HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
Відкрити в Telegram
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
Показати більше2 279
Підписники
Немає даних24 години
+57 днів
+3230 день
Архів дописів
ሰይጣን አራት ምርጫዎች ያቀርብልሃል ጠንቋይ ሆነው ዝክር የሚዘክሩ የጥሎሽ አመጣጥ ከመጽሐፍ ቅዱስ #ethiopia #orthodox #sibket 😰😭🙄🙏
https://youtu.be/F_7ng7IDLUk
የሴተኛ አዳሪዎቹ ጥብቅ መልእክት ለዕውቀትና ለትምህርት ተብሎ የገባ የአብሾ መንፈስ ቀዳር ለመጠመቅ የሚያበቁ ኃጢአቶች #ethiopia 🙏🙏
https://youtu.be/1Nak3_SoA90
ትክክለኛ አምልኮት እንዲህ ነው አደራ ልጆቻችሁን ጠብቁ የዕድል መተት በልጅነት ሲዋረሰን #በማለዳ_ንቁ_2024 #ethiopia #sibket #eotc
https://youtu.be/Y4wzxUJ8Hec
◈ አስተርእዮ 🌹 ሞት ለሚሞት ይገባል የማርያም ሞት ግን ለሁሉ ይደንቃል።
"ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የአፅብ ለኩሉ"
እንኳን ለ 2016 ዓ.ም #አስተርእዮ ማርያም በዓል አደረሳችሁ!! እንኳን ለወለላይቱ እመቤት ለድንግል ማርያም በዓለ እረፍት አደረሳችሁ!
ወዳጆቼ ነገ የእመቤታችን ታላቅ የዓመት በረከት ነውና እንደምንም በርትታችሁ ውዳሴ ማርያም፣ መልክአ ማርያም እና አርጋኖንን ጸልዩ። ካልቻላችሁ ከሦስቱ አንዱን ሳትጸልዩ እንዳትውሉ አደራ!
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
◈ ደግ መሆን ሁለት መሥፈርት አለው፡፡ አንደኛ ደግ ነገር ማድረግ፥ ሁለተኛ ደግ ያልሆነውን አለማድረግ የሚባሉ ሁለት መሥፈርቶች አሉ፡፡ ደግ ነገር የሚያደርግ ሰው ክፉውንም የሚያደርግ ከሆነ ደግ አይባልም፡፡ ክፉውንም ደጉንም የማያደርግ ሰው ደግነትን አልኖራትም፡፡ መብትም እንደዚሁ ሁለት መሥፈርት አለው፡፡ አንደኛ የራስን ፈቃድ መፈጸም፥ ሁለተኛ የሌሎችን ፈቃድ አለመንካት፡፡ (ለምሳሌ በዲሞክራሲው ርዕዯት ሁሉም ሰው ያለመታሰር መብት አለው፤ የሌላው ሰው ያለመታሰር መብት ከጣሰ ግን መብቱ ይገፈፋል)
◈ በዚህም መሠረት እውነተኛ የእግዚአብሔር ልጅ መሆን ሁለት መሥፈርቶችን አሟልቶ መያዝ ይኖርበታል፡፡ አንደኛ ራሱን ከአባቱ ፈቃድ አለመለየት፥ ሁለተኛ ወንድም እህቶቹን ሁሉ ከአባቱ አለመለየት፤ እንዳይለዩ መጠበቅ፤ ከወጡም መመለስ፡፡ እነዚህን ሁለቱንም ኩታ ገጠም አድርጎ ማንነቱን በማይገነባ ቤተመቅደስ ላይ እግዚአብሔር አያድርበትም ይላል መጽሐፍ ቅዱስ፡፡ "የእግዚአብሔር ልጆችና የዲያብሎስ ልጆች በዚህ የተገለጡ ናቸው፤ ጽድቅን የማያደርግና ወንድሙን የማይወድ ሁሉ ከእግዚአብሔር አይደለም።" (1ኛ የዮሐንስ መልእክት 3፥10)
◈ ሰው ጽድቅን ሁሉ ፈጽሞ አንድ ሰውን እንኳ ባይወድ (ቢያማ፣ ቢሰድብ፣ ቢገፋ፣ ቢጥል፣ ቢያጎሳቁል፣ ቢቀማ፣ ቢፈርድ፣ ቢከለክል፣ ቢነጥቅ፣...) ሰውየው ከክፉው መንፈስ ጋር ነው፡፡ ጽድቅን በሚችለው እያደረገ ሁሉንም ሰው ከአንጀቱ የወደደ እርሱ ከተቀደሰው መንፈስ ነው፡፡ (ዐሥርቱ ትእዛዛት ስለ እግዚአብሔርና ስለ ሰው ለምን እንደሆኑ ልብ ይሏል! "እግዚአብሔርንም የሚወድ ወንድሙን ደግሞ እንዲወድ ይህች ትእዛዝ ከእርሱ አለችን።" (1ኛ የዮሐንስ መልእክት 4፥21))
◈ አጠገብ ያለን ቤተሰብ አሊያ ወዳጅ መውደድ በእግዚአብሔር ዘንድ ያለቺውን የባሕሪይ ፍቅር አትወክልም፡፡ እንስሳትም እንዲሁ ያደርጋሉና፡፡ ሰው ግን የተፈጥሮ ገጽታው ፍቅር ነውና፤ አባቶችን ሁሉ እንደ አባቱ፣ እናቶችን ሁሉ እንደ እናቱ፣ ወንድሞችን ሁሉ እንደ ወንድሙ፣ እህቶችን ሁሉ እንደ እህቱ ሲወድ በእርግጥም እርሱ የአምላክ ምሳሌ ስለመሆኑ ያስረግጣል፡፡ (ክርስቲያን አብን፣ ወልድንና መንፈስ ቅዱስን የመሰለበት ልጅነቱ የሚተረጎመው ሌሎችን በመወደዱ ፍቅር ውስጥ ነው፡፡ አብ በራሱ አካል ለራሱ አሳቢ ሆኖ ሳለ፥ ለወልድና ለመንፈስ ቅዱስም አሳባቸው እንደሆነ፤ ክርስቲያንም ለራሱና ለወገኑ ሁሉ ያስባል፡፡ ወልድ በራሱ አካል ለራሱ ተናጋሪ ሆኖ ሳለ፥ ለአብና ለመንፈስ ቅዱስም ቃላቸው እንደሆነ፤ ክርስቲያንም ለራሱና ለወገኑ ሁሉ ድምፅ ይሆናል፡፡ መንፈስ ቅዱስ በራሱ አካል ለራሱ እስትንፋስ ሆኖ ሳለ፥ ለአብና ለወልድም ሕይወታቸው እንደሆነ፤ ክርስቲያንም ለራሱና ለወገን ሁሉ ሕይወት ይኖራል፡፡)
◈ እግዚአብሔር ሕዝብን ሁሉ እንደ ግለሰብ፥ ግለሰብን ሁሉ እንደ ሕዝብ የወደደበት ፍጹም ፍቅሩ በልባችን ማኅደር ሳይታተም፤ መርጠን የምንወድና መርጠን የምንጠላ ከሆን የሃይማኖት መሠረታዊ ሕጎች ከውስጣችን ተንደውብናል ማለት ነው፡፡
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
"ድንጋይ የጨበጡ ፈራጅ እጆች"
ይህ ልጅ ካጭበረበረ በንሰኃ እና ፍትህ ያልፋል። የውሸት ከተወራበትም በረከት አፋሽ ይሆናል። ወንጀል ከሰራም ሀገር ውስጥ ነው ተይዞ ለፍርድ ማቅረብ ብዙም የሚከብድ ሥራ አይደለም። ለዛውም ተሳዳጅ በሆነበት በእዚህ ዘመን። ቤተሰቦቼ አድርጎታል አላደረገም የሚለውን ለሰይጣን፣ ለእግዚአብሔር ለከሳሾቹ እና ለእርሱ እንተው።
ነገር ግን በእዚህ የጥፋት ርዕስ ላይ የሚነሳው ስም ልጅ ቢኒ ሆኖ ቤተክርስቲያንን መምታት የፈለጉ ምንዱባዮች ከእዚህም ከእዛም ጉዳዩን እየለጠጡ በመርዝ ምላሳቸው አገልግሎት እና አገልጋዮችን ሊናደፉ እየዳዱ ነው።
የሚገርመው በልጁ ምክንያት ብሔሩ፣ እምነቱ እንደ ማጣቀሻ እየተነሳ እየተብጠለጠለ ነው። አንዳንድ ቤተክርስቲያንን አምርረው የሚጠሉ ነፍሳት ስለቤተክትስቲያን የወገኑ ይመስል የቁራ ጩኸት እየጮኹ ነው።
እንዴት የቆሸሹ ሰዎች በቤተክርስቲያን አገልጋይ ስም ይገናሉ ሲሉ የእግዚአብሔር አማካሪ ካልሆን እያሉ ነው። ወዳጄ አስተውል....ነፍሰ ገዳዩን ሙሴ እግዚአብሔር ምልክት አድርጎት እንደተጠቀመው አላነበብክም ወይ?
ለፍትወተ ሥጋው ምኞት ኦሪዮንን አስገድሎ ሚስቱን እቁባት ያደረገው ዳዊት እንደ ልቤ እንደተባለ አልሰማህም ወይ? የእስጢፋኖስ ደምን በእጁ የጨበጠው ጳውሎስ የአለም ብርሃን ተብሎ ሲከብር አላየህም ወይ?
ስለዚህ ንጽሁ በሆነችው ቅድስት ቤተክርስቲያን ዙርያ የተሰበሰብነው የኃጢያት እድፍ ያጦቀረን ነን። የምንነጻው በእርሷ ነው እና ከምታነጻን ተነጥለን ከወዴት እንጣል? ህመምተኞች ከመድኃኒታችን ሸሸተን እንዴት መዳን ይቻለናል።
ስለዚህ ወዳጄ....እርሱ አይግለጠን እንጅ ቢገልጠን እንኳን ከእርሱ ከወለደችን እናታችን ፊት ማን ይቆም ዘንድ ኃይል አለው? ዘንድሮ የሚሰቀል ኢየሱስ የለም እንጅ ስቃይ እጆች እንደ አሸን ሞልተዋል። ዘማዊቷም ሴት አልተገለጠችም እንጅ ድንጋይ የጨበጡ ወጋሪ ክንዶች በብዛት ተሰንዝረዋል። ለእዛውም ክርስቲያን ነኝ በሚሉ ሰዎች። ይሄ በጣም የሚያሳዝንና ከባድ የሆነ ጉዳይ ነው።
እግዚአብሔር ይቅር ይበለን በእውነት!!!
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
አቤቱ፥በፍጹም፡ ልቤ፡ አመሰግንኻለኹ፥ የአፌን፡ ነገር፡ ሰምተኸኛልና፤ በመላእክት፡ ፊት፡ እዘምርልኻለኹ።
ወደ፡ ቅዱስ፡ መቅደስኽ፡ እሰግዳለኹ፤ ስለ፡ ምሕረትኽና፡ ስለ፡ እውነትኽ፡ ስምኽንም አመሰግናለኹ፥ በዅሉ፡ ላይ፡ ቅዱስ፡ ስምኽን ከፍ፡ ከፍ፡ አድርገኻልና። በጠራኹኽ፡ ቀን በፍጥነት፡ አድምጠኝ፤ ነፍሴን፡ በኀይልኽ በብዙ፡ አጸናኻት።
አቤቱ፥ የምድር፡ ነገሥታት፡ ዅሉ ያመሰግኑኻል፤ የአፍኽን፡ ቃል፡ ዅሉ ሰምተዋልና። በእግዚአብሔርም፡ መንገድ፡ይዘምራሉ፤ የእግዚአብሔር፡ ክብር፡ ታላቅ ነውና። እግዚአብሔር፡ ከፍ፡ ያለ፡ ነውና፥ ወደ ችግረኛዎችም ይመለከታልና፤ ትዕቢተኛዎችንም፡ ከሩቅ፡ ያውቃል።
በመከራ፡ መካከል፡ እንኳ፡ ብኼድ፥ አንተ ሕያው፡ ታደርገኛለኽ፤ በጠላቶቼ፡ ቍጣ፡ ላይ፡እጆቼን፡ ትዘረጋለኽ፥ ቀኝኽም፡ ታድነኛለች።
እግዚአብሔር፡ ብድራትን ይመልስልኛል፤ አቤቱ፥ ምሕረትኽ፡ ለዘለዓለም፡ ነው፤ አቤቱ፥ የእጅኽን፡ ሥራ፡ ቸል፡ አትበል።
መዝሙር (137፡ (138))
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
"ቤተሰቦቼ ዛሬ በጣም ደስ ብሎኛል። እግዚአብሔር የልጅ አባት አድርጎኛልና። በትላንትናው ዕለት በ 17 በቅዱስ እስጥፋኖስ እና በሰማዕቱ በቅዱስ ጊዮርጊስ ዋዜማ ቀን እግዚአብሔር ሥራውን ሠራልኝ። ተመስገን ነው በእውነት። ቤተሰቦቼ እግዚአብሔርን አመስግኑልኝ ሁላችሁም። 🙏🙏
አምላከ ቅዱስ እስጥፋኖስ፣ አምላከ ቅዱስ ጊዮርጊስ የተመሰገነ ይሁን። 🙏
መንፈሳዊ ሕይወት የምለካው መከራ ሲመጣ ነው || የቅዱስ ሚካኤልን ረድኤት ለማግኘት ይሄን አድርጉ #በማለዳ_ንቁ_2024 #ethiopia #orthodox 🙄😰
https://youtu.be/FTObLRVaaoE
አጋንንት መቋቋም የማይችሉት ከባዱ ጸሎት || የአርጋኖን ጸሎት ተጀምሮ ሲቋረጥ ሰይጣን ይመታናል? አርጋኖን ተበልቶ ይጸለያል? ጸሎቱ ከተጀመረ አይቋረጥም? 🙄🙏 https://youtu.be/CZHSKSO5HsI
«ጸሎት››
** የሞት ጣር ያዘኝ፤ የዓመፅ ፈሳሽም አስፈራኝ፤ የሲኦል ጣር ከበበኝ፤ የሞት ወጥመድ ደረሰብኝ። በጨነቀኝ ጊዜ እግዚአብሔርን ጠራሁት፥ ወደ አምላኬም ጮኽሁ፤ ከመቅደሱም ቃሌን ሰማኝ፥ ጩኸቴም በፊቱ ወደ ጆሮው ገባ። (መጽሐፈ ሳሙኤል ካል 22:5-7)
** የችግረኛን ችግር አልናቀምና፥ ቸልም አላለምና፤ ፊቱንም ከእኔ አልሰወረምና፥ ነገር ግን ወደ እርሱ በጮኽሁ ጊዜ ሰማኝ። (መዝሙረ ዳዊት 22:24)
** (ቆፍ)። ተነሺ፥ በሌሊት በመጀመሪያ ክፍል ጩኺ፥ በጌታም ፊት ልብሽን እንደ ውኃ አፍስሺ፤ በጐዳና ሁሉ ራስ ላይ በራብ ስለ ደከሙ ስለ ሕፃናትሽ ነፍስ እጆችሽን ወደ እርሱ አንሺ። (Lamentations 2:19)
** (ኖን)። መንገዳችንን እንመርምርና እንፈትን፥ ወደ እግዚአብሔርም እንመለስ። ልባችንን ከእጃችን ጋር በሰማይ ወዳለው ወደ እግዚአብሔር እናንሣ። (Lamentations 3:40, 41)
** እግዚአብሔር በሚገኝበት ጊዜ ፈልጉት፥ ቀርቦም ሳለ ጥሩት፤ (ትንቢተ ኢሳይያስ 55:6)
** እናንተ ትሹኛላችሁ፥ በፍጹም ልባችሁም ከሻችሁኝ ታገኙኛላችሁ። (ትንቢተ ኤርምያስ 29:13)
** ስትጸልዩም እንደ ግብዞች አትሁኑ፤ ለሰው ይታዩ ዘንድ በምኩራብና በመንገድ ማዕዘን ቆመው መጸለይን ይወዳሉና፤ እውነት እላችኋለሁ፥ ዋጋቸውን ተቀብለዋል። (የማቴዎስ ወንጌል 6:5) አንተ ግን ስትጸልይ፥ ወደ እልፍኝህ ግባ መዝጊያህንም ዘግተህ በስውር ላለው አባትህ ጸልይ፤ በስውር የሚያይ አባትህም በግልጥ ይከፍልሃል። አሕዛብም በመናገራቸው ብዛት እንዲሰሙ ይመስላቸዋልና ስትጸልዩ እንደ እነርሱ በከንቱ አትድገሙ። (የማቴዎስ ወንጌል 6:6,7)
** ለምኑ፥ ይሰጣችሁማል፤ ፈልጉ፥ ታገኙማላችሁ፤ መዝጊያን አንኳኩ፥ ይከፈትላችሁማል። (የማቴዎስ ወንጌል 7:7)
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
አጋንንት ሁለት ዓይነት ባሕሪይ አላቸው || በአምልኮት መንገድ የተወለዱ ልጆችና የጸሎት መንገድ || ክርስቶስ ለምን በ30 ዓመቱ ተጠመቀ #ethiopia 🙏🙄🙄 https://youtu.be/AoBU1sc95_o
«ሰው ራሱን ሳያውቅ የሚቀረው ስላልቻለ ብቻ አይደለም፡፡ ራሱን ማወቅ ስለማይፈልግም ጭምር ሊሆን ይችላል፡፡ ምክንያቱም ‹ራስን ማወቅ› ይዞ የሚያመጣው ጊዜያዊ ሕመም ወይም ትንሽ ስቃይ አለ፡፡ ወደ ራሳችን መመልከት ስንጀምር የማንፈልገውን ‹‹እኛነት›› በውስጣችን ልናገኘው እንችላለን፡፡ በዚህም መረበሽ፣ መቆጨት፣ ኃፍረት ይሰማን ይሆናል፡፡ ነገር ግን ከዚህ ስሜት ለማምለጥ ብለን ወደ ቅዠታዊ ዓለም ይሄድ ዘንድ ለራሳችን ልንፈቅድለት አይገባም፡፡ ለእኛ ከማንም በላይ ጠላት የሚሆንብን ይህ በውስጣችን የተደበቀውና ማወቅ የማንፈልገው ‹‹ስውር እኛነታችን›› ነው፡፡ ስለዚህም በጊዜ ራስን መርምሮ አፋጣኝ መልስ መስጠት ያስፈልጋል፡፡»
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
ስንፈተ ሩካቤ እና የሐበሻ መድኃኒት ጣጣው || ስንፈተ ሩካቤ በሳይኮሎጂ ውጤት አለው? ስንፈተ ሩካቤ ከምን ይመጣል? መፍትሔውስ ምንድነው? #ethiopia 😰🙄 https://youtu.be/MRMajH_5-5E
"መነኩሴ ሆይ!"
በእግዚአብሔር ዘንድ ከፍ ከፍ ትል ዘንድ መደላደልን መቀማጠልን ተው ለመነኩሴ አልታዘዘምና።
** ልብህን ፀጥ ማድረግ ባይቻልህ አንደበትህን ፀጥ ማድረግ ይቻልሃል፤ በጎ ምግባርን ክብርን ገንዘብ ታደርግ ዘንድ ከብዙ ሰዎች ጋር መኖርን ተው። ኃጢአት አብዝቶ ከሚመገብ ሆድ ይገኛልና። ቂመኛ ሰው ሥጋ የለበሰ ሰይጣን ነው።
ከሰይጣን ይልቅ ልማድህን ፍራ። መነኩሴ ከዚህ ዓለም በሞት ካልተለየ በቀር ፆር አይጠፋለትምና ትጋ። የምንኩስና ፍጹም ሥራ ራስን መንቀፍ ነው። ቁጡ ሰው ሙት ቢያስነሳ አትመኑት ከፀጋ ይደርሳል ጣዕም ይቀምሳል አትበሉት ሠርቶ ሠርቶ የተቆጣ ዕለት ያፈርሰዋልና። የሰይጣን ሽመቃው ከገዳም ማውጣት ነውና በበአትህ ጽና።
ውዳሴ ከንቱን ሽሽ ውዳሴ ከንቱ ምቀኝነትን፣ ፉክክርን፣ ተንኮልን፣ እኔ ያልኩት ይሁን ብሎ በነገር ማሸነፍን፣ መዳራትን፣ ቂም በቀልን፣ ሐሰትን፣ አጥብቆ ድፍረትን ወዘተ ... ሁሉ ፆር ያመጣል ተንኮሉ የበዛ ሰይጣን በውዳሴ ከንቱ ይጥላል።
መነኩሴ ሆይ! ነጭ ሐር ሳይሆን ትህትናን ልበስ። ሱባኤህን በትዕግስትና በአርምሞ ያዝ። ይበድሉህ አትበድል፣ ይክሰሱህ አትክሰስ፣ ይምቱህ አትምታ፣ ክፉውን ሁሉ በሀሰት ያውሩብህ ካንተ ክፉ አይውጣ፤ ያኔ ምድራዊ መልአክ ትሆናለህ።
(ከመጽሐፈ መነኮሳት (የበረሃው ምስጥር))
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
የጋብቻ እርግማንና የመረጋገም ፍዳ || የጣዖት መንፈስ በእኛ ሕይወት || የባሕልና የእምነት ውጊያዎች || የእርግማን መንፈስ || በማለዳ ንቁ 2024 😭😰🙄 https://youtu.be/_-aP8LPYRp0
"እረኞች በግ ሆነው"
--
ሕመሙ፥ ለካ ለቤተ ክርስቲያን በዚህ ልክ ፍቅር አለን? ያሰኘ ነበር። ፍቅራችንን በሕመማችን ለካነው። በእርግጥ፥ ሕመማችን አልተፈወሰም። መለስ እንዳለ ነው። ካልጠብቅነው ቦታ ያልተጠበቀ ድርጊትም ተከትሎታል። እረኞቻችን የበጎችን ጥበቃ የፈለጉበት ከባድ ጊዜ። ቸሩ እረኛ እርሱ ቤቱን እስከ መጨረሻው ያብጀው። ያለፈውን ዓመት፥ ኦርቶዶክሳዊ ኅብረትን የሚያናጋና ክብረ ክህነትን ዝቅ የሚያደርግ አካሔድ ዳግም አያሳየን። የምንናፍቀው እንደ ኖኅ መርከብ ሁሉን እንደ ጠባዩ አቅፋ በምታኖረው ቤተክርስቲያን በአንድ ልብ መኖር ነው። አሁንም ፈጽሞ ይሰብስበን። በግፍ የወደቁት ግፉዓን በረከታቸው ይደርብን። አሜን።
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
ጉድ ነው! ጫትን በኪኒን መልክ ልያቀርቡልን ነው || ሽምግልና ባሕላዊ ነው ወይስ መንፈሳዊ? ሰው መሆን ያቃተው ትውልድ #ethiopia #orthodox 😰😰😭 https://youtu.be/BS1y-8S-6Y4
እኛን ለጸሎት እንዴት እናስተካክል? መናፍስት አብረውን እንድጸልዩ፣ እንድሰግዱ እንዴት እንዘዝ? ፍላጎትና ስሜት በጸሎት ሰዓት #ethiopia #sibket 🙏😭
https://youtu.be/cGQzB2pAQoU
