አያሌው ቢታኔ በማናቸውም የፌዴራል እና የክልል ፍርድ ቤቶች ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ቢሮ
Відкрити в Telegram
ይህ ገፅ ለማንኛውም ሰው ስለ ህግ እና ህግ ነክ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ የሚሰጥበት ፣ በተለያዩ ጊዜያት የወጡ አዋጆች ፣ደንቦች እና መመሪያዎች የሚጋሩበት ነው ለበለጠ መረጃ 0911911313 Telegram username:- @Justicehastobeserved
Показати більше1 070
Підписники
+224 години
+27 днів
+130 день
Архів дописів
ማስታወቂያ
ለክቡራን የውክልና ስልጣን መስጠት እና የሰነድ ማረጋገጥ አገልግሎት ፈላጊዎች፡-
የDigital MOFA የስልክ መተግበሪያን በተመለከተ እ.ኤ.አ. ከኤፕሪል 2026 ጀምሮ የውክልና ስልጣን መስጠት እና የሰነድ ማረጋገጥ አገልግሎት ሙሉ በሙሉ በመተግበሪያው (Application) ብቻ እንዲሰጥ የተወሰነ በመሆኑ አመልካቾች መተግበሪያውን ከ (APP Store) ወይም (Play store) በማውረድ እና በመመዝገብ ባሉበት ሆነው ማመልከት እንደሚችሉ በአክብሮት እንገልፃለን።
Please note that, effective April 2026, Power of Attorney and Document Authentication services that were previously provided in person at the Embassy have been fully digitalized.
Applicants seeking Power of Attorney, document authentication, and related services should apply through the Digital MOFA mobile application.
The Digital MOFA application is available for download from both the Apple App Store and Google Play Store.
🇪🇹የ2019 በጀት አመት የተደገፈ በጀት👆
🔱@ethiopiantaxgroup
🔱@ethiopiatax
ምክር ቤቱ የጉምሩክ አዋጅን እንደገና ለማሻሻል የቀረበ ረቂቅ አዋጅን መርምሮ አጸደቀ
#########################
(ጉምሩክ ኮሚሽን ፤ ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም )
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ24ኛ መደበኛ ስብሰባው የጉምሩክ አዋጅን እንደገና ለማሻሻል የቀረበ ረቂቅ አዋጅን መርምሮ አጽድቋል፡፡
በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ አቶ ደሳለኝ ወዳጆ ሪፖርት እና የውሳኔ ሀሳብ ለምክር ቤቱ አቅርበዋል፡፡
ረቂቅ አዋጁ የኮንትሮባንድ ንግድን ለመከላከል የሚደረገውን ጥረት በማጠናከር ረገድ ጉልህ ሚና እንዳለው ሰብሳቢው ገልጸዋል።
የተከበሩ አቶ ደሳለኝ ወዳጀ አያይዘው እንደገለጹት፣ ረቂቅ አዋጁ በዘርፉ ሀገራችን ከፈረመቻቸው ዓለም አቀፍ ስምምነቶች ጋር የተጣጣመ እንዲሆን የሚያስችል ሲሆን፣ በጉምሩክ አሠራር ውስጥም ፍትሃዊነት እንዲረጋገጥ ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር ነው።
በተጨማሪም፣ ረቂቅ አዋጁ በሀገራችን እያደገ የመጣውን የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ልማት የሚደግፍ እንዲሁም ኢንቨስትመንትን የሚያበረታታ መሆኑን አመላክተዋል።
ረቂቅ አዋጁ በነባሩ አዋጅ ውስጥ የተደነገጉ ገደቦችን በተግባር ላይ ሲውሉ ይስተዋሉ የነበሩ የአተገባበር ችግሮችን ለመቅረፍ ያስችሉ ዘንድ አስፈላጊ ድንጋጌዎችን ያካተተ መሆኑን አንስተዋል።
አስመጪዎች በቀረጥና ታክስ አወሳሰን ላይ ያላቸውን አቤቱታ በማቅረብ ሂደት ያጋጥሟቸው የነበሩ የአሠራር መሰናክሎችን ለማስወገድ የሚያስችሉ ድንጋጌዎችን ያካተተ ረቂቅ አዋጅ መሆኑን ጠቁመዋል።
የምክር ቤት አባላት በበኩላቸው፣ በረቂቅ አዋጁ ዝግጅት ወቅት የተከናወነው ሥራ አስፈላጊውን የሕግ ምርመራ እና ግምገማ ሂደት የተከተለ ሲሆን፣ አዋጁም በተገቢው ሁኔታ ታይቶና ተገምግሞ የቀረበ መሆኑን ገልጸዋል።
በኮንትሮባንድ ጭነት ምክንያት ተሽከርካሪ እንዲወረስ የሚያስችል ድንጋጌ ቢኖርም፣ ባለቤቱ በድርጊቱ ተሳታፊ ባልሆነበት ሁኔታ ንብረቱ ሊወረስ እንደማይገባም አንስተዋል።
ባለቤቱ ተሽከርካሪውን አሽከርካሪ እንዲጠቀምበት በውል ሲያስረክብ፣ ታማኝና ለሕግ ተገዥ የሆነ ሹፌር መቅጠር እንዲሁም ለሚደርስ ጉዳት ወይም ሕገ-ወጥ ድርጊት ተገቢ ዋስትና መውሰድ እንዳለበት ተጠቁሟል።
በመጨረሻም ምክር ቤቱ በረቂቅ አዋጁ ላይ ሰፊ ውይይት ካደረገ በኋላ፣ የጉምሩክ አዋጅን እንደገና ለማሻሻል የቀረበ ረቂቅ አዋጅን፣ አዋጅ ቁጥር 1425/2018 አድርጎ በሁለት ተቃውሞ በአብላጫ ድምጽ ማጽድቁን ከህዝብ ከተወካዮች ምክር ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክተል።
#ተጨማሪ
የጉምሩክ አዋጁ ያሻሻላቸው ተጨማሪ ጉዳዮች ምንድናቸው?
አስመጪዎችና ላኪዎች በባህር እንዲሁም በየብስ የሚያስገቧቸው ዕቃዎች በመጋዘን የሚቆዩበት ጊዜ ከ15 ወደ 45 ቀናት ፣ በአየር የሚገቡ ደግሞ ከ10 ወደ 30 ቀናት እንዲያድግ ተደርጓል።
በተጨማሪም አስመጪዎች በአንድ ዲክላራሲዮን ላስገቧቸው ዕቃዎች ሙሉ ቀረጥ በአንዴ ለመክፈል የገንዘብ እጥረት ካጋጠማቸው፣ ቀረጥ የከፈሉበትን የዕቃ መጠን ብቻ ለይተው በክፍልፋይ እንዲያወጡ የሚፈቅድ አዲስ አሰራር ተዘርግቷል።
የቴክኖሎጂ ሽግግርን ለማገዝም፣ ሶፍትዌር ወደ አገር ሲገባ የሚታሰበው ቀረጥ በውስጡ ባለው መረጃ ዋጋ ላይ ሳይሆን፣ ሶፍትዌሩ በተጫነበት መሣሪያ (Carrier Medium) ዋጋ ላይ ብቻ እንዲሆን ተወስኗል።
የውጭ ምንዛሬ ተመን አወሳሰን ላይም የቀረጥ ስሌት የሚከናወነው ዲክላራሲዮኑ በጉምሩክ ተመዝግቦ ተቀባይነት ባገኘበት ቀን ብሔራዊ ባንክ በሚያወጣው ጠቋሚ (Indicative) የምንዛሬ ተመን መሠረት እንዲሆን ተደንግጓል።
በገዥና በሻጭ መካከል ግንኙነት ባለበት ሁኔታ ደግሞ፣ አስመጪው ዝምድናው በዋጋው ላይ ተጽዕኖ አለማሳደሩን ማረጋገጥ ካልቻለ ጉምሩክ የቀረበውን ዋጋ ውድቅ የማድረግ ሥልጣን ተሰጥቶታል።
ረቂቅ አዋጁ ኮንትሮባንድ ለመከላከል የኮንትሮባንድ ዕቃዎችን ለመደበቅ ተብለው ተሻሽለው የተሠሩ ወይም ከፍተኛ መጠን ያለው የኮንትሮባንድ ዕቃ የጫኑ ተሽከርካሪዎች፣ የዕቃው ዋጋ ግምት ውስጥ ሳይገባ በቀጥታ እንዲወረሱ ይደረጋል።
በኮንትሮባንድ ተግባር ላይ የተገኘ እንስሳ ባለቤት፣ የእንስሳውን ወቅታዊ የገበያ ዋጋ 100 በመቶ እኩል የገንዘብ መቀጫ እንዲከፍል ተደንግጓል።
በተጨማሪም መረጃ ለሚሰጡ እና ለሚተባበሩ አካላት የገንዘብ ወሮታ እንዲከፈል የተወሰነ ሲሆን፣ ከኮንትሮባንድ ዕቃ ሽያጭ የሚገኘው ገቢም ለኮሚሽኑ አቅም ግንባታ እንዲውል ይደረጋል።
ሌላው፣ አንድ አስመጪ በጉምሩክ ውሳኔ ላይ ቅሬታ ካለው ይግባኝ ማለት የሚችለው፣ ክርክር የተነሳበትን ቀረጥና ታክስ 50 በመቶ አስቀድሞ መክፈሉ ሲረጋገጥ ብቻ ነው።
በተጨማሪም አስመጪዎች ለጉምሩክ የሚሰጡት የዋጋ መረጃ እንደ ምስጢር ተጠብቆ እንዲቆይ ሕጋዊ ዋስትና ተሰጥቷል። መረጃው ሊገለጽ የሚችለው ለፍርድ ቤት ክርክር ሲፈለግ ብቻ ይሆናል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
የግብርና ቢዝነስ ኩባንያዎች ለሥራቸው የሚያስፈልጓቸውን የግብርና ግብዓቶች፣ መሣሪያዎችና፣ ተሽከርካሪዎችን ከውጭ "ከታክስ ነፃ" እንዲያስገቡ የሚፈቅድ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጀ።
የሚኒስትሮች ምክር ቤት የግብርና ዘርፍን ከተለምዶአዊ አሰራር ወደ ቢዝነስ መር ስርአት ለማሸጋገር ያግዛል ያለውን "የግብርና ቢዝነስ ኩባኒያ አዋጅ" ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መምራቱ ይታወቃል።
ይህ አዋጅ ኋላ ቀር የግብርና አሠራር ተወስነው የቆዩ አነስተኛ አርሶ አደሮችን፣ አርብቶ አደሮችንና ከፊል አርብቶ አደሮችን ወደ ዘመናዊና ተወዳዳሪ የንግድ ሥርዓት ለማሸጋገር ያለመ ነው።
የዚህ ሪቂቅ አዋጅ ዋነኛ ትኩረት አነስተኛ ይዞታ ያላቸውን አምራቾች በ "ክላስተር" በማደራጀት ወደ ግብርና ቢዝነስ ኩባኒያነት መለወጥ ነው።
አዲሱ ሕግ አርሶ አደሩ ያለውን መሬት የመጠቀም መብት፣ የእንስሳት ሀብትና ጉልበት ወደ ካፒታል በመለወጥ የኩባኒያ ባለቤትና ባለድርሻ እንዲሆን ዕድል ይከፍታል።
ይህም አርሶ አደሩ በግል ከመልፋት ይልቅ በጋራ በመደራጀት በገበያ ላይ የመደራደር አቅሙን እንዲያሳድግ፣ ምርቱን እንዲያሰባስብና እሴት በመጨመር የተሻለ ዋጋ እንዲያገኝ እንደሚያስችለው አዋጁ ያስረዳል።
በአዋጁ መሠረት አንድ የግብርና ቢዝነስ ኩባኒያን ለመመስረት ዝቅተኛ የአባላት ቁጥር ተቀምጧል።
በአዝርዕት ዘርፍ የተሰማሩ ከሆኑ ቢያንስ 300 አባላት፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ወይም በእንስሳት እርባታ ዘርፍ ከሆነ ደግሞ ቢያንስ 150 አባላት ሊኖሩት ይገባል።
ኩባኒያዎቹ ሲመሰረቱ ዝቅተኛ የተከፈለ ዋና ካፒታላቸው ከ1.5 ሚሊዮን ብር ማነስ የለበትም።
እያንዳንዱ አባል በኩባኒያው ውስጥ ሊኖረው የሚችለው የአንድ ድርሻ (Share) ዋጋም ከ1,000 ብር በታች እንዳይሆን ተደንግጓል።
የግብርና ቢዝነስ ኩባኒያዎቹ እንደ ማንኛውም ዘመናዊ የንግድ ተቋም በጠቅላላ ጉባኤ፣ በሥራ አመራር ቦርድ እና በዋና ሥራ አስኪያጅ የሚመሩ ይሆናሉ።
ከዚህ በተጨማሪ ኩባኒያዎቹ ስትራቴጂካዊ አቅጣጫዎችን የሚጠቁሙና ሙያዊ ምክር የሚሰጡ፣ "የአማካሪ ቦርድ" እንዲኖራቸው አዋጁ ይፈቅዳል፣ የአማካሪ ቦርድ የስራ አባላት ዘመንም ሦስት አመት ነው።
ይህም የኩባኒያዎቹ አመራር በሳይንሳዊና በዘመናዊ የቢዝነስ ዕውቀት ላይ የተመሰረተ እንዲሆን ለማድረግ ነው።
ይህንን ሽግግር ለማገዝም ልዩ ልዩ ማበረታቻዎችን ረቂቅ አዋጁ አካቷል።
የግብርና ቢዝነስ ኩባኒያዎቹ ለሥራቸው የሚያስፈልጉ የግብርና ግብዓቶችና ቴክኖሎጂዎችን፣ የእርሻ መሣሪያዎችንና ተሽከርካሪዎችን እንዲሁም መለዋወጫዎችን ከውጭ ሲያስገቡ "ከታክስ ነፃ" የመሆን መብት ይኖራቸዋል።
የግብርና ቢዝነስ ኩባኒያ አባላት ያመረቱተትን የግብርና ምርት ሲሽጡ ወይም ከኩባኒያው በሚያገኙት የትርፍ ክፍፍል ላይ የገቢ ግብር አይከፍሉም፡፡
ሆኖም ኩባንያው ከሚያገኘው ገቢ ላይ በገቢ ግብር አዋጁ መሰረት ግብር ይከፍላል፡፡
በተጨማሪም ኩባንያዎቹ ግብዓቶችን ለማስገባት ለሚያስፈልጋቸው የውጭ ምንዛሬ ቅድሚያ የሚሰጣቸው ሲሆን፣ ለሥራ አመራር ቦርድና ለአባላት የአቅም ግንባታ ሥልጠናዎች እንደሚመቻቹ እንደሚደረግ ረቂቅ መመሪያው ያሳያል።
ግንቦት 18 በተካሄደው 55ኛው የሚኒስትሮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ፣ አዋጁ ላይ ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መርቶታል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
#ለመረጃ፡ በኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ መረጃዎች የሚደራጁበት እና የሚተነተኑበት (የዋጋ ንረትን ጨምሮ) የኢትዮጵያ የስታቲስቲክስ አዋጅ ተሻሽሏል! ሙሉ ሰነዱን ማንበብ ለምትፈልጉ ከላይ ተቀምጧል!
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አዲስ የፍራንኮ ቫሉታ መመሪያ ይፋ አድርጓል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በሀገሪቱ የውጭ ምንዛሬ ክምችት ላይ ጫና ሳይፈጥሩ ኢንቨስትመንትና ንግድን ለማሳለጥ ያስችላል ያለውን “የፍራንኮ ቫሉታ ገቢ ዕቃዎች መመሪያ ቁጥር FVD/01/2026” የተሰኘ አዲስ የሕግ ማዕቀፍ ይፋ አድርጓል።
ይህ አዲስ መመሪያ ከዚህ ቀደም በፍራንኮ ቫሉታ አሠራር ላይ ይታዩ የነበሩ የቁጥጥር ክፍተቶችን ለመድፈንና ግልጽነትን ለማስፈን ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
ባንኩ በመመሪያው መግቢያ ላይ እንደገለጸው፣ ከዚህ ቀደም አጠቃላይና ዘመናዊ የቁጥጥር ሥርዓት ባለመኖሩ ምክንያት በፍራንኮ ቫሉታ ስም ሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር፣ የተዛባ ሪፖርት አቀራረብ እና የውጭ ምንዛሬ ቁጥጥርን የማለፍ አዝማሚያዎች ሲታዩ ቆይተዋል።
በአዲሱ መመሪያ መሠረት በፍራንኮ ቫሉታ ዕቃዎችን ወደ ሀገር ውስጥ እንዲያስገቡ የተፈቀደላቸው አካላት በዝርዝር ተቀምጠዋል።
እነዚህም:-
• የሀገር ውስጥ (በኢኮኖሚ ቀጠናዎች ያሉ)፣ የዲያስፖራ እና የውጭ ሀገር ባለሀብቶች፣
• በውጭ ባለሀብቶች የተያዙ የማኑፋክቸሪንግ እና የኢንዱስትሪ ተቋማት፣
• ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያላቸው የልማት ፕሮጀክቶች፣
• ዲፕሎማቶች፣ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች እና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች (NGOs)፣
• ዕርዳታ የሚቀበሉ የሃይማኖት እና የሲቪክ ማኅበራት፣ እንዲሁም የግል ንብረቶቻቸውን የሚያስገቡ ግለሰቦች ናቸው።
ከእነዚህም በተጨማሪ የግል ንብረቶቻቸውን የሚያስገቡ ግለሰቦችና በቋሚነት ወደ ሀገር የሚመለሱ ኢትዮጵያውያንም ተጠቃሚ ይሆናሉ።
ለሰው ሕይወት አስፈላጊ የሆኑ መድኃኒቶች ያለምንም የዋጋ ገደብ በፍራንኮ ቫሉታ እንዲገቡ የተፈቀደ ሲሆን፤ የማምረቻ ጥሬ ዕቃዎች፣ የካፒታል ዕቃዎችና የቴክኖሎጂ መሣሪያዎችም በመመሪያው ውስጥ ተካተዋል።
የጉምሩክ ኮሚሽን ሁሉንም የፍራንኮ ቫሉታ ግብይቶች "FEMoUS" በሚባለው የውጭ ምንዛሬ ክልከላና ቁጥጥር ሥርዓት ውስጥ የመመዝገብ ግዴታ ተጥሎበታል።
ተጠቃሚዎችም ትክክለኛ የንግድ ፈቃድ የመያዝ፣ አስፈላጊ ሰነዶችን ለጉምሩክ የማቅረብ እና ኦዲት ሊደረጉ የሚችሉ መዝገቦችን በሥርዓቱ የመያዝ ግዴታ አለባቸው።
በመመሪያው ላይ የተቀመጡ ደንቦችን በመተላለፍ የተሳሳተ መግለጫ መስጠት፣ አሠራሩን ለሕገ-ወጥ ተግባር ማዋል እና የቁጥጥር ሥርዓቱን ለማለፍ መሞከር ጥብቅ ቅጣት እንደሚያስከትል ተደንግጓል።
ማንኛውም ጥፋት ፈጽሞ የሚገኝ አካል በገንዘብ ቅጣት፣ ንብረቱ በመወረስ አልፎ ተርፎም በብሔራዊ ባንክ አዋጅ መሠረት በወንጀል ተጠያቂ እንደሚሆን መመሪያው ያስረዳል።
ይህ አዲስ የፍራንኮ ቫሉታ መመሪያ ከዛሬ ግንቦት 21 ቀን 2018 ዓ.ም (May 29, 2026) ጀምሮ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ሆኗል።
በብሔራዊ ባንክ መመሪያ (አንቀጽ 2.4) ላይ በተቀመጠው ትርጓሜ መሰረት እንዲሁም የኢኮኖሚ ባለሞያዎች ትርጉም መሰረት "ፍራንኮ ቫሉታ" ማለት አንድ አስመጪ ዕቃዎችን ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት የሚያስፈልገውን የውጭ ምንዛሬ (ለምሳሌ ዶላር ወይም ዩሮ) ከሀገር ውስጥ ባንኮች ሳይጠይቅ፣ በራሱ የውጭ ምንዛሬ ምንጭ ዕቃዎችን ወደ ሀገር የሚያስገባበት አሠራር ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
ግንቦት 21 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
ቤቱ ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
10. በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየው የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣንን አደረጃጀት፤ ስልጣንና ተግባር ለመወሰን የቀረበ ማሻሻያ ረቂቅ ደንብ ላይ ነው፡፡ ባለስልጣኑ በህግ የተሰጠውን ተግባርና ሃላፊነት በብቃት ለመወጣት እንዲያስችለው ማሻሻያ ረቂቅ ደንቡ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በቀረበው ረቂቅ ደንብ ላይ በሰፊው ከተወያየበት በኋላ ግብአቶችን በማከል ደንቡ በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
11. ከዚያም ምክር ቤቱ የተወያየው በህግ የሰውነት መብት የተሰጣቸው አካላት ተጠቃሚ የሚሆኑ ባለቤቶችን መረጃ ግልጸኝነት ለመደንገግ የቀረበ ረቂቅ ደንብ ላይ ነው፡፡ በወንጀል ድርጊት የተገኘ ገንዘብ ወይም ንብረት ሕጋዊ አስመስሎ ማቅረብንና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ በአግባቡ ለማስፈጸም እንዲያስችል ረቂቅ ደንቡ ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በቀረበው ረቂቅ ደንብ ላይ በሰፊው ከተወያየበት በኋላ ግብአቶችን በማከል ደንቡ በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
12. ሌላው ምክር ቤቱ የተወያየው የምግብ ስርዓት እና ስርዓተ ምግብ ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ ከሥርዓተ ምግብ መዛባት ጋር የተያያዙ በሽታዎች በጤና፣ በትምህርት፣ በአካባቢያዊ፣ በምርታማነትና በማህበራዊ መስተጋብር እና በሀገር ኢኮኖሚ ላይ የሚያሳድሩትን አሉታዊ ተጽእኖ ለመቀነስና ለማጥፋት የሚያስችሉ ተግባራትን ለማከናወን፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ ይህን ስራ የሚያስተባብር አደረጃጀት ለመፍጠር፤ ሀብት በዘላቂነት ለመመደብና የማህበረሰቡን ተሳትፎ ለማሳደግ፣ ሀገራችን የገባቻቸውን አለም አቀፍ ስምምነቶችና የተቀመጡ የምግብ ስርዓትና ሥርዓተ ምግብ ግቦችን ለማሳካት የህግ ማዕቀፍ ሆኖ እንዲያገለግል ረቂቅ አዋጁ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል ወደ ሀዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
13. በመጨረሻም ምክር ቤቱ የተወያየው ለራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ ከመንግስት የሚሰጥ የበጀት ድጋፍ አፈጻጸምን ለመደንገግ በቀረበ ረቂቅ ደንብ ላይ ነው፡፡ ለራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ ከመንግስት የሚሰጥ የበጀት ድጋፍ በታወቀ ጥቅል የበጀት ድጋፍ ስርዓት ላይ የተመሰረተ ለማድረግ፣ የፋይናንስ ተጠያቂነት፣ ፍትሃዊነት እና ውጤታማነትን ለማረጋገጥ፣ የራስን ወጪ በራስ የመሸፈን ድርሻን ከጊዜ ወደ ጊዜ ለማሳደግ፣ በተቋማቱ መካከል ተመጣጣኝ የመማር-ማስተማር፣ የአገልግሎት ጥራት እና ፍትሃዊነትን ባረጋገጠ ሁኔታ ሀላፊነት የተሞላበት ስራዎችን እንዲያከናውኑ ለማስቻል ረቂቅ ደንቡ ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ ደንቡ ላይ በሰፊው ከተወያየበት በኋላ ግብአቶችን በማከል በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምጽ አጽድቆታል፡፡
55ኛ መደበኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ውሳኔዎች
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 55ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ፡፡
1. በቅድሚያ ምክር ቤቱ የተወያየው በሁለት የፋይናንስ ድጋፍና ብድር ስምምነቶች ላይ ነው፡፡ የመጀመሪያው ለአርብቶ አደር ምግብና የኑሮ ዘይቤ ማሻሻያ ፕሮጀክት ማስፈፀሚያ የሚውል ከአፍሪካ ልማት ባንክ የአርባ ስድስት ሚሊዮን ሶስት መቶ ሺህ (46,300,000) የአሜሪካን ዶላር ብድር ስምምነት ነው፡፡ ሁለተኛው ለስድስተኛ ምዕራፍ ልማታዊ ሴፍትኔት ፕሮጀክት ማስፈፀሚያ የሚውል ከዓለም ዓቀፍ የልማት ማህበር የአንድ መቶ አርባ ስድስት ሚሊዮን አንድ መቶ ሺ (146,100,000) ኤስ ዲ አር ብድር ስምምነት ነው፡፡ ምክር ቤቱ ሁለቱም የብድር ስምምነቶች ከአገራችን የብድር አስተዳደር ፖሊሲ ጋር የሚጣጣሙ መሆናቸውን በማረጋገጥ የብድር ስምምነት ማጽደቂያ ረቂቅ አዋጆቹ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፉ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
2. በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየው የፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ ለማሻሻል በቀረበ ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ የታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/2008 ወጥቶ ሲሰራበት የቆየ ቢሆንም ባለፉት አመታት በሀገራችን በርካታ የኢኮኖሚ ለውጦች የተደረጉ በመሆኑ የታክስ አስተዳደር ሥርዓቱን ከዘመናዊ ዓለም አቀፍ ልምዶች ጋር ለማጣጣም፤ የታክስ አለመግባባቶችን በፍትሐዊነት፣ በሰላማዊ መንገድና በቅልጥፍና ለመፍታትና የተጠያቂነትና ግልጸኝነት አሰራር ለማስፈንና የታክስ ሕጎችን በተጠናከረ መልኩ ለማስፈጸም እንዲያስችል ተደርጎ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጁ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል ወደ ሀዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
3. ከዚያም ምክር ቤቱ የተወያየው የግብርና ቢዝነስ ኩባንያ ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ የግብርና ዘርፍን ከተለምዶአዊ አሰራር ወደ ቢዝነስ መር ሥርዓት ለማሸጋር፤ አነስተኛ አምራቾችን የገበያ የመደራደር አቅም ለማሳደግ፣ የእሴት ጭማሪና የኢንዱስትሪ ግብዓት ትስስርን ለመፍጠር፤ የተሻለ አቅም ያላቸው ወደ መካከለኛ አልሚነት የሚደርጉትን ሽግግር በሕግ ለመደገፍ፤ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና የሥራ ዕድል ለመፍጠር የህግ ማዕቀፍ ሆኖ እንዲያገለግል ረቂቅ አዋጁ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል ወደ ሀዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
4. ሌላው ምክር ቤቱ የተወያየበት የኢትዮጵያ የካርበን ገበያ ረቂቅ አዋጅ ነው፡፡ የኢትዮጵያን የካርበን ገበያ ስትራቴጂ ወደ ተግባር ለመለወጥ፣ ለአረንጓዴ ኢንቨስትመንት እና ለቴክኖሎጂ ሽግግር ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር፣ የካርበን ግብይት አሰራሮችንና ሂደቶችን በግልፅ ለመደንገግ፣ በካርቦን ፕሮጀክት አካባቢ በሚኖረው ማህበረሰብና አካባቢው ላይ ጉዳት እንዳይደርስ አሰራሮችን ለመዘርጋት፤ ከካርበን ንግድ የሚገኘው ገቢ በመንግስት፣ በአልሚዎች፣ በአካባቢው ማህበረሰብ እና በባለድርሻ አካላት መካከል በፍትሃዊነት የሚከፋፈልበትን አሰራር ለመዘርጋት እና ኢትዮጵያ የፈረመቻቸውን ዓለም አቀፍ ውሎችና የገባቻቸውን የሙቀት አማቂ ጋዞች ልቀት ቅነሳ ቃል ኪዳኖች ከሌሎች ጋር በትብብር እንድትወጣ የህግ ማዕቀፍ ሆኖ እንዲያገለግል ረቂቅ አዋጁ ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል ወደ ሀዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
5. የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ ረቂቅ አዋጅ ምክር ቤቱ የተወያየበት ሌላው አጀንዳ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ሞያዊ ነፃነትን ለማረጋገጥ፣ የተቆጣጣሪ እና የፈጻሚ አካላትን የቁጥጥር እና የአሠራር ተግባራትን ሚና በግልፅ ለመለየት፣ በሁሉም ኦፊሽያል ስታቲስቲክስ አመንጪዎች መካከል ያለውን ትብብር ለማጠናከር፣ የመረጃ ምስጢራዊነትን ለመጠበቅ፣ የስታቲስቲክስ ውጤቶችን ጥራት ለማሻሻል፣ ተደራሽነታቸውን ለማረጋገጥ እና ሀገራዊ አሠራሮችን ከዓለም አቀፍ የስታቲስቲክስ መርሆዎች እና ደረጃዎች ጋር ለማጣጣም እንዲያስችል ረቂቅ አዋጁ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል ወደ ሀዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
6. አስከትሎም ምክር ቤቱ የተወያየው የኢነርጂ ረቂቅ ፖሊሲ ላይ ነው፡፡ ፖሊሲው ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም፣ ከአሥር አመቱ የልማት ዕቅድ፣ ከአረንጓዴ ኢኮኖሚ ልማት ስትራቴጂ፣ ከምዕተ አመቱ የልማት ግቦች እና ከሌሎች ፖሊሲዎች ጋር ተጣጥሞ የአገራችንን የኢነርጂ ሀብት በአነስተኛ ዋጋ በማልማት ዘላቂ፣ አስተማማኝ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ፣ በዋጋ ተመጣጣኝና ተወዳዳሪ የኢነርጂ አቅርቦት እንዲኖርና የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንዲያስችል ረቂቁ ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በፖሊሲው ላይ በሰፊው ከተወያየበት በኋላ ግብአቶችን በማከል በምክር ቤቱ ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
7. ከዚያም ምክር ቤቱ የተወያየው ብሄራዊ የሴቶች ማብቃት እና የስርዓተ ጾታ እኩልነት ረቂቅ ፖሊሲ ላይ ነው፡፡ ፖሊሲው ለስርአተ ጾታ መዛባት ስር ነቀል የሆኑ ጉዳዮች ላይ በቂ ትኩረት ለመስጠት፣ ጾታን መሰረት ያደረገ ጥቃትን በአግባቡ ለመከላከል እና ጥበቃና ምላሽ ለመስጠት፣ ልዩ ትኩረት ለሚሹ ሴት አካል ጉዳተኞች እና ለተለያዩ ችግሮች ተጋላጭ ለሆኑ ሴቶች ምላሽ ለመስጠት እንዲያስችል ኢትዮጵያ ከተቀበለቻቸው ስርአተ-ጾታን መሰረት ካደረጉ አለም አቀፍና አህጉራዊ ስምምነቶች ጋር በማጣጣም ረቂቁ ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ ፖሊሲው ላይ በሰፊው ከተወያየበት በኋላ ግብአቶችን በማከል በምክር ቤቱ ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
8. ቀጥሎም ምክር ቤቱ የተወያየው የኢንሹራንስ ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ የኢንሹራንስ ገበያውን ተኣማኒነት የሚያጠናክር፣ ፍትሃዊ፣ ደህንነቱ ተረጋገጠ እና የተረጋጋ የኢንሹራንስ ገበያ እንዲኖር የሚያበረታታ፣ የመድን ገቢዎችን እና የመድን አገናኞችን ደንበኞች ጥቅም የሚያስጠብቅ፣ የኢንሹራንስ ገበያውን ለመቆጣጠርና ለመምራት የሚያስችል የህግ ማዕቀፍ ሆኖ እንዲያገለግል ረቂቅ አዋጁ ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል ወደ ሀዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
9. በማስከተል ምክር ቤቱ የተወያየው የኢትዮጵያ የንግድ ረቂቅ ፖሊሲ ላይ ነው፡፡ የሀገር ውስጥና ዓለም አቀፍ የንግድ ስርአትን በአግባቡ ለመምራት፣ በተመረጡ የገበያ ክፍተት ባለባቸው ዘርፎች ክፍተቶችን ለመሙላት የሚደረገውን ጥረት ለማጠናከር፣ የሀገራችንን የወጪ ንግድ በግብርና ምርቶች ያለውን ጥገኝነት በማላቀቅ የወጪ ምርትና አገልግሎት ብዝሃነትና ተወዳዳሪነት ለማሳደግ፣ የምርት ደህንነት መስፈርቶችን ለማውጣት እና ፍትሃዊ የንግድ አሰራርን ለመዘርጋት፣ የአገር ውስጥ ኢንዱስትሪዎች ተወዳዳሪነትን እንዲገነቡ፣ ምርታማነትን እንዲያሳድጉና የአካባቢ አቅምን እንዲያዳብሩ ድጋፎችን በመስጠት በዘርፉ ያሉ ተግዳሮችን ለመፍታት እንዲያስችል ረቂቅ ፖሊሲው ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በፖሊሲው ላይ በሰፊው ከተወያየበት በኋላ ግብአቶችን በማከል በምክር
በታክስ አስተዳደር አዋጅ ማሻሻያ ረቂቅ ላይ ከባለድርሻ አካላት አስተያየት ለማሰባሰብ እና ውይይት ለማድረግ የተደረገ ጥሪ
የታክስ አስተዳደር ሥርዓቱን ይበልጥ ቀልጣፋ፣ ፍትሃዊ እና ከወቅቱ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ጋር የተጣጣመ ለማድረግ ይቻል ዘንድ፤ ነባሩን የታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/2008 ለማሻሻል አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል። በዚህም መሠረት የገንዘብ ሚኒስቴር ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ አዘጋጅቷል።
የሕጉ ረቂቅ ጸድቆ ወደ ሥራ ከመግባቱ በፊት፣ በሕጉ ቀጥተኛ ተገዢ የሆኑ የኅብረተሰብ ክፍሎችንና ባለሙያዎችን ማሳተፍ፣ ግብዓት
መሰብሰብና ግልጽ ውይይት ማድረግ አፈላጊ በመሆኑ፣ የታክስ አስተዳደር አዋጅ ማሻሻያ የሚመለከታችሁ ግብር ከፋዮች፣ የንግዱ ማኅበረሰብ አባላት፣ የሕግና የኢኮኖሚ ባለሙያዎች እንዲሁም ፍላጎት ያላችሁ የኅብረተሰብ ክፍሎች በሙሉ ግንቦት 11 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ጀምሮ ስድስት ኪሎ በሚገኘው የገንዘብ ሚኒስቴር ዋና መሥሪያ ቤት ቅጥር ግቢ፤በአካል በመገኘት አስተያየታችሁን እንድትሰጡ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
በተጨማሪም፣ በረቂቅ አዋጁ ላይ የጽሑፍ አስተያየት መስጠት ለምትፈልጉ አካላት፣ የአዋጁን ዝርዝር የድንጋጌዎች ረቂቅ (በአማርኛ ቅጂ) በገንዘብ ሚኒስቴር ድኅረ-ገጽ ላይ መመልከት የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን፤ ያዘጋጃችሁትን ዝርዝር አስተያየት እስከ ግንቦት 12 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በኢሜይል አድራሻ arega@mofed.gov.et እንድትልኩልን በአክብሮት እንጋብዛለን።
Website link :- https://www.mofed.gov.et/media/filer_public/ea/58/ea58858b-a3c1-4640-88c6-dadac6fe088a/yataakese_asetadaadare_awaaje_maashaashaayaa_amaa
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
