents: 26 Pages Production . abiyot primary school yeka

ለተማሪዎች ጠቃሚ የጥናት ምክሮች 1. የክፍለ ጊዜ ማስታወሻ መጠቀም ሁሉንም የክፍል ክፍለ ጊዜዎች መገኘት፣ ንግግሮቹ በትኩረት መከታተል፣ እና ትርጉም በሚሰጥ መንገድ ማስታወሻ መያዝ ጠቃሚ 2. ከክፍል ጓደኞች ጋር ማጥናት ጓደኞችን ከማፍራት በተጨማሪ፣ በእያንዳንዱ ክፍል ውስጥ የጥናት ቡድኖችን መፍጠር  አብሮ መስራት ጥሩ የጥናት ልምዶችን ለማዳበር ይረዳል, በቡድን ፕሮጀክቶች ላይ ትብብርን ይጨምራል እና በራስ መተማመንን ይጨምራል. "አብረህ መስራት፣አብረህ ማጥናት፣መረዳዳት እና የተሻለ ለመሆን መገፋፋት ትችላለህ" 3. መምህራችን ነፃ የሚሆንበትን ሰዓቶች መጠቀም በአንድ ጽንሰ-ሀሳብ ወይም ርዕስ ላይ ችግር ካጋጠመዎት መምህርዎ ሊረዱዎት ይችላሉ። የክፍል ትምህርቱን በተሻለ ለመረዳት፣ ለፈተናዎችዎ እንዴት መዘጋጀት እንደሚችሉ  አጋዥ ምክሮችን ለማግኘት መምህዎ ነፃ ሲሆን መወያየት ። 4.ለጥናት ጥሩ ቦታ መምረጥ አንዳንድ ሰዎች የቤተ መፃህፍት መቼት ሙሉ ዝምታ ይወዳሉ፣ ሌሎች ደግሞ ስራ የበዛበትና ማነቃቂያ ይወዳሉ። አንዳንድ ተማሪዎች በጠረጴዛቸው ላይ መሥራትን ይመርጣሉ፣ ሌሎች ደግሞ ፀሐያማ የሆነ የውጪ ቦታ የበለጠ ምቹ ሆነው ሊያገኙ ይችላሉ። 5. ያንብቡ እና ይከልሱ የተማርነውን 70% በ24 ሰዓታት ውስጥ እንረሳለን። ከክፍል አንድ ቀን በኋላ አዳዲስ ሀሳቦችን ማየቱ ማቆየት እና ግንዛቤን ለመጨመር ይረዳል - ስለዚህ በእያንዳንዱ ምሽት ፈጣን ግምገማ ጊዜ ይውሰዱ። ከመቀጠልዎ በፊት ምዕራፎችን ወደ ክፍሎች ይከፋፍሏቸው እና በእያንዳንዱ መጨረሻ ላይ ያለውን ጽሑፍ ይከልሱ። ሙሉ ምዕራፎችን እንደገና ማንበብ ሳያስፈልግ በቀላሉ መገምገም እንዲቻል የንባቡን ወሳኝ ገጽታዎች በማጠቃለል ማስታወሻ መያዝ። 6. እቅድ ይጠቀሙ የክፍል እና የቤት ስራዎችን፣ ፕሮጀክቶችን እና ሌሎችንም ፕሮግራም ማስያዝ፣ ተደራጅቶ ለመቆየት ወሳኝ ነው። ማንኛውንም አስፈላጊ ነገር እንዳይረሱ የጊዜ ገደቦችን፣ ቀኖችን እና ሰአቶችን ለመከታተል እቅድ ይጠቀሙ። 7. ቁሳቁሱን በዓይነ ሕሊናህ ተመልከት ትምህርቱን በማጣመር እና ቁልፍ ቃላትን እና ፅንሰ-ሀሳቦችን በማስመር ወይም በማድመቅ በክፍል ማስታወሻዎችዎ በጣም አስፈላጊ ክፍሎች ላይ ያተኩሩ። የተወሳሰቡ ፅንሰ-ሀሳቦችን እንዲረዱ የሚያግዙ ምስሎችን ለመፍጠር ወደ ስዕላዊ መግለጫዎች፣ የአእምሮ ካርታዎች ወይም ዝርዝር መግለጫዎች እንደገና ለመቅረጽ ይሞክሩ። 8. ጎበዝ ተማሪዎች እንዲያስረዱህ አድርግ በተለይም በአንድ ርዕስ ላይ ልዩ ችሎታ ያላቸው ወይም የላቀ ችሎታ ያላቸውን ተማሪዎች እንዲያስረዱህ ጠይቅ። እንድሁም በተለያዩ ድህረ ገፆች የሚያስተምሩ መምህራን ለመረዳት ጣር። 9. በመረዳት ላይ ያተኩሩ ማስታወስ ማለት እውነታዎችን ለማስታወስ እና ለመድገም መንገዶችን መፈለግ ማለት ነው። መረዳት ትንሽ ጠለቅ ያለ ነው እና አዲስ እውቀትን በተለያዩ ሁኔታዎች ላይ ምን ያህል በጥሩ ሁኔታ መተግበር እንደሚችሉ እና ከሌሎች ፅንሰ-ሀሳቦች ጋር እንዴት እንደሚዛመድ ማወቅን ያመለክታል። የማጠቃለያ ፈተናዎች ብዙውን ጊዜ ማስተዋልን ይፈትኑታል እንጂ ማስታወስን ብቻ አይፈትኑም። 10. በክለሳ ክፍለ ጊዜ መገኘት በፈተናው ቅርጸት እና በጥያቄዎች ውስጥ ምን ሊካተቱ እንደሚችሉ እንዲሁም በጥናትዎ ወቅት ትኩረት ሊሰጡባቸው የሚገቡ ቁልፍ ርዕሶች ላይ ጠቃሚ መረጃ የሚማሩበት በዚህ ነው። 11. እረፍት ይውሰዱ አንጎልዎ እና ሰውነትዎ እንዲያድሱ እድል ይስጡት። እንደ ፎርብስ ዘገባ፣ የ25 ደቂቃ የረጅም ጊዜ የጥናት ክፍለ ጊዜዎችን ከአምስት እስከ 10 ደቂቃ ዕረፍት ይውሰዱ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ወደ አንጎል የደም ፍሰትን ይጨምራል ይህም የበለጠ ጉልበት እና የተሻለ ግንዛቤ ይሰጥዎታል. 12. እራስዎን በደንብ ይንከባከቡ ጊዜን ለመቆጠብ አላስፈላጊ ምግቦችን መሙላት በጣም ብልጥ ስልት አይደለም. በምትኩ፣ እንደ ትኩስ ፍራፍሬ እና አትክልት ያሉ ​​“የአንጎል ምግቦችን”፣ ከፕሮቲን እና ጤናማ ስብ ጋር ሚዛናዊ በሆነ መልኩ አእምሮዎን ለማቀጣጠል ያቆዩ። ለእንቅልፍም ተመሳሳይ ነው: ከፈተናው በፊት ባለው ምሽት ሳይበዛ እረፍት ለማግኘት እቅድ ያውጡ. 13. እራስዎን ያረጋጉ በመጨረሻው ሳምንት በሁሉም የፈተና መሰናዶዎ ውስጥ መጨናነቅ ወደ  ጭንቀት ሊመራ ይችላል። ትምህርቱን ወደ ርእሶች ይከፋፍሉት እና መረጃን ሙሉ በሙሉ ወደ እውነተኛ ግንዛቤ ለመውሰድ ከፈተናው በፊት ለመመልከት ጥቂት ቁልፍ ሀሳቦችን በማስታወሻ ለይ ይፃፉ ። 14. የፈተነውን ቅርፀት ማወቅ የተለያዩ ሙከራዋች፣ ሞደል ፈተናዎች የተለያዩ አካሄዶችን ይፈልጋሉ። ብዙ ምርጫ ማለት በትርጉሞች እና ጽንሰ-ሐሳቦች ላይ ማተኮር ማለት ነው. የፅሁፍ ሙከራዎች ስለ ቁሳቁሱ ፅንሰ-ሃሳባዊ ግንዛቤ እንዲያሳዩ ይፈልጋሉ። ስለዚህ ፈተናው እንዴት እንደሚዘጋጁ እንዲያውቁ የፈተናውን ቅርጸት መምህሩን ይጠይቁ። 15. ሌሎችን በማስተማር ተማር ለክፍል ጓደኛዎ ፅንሰ-ሀሳቦችን ማስረዳት ትምህርቱን እራስዎ በትክክል መረዳትዎን ለማረጋገጥ እና እንዲማሩ ለመርዳት ጥሩ መንገድ ነው። ፅንሰ-ሀሳብን ለማብራራት አዳዲስ መንገዶችን ሲያገኙ፣ መረጃውን ለሌሎች በማቀናበር እየተካኑ ነው። 16. ቃላት መፍጠር የኮርስዎን ይዘት ወደ አጭር ክፍሎች መከፋፈል እና ምህፃረ ቃላትን ፣ ሀረጎችን ፣ ግጥሞችን ወይም ዘይቤዎችን መፍጠር ጠቃሚ እና አስደሳች - ጽንሰ-ሀሳቦችን ለማስታወስ የምንጠቀምበት ሌላኛው ዘዴ ነው። 17. እውቀትዎን ይፈትሹ ቅርጸቱን አንዴ ካወቁ፣ ፈተናው ሊሸፍን ይችላል ብለው ባሰቡት መሰረት የልምምድ ፈተና ለመፍጠር ይሞክሩ። ይህ ትምህርቱን በጥልቅ ደረጃ እንዲረዱ እና ግልጽ የመማሪያ ዓላማዎችን እንዲያዘጋጁ ይረዳዎታል። ከዚያ እራስዎን እና የጥናት ቡድንዎን ለመጠየቅ የተግባር ፈተናዎን መጠቀም ይችላሉ። በዚህም ለራስ ፈተና በማዘጋጀት መለማመድ 18. ትምህርት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ከሚያሳድሩ ተማሪዎች እራስን መለየት ይህም አንዳንድ ተማሪዎች በትምህርታችን ውጤታማ እንዳንሆን በወሬ፣ ዝለን፣ ድብድብ፣ ጫዋታ፣ ልፊያ፣ ፌዝ፣ እና ቀልድ በጥቅሉ ለትምህርት ትኩረት ከማይሰጡ እራሳቸውን ከመቀየር ይልቅ ሌሎችም እንደነሱ እድሆኑ ከሚጥሩ ተማሪዎች ጋር አብረህ እየዘለልክ ጊዜህን ከማጥፋት ተቆጠብ። @Ethiopian_Digital_Library @Ethiopian_Digital_Library

ለኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞቻችን እንኳን ለጥምቀት በዓል በሰላም አደረሳችሁ! በዓሉ የሰላም ፣ የፍቅርና የመተሳሰብ እንዲሆን ልባዊ ምኞታችንን እንገልፃለን! ብስራት ትም
ለኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞቻችን እንኳን ለጥምቀት በዓል በሰላም አደረሳችሁ! በዓሉ የሰላም ፣ የፍቅርና የመተሳሰብ እንዲሆን ልባዊ ምኞታችንን እንገልፃለን! ብስራት ትምህርት ቤት።

ዛሬ ማለትም 08/05/2016 በከተማ ደረጀ በተዘጋጀው 6ኛ እና 8ኛ ክፍል ሞዴል ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎችን እውቅናና ሽልማት ከዚህ በታች በለው ሁኔታ ተበርክቶላቸዋል ።

ሰላም። አርብ ለተማሪዋቻችን የትራንስፖርት ችግር እንዳይኖር ሲባል ትምህርት ዝግ ይሆናል።

ሰላም። አርብ ለተማሪዋቻችን የትራንስፖርት ችግር እንዳይኖር ሲባል ትምህርት ዝግ ይሆናል።