Construction Contractors Association of Ethiopia
Відкрити в Telegram
Показати більше
3 094
Підписники
+524 години
+287 днів
-2730 день
Архів дописів
Repost from ኢትዮ - ኮን ሬድዮ ፕሮግራም/Ethio con radio program/
👉 ማስታወቂያ፡ ለአርሶ አደር የይዞታ ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት እግድ ተነሳ!
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ከቀን 14/12/18 ዓ.ም ጀምሮ በአርሶ አደር ይዞታዎች ላይ ተጥሎ የነበረውን የዝውውር እና የሶስተኛ ወገን ማስተላለፍ እግድ ሙሉ በሙሉ ማንሳቱን አሳወቀ።
📌 ቁልፍ ነጥቦች፡
የተነሳበት ምክንያት፡ በእግዱ ምክንያት በጽ/ቤቶች እየተከሰቱ ያሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት።
አቅጣጫ፡ ሂደቱ በመመሪያ ቁጥር 20/2013 መሰረት በከፍተኛ ጥንቃቄ እና በጥብቅ ዲስፕሊን መፈጸም እንዳለበት ተገልጿል፤
የሚመለከተው አካል፡ ለ11ዱም ክ/ከተማ መሬት ልማትና አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች እና ለሚመለከታቸው ዘርፎች የተላለፈ ነው።
ኢትዮ ኮን - ትክክለኛ የመረጃ ምንጭ
አስቸኳይ ማስታወቂያ
✏️ የConstruction Health and Safety እንዲሁም Construction Ethics ስልጠናን ከ7ኛው ዙር እስከ 12ኛው ዙር ስልጠናውን ወስዳችሁ ሰርተፍኬት ያልተሰጣችሁ መሆኑ የሚታወቅ መሆኑን እየገለጽን ሳይሰጣችሁ በመዘግየታችን ከወዲሁ ይቅርታ እየጠየቅን አና ሰርተፍኬቱ መዘጋጀቱን እየገለጽን የያዝነው አመት ከመጠናቀቁ በፊት ባምቢስ አካባቢ በሚገኘው ቢሮአችን በመምጣት የሚጠበቅባችሁን 3000 ብር ብቻ በመክፈል እንድትወስዱ እናሳስባለን።
ለበለጠ መረጃ 0115524723/0984777722 ይደውሉ
የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራ ተቋራጮች ማህበር
የ Health and Safety in Construction ስልጠና ያልወሰዳችሁ አባላት በሙሉ
🚧 ከኮንስትራክሸን ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት ከአ.አ ግንባታ እና ቁጥጥር ባለስልጣን ጋር በመተባበር የ2019 ዓ.ም በጀት አመትን ስልጠና ማስጀመራችን የሚታወቅ ሲሆን የፊታችን ከነሀሴ 27/2018 እስከ ነሀሴ 29 /2018 ዓ.ም 13ኛው ዙር ስልጠና ሊሰጥ ስለታሰበ እድሉን ያላገኛችሁ አባላቶች በመሉ ያለባችሁን አመታዊ የአባልነት ክፍያ ቀድማችሁ በማጠናቀቅ እንድትመዘገቡ እናሳስባለን፡፡
🚧 የድርጅት ስም፣የሰልጣኝ ስም እና ስልክ ቁጥር በመጻፍ በዚሁ ቻናል ወይንም በስ.ቁ 0984777722 ላይ መመዝገብ ይቻላል፡፡
የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራ ተቋራጮች ማህበር
አስቸኳይ
ውድ የማኅበራችን አባላቶች
ከላይ በተጠቀሰው የምክክር መድረክ ለመሳተፍ ይመለከተናል የምትሉ ነገ ከጠዋቱ 2:00 ሰአት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ቢሮ በመገኘት ተሳታፊ እንድትሆኑ ተጋብዛችኋል።
ቀድሞ ላሳወቀን ዕድሉን የምንሰጥ ሲሆን የተሳታፊ ስምና ስልክ ቁጥር በውስጥ መስመር 0984777722 ይላኩልን።
አስቸኳይ
ውድ የማኅበራችን አባላቶች
ከላይ በተጠቀሰው የምክክር መድረክ ለመሳተፍ ይመለከተናል የምትሉ ነገ ከጠዋቱ 2:00 ሰአት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ቢሮ በመገኘት ተሳታፊ እንድትሆኑ ተጋብዛችኋል።
ቀድሞ ላሳወቀን ዕድሉን የምንሰጥ ሲሆን የተሳታፊ ስምና ስልክ ቁጥር በውስጥ መስመር 0984777722 ይላኩልን።
Repost from ኢትዮ - ኮን ሬድዮ ፕሮግራም/Ethio con radio program/
📢 የዛሬ ምሽት ነሀሴ 18 ቀን 2018 ዓ.ም የ«ኢትዮ ኮን» ልዩ የሬዲዮ ፕሮግራም! 🧱🇪🇹
በሀገራችን የኮንስትራክሽን ዘርፍ ውስጥ ታይቶ የማይታወቅ ትልቅ ለውጥ ያመጣል ተብሎ የሚጠበቀውን አዲስ ዲጂታል ፕላትፎርም ሊያወቁ ዝግጁ ኖት?
በዓመት እስከ 300 ቢሊዮን ብር ማዳን የሚያስችለውን እና በዓፍሪካ ደረጃ የመጀመሪያ የሆነውን የተቀናጀ ሥነ-ምህዳር (Ecosystem) ፈጥሮ ወደ ሥራ የገባውን 'ኤቫኮኔት' (Evaconect) ፕላትፎርም ባለቤትና የሲቪል መሐንዲስ የሆነውን እንግዳችንን አቤሴሎምን ዛሬ ምሽት በቀጥታ ስርጭት ጋብዘናል!
በዘርፉ ላይ ያላችሁን ማንኛውንም ጥያቄ፣ ሃሳብ እና አስተያየት በሚከተሉት አድራሻዎች ማድረስ ትችላላችሁ።
💬 ጥያቄዎን
💡 ሃሳብዎን
🗣 አስተያየትዎን 0974466655
📩 በአጭር የጽሁፍ መልዕክት ላኩልን!
⏰ ዛሬ ምሽት ከ2:00-3:30 በአሀዱ ሬድዮ 94.3 በቀጥታ ስርጭት ይጠብቁን!
🏗 “የነገውን ግንባታ በጋራ እንገንባ!”
ኢትዮ ኮን - ትክክለኛ የመረጃ ምንጭ 📻
Repost from Ethio con Tender
+9
የግንባታ ስራ ጨረታ ማስታወቂያ፡
የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን "ከ ኮካ -ገዳመ እየሱስ መሳለሚያ የአስፋልት መንገድ ግንባታ የግንባታ ሥራዎች " በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል።
ፍላጎት ያላቸው ተቋራጮች በሙሉ ከታች ባለው የeGP system ሊንክ በመግባትና አስፈላጊውን መረጃ በመሙላት መሳተፍ ይችላሉ።
Construction Works Tender Notice:
The Addis Ababa City Roads Authority invites eligible contractors through an Open Tender for the Construction Works of Coca - Gedame Eyesus - Mesalemia Asphalt Road Project. Qualified firms can participate by registering and submitting all required information through the official eGP System link below.
Procurement Reference No.: AACRA-ICB-W-0007-2019-BID-Open
eGP System Link:
https://production.egp.gov.et/egp/bids/report/tendering/fea30a5e-b8f7-4e3a-8bff-a88fac1684fb/open
Repost from ኢትዮ - ኮን ሬድዮ ፕሮግራም/Ethio con radio program/
👉 ከዛሬ ጀምሮ ከአያት 49 ወደ ፊጋ የሚወስደው መንገድ በከፊል ይዘጋል ተባለ።
የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን ከአያት 49 ወደ ፊጋ በሚወስደው መንገድ 72 ድልድይ አካባቢ የመንገድ ጥገና ሥራ ሊካሄድ በመሆኑ መንገዱ ከዛሬ ሰኞ ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በከፊል ለትራፊክ ዝግ እንደሚደረግ አስታውቋል ።
ከአያት 49 ወደ ፊጋ በሚወስደው መንገድ ላይ 72 ድልድይ አካባቢ የሚካሄደው የመንገድ ጥገና ሥራ በፍጥነት እንዲጠናቀቅ መንገዱን በከፊል ለትራፊክ መዝጋት እንዳስፈለገ ገልጸዋል።
የጥገና ሥራው በሚካሄድበት ወቅት በአካባቢው የትራፊክ መጨናነቅ ሊፈጠር እንደሚችል የተጠበቀ ሲሆን ለመንገድ ተጠቃሚዎች እንቅስቃሴ ችግር እንዳይፈጠር አሽከርካሪዎች ቀድመው የጉዞ እቅዳቸውን እንዲያስተካክሉ ባለሥልጣኑ አሳስቧል።
በመሆኑም አሽከርካሪዎች በ72 ድልድይ አካባቢ ሲያልፉ ተጨማሪ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ የትራፊክ መመሪያዎችን እንዲከተሉና በተቻለ መጠን አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ ጥሪ አቅርቧል።
Repost from ኢትዮ - ኮን ሬድዮ ፕሮግራም/Ethio con radio program/
📌 አዲስ መሬት የያዘው የብሔራዊ ባንክ ስትራቴጂ፡
ከወለድ ነፃ የባንክ ገበያ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በፍጥነት እያደገ ላለው ከወለድ ነፃ የፋይናንስ ዘርፍ አጠቃላይ ስትራቴጂያዊ መመሪያ ማዘጋጀቱ ተሰማ።
📊 የዘርፉ ወቅታዊ ሁኔታ፡
31 የንግድ ባንኮች በአገሪቱ ውስጥ ይገኛሉ።
ከነዚህም ውስጥ 23ቱ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት በመስጠት ላይ ናቸው።
በ26 ሚሊዮን የባንክ ሂሳቦች ውስጥ ከ331 ቢሊዮን ብር በላይ ቁጠባ ተከማችቷል።
✨ በአዲሱ ስትራቴጂ የሚተገበሩ ዋና ዋና ነጥቦች፡
ግብር፡ ከወለድ ነፃ ፋይናንስን ከመደበኛው ብድር ጋር እኩል የግብር ተተኳሪነት እንዲኖረው ማድረግ።
አዳዲስ ምርቶች፡ የሱኩክ ቦንድ ማስተዋወቅ።
ቁጥጥር፡ ብሔራዊ የሸሪዓ ቁጥጥር ቦርድ ማቋቋም።
ማስፋፋት፡ አገልግሎቱን ወደ አነስተኛ ፋይናንስ እና ዲጂታል ቴክኖሎጂ ማድረስ።
ይህ እርምጃ የኢትዮጵያን የፋይናንስ ሥርዓት አካታችና ይበልጥ አዋጪ በማድረግ ረገድ ትልቅ ሚና ይጫወታል ተብሎ ይጠበቃል።
ኢትዮ ኮን — ትክክለኛ የመረጃ ምንጭ
Repost from ኢትዮ - ኮን ሬድዮ ፕሮግራም/Ethio con radio program/
▶️ ሳምንታዊ ዓለም አቀፍ የኮንስትራክሽን እና ኢንጂነሪንግ ዳሰሳ
ዓለም አቀፍ የኮንስትራክሽን፣ የኢንጂነሪንግ እና የቴክኖሎጂ ዜና ምንጮች
🌍 የሳምንቱ ዓለም አቀፍ የኮንስትራክሽን ገበታ እና ዋና ዋና ዜናዎች
1. የሜጋ ፕሮጀክቶች አፈፃፀም እና የትኩረት ማዕቀፍ
በዓለም አቀፍ ደረጃ የኮንስትራክሽን ገበያው ከሰፊው የዕድገት ትንበያ ይልቅ አሁን ላይ "በአስፈላጊ ፍላጎት (Essential Demand)" ላይ የተመሰረተ ምርጫ እያደረገ ይገኛል። እንደ የትራንስፖርት መሠረተ ልማቶች፣ የታደሰ ኃይል ማመንጫዎች እና የዲጂታል ዳታ ማዕከላት ያሉ ወሳኝ ፕሮጀክቶች ቀዳሚውን የፋይናንስ ድልድል እያገኙ ሲሆን፣ በግል ባለሀብቶች የሚመሩ የቅንጦት እና የቢሮ ግንባታዎች ጥብቅ የኢኮኖሚ ምዘና እየተደረገባቸው ይገኛል።
2. የሳውዲ አረቢያው የኒዮም (NEOM) እና የሜጋ ፕሮጀክቶች ምዕራፍ
የሳውዲ አረቢያው የትራንስፎርሜሽን ፕሮጀክት የሆነው NEOM በዓለም ትኩረት ማዕከልነቱን ቀጥሏል።
በተለይም በኦክሳጎን (Oxagon) የኢንዱስትሪ ማዕከል እና በሲንዳላህ (Sindalah) የቱሪዝም መዳረሻዎች ላይ እየተከናወኑ ያሉ የዲጂታል ቴክኖሎጂዎችና የታደሰ ኃይል (Green Hydrogen) ዝርጋታዎች ለቀጣዩ ትውልድ ስማርት ከተሞች ግንባታ አርአያ እየሆኑ ይገኛሉ።
3. የሆቴል እና ቱሪዝም ኢንፍራስትራክሽን ዕድገት
በዓለም አቀፍ ደረጃ የሆቴል ግንባታ ማዕቀፍ (Global Hotel Construction Pipeline) አዲስ ክብረ ወሰን አስመዝግቦ እጅግ ከፍ ባለ ደረጃ ላይ ይገኛል። በተለይም አሜሪካ እና እስያ (ቻይናን ጨምሮ) ግንባር ቀደም ተጠቃሽ ሲሆኑ፣ የቅንጦት (Luxury) እና የምርት ስም ማሻሻያ (Brand Conversion) ፕሮጀክቶች የገበያውን ሰፊ ድርሻ ይዘዋል።
4. በግንባታ ቴክኖሎጂ እና አረንጓዴ ዕድገት (ConTech & BIM)
የህንፃ መረጃ ሞዴሊንግ (BIM)፣ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) በዕቅድ አስተዳደር ውስጥ ያለው ሚና፣ እንዲሁም የካርቦን ልቀትን የሚቀንሱ አረንጓዴ የኮንስትራክሽን ግብዓቶች አጠቃቀም በዓለም አቀፍ ተቋራጮች ዘንድ የውድድር መመዘኛ እየሆኑ መጥተዋል።
ኢትዮ ኮን - ትክክለኛ የመረጃ ምንጭ
Repost from ኢትዮ - ኮን ሬድዮ ፕሮግራም/Ethio con radio program/
👉 የተሻሻለዉ የፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ሐምሌ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ስራ ላይ ውሏል።
Repost from ኢትዮ - ኮን ሬድዮ ፕሮግራም/Ethio con radio program/
ኢትዮ ኮን መረጃ 📢
የግንባታ ፕሮጀክቶች ስኬት ለዘላቂ ተወዳዳሪነት 🏗️
የግንባታ ፕሮጀክቶች በታለመላቸው ጊዜ፣ በጀት እና ጥራት እንዲጠናቀቁ እና ለሀገር እድገት ያላቸው አስተዋጽኦ አስተማማኝ እንዲሆን የሚከተሉትን ቁልፍ ጉዳዮች መተግበር ያስፈልጋል፡
አስተዳደር እና አመራር፡ ግልጽ እቅድ፣ ቅንጅታዊ አሰራር፣ ውጤታማ ክትትል እና ፈጣን ውሳኔ ሰጪነት
የጥራት ቁጥጥር፡ የግብዓት፣ የሰው ሃይል እና የአፈጻጸም መመሪያዎችን በትክክል መከተል።
ብቃት ያለው የሰው ሃይል፡ ባለሙያዎችን መመደብ፣ ክህሎትን በስልጠና ማሳደግ እና ደህንነትን መጠበቅ።
ግዥና አቅርቦት፡ ማቴሪያሎችን፣ ማሽኖችን እና ፋይናንስን በህጋዊና ጥራት ባለው መልኩ ማስተዳደር።
ዘመናዊ ቴክኖሎጂ፡ የቢውልዲንግ ኢንፎርሜሽን ሞዴሊንግ (BIM) እና ዲጂታል የፕሮጀክት ማናጅመንት መጠቀም።
ዲዛይንና ደህንነት፡ ቴክኒካዊ ምሉዕነት ያለው ዲዛይን እና የሰራተኞች ጤንነትና ደህንነት አጠባበቅ ስርዓት።
ቅንጅትና ተግባቦት፡ የስራ ስህተቶችን ለመቀነስ እና ውጤታማነትን ለማሳደግ እንደ ኦርኬስትራ ተናቦ መስራት።
ማጠቃለያ፡
እነዚህን እሴቶች በቁርጠኝነት እና በሙያ ስነምግባር ስንተገብር የኮንስትራክሽን ዘርፉ ብቃት ያለውና ተወዳዳሪ በመሆን ለሀገራዊ የምርት ዕድገት ያለው ሚና የጎላ ይሆናል! 🇪🇹
#ኢትዮኮን #ኢኮባ #ኮንስትራክሽን #የግንባታፕሮጀክት #ስኬት #ተወዳዳሪነት
Repost from ኢትዮ - ኮን ሬድዮ ፕሮግራም/Ethio con radio program/
🏗 የዛሬ ምሽት ነሀሴ 11 ቀን 2018 ዓ.ም የሬዲዮ ፕሮግራማችን ዝግጅት! 🧱
የኮንስትራክሽን ዘርፍ የአንድ አገር እድገትን የሚያሳይ ዋና የልማት መስክ ነው። ቤቶች፣ መንገዶች፣ ድልድዮች፣ ህንጻዎችና ሌሎች መሠረተ ልማቶች ሲገነቡ ከጥሬ ዕቃ ዋጋ እስከ ቴክኖሎጂ፣ ከባለሙያዎች እስከ የፖሊሲ አቅጣጫዎች ድረስ በርካታ ጉዳዮች ይነሳሉ።
እነዚህን ወቅታዊ ጉዳዮች በባለሙያዎችና በአድማጮች ሃሳብ በማዳመጥ የምንወያይበት ፕሮግራም ነው።
━━━━━━━━━━━━━━
🎙 የዛሬው የኮንስትራክሽን ጉዳዮች አንወያይ
📋 ርዕሰ ጉዳይ፦
በአገራችን የኮንስትራክሽን ግብዓቶች ዋጋ መናር እና ሊወሰዱ የሚገባቸው የመፍትሔ አቅጣጫዎች
👉 የዋጋ ጭማሪው በግንባታ ሥራዎች ላይ ምን ተፅዕኖ እያሳደረ ነው?
👉 ለችግሩ ሊወሰዱ የሚገባቸው ዘላቂ የመፍትሔ አቅጣጫዎችስ ምንድናቸው?
🔥 ዛሬም ክፍል ሁለት ይቀጥላል!
━━━━━━━━━━━━━━
🤖 ወቅታዊ ጉዳይ
🤖 ኤ.አይ. (Artificial Intelligence) የዘመኑ ምርጫ
ፎር ኮንስትራክሽን — ዘመን የማይሽረው ምርጫ
በዛሬው የወቅታዊ ጉዳይ ክፍላችን ስለ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ እና ስለ ኮንስትራክሽን ዘርፉ የወደፊት አቅጣጫ እንመለከታለን።
📱 በኮንስትራክሽን ኢንደስትሪው ምን ዓይነት Apps መጠቀም አለብን?
💡 እነዚህን ቴክኖሎጂዎች መጠቀም ለግንባታ ዘርፉ ምን ጠቀሜታ አለው?
🏗 የኤ.አይ. ቴክኖሎጂ የግንባታውን ዘርፍ ወዴት እየወሰደው ነው?
📚 በአንድ ታላቅ ባለሙያ የቀረበውን ጥናት መሠረት አድርገን ሌሎችም ጠቃሚ ጉዳዮችን እንመለከታለን።
📢 የእርስዎ ሃሳብ ወሳኝ ነው!
የዛሬውን ውይይት በመከታተል፦
💬 ጥያቄዎን
💡 ሃሳብዎን
🗣 አስተያየትዎን በ0974466655 📩 ለአጭር የጽሁፍ መልዕክት
⏰ ምሽት ከ2፡00-3፡30 በቀጥታ ስርጭት ይጠብቁን!
🏗 “የነገውን ግንባታ በጋራ እንገንባ!” 🇪🇹
#ኮንስትራክሽን_ጉዳዮች_እንወያይ
#ኢትዮ_ኮን
#Construction
#ArtificialIntelligence
#AIForConstruction
Repost from ኢትዮ - ኮን ሬድዮ ፕሮግራም/Ethio con radio program/
**ማስታወቂያ *
የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማት ኮርፓሬሽን ከተማ አስተዳደሩ በልዩ ትኩረት እየተገበረ ለሚገኘው መጠነ ሰፊ የቤት ልማት ፕሮግራም በግንባታው ዘርፍ ላይ የተሰማሩ እና መስፈርቱን የሚያሟሉ ስራ ተቋራጮችን አወዳድሮ ለማሰራት ይጋብዛል፡፡
በዚሁ መነሻ
1. ለስራ ተቋራጮች ምዝገባ መሟላት ያሉባቸው መረጃዎች፡-
ሀ) የታደሰ የንግድ ፍቃድ፣የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርተፍኬት፣የታደሰ የብቃት ማረጋገጫ ምዝገባ ሰርተፍኬት እና የአቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ ስለመመዝገቡ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል፤
ለ) በምዝገባው ወቅት የሰነዶቹን ዋና እና አንድ የማይመለስ ቅጂ በአካል የሚቀርብ ሆኖ የስራ ተቋራጩ የበላይ ኃላፊ፣ ባለቤት ወይም ህጋዊ ውክልና ያለው ተወካይ ፊርማ እና የድርጅቱ ህጋዊ ማህተም በማድረግ ማቅረብ ይጠበቅበታል፡፡
2. ከደረጃ 1-4 ጠቅላላ ስራ ተቋራጭ(GC) እና ( BC )ህንፃ ተቋራጭ እንዲሁም ጠቅላላ ስራ ተቋራጭ (GC) ደረጃ 5 የብቃት ማረጋገጫ ያላቸው በግንባታው ዘርፍ ላይ የተሰማሩ ስራ ተቋራጮች ተሳታፊ መሆን ይችላሉ ።
3. ከቅዳሜ 9 /12/2018 ዓ/ም (ከጠዋቱ 2፡30) ቅዳሜ ሙሉ ቀን ጨምሮ ለ5 (አምስት) ተከታታይ የስራ ቀናት( እስከ ሀሙስ 14/12/2018 ዓ/ም ከሰዓት 11፡30) በአካል በመቅረብ በኮርፖሬሽኑ 11ኛ ወለል በሚገኝ አዳራሽ ላይ ምዝገባ በማድረግ መረጃዎቹ መሟላታቸው በመዝጋቢው ሲረጋገጥ ለዚሁ የተዘጋጀ የቴክኒካል ሰነድ መግዛት ይቻላል።
4. ተገቢውን ሰነድ በማቅረብ የምዝገባ ሂደቱን በሚገባ ያሟለ ተቋራጮችን በተመለከተ ምዝገባው በተጠናቀቀ በ 24 ሰዓት ውስጥ በቀን 15/12/2018 ዓ/ም በተቋሙ ማህበራዊ ድህረ ገጽ እና በኮርፖሬሽኑ የማስታወቂያ ቦርድ 11ኛ ወለል የሚለጠፍ ይሆናል፡፡
5. ተቋራጮች የቅድመ ምዝገባ ውጤት ከታወቀበት ቀን ጀምሮ በአስር (10) ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ አንድ ኦርጅናል እና ሁለት ቅጂ የቴክኒካል ፕሮፖዛላቸውን ለዚሁ በተዘጋጀ ሳጥን እስከ ቀን 27/12/2018 ዓ/ም ከሰዓት 11:30 ድረስ ብቻ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
6. ተቋራጮች ለምዝገባ እና ለቴክኒካል ሰነድ ግዢ የማይመለስ ብር ለደረጃ 1 ብር 7,500 (ሰባትሺ አምስት መቶ ብር ) ፣ ለደረጃ 2 ብር 6,500 ( ስድስት ሺ አምስት መቶ ብር ) እና ለደረጃ 3 ብር 5,500 አምስት ሺ አምስት መቶ ብር ) ፣ ለደረጃ 4 ብር 5,000 (አምስት ሺ ብር ) ፣ ለደረጃ 5 ብር 4,500 አራት ሺ አምስት ብር ) መክፈል ይጠበቅባቸዋል፡፡
**
አድራሻ
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቂርቆስ ክ/ተማ ወረዳ 01
በተለምዶ ባምቢስ አከባቢ ግሪክ ት/ቤት ፊት ለፊት በሚገኘው የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማት ና አስተዳደር ቢሮ ህንፃ ላይ 11ኛ ወለል እንገኛለን።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጭ:-
https://linktr.ee/aahdc
ነሀሴ 9 ቀን 2018 ዓ/ም
የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን
ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት
Repost from ኢትዮ - ኮን ሬድዮ ፕሮግራም/Ethio con radio program/
**ማስታወቂያ *
የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማት ኮርፓሬሽን ከተማ አስተዳደሩ በልዩ ትኩረት እየተገበረ ለሚገኘው መጠነ ሰፊ የቤት ልማት ፕሮግራም በግንባታው ዘርፍ ላይ የተሰማሩ እና መስፈርቱን የሚያሟሉ ስራ ተቋራጮችን አወዳድሮ ለማሰራት ይጋብዛል፡፡
በዚሁ መነሻ
1. ለስራ ተቋራጮች ምዝገባ መሟላት ያሇባቸው መረጃዎች፡-
ሀ) የታደሰ የንግድ ፍቃድ፣የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርተፍኬት፣የታደሰ የብቃት ማረጋገጫ ምዝገባ ሰርተፍኬት እና የአቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ ስለመመዝገቡ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል፤
ለ) በምዝገባው ወቅት የሰነዶቹን ዋና እና አንድ የማይመለስ ቅጂ በአካል የሚቀርብ ሆኖ የስራ ተቋራጩ የበላይ ኃላፊ፣ ባለቤት ወይም ህጋዊ ውክልና ያለው ተወካይ ፊርማ እና የድርጅቱ ህጋዊ ማህተም በማድረግ ማቅረብ ይጠበቅበታል፡፡
2. ከደረጃ 1-4 ጠቅላላ ስራ ተቋራጭ(GC) እና ( BC )ህንፃ ተቋራጭ እንዲሁም ጠቅላላ ስራ ተቋራጭ (GC) ደረጃ 5 የብቃት ማረጋገጫ ያላቸው በግንባታው ዘርፍ ላይ የተሰማሩ ስራ ተቋራጮች ተሳታፊ መሆን ይችላሉ ።
3. ከቅዳሜ 9 /12/2018 ዓ/ም (ከጠዋቱ 2፡30) ቅዳሜ ሙሉ ቀን ጨምሮ ለ5 (አምስት) ተከታታይ የስራ ቀናት( እስከ ሀሙስ 14/12/2018 ዓ/ም ከሰዓት 11፡30) በአካል በመቅረብ በኮርፖሬሽኑ 11ኛ ወለል በሚገኝ አዳራሽ ላይ ምዝገባ በማድረግ መረጃዎቹ መሟላታቸው በመዝጋቢው ሲረጋገጥ ለዚሁ የተዘጋጀ የቴክኒካል ሰነድ መግዛት ይቻላል።
4. ተገቢውን ሰነድ በማቅረብ የምዝገባ ሂደቱን በሚገባ ያሟለ ተቋራጮችን በተመለከተ ምዝገባው በተጠናቀቀ በ 24 ሰዓት ውስጥ በቀን 15/12/2018 ዓ/ም በተቋሙ ማህበራዊ ድህረ ገጽ እና በኮርፖሬሽኑ የማስታወቂያ ቦርድ 11ኛ ወለል የሚለጠፍ ይሆናል፡፡
5. ተቋራጮች የቅድመ ምዝገባ ውጤት ከታወቀበት ቀን ጀምሮ በአስር (10) ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ አንድ ኦርጅናል እና ሁለት ቅጂ የቴክኒካል ፕሮፖዛላቸውን ለዚሁ በተዘጋጀ ሳጥን እስከ ቀን 27/12/2018 ዓ/ም ከሰዓት 11:30 ድረስ ብቻ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
6. ተቋራጮች ለምዝገባ እና ለቴክኒካል ሰነድ ግዢ የማይመለስ ብር ለደረጃ 1 ብር 7,500 (ሰባትሺ አምስት መቶ ብር ) ፣ ለደረጃ 2 ብር 6,500 ( ስድስት ሺ አምስት መቶ ብር ) እና ለደረጃ 3 ብር 5,500 አምስት ሺ አምስት መቶ ብር ) ፣ ለደረጃ 4 ብር 5,000 (አምስት ሺ ብር ) ፣ ለደረጃ 5 ብር 4,500 አራት ሺ አምስት ብር ) መክፈል ይጠበቅባቸዋል፡፡
**
አድራሻ
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቂርቆስ ክ/ተማ ወረዳ 01
በተለምዶ ባምቢስ አከባቢ ግሪክ ት/ቤት ፊት ለፊት በሚገኘው የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማት ና አስተዳደር ቢሮ ህንፃ ላይ 11ኛ ወለል እንገኛለን።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጭ:-
https://linktr.ee/aahdc
ነሀሴ 9 ቀን 2018 ዓ/ም
የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን
ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት
አስቸኳይ ማስታወቂያ
✏️ መላው የማህበራችን አባላቶች በሙሉ ከዚህ በፊት:-
1-Refrigeration,Air Conditioning,and Heat pump Technology
2-Solar-PV off-Grid Systems and PLC Monitoring ስልጠናዎችን ለመስጠት ፍላጎቱ ያላችሁ አባላቶች እንድትመዘገቡ ያሳወቅን መሆኑ ይታወቃል። ሆኖም 2ቱም የስልጠና አይነቶች የሚሰጡት በተመሳሳይ ሰአት ወይም ጎን ለጎን በመሆኑ አንድ ሰው ሊወስድ የሚችለው አንዱን ብቻ ነው።ስለሆነም ስልጠናውን ለመውሰድ የተመዘገባችሁ በሙሉ ምርጫችሁን ከወዲሁ እንድታሳውቁን በአክብሮት እንጠይቃለን።
ለበለጠ መረጃ 0984777722 ላይ ይደውሉ
የሥልጠና ማስታወቂያ
✏️ መላው የማህበራችን አባላቶች በሙሉ ከዚህ በፊት:-
1-Refrigeration,Air Conditioning,and Heat pump Technology
2-Solar-PV off-Grid Systems and PLC Monitoring ስልጠናዎችን ለመስጠት ፍላጎቱ ያላችሁ አባላቶች የአባልነት መዋጮ ክፍያ ማጠናቀቃችሁን በማረጋገጥ የእድሉ ተጠቃሚ እንድትሆኑ ማሳወቃችን ይታወቃል። ስለሆነም አሁንም ውስን ቦታ ስላለን ያልተመዘገባችሁ የተከበራችሁ አባለት የሰልጣኝ ባለሞያዎቻችሁን ሙሉ ስም እና ስልክ በደብዳቤ ወይም በቴሌግራም ገጻችን እስከ ፊታችን አርብ ማለትም ነሐሴ 8/2018 ዓ.ም ድረስ በመራዘሙ ይሔን እድል ተጠቅማችሁ ከወዲሁ እንድትልኩልን እናሳውቃለን።
ለበለጠ መረጃ 0984777722 ላይ ይደውሉ
Repost from ኢትዮ - ኮን ሬድዮ ፕሮግራም/Ethio con radio program/
🏗 የዛሬ ምሽት ነሀሴ 4 ቀን 2018 ዓ.ም የሬዲዮ ፕሮግራማችን ዝግጅት! 🧱
🎙 👷♂ የእንግዳ ሰዓት፡
የድሬዳዋ ከተማ የመንገድ መሠረተ ልማት ዕድገት
በሰሙኑ ወደ ድሬዳዋ ከተማ ባደረግነው የሥራ ጉዞ ከድሬዳዋ አስተዳደር የመንገዶች ባለስልጣን ኃላፊ ከአቶ ቴውድሮስ ፍቅሬ ጋር ስለ ኮሪደር ልማትና ዕድገት፡ የድሬዳዋን ገጽታ የሚቀይሩ ዘመናዊ የኮሪደር ልማት ሥራዎች ሌሎችንም እያነሳን ልዩ ቆይታ አድርገናል!
💬 . "የኮንስትራክሽን ጉዳዮች እንወያይ" 📋
ርዕሰ ጉዳይ፦
"በአገራችን የኮንስትራክሽን ግብዓቶች ዋጋ መናር እና ሊወሰዱ የሚገባቸው የመፍትሔ አቅጣጫዎች" በሲሚንቶ፣ በብረት እና በሌሎችም የግንባታ ግብዓቶች ዋጋ መናር ዙሪያ የሚስተዋሉ ተግዳሮቶች እና መፍትሔዎቻቸው ላይ እንወያያለን።
📩 የእርስዎን ሃሳብ እና ጥያቄ ለአጭር የጽሁፍ መልዕክት መላኪያ ፦ 0974466655
ውይይቱ የእርስዎን ተሳትፎ ይጠብቃል! 📻
“የነገውን ግንባታ በጋራ እንገንባ!” 🏗
🇪🇹🏗
ምሽት ከ2፡00-3፡30 ሰዓት በአሀዱ ሬድዮ 94.3 የቀጥታ ስርጭት ፕሮግራማችን ይጠብቁን
