uk
Feedback
Mimoza Youth Academy/ሚሞዛ ዩዝ አካዳሚ

Mimoza Youth Academy/ሚሞዛ ዩዝ አካዳሚ

Відкрити в Telegram

Показати більше
532
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
Немає даних30 день
Архів дописів
#ለጥንቃቄ የተከሰተው ጉንፋን መሰል በሽታ በከፍተኛ ሁኔታ የመሰራጨት ባህሪ ስላለው በመከላከያ መንገዶች ላይ ትኩረት ማድረግ ያስፈልጋል ሲል የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ አሳስቧል። ቢሮው ምን አለ ? - በከተማው በተለይ ከጥቅምት ወር መጀመሪያ ጀምሮ በብዙ ሰዎች ላይ ጉንፋን መሰል በሽታ ተከስቷል። - ይህ ወቅታዊና በየዓመቱ ከቅዝቃዜ ጋር ተያይዞ የሚከሰት ሲሆን፤ በወረርሽኝ መልክ የሚገለጽ አይደለም። - የተከሰተውን የቫይረስ አይነት ለመለየት ከትምህርት ቤቶች፣ ጤና ተቋማት እንዲሁም ከፍተኛ መተላለፊያ በሆኑ ቦታዎች ላይ ከሚገኙ ከ178 ሰዎች ናሙና ተወስዶ ምርመራ ተደርጓል። በዚህም 17 በመቶ በላይ የኢንፍሉዌንዛ ቫይረስ እና 3 በመቶ የሚሆነው ከኮቪድ-19 ቫይረስ ጋር የተገናኘ መሆኑ ተረጋግጧል። - ይህ ህመም በተለይም እድሜያቸው ከ5 ዓመት በታች የሆኑ ህጻናት ላይ የሚከሰት ሲሆን፤ ከመቶ ሰዎች መካከል ሃያ የሚሆኑት ላይ ይስተዋላል። ምልክቶቹ ፦ ° ከፍተኛ ራስ ምታት፣ ° ሳል፣ ° ከአፍንጫ ብዙ ፈሳሽ መውጣት፣ ° ጉሮሮን የማቃጠል ስሜት፣ ° ጡንቻ አካባቢ ህመም፣ ° የድካም እና የምግብ ፍላጎት መቀነስ የመሳሰሉት ናቸው። - ምልክቶቹ ሲታዩ ወደ ህክምና ተቋም በመሄድ እራስን ከከባድ ህመም መከላከል ያስፈልጋል። - በበሽታው የተያዙ ሰዎች አፋቸውን እና አፍንጫቸውን ሳይሸፍኑ ሲያስሉ ወይም ሲያስነጥሱ እንዲሁም ቫይረሱ ያረፈባቸውን ነገሮች ከነኩ በኋላ አፍን፣ አፍንጫ ወይም ዓይንን መንካት ቫይረሱ እንዲሰራጭ የሚያደርጉ መንገዶች ናቸው። የመከለከያ መንገዶች ምንድናቸው ? ▫ትምህርት ቤቶች እንዲሁም ሰው በተሰበሰበበት ቦታዎች የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብል ማድረግ፣ ▫በሕዝብ ማመላለሻ ትራንስፖርት ውስጥ መስኮቶችን መክፈት፣ ▫የእጅን ንፅህና በአግባቡ መጠበቅ ▫በንክኪ ወቅት እጅን በመታጠብ በሽታውን በቀላሉ መከላከል ይቻላል። * በሽታው በከፍተኛ ሁኔታ የመሰራጨት ባህሪ ስላለው በመከላከያ መንገዶች ላይ ትኩረት ማድረግ ያስፈልጋል። በበሽታው የተያዙ ሰዎች ማድረግ ያለባቸው ምንድነው ? በበሽታው የተያዙ ሰዎች ህክምናው ከቤት የሚጀምር ሲሆን ህመሙን ለመከላከል እና ለማስታገስ ፦ ☑ በቂ እረፍት መውሰድ፣ ☑ ፈሳሽና ትኩስ ነገሮች መጠቀም ☑ በአካባቢው በቂ የአየር ዝውውር እንዲኖር ማድረግ ከዚህ በተጨማሪ ተገቢውን ህክምና በማግኘት ስርጭቱ እንዳይስፋፋ ማድረግ ይገባል። #ማሳሰቢያ ፦ በሽታው ከአንድ ሳምንት በላይ የሚቆይ ከሆነ በአቅራቢያው ወደሚገኝ የህክናምና ተቋም በመሄድ አስፈላጊውን አገልግሎትና የጤና ባለሙያዎች ምክረ ሃሳቦች ማግኘት ይገባል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃው ከኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ነው ያገኘው። @tikvahethiopia

ዉድ ወላጆች ከነገ ሀሙስ ጥቅምት 29 ቀን 2016 ጀምሮ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት ሲመጡ ማስክ ለብሰዉ መምጣት ያለባቸዉ መሆኑን እናስታዉቃለን።

ለዉድ ወላጆች ወርሀዊ ክፍያችሁን ወር በገባ ከ1_10 ባለዉ ግዜ ያለመቀጫ እንድትከፍሉ እያሳሰብን 10 ካለፈ መቀጫ የምናስከፍል መሆኑን እናስታዉቃለን። አካዉንት:-አዋሽ ባንክ mi002

አርብ መስከረም 24 ትምህርት የሌለ መሆኑን እናሳውቃለን።

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2016 የትምህርት ዘመን ትምህርት መስከረም 7 /1/2016 ዓ.ም በሁሉም ትምህርት ተቋማት ይጀመራል። የትምህርት ሚኒስቴር የ2016 የትምህርት ዘመን ትምህርት በሀገር አቀፍ ደረጃ መስከረም 14/1/2016 ዓ.ም እንደሚጀመርና ክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች በራሳቸው መርሀ-ግብር ማስጀመር እንደሚችሉ መግለፁ ይታወቃል። ይሁን እንጂ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2016 የትምህርት ዘመን ትምህርት መስከረም 14 /1/2016 ዓ.ም እንደሚጀመር በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች እየተሰራጨ የሚገኘው መረጃ የተሳሳተ መሆኑን እናሳውቃለን።

ትምህርት መስከረም 7 የሚጀምር መሆኑን እናሳዉቃለን

ለዉድ ወላጆች የ8ኛ ክፍል ሚኒስትሪ ካርድ ስለመጣ መጥታችሁ መዉሰድ የምትችሉ መሆኑን እናሳዉቃለን

እንኳን ደስ አላችሁ በ2015 የ6ኛ ክፍል ፈተና የወሰዱ ተማሪዎቻችን 100%ከፍተኛ ዉጤት በማስመዝገብ አልፈዋል Congratulations

ተማሪዎች ውጤታችሁን ሊንኮቹን በመጫን መመልከት ተችላላችሁ https://aa6.ministry.et/#/result

የ2015 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ፡፡ አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 25፣ 2015 (ትምህርት ቢሮ) ከ28 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ እንዲሁም በሀገር አቀፍ ደረጃ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ብቻ የተሰጠው ከተማ አቀፉ የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት በዛሬው እለት ይፋ ሲሆን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ ጉዳዩን አስመልክቶ ለተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች መግለጫ ሰተዋል፡፡ ኃላፊው በመግለጫቸው ዘንድሮ ፈተናውን 73,667 ተማሪዎች መውሰዳቸውን ጠቁመው 50% እና ከዛ በላይ ያስመዘገቡ መደበኛ ተማሪዎች ወደ 7ኛ ክፍል እንዲዘዋወሩ መወሰኑን በመጥቀስ የተለያየ የአካል ጉዳት ላለባቸው ተማሪዎች የማለፊያ ነጥቡ 45% መሆኑንም አስታውቀዋል፡፡

እንኳን ደስ አላችሁ በ2015 የ8ኛ ክፍል ፈተና የወሰዱ ተማሪዎቻችን 100%ከፍተኛ ዉጤት በማስመዝገብ አልፈዋል Congratulations

ውድ ወላጆች የነባር ተማሪዎች ምዝገባ የመጨረሻ ቀን ሰኞ ሐምሌ 17 መሆኑን መሆኑን በአክብሮት እንገልፃለን።

ውድ ወላጆች የነባር ተማሪዎች ምዝገባ እስከ ሐምሌ 15 ብቻ መሆኑን እያሳወቅን አርፍዶ ለሚመጣ ወላጅ ሃላፊነቱን የማንወስድ መሆኑን በአክብሮት እንገልፃለን።