uk
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

Відкрити в Telegram

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

Показати більше
2 273
Підписники
+424 години
+127 днів
+2530 день
Архів дописів
እረሳት ኢትዮጵያን በእርፈ መስቀል አባ ተክለሃይማኖት ሰባኬ ወንጌል እንኳን ለዳማዊው ዮሐንስ ለጸጋ ዘአብ እና ለእግዚእ ኃረያ ፍሬ ለኢትዮጵያዊው ሐዲስ ሐዋርያ አባ ተክለሃይማኖት በዓለ ልደት በሰላም
እረሳት ኢትዮጵያን በእርፈ መስቀል አባ ተክለሃይማኖት ሰባኬ ወንጌል እንኳን ለዳማዊው ዮሐንስ ለጸጋ ዘአብ እና ለእግዚእ ኃረያ ፍሬ ለኢትዮጵያዊው ሐዲስ ሐዋርያ አባ ተክለሃይማኖት በዓለ ልደት በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ። የአባታችን ምላጃው በረከቱ ከእኛ ጋር ትሁን! #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.facebook.com/hailegebrieltube2021 https://www.tiktok.com/@walkinaddistv

ታሕሳስ ፳፬ /24/ በዚችም ዕለት ሰሎንቅያ በምትባል በምስር አገር ሰይጣንን ያነጋገረው አባ ጳውሊ አረፈ። የዚያችም አገር ሰዎች የሔሮድስ ወገን የሆኑ ክፉዎች ናቸው ለእነርሱም ከውሽባ (ዘማዊ) ቤት
ታሕሳስ ፳፬ /24/ በዚችም ዕለት ሰሎንቅያ በምትባል በምስር አገር ሰይጣንን ያነጋገረው አባ ጳውሊ አረፈ። የዚያችም አገር ሰዎች የሔሮድስ ወገን የሆኑ ክፉዎች ናቸው ለእነርሱም ከውሽባ (ዘማዊ) ቤት ገብተው ያድራሉ አባ ጳውሊም ወደዚያች አገር ደረሰ በሚያደርጉት ነገር አዝኖ ወደ እግዚአብሔር ይጸልይ ጀመር። ጸሎቱንም ሲፈጽም ጥቁር ሰው ከውሽባ ቤት ዕራቁቱን የእሳት ሰይፍ ተሸክሞ መጣ ። አባ ጳውሊም አንተ ማን ነህ ማንንስ ትሻለህ አለው እኔ ሰይጣን ነኝ አንተ ወደርሱ በለመንክ ጊዜ ጌታ ላከኝ አለ ። አባ ጳውሊም ሰዎችን የምታስትበትን ሁሉ ንገረኝ አለው።ሰይጣንም የእግዚአብሔርን ፍቃድ የማያደርጉትን እንደሚያስት ነገረው። በዚያችም ሌሊት ከእግዚአብሔር የታዘዘ መቅሠፍት ወርዶ በውሽባ ቤት ያሉትን አጠፋቸው ከአምስት ወንዶችና ከአምስት ሴቶች በቀር አልተረፉም። አባ ጳውሊም ለምን እንዲህ ታደርጋላችሁ አላቸው ። በየወሩ አንዲት ቀን ወደ ውሽባ ቤት እየገባን ከሚስቶቻችን ጋር ተድላ ደስታ እንድናደርግ አባቶቻችን አዘዙን በሩንም ዘግተን መብራትንም አጥፍተን ከእጃችን የገባችዋን ሴት ይዘን እንተኛለን አሉት። ከዚህም በኃላ አባ ጳውሊ የክብር ባለቤት የሆነ የክርስቶስን ሃይማኖት አስተምሮ የክርስትና ጥምቀትን አጠመቃቸው ሥጋውንና ደሙንም አቀበላቸው ከዚህም በኃላ ወደ በዓቱ ተመልሶ ገድሉን በፈጸመ ጊዜ በመልካም ሽምግልና ወደ እግዚአብሔር ሔደ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከቱ ረድኤቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.facebook.com/hailegebrieltube2021 https://www.tiktok.com/@walkinaddistv

"ታኅሣሥ 22 ቀን የብስራት መታሰቢያ መሆኑን አስመልክቶ አንድ ጥያቄ ነበረኝ። ጌታ የተወለደው ታኅሣሥ 29 ከሆነ፣ በ7 ቀን ልዩነት እንዴት የልደትና የብስራት በዓል ሊከበር ይችላል? (የ9 ወሩ ቆይታስ የት ሄደ?) ደግሞስ መጽሐፍ ቅዱስ መልአኩ የመጣው በስድስተኛው ወር (መጋቢት) ነው እያለ፣ ለምን ዛሬ ታኅሣሥ ላይ እንድናስበው ተደረገ? ይኼንን በቤተክርስቲያን ትምህርት መሠረት ብታብራራልኝ።" ይህ ጥያቄ ብዙዎችን ግራ የሚያጋባ ቢሆንም፣ የቤተክርስቲያን ሥርዓት ግን በጣም ጥልቅና የተሰላ ነው። 1. ትክክለኛው የብስራት ቀን መቼ ነው? በቤተክርስቲያናችን ትምህርት መሠረት ቅዱስ ገብርኤል እመቤታችንን ያበሰረበትና ጌታ የተፀነሰበት ትክክለኛው ቀን መጋቢት 29 ቀን ነው። ከመጋቢት 29 ቀን ጀምረን ብንቆጥር እስከ ታኅሣሥ 29 ቀን ድረስ ያለው ጊዜ 9 ወር ከ 5 ቀን ይሆናል። ይህም አንድ ሕፃን በእናቱ ማኅፀን የሚቆይበት የተሟላ ጊዜ ነው። ስለዚህ "በስድስተኛው ወር" (ሉቃስ 1፡26) የሚለው ቃል መጋቢትን የሚያመለክት መሆኑ ትክክል ነው። (ይህም ኤልሳቤጥ በፀነሰች በስድስተኛው ወር ማለት ነው)። 2. ታዲያ ለምን ታኅሣሥ 22 ቀን "የብስራት ቀን" ተብሎ ይከበራል? ታኅሣሥ 22 ቀን የሚከበረው ብስራት "የታሪክ መታሰቢያ" እንጂ ጌታ የተፀነሰበት ዕለት ሆኖ አይደለም። ለዚህም ምክንያቶቹ የሚከተሉት ናቸው፡ - ሀ. የገና ጾም (የነቢያት ጾም) ሥርዓት፡ ከኅዳር 15 እስከ ታኅሣሥ 29 ያለው የጾም ወቅት "የስብከት ዘመን" ይባላል። በዚህ ወቅት ቤተክርስቲያን የጌታን መምጣት በሥርዓተ ማኅሌቷና በቅዳሴዋ ታስባለች። የልደቱን በዓል በታላቅ ድምቀት ለማክበር ዝግጅት የምታደርግበት ወቅት ነው። - ለ. አራቱ እሑዶች (የአስተምህሮ ቅደም ተከተል)፡ ከታኅሣሥ 1 ጀምሮ ያሉት እሑዶች በቤተክርስቲያን የየራሳቸው ስያሜ አላቸው፡ - ስብከት፡ ነቢያት ስለ ክርስቶስ መምጣት የሰበኩበት። - ብርሃን፡ ክርስቶስ ለዓለም ብርሃን ሆኖ መምጣቱ። - ኖላዊ (እረኛ)፡ እርሱ እውነተኛ እረኛ መሆኑ። - ብስራት፡ የልደቱ በዓል ከመድረሱ ከአንድ ሳምንት በፊት፣ የልደቱን ዜና ያበሰረውን የቅዱስ ገብርኤልን ታሪክ በማንሳት በዓሉን በሃይማኖታዊ ዝግጅት እንድንጠብቅ ይደረጋል። ስለዚህ ታኅሣሥ 22 ቀን የሚከበረው በዓል፣ ልክ እንደ ታኅሣሥ 19 (የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል) እና እንደ ታኅሣሥ 29 (ልደት) በመካከላቸው ያለውን "የብስራት ታሪክ" ለመዘከር የተደረገ ሥርዓት ነው። 3. ለምን በመጋቢት 29 በድምቀት አይከበርም? መጋቢት 29 ቀን ጌታ የተፀነሰበት እውነተኛው ቀን ቢሆንም፣ አብዛኛውን ጊዜ ይህ ቀን በዐቢይ ጾም (በሰሙነ ሕማማት) ወቅት ይውላል። በሰሙነ ሕማማት ደግሞ ትኩረቱ በጌታ መከራና ሞት ላይ ስለሚሆን፣ የብስራቱን ደስታ በታላቅ ድምቀት (በከበሮና በጭብጨባ) ማክበር ከወቅቱ ጋር አይሄድም። ስለዚህ ቤተክርስቲያን፡ መጋቢት 29 ቀን በዐቢይ ጾም ውስጥ ስለምትውል በዝምታና በጸሎት ታስበዋለች። ያንን በዓል ደግሞ በታኅሣሥ ወር በልደት ዋዜማ ላይ "የብስራት ሳምንት" ብላ በድምቀት እንድናስበው ሥርዓት ሠራች። በአጭሩ፡ መጋቢት 29፡ ጌታ የተፀነሰበት ትክክለኛው ቀን (9 ወር ከ 5 ቀን በፊት)። ታኅሣሥ 22፡ ለልደት በዓል ዝግጅት እንዲሆን፣ መልአኩ ያበሰረውን የምስራች የምናስታውስበት የሥርዓት ቀን ነው። በዚህ ምክንያት "በ7 ቀን ውስጥ ወለደች" የሚል ትርጉም አይኖረውም። ይልቁንም "የተበሰረውን ታሪክ አስታውሰን፣ ለልደቱ በዓል በዝግጅት ደረስን" ማለት ነው። ኦርቶዶክሳዊ መልሱ ይህ ነው ወንድሜ። ሌላ ጥያቄ ካለህ ለመመለስ ዝግጁ ነኝ።

ብስራተ ገብርኤል እንኳን አደረሳችሁ! መልአኩም ወደ እርስዋ ገብቶ፦ + #ደስ_ይበልሽ፥ + #ጸጋ_የሞላብሽ_ሆይ፥ + #ጌታ_ከአንቺ_ጋር_ነው፤ + #አንቺ_ከሴቶች_መካከል_የተባረክሽ_ነሽ_አላት። እርስዋ
ብስራተ ገብርኤል እንኳን አደረሳችሁ! መልአኩም ወደ እርስዋ ገብቶ፦ +    #ደስ_ይበልሽ፥ +    #ጸጋ_የሞላብሽ_ሆይ፥ +     #ጌታ_ከአንቺ_ጋር_ነው፤ +     #አንቺ_ከሴቶች_መካከል_የተባረክሽ_ነሽ_አላት። እርስዋም ባየችው ጊዜ ከንግግሩ በጣም ደነገጠችና፦ ይህ እንዴት ያለ ሰላምታ ነው? ብላ አሰበች። 🙏

photo content

❤️ #_የንስሐና_የቄደር_ጥምቀት_የጸበል_ጥምቀት_ጥሪ! ❤️ #_በጎሮ_ኪዳነ_ምህረት_ቤተ_ክርስቲያን! ❤️ #_እሑድ_ታህሳስ_26_ጠዋት_2_ሰዓት! ቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም #_ሼር_በማድረግ_የነፍስ_ግዴታዎትን_ይወጡ! "ጥሩ ውኃንም እረጭባችኃለሁ እናንተም ትጠራላችሁ" ሕዝቅ 36፥25 "የትኛውንም ኃጢአት ብንሠራ ሁሉም ኃጢአተቶች ከንስሐ በታች ናቸው። ከንስሐ በላይ የሆነ ኃጢአት የለም። የእኛ ኃጢአት ከእግዚአብሔር ቸርነት በላይ አይደለም" ❤️ #_ቄደር_ለመጠመቅ_የሚያበቁን_ኃጢአቶች_የትኞቹ_ናቸው? ❤️ #_ቄደር_ለምን_እንጠመቃለን? ❤️ #_ቄደር_በመጠመቃችን_ምን_ጥቅም_እናገኛለን? #_የነፍስ_ጉዳይ_ነውና_ሳትቸኩሉ_በደንብ_አንብቡት! ተወዳጆች ሆይ እሑድ ታህሳስ 26 ጠዋት 2 ሰዓት ከቅዳሴ መልስ በጎሮ ኪዳነ ምህረት ቤተ ክርስቲያን የፆመ ነብያት የመጨረሻው ንስሐ የመስጠት እና የቄደር ጥምቀት እንዲሁም የመደበኛ የጸበል የጥምቀት አገልግሎት ስላለ መጥታችሁ ንስሐ ግቡ ቄደር ተጠመቁ። የጸሎት መርሃ ግብሩ ካለቀ በኃላ ብትጠመቁ ዋጋ የለውም። ምክንያቱም ለምሳሌ የጸሎቱ መርሃ ግብር ላይ አቡነ ዘበሰማያት 41 ጊዜ ካርያላይሶን 41 ጊዜ እግዚኦ መሃረነ ክርስቶስ ወዘተ እንድትጸልዩ ስለሚሰጣችሁ እነዚህን ጸሎቶች ሳትካፈሉ ሰዓት አርፍዳችሁ ብትመጡ መጠመቅ አይቻልም። ስለዚህ የነፍስ ጉዳይ ነውና ሰዓት ይከበር። ❤️ #_ቄደር_ለመጠመቅ_የሚያበቁን_ኃጢአቶች_የትኞቹ_ናቸው? ቀደር ለመጠመቅ የሚያበቁን ኃጢአቶች ለምሳሌ ረቡዕ ብና አርብ የፍስክ ከበላን፣ ውርጃ ከፈጸምን፣ ከሃይማኖታችን ውጪ ካሉ ሰዎች ጋር ሩካቤ ሥጋ ከፈጸምን፣ በልጅነት እና ካደግን በኃላ ግብረ ሰዶም ከፈጸምን፣ ከእንስሳት ጋር ግንኙነት ካደረግን፣ በልጅነት መሬትን ካወሰብን፣ ከሥጋ ዘመድ ጋር ግንኙነት ከፈጸምን፣ ቅዱስ ቁርባን ተቀብለን በዝሙት ከወደቅን፣ በቅዱስ ቁርባን አግብተን ባል በሚስት ላይ ሚስት በባል ላይ ከዘሞተች፣ ኢ- ሩካቤ ከፈጸምን ማለት ከተፈጥሮ ውጪ የሆኑ ግንኙነቶችን ከፈጸምን፣ የአሕዛብን ምግብ ከበላን፣ ኦርቶዶክስ ሆነን ወደ ሌላ እምነት ገብተን ከተመለስን፣ ለዛር ለጨሌ ለአቴቴ ከገበርን፣ የተገበረውን መስዋዕት ከበላን፣ ጠንቋይ ቤት ከሄድን፣ ዛር አንጋሽ ጋር ከሄድን፣ ግለ ወሲብን ከፈጸምን፣ ሴት የወር አበባዋን ሳትጨርስ ግንኙነት ካደረገች፣ ወንድም የወር አበባ ካልጨረሰች ሴት ጋር ግንኙነት ካደረገ፣ ጫት ሲጋራ ከተጠቀምን ወዘተ ቄደር የግድ መጠመቅ አለብን። ወዳጆቼ ልብስ በሳሙና ይታጠባል በመጨረሻ በኦሞ ተዘፍዝፎ ይለቀለቃል። በዚህም ጸዐዳ ይመስላል። ንስሐ ኃጢአታችንን የምናጥብበት ሳሙና ነው። ቄደር ደግሞ ኦሞ ነው ያነጻናል። በተለይ ንስሐ ገብታችሁ ቅዱስ ቁርባን ለመቀበል ያሰባችሁ ቄደር ተጠምቃችሁ ብትቀበሉ መልካም ነው። በንስሐ ያላካተትነው ኃጢአት በቄደር ይነጻልና። እንዲሁም በቄደር ነጽተን ቅዱስ ቁርባን ብንቀበል ይሰምርልናል። ሌላው ንስሐ ለመግባት አስባችሁ የንስሐ እድሉን ያላገኛችሁ እና ንስሐ አባት የሌላችሁ እሑድ ታህሳስ 26 ጠዋት 2 ሰዓት መጥታች በደብሩ ካህናት ንስሐ መግባት ትችላላችሁ። የእናንተን ችግር የሚረዱ በተለይ ለካህናት መናገር የምትጨነቁበትንና የምታፍሩበትን ለምሳሌ ግለ ወሲብንና የወሲብ ፊልምን የተመለከቱ ወዘተ ዘመን አመጣሽ ኃጢአትን የሚረዱ ካህናትን ስላዘጋጀን መጥታችሁ በነፃ ንስሐ ግቡ፣ የኃጢአት ሸክምን በእናታችሁ ቤት አራግፉ። የወለላይቱ እመቤት ልጆች የትኛውንም ኃጢአት ብንሠራ ሁሉም ኃጢአተቶች ከንስሐ በታች ናቸው። ከንስሐ በላይ የሆነ ኃጢአት የለም። የእኛ ኃጢአት ከእግዚአብሔር ቸርነት በላይ አይደለም። የእኛ ኃጢአት የደም ጠብታ ነው። የእግዚአብሔር ቸርነት ደግሞ ውቅያኖስ ነው። ስለዚህ የደም ጠብታ የውቅያኖስን ውሃ እንደማያደፈርስ ሁሉ የትኛውም የእኛ ኃጢአት የእግዚአብሔርን ቸርነት አይበልጥም። ንስሐ ግቡ ቄደር ተጠመቁ። ስለዚህ እሑድ ታህሳስ 26 ከጠዋቱ ሁለት ሰዓት ጎሮ ኪዳነ ምህረት ቤተ ክርስትያን ኑ። ከጠዋቱ ሦስት ሰዓት ጸሎቱ ይጀመራል መጥታችሁ ተጠመቁ። ❤️ #_ማሳሰቢያ :- ሴቶች ቀለል ያለ የመጠመቅያ ልብስ ልበሱ ወይም ያዙ! ❤️ ወንዶችም ቀለል ያለ መጠመቂያ ወይም ቱታ ልበሱ ወይም ያዙ! ❤️ #_የቦታው_አድራሻ_እና_የትራንስፖርት_መምጫው ፦ ❤️ ከየትኛውም አቅጣጫ የምትመጡ ጎሮ አደባባይ ወርዳችሁ፤ ከጎሮ አደባባይ ወደ ኮዬ በሚወስደው አስፖልት ትንሽ ዝቅ እንዳላችሁ አስፓልቱ አጠገብ በስተ ግራ በኩል ቤተ ክርስትያኗ ትገኛለች። ❤️ ከመገናኛ በቀጥታ ጎሮ ብለው ተሳፍራችሁ፣ ጎሮ አደባባይ ወርዳችሁ፣ ወደ ኮዬ በሚወስደው አስፖልት ትንሽ ዝቅ እንዳላችሁ ቤተ ክርስቲያኗ ትገኛለች! ❤️ ከመገናኛ 113 ቁጥር ይዘው ጎሮ አደባባይ ወርደው ትንሽ ዝቅ እንዳሉ ቤተ ክርስቲያኗ ትገኛለች! ❤️ ከፒያሳ ከእሳት አደጋው ዝቅ ብሎ ኮዬ ፈጬ በሚለው 131 ቁጥር ባስ ይዘው ጎሮ ኪዳነ ምህረት ቤተ ክርስቲያኑ ጋር ይወርዳሉ! ❤️ ከሜክሲኮ ሸበሌ ጋር 29 ቁጥር ባስ ይዘው ጎሮ አደባባይ ወርደው ትንሽ ዝቅ እንዳሉ ቤተ ክርስቲያና ትገኛለች! ❤️ ከሲኤምሲ፣ ከአያት፣ ከሰሚት የምትመጡ ጎሮ አደባባይ ወርዳችሁ፣ ወደ ኮዬ በሚወስደው አስፖልት ትንሽ ዝቅ እንዳላችሁ አስፖልቱ ጫፍ ትገኛለች! ❤️ ከቃሊቲ፣ ከቱሉ፣ ዲምቱ፣ ከኮዬ ፈጩ የምትመጡ ጎሮ አደባባይ ሳትደርሱ ወርዳችሁ ቤተ ክርስቲያኗ በስተቀኝ አስፖልቱ ዳር ትገኛለች፡፡ ሰኞ ታህሳስ 20-4-2018 ዓ.ም አዲስ አበባ

«እመቤታችን ሆይ ወገኖቹ ያልነበርን እኛን ወገኖቹ ካደረገን ልጅሽ ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኝልን፤ ጥበቡን፣ ማስተዋሉን፣ ሰላሙን፣ ፍቅሩን፣ በአእምሯችን በልቦናችን ሳይብን አሳድሪብን። 🙏🏾
«እመቤታችን ሆይ ወገኖቹ ያልነበርን እኛን ወገኖቹ ካደረገን ልጅሽ ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኝልን፤ ጥበቡን፣ ማስተዋሉን፣ ሰላሙን፣ ፍቅሩን፣ በአእምሯችን በልቦናችን ሳይብን አሳድሪብን። 🙏🏾 …..አሜን…..🙏🏾 #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.facebook.com/hailegebrieltube2021 https://www.tiktok.com/@walkinaddistv

አዲስ ቪዲዮ ተለቋል ተከታተሉ ውዶቼ!! https://youtu.be/lPyCYTkGQl0

"ሳያቋርጥና በማስተዋል የሚጸልይ ሰው ምንም እንኳን [በአፍአ ሲታይ] ከሰው ኹሉ ይልቅ እጅግ ድኻው ቢኾንም እጅግ ባለጸጋው እርሱ ነው፡፡ የማይጸልይ ሰው ግን ምንም ያኽል በነገሥታት ዙፋን ላይ ቢቀመጥም እንኳን እጅግ ምስኪኑና ድኻው እርሱ ነው!!" ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

ታሕሳስ ፳ /20/ በዚች ቀን ከሌዊ ነገድ ከአሮን ትውልድ የሆነ ነቢይ ሐጌ አረፈ። እርሱም ከዐሥራ ሁለቱ ደቂቀ ነቢያት አንዱ ነው ናቡከደነጾርም የኢየሩሳሌምን ሕዝብ በማረከ ጊዜ የዚህ ጻድቅ ነቢይ
ታሕሳስ ፳ /20/ በዚች ቀን ከሌዊ ነገድ ከአሮን ትውልድ የሆነ ነቢይ ሐጌ አረፈ። እርሱም ከዐሥራ ሁለቱ ደቂቀ ነቢያት አንዱ ነው ናቡከደነጾርም የኢየሩሳሌምን ሕዝብ በማረከ ጊዜ የዚህ ጻድቅ ነቢይ ወላጆች ከእስራኤል ልጆች ጋር ወደ ባቢሎን አገር ተማርከው ሔዱ ዳርዮስ የተባለውም ኵርዝ በነገሠ ጊዜ በሁለተኛው ዘመነ መንግሥቱ ይህ ነቢይ ትንቢት ተናገረ። የእስራኤልን ልጆች ወደ አገራቸው ይገቡ ዘንድ ኵርዝ ዳርዮስ በአሰናበታቸው ጊዜ እነርሱም ከገቡ በኋላ ቤተ መቅደስን ከመሥራት ቸል በአሉ ጊዜ እነርሱ ግን በአማሩና በተሸለሙ ቤቶች ውስጥ ይኖሩ ነበርና እንዲህ አላቸው። «ሁሉን የሚገዛ እግዚአብሔር እንዲህ አለ የኔ ቤት ፈርሷል እናንተ ግን ሁላችሁም ቤታችሁን ታጸናላችሁ አላቸው። ስለዚህ ከምድር በላይ ያለች ሰማይ ዝናም ለዘር ትነሣለች ምድርም ፍሬዋን አትሰጥም አላቸው።» ከሕዝቡም ደጋጎቻቸው ሰምተው እጅግ ፈሩ የእግዚአብሔርንም መመስገኛ ቤት እንደሚገባ መሥራት ጀመሩ። ይህም ጻድቅ ነቢይ ሰባ ዓመት ያህል ኖረ የትንቢቱም ወራት ክብር ይግባውና ክርስቶስ ከመምጣቱ በፊት በአራት መቶ ሠላሳ ዓመት ነው። ከዚህ በኋላም በሰላም በፍርቅ አረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ፦ መጽሐፈ ስንክሳር #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.facebook.com/hailegebrieltube2021 https://www.tiktok.com/@walkinaddistv

ድምጽን ከፍ አድርጎ መጸለይ ከመናፍስት ውጊያ አንጻር ያለው ትልቁ በረከት!! ሰይጣን የሰውን ልብ አያውቅም ግን ወረኛ ያደርገናል!! #ጸሎት #ንስሐ #ንቁ https://youtu.be/Yq1OQvlynjI

«እንኳን ለኃያሉ መልአክ ለቅዱስ ገብርኤል አመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደራሳችሁ!» ...ናቡከደነፆርም መልሶ ‹መልአኩን የላከ ከአምላካቸውም በቀር ማንም አምላክ እንዳያመልኩ ለእርሱም እንዳይሰግዱ
«እንኳን ለኃያሉ መልአክ ለቅዱስ ገብርኤል አመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደራሳችሁ!» ...ናቡከደነፆርም መልሶ ‹መልአኩን የላከ ከአምላካቸውም በቀር ማንም አምላክ እንዳያመልኩ ለእርሱም እንዳይሰግዱ ሰውነታቸውን አሳልፈው የሰጡትን የንጉሡንም ቃል የተላለፉትን በእርሱ የታመኑትን ባሪያዎቹን ያዳነ፣ የሲድራቅና የሚሳቅ የአብደናጎም አምላክ ይባረክ፡፡ እኔም እንደዚህ የሚያድን ሌላ አምላክ የለምና በሲድራቅና በሚሳቅ በአብደናጎም አምላክ ላይ የስድብን ነገር የሚናገር ወገንና ሕዝብ በልዩ ልዩም ቋንቋ የሚናገሩ ይቈረጣሉ፣ ቤቶቻቸውም የጕድፍ መጣያ ይደረጋሉ ብዬ አዝዣለሁ› አለ፡፡ የዚያን ጊዜም ንጉሡ ሲድራቅንና ሚሳቅን አብደናጎንም በባቢሎን አውራጃ ውስጥ ከፍ ከፍ አደረጋቸው፡፡›› ትንቢተ ዳንኤል 3፡1-30፡፡ ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በመልአኩ አማላጅነት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.facebook.com/hailegebrieltube2021 https://www.tiktok.com/@walkinaddistv

አዲስ ጠቃሚ ቪዲዮ ይኼው እንዳያመልጣችሁ ውዶች! ሸር አድርጉ! https://youtu.be/jVAW6IadjkI

"በመከራ ጊዜ ያለህ ብቸኛ መጽናኛ፥ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር መሆኑን ማወቅ ነው።" አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ

ወዳጆች አሁን ይኼንን ማን ያምናል በእውነት አስገራሚው ተዓምርና ገጠመኝ! አንቺ አትፈለግም ተብላ የተናቀችው ልጅ የሆነላትን ተመልከቱ!! #እግዚአብሔር #ጸሎት https://youtu.be/BFNMJj6JILc

ውድ ቤተሰቦቼ ይህንን በቀሲስ ዶ/ር መዝገቡ የተሰጠውን “በነጻ ፈቃድ እና ቅድመ ውሳኔ” ላይ ያጠነጠነ የሦስት ክፍል Lectures እንድታዩት አደራ እላለሁ። እንዲህ ዘመኑን የሚረዳ፣ በምክንያት የሚሞግት፣ ማለቂያ የሌለው የወጣቶችን ጥያቄ ሰምቶ ከመደንገጥ ይልቅ በንባብ እና በጥሩ አስተውሎት በተሞላ ብስለት በሙሉ መተማመን ደስ እያለው የሚወያይ ካህን ማየት እንዴት ልብን ያሞቃል። ካህንስ እንዲህ ነው!!! ሸር አድርጉ ለብዙዎች!! ክፍል 1፡ https://youtu.be/yudM5aX1mV0?si=m1xQrrI4-knNLF41 ክፍል 2፡ https://youtu.be/ZGhBD_orTPA?si=aAzhppVV_qCgeg9v ክፍል 3፡ https://youtu.be/pKBAmL0ugyg?si=T1Vj1HPrKM9lo9W6 #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.facebook.com/hailegebrieltube2021 https://www.tiktok.com/@walkinaddistv

ለመምህር ግርማ ተማሪዎች ብድር አልሰጥም ያለው ባንክና ድብቁ አላማው ሲገለጥ!! ካንተ ከሚወልድ ማሕጸነ ብዘጋ ይሻላል ያላችሁ!! #መወለድ #ንቁ #አጋንንት https://youtu.be/LTVeJkvPUBU

ፈተና መከራ የለም አይኖርም ብዬ አልዋሻችሁም ከዚም በኋላ ይኖራል በብዙ እንፈተናለን... አንድ ነገር ግን እናምናለን ከሁሉም ነገር በላይ የሆነ እግዚአብሔር ግን ከእኛ ጋር ነው ! መልካም ቀን ይሁንላችሁ!!

አዲስ ዝማሬ "ጌታን ተቀበሉ" ዘማሪት ሲስተር ሕይወት ተፈሪ Getan tekebelu zemarit sister hiwot teferi https://youtu.be/v0Qe2PTvzQM?list=RDv0Qe2PTvzQM

መምህር ተስፋዬ የገጠመው አሳዛኝ ነገርና ከዲያቆኑ የማይጠበቅ ድርጊት!! ቶሎ መፈወስና መዳን አልቻልኩም ምን ላድርግ ላላችሁ! #መምህር_ግርማ #መምህር_ተስፋዬ https://youtu.be/-IRfIR-HZYg