HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
Відкрити в Telegram
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
Показати більше2 280
Підписники
+124 години
+117 днів
+3230 день
Архів дописів
ለቅኔ ተማሪዎች የመናፍስት ውጊያ መረጃና ወንድማዊ ምክር!! ደብረ ሊባኖስ አንድነት ገዳም!! Haile Gebriel Reacts19 - በማለዳ ንቁ! https://youtu.be/2-uyHoA9zu8
ተመስገን ጌታዬ እግዚአብሔር ፍቅዶ በትላንትናው እለት ደብረ ሊባኖስ ለሚገኙ የቅኔና አቋቋም ተማሪዎች በጠየቁኝ መሠረት የሚያስፈልጋቸውን መጽሐፍ አድርሻለሁ። በዚህ የበረከት ሥራ የተሳተፋችሁ ቤተሰቦቼ እግዚአብሔር አምላክ ቤታችሁን በበረከት ይሙላላችሁ።
ደብረ ሊባኖስ የነበረኝን ቆይታ በቪዲዮ ያስቀረሁትና ለወንድሞቼ በመናፍስት ውጊያ ዙሪያና አጠቃላይ መሠረታዊ የአምልኮተ እግዚአብሔር አንዳንድ ምክሮችን ለግሻለሁና ዛሬ እለቀዋለሁ በዩቱብ ገጻችን ሁላችሁም ተከታተሉ።
በቀጣይም እንዲህ ሌሎች ተማሪዎች መጽሐፍ የሚፈልጉ ልጆች አሉና በዚህ የበረከት ሥራ መሳተፍ የምትፈልጉ ጻፉልኝ። መልካም ቀን።
እንኳን አደረሳችሁ ውድ ቤተሰቦቼ ለሆሳዕና ለስምንተኛው ሳምንት ለዓብይ ጾም። እግዚአብሔር ሁላችንንም በበረከቱ ይሙላን። ሰላምን ፍቅርን ያድለን። ያታሰርነውን እግዚአብሔር አምላክ ይፍታን። የተዘጋውን ይክፈትልን። በርቱ
#ሰሞኑን_መነጋገሪያ_የነበረው_ዲያቆን_ምህረት_ለእኛ_ያስተላለፈው_መልዕክትና_ምክር!! በሞት አፋፍ ላይ እያለች የUK ደብተራዎች ድጋሚ ጥላወጊ መተት ላኩባት!! https://youtu.be/9oXwrH8A9xQ
መዝሙረ ዳዊት 36(37)
በክፉዎች ላይ አትቅና፥ ዓመፃንም በሚያደርጉ ላይ አትቅና፤ እንደ ሣር ፈጥነው ይደርቃሉና፥ እንደ ለመለመ ቅጠልም ይረግፋሉና። በእግዚአብሔር ታመን፥ መልካምንም አድርግ፥ በምድርም ተቀመጥ፥ ታምነህም ተሰማራ። በእግዚአብሔር ደስ ይበልህ፥ የልብህንም መሻት ይሰጥሃል። መንገድህን ለእግዚአብሔር አደራ ስጥ፥ በእርሱም ታመን፥ እርሱም ያደርግልሃል። ጽድቅህን እንደ ብርሃን። ፍርድህንም እንደ ቀትር ያመጣል። ለእግዚአብሔር ተገዛ ተስፋም አድርገው። መንገድም በቀናችለትና ጥመትን በሚያደርግ ሰው አትቅና። ከቁጣ ራቅ መዓትንም ተው፤ እንዳትበድል አትቅና።
ክፉ አድራጊዎች ይጠፋሉና፤ እግዚአብሔርን ተስፋ የሚያደርጉ ግን እነርሱ ምድርን ይወርሳሉ። ገና ጥቂት፥ ኃጢአተኛም አይኖርም፤ ትፈልገዋለህ ቦታውንም አታገኝም። ገሮች ግን ምድርን ይወርሳሉ፥ በብዙም ሰላም ደስ ይላቸዋል። ኃጢአተኛ ጻድቁን ይመለካከተዋል፥ ጥርሱንም በእርሱ ላይ ያንገጫግጫል። እግዚአብሔር ይሥቅበታል፥ ቀኑ እንደሚደርስ አይቶአልና። ኃጢአተኞች ሰይፋቸውን መዘዙ፥ ቀስታቸውንም ገተሩ ድሀውንና ችግረኛውን ይጥሉ ዘንድ ልበ ቅኖችንም ይወጉ ዘንድ፤ ሰይፋቸው ወደ ልባቸው ይግባ፥ ቀስታቸውም ይሰበር። ለጻድቅ ያለው ጥቂት ከብዙ ከኃጢአተኞች ሀብት ይበልጣል።
የኃጥአን ክንድ ትሰበራለችና፤ እግዚአብሔር ግን ጻድቃንን ይደግፋቸዋል። የንጹሓንን መንገድ እግዚአብሔር ያውቃል፥ ርስታቸውም ለዘላለም ነው፤ በክፉ ዘመንም አያፍሩም በራብ ዘመንም ይጠግባሉ። ኅጥአን ግን ይጠፋሉ፥ የእግዚአብሔር ጠላቶች በከበሩና ከፍ ከፍ ባሉ ጊዜ እንደ ጢስ ይጠፋሉ። ኃጢአተኛ ይበደራል አይከፍልምም፤ ጻድቅ ግን ይራራል ይሰጣልም። እርሱን የሚባርኩት ምድርን ይወርሳሉና፤ የሚረግሙት ግን ይጠፋሉ። የሰው አካሄድ ከእግዚአብሔር ዘንድ ይጸናል፥ መንገዱንም ይወድዳል። ቢወድቅም ለድንጋፄ አይጣልም፥ እግዚአብሔር እጁን ይዞ ይደግፈዋልና።
ጐለመስሁ አረጀሁም፤ ጻድቅ ሲጣል፥ ዘሩም እህል ሲለምን አላየሁም። ሁልጊዜ ይራራል ያበድርማል፥ ዘሩም በበረከት ይኖራል። ከክፉ ሽሽ፥ መልካምንም አድርግ፤ ለዘላለምም ትኖራለህ። እግዚአብሔር ፍርዱን ይወድዳልና፥ ቅዱሳኑንም አይጥላቸውምና፤ ለዘላለምም ይጠብቃቸዋል ለንጹሓንም ይበቀልላቸዋል፤ የኅጥኣን ዘር ግን ይጠፋል። ጻድቃን ምድርን ይወርሳሉ፥ በእርስዋም ለዘላለም ይኖራሉ። የጻድቅ አፍ ጥበብን ያስተምራል፥ አንደበቱም ፍርድን ይናገራል። የአምላኩ ሕግ በልቡ ውስጥ ነው፥ በእርምጃውም አይሰናከልም። ኃጢአተኛ ጻድቁን ይመለከተዋል፥ ሊገድለውም ይወድዳል። እግዚአብሔር ግን በእጁ አይተወውም፥ በተፋረደውም ጊዜ አያሸንፈውም።
እግዚአብሔርን ደጅ ጥና፥ መንገዱንም ጠብቅ፥ ምድርንም ትወርስ ዘንድ ከፍ ከፍ ያደርግሃል፤ ኃጢአተኞችም ሲጠፉ ታያለህ። ኃጥአን ከፍ ከፍ ብሎ እንደ ሊባኖስ ዝግባም ለምልሞ አየሁት። ብመለስ ግን አጣሁት፤ ፈለግሁት ቦታውንም አላገኘሁም። ቅንነትን ጠብቅ፥ ጽድቅንም እይ፤ ለሰላም ሰው ቅሬታ አለውና። በደለኞች በአንድነት ይጠፋሉ። የኃጢአተኞች ቅሬታ ይጠፋል። የጻድቃን መድኃኒታቸው ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው፤ በመከራቸውም ጊዜ መጠጊያቸው እርሱ ነው። እግዚአብሔር ይረዳቸዋል፥ ያድናቸዋልም፥ ከኃጢአተኞችም እጅ ያወጣቸዋል፥ ያድናቸዋል፥ በእርሱ ታምነዋልና።
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
#የበርሜል_ቅዱስ_ጊዮርጊስ_ጸበል_ይዘጋ_መባሉ_ያስደሰታቸው_መምህራንና_ደብተራዎች!! በጸጥታ አካላት የተደፈረችው እህታችን! Haile Gebriel Reacts19 https://youtu.be/Jf-C7F-CK3A
መዝሙረ ዳዊት 34(35)
አቤቱ፥ የሚበድሉኝን በድላቸው፥ የሚዋጉኝንም ተዋጋቸው። ጥሩርና ጋሻ ያዝ፥ እኔንም ለመርዳት ተነሥ። ሰይፍህን ምዘዝ የሚያሳድዱኝንም መንገዳቸውን ዝጋ፤ ነፍሴን። መድኃኒትሽ እኔ ነኝ በላት። ነፍሴን የሚሹ ሁሉ ይፈሩ ይጐስቈሉም፤ ክፉትን በእኔ ላይ የሚያስቡ ይፈሩ ወደ ኋላቸውም ይበሉ። በነፋስ ፊት እንዳለ ትቢያ ይሁኑ፥ የእግዚአብሔርንም መልአክ ያስጨንቃቸው። መንገዳቸው ዳጥና ጨለማ ይሁን፥ የእግዚአብሔርም መልአክ ያሳድዳቸው። በከንቱ ያጠፉኝ ዘንድ ወጥመዳቸውን ሸሽገውብኛልና፥ ነፍሴን በከንቱ አበሳጭተዋልና።
ያላወቁት ወጥመድ ይምጣባቸው፥ የሸሸጉትም ወጥመድ ይያዛቸው፤ በዚህ ወጥመድ ውስጥ ይውደቁ። ነፍሴ ግን በእግዚአብሔር ደስ ይላታል፥ በማዳኑም ሐሴት ታደርጋለች። አጥንቶቼ ሁሉ እንዲህ ይሉሃል። አቤቱ፥ እንደ አንተ ማን ነው? ችግረኛን ከሚቀማው እጅ፥ ችግረኛንና ድሀውንም ከሚነጥቀው እጅ ታድነዋለህ። የክፋት ምስክሮች ተነሡብኝ፥ የማላውቀውንም በእኔ ላይ ተናገሩ። ስለ በጎ ክፋትን መለሱልኝ፥ ነፍሴንም ልጆችን አሳጡአት። እኔስ እነርሱ በታመሙ ጊዜ ማቅ ለበስሁ፥ ነፍሴንም በጾም አደከምኋት፤ ጸሎቴም ወደ ብብቴ ተመለሰ።
ለወዳጄና ለወንድሜ እንደማደርግ አደረግሁ፤ ለእናቱም እንደሚያለቅስ ራሴን ዝቅ ዝቅ አደረግሁ። በእኔ ላይ ተሰበሰቡ ደስም አላቸው፤ ግፈኞች በእኔ ላይ ተሰበሰቡ እኔም አላውቅሁም፤ ቀደዱኝ አልተውኝምም። ፈተኑኝ በሣቅም ዘበቱብኝ፥ ጥርሳቸውንም በእኔ ላይ አንቀጫቅጩ። አቤቱ፥ እስከ መቼ ድረስ ታይልኛለህ? ነፍሴን ከክፉ ሥራቸው ብችነቴንም ከአንበሶች አድናት። አቤቱ፥ በታላቁ ጉባኤ ውስጥ እገዛልሃለሁ፥ በብዙ ሕዝብ መካከልም አመሰግንሃለሁ። በግፍ የሚጠሉኝ በላዬ ደስ አይበላቸው፥ በከንቱ የሚጣሉኝም በዓይናቸው አይጣቀሱብኝ። ለእኔስ ሰላምን ይናገሩኛልና፥ በቍጣም ሽንገላን ይመክራሉ። አፋቸውንም በእኔ ላይ አላቀቁ፤ እሰይ እሰይ፥ ዓይናችን አየው ይላሉ።
አቤቱ፥ አንተ አየኸው፤ ዝም አትበል፤ አቤቱ፥ ከእኔ አትራቅ። አምላኬ ጌታዬም፥ ወደ ፍርዴ ተነሥ፥ አቤቱ፥ ፍርዴን አድምጥ። አቤቱ አምላኬ፥ እንደ ጽድቅህ ፍረድልኝ፥ በላዬም ደስ አይበላቸው። በልባቸው። እሰይ እሰይ፥ ነፍሳችንን ደስ አላት አይበሉ፤ ደግሞም። ዋጥነው አይበሉ። በመከራዬ ደስ የሚላቸው ይፈሩ፥ በአንድነትም ይጐስቍሉ፤ በእኔ ላይ የሚታበዩ እፍረትንና ጕስቍልናን ይልበሱ። ጽድቄን የሚወድዱአት ደስ ይበላቸው ሐሴትንም ያድርጉ፤ የባሪያውን ሰላም የሚወድድ እግዚአብሔር ታላቅ ይሁን ዘወትር ይበሉ። ምላሴ ጽድቅህን ሁልጊዜም ምስጋናህን ይናገራል።
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
መዝሙረ ዳዊት 90(91)
በልዑል መጠጊያ የሚኖር ሁሉን በሚችል አምላክ ጥላ ውስጥ ያድራል።
እግዚአብሔርን። አንተ መታመኛዬ ነህ እለዋለሁ፤ አምላኬና መሸሸጊያዬ ነው፥ በእርሱም እታመናለሁ።
እርሱ ከአዳኝ ወጥመድ ከሚያስደነግጥም ነገር ያድንሃልና።
በላባዎቹ ይጋርድሃል፥ በክንፎቹም በታች ትተማመናለህ፤ እውነት እንደ ጋሻ ይከብብሃል።
ከሌሊት ግርማ፥ በቀን ከሚበርር ፍላጻ፥
በጨለማ ከሚሄድ ክፉ ነገር፥ ከአደጋና ከቀትር ጋኔን አትፈራም።
በአጠገብህ ሺህ በቀኝህም አሥር ሺህ ይወድቃሉ፤ ወደ አንተ ግን አይቀርብም።
በዓይኖችህ ብቻ ትመለከታለህ፥ የኃጥኣንንም ብድራት ታያለህ።
አቤቱ፥ አንተ ተስፋዬ ነህና፤ ልዑልን መጠጊያህ አደረግህ።
ክፉ ነገር ወደ አንተ አይቀርብም፥ መቅሠፍትም ወደ ቤትህ አይገባም።
በመንገድህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ መላእክቱን ስለ አንተ ያዝዛቸዋልና፤
እግርህም በድንጋይ እንዳትሰናከል በእጆቻቸው ያነሡሃል።
በተኵላና በእባብ ላይ ትጫማለህ፤ አንበሳውንና ዘንዶውን ትረግጣለህ።
በእኔ ተማምኖአልና አስጥለዋለሁ፤ ስሜንም አውቆአልና እጋርደዋለሁ።
ይጠራኛል እመልስለትማለሁ፥ በመከራውም ጊዜ ከእርሱ ጋራ እሆናለሁ፤ አድነዋለሁ አከብረውማለሁ።
ረጅምን ዕድሜ አጠግበዋለሁ፥ ማዳኔንም አሳየዋለሁ።
🛑አጋንንት ሌሊት በመኝታችን እንዲህ ይፈትኑናል ይኼንን ጉድ ተመልከቱ!! ጸሎትና ምስጋናን እንደ ሸኪም የሚቆጥሩ ፍልስፍናዎች!! መጸጸት በክርስትና ሕይወታን!! https://youtu.be/QofFWBPRcvQ
ሚያዝያ ፩ /1/
በዚችም ቀን በእስክንድርያ ከተማ በሚገኝ በግብጻውያን መጻሐፍ እንደ ተጻፈ በላዕላይ ግብጽ ያለ ግብጻዊውም እንደጻፈ ለእንበረም ልጅ ለሙሴ ወንድሙ የሆነ የካህኑ አሮን የዕረፍቱ መታሰቢያ ሆነ ይላሉ።
በኦሪቱ መጻሐፍ የተጻፈው ግን እስራኤል ከግብጽ ከወጡ በሁለተኛው ወር በሦስተኛው ቀን አረፈ ይላሉ። ይኸውም ግንቦት ስምንት ነበር የእስራኤል ወሮች በጨረቃ እየተቈጠሩ ዓመቱን ስለሚዞሩ በዚያች ዓመት ሚያዝያ አንድ ቀን ሁኖ ስለተገኘ።
በእኛ ዘንድ ግን የኦሪት ዘኁልቍ መጻሐፍ በአምስተኛው ወር መባቻ ስለሚል መታሰቢያውን ነሐሴ አንድ ቀን እናደርጋለን። ይህም ጻድቅ ሰው የነቢያት አለቃ ለኦሪት ሕግ መምህር ለሆነ ለሙሴ ለነቢዪት ማርያምም ወንድም ነው እነርሱም ከሌዊ ነገድ ናቸው።
እግዚአብሔርም በግብጽ ምድር ብዙ አስደናቂ ተአምራትን በእጆቹ አደረገ። እግዚአብሔርም እርሱንና ልጆቹን መርጦ ካህናቶቹ አድርጎ ከእስራኤል ልጆች ከገንዘባቸውና ከመሥዋዕታቸው ዐሥራትን ሰጣቸው።
የቆሬም ልጆች በጠላትነት በተነሡበት ጊዜ እግዚአብሔር ፈርዶ አጠፋቸው ምድርንም አዘዛት አፍዋንም ከፍታ ዋጠቻቸው።
በበጎ ተጋድሎውና የኦሪትንም ሕግ በመጠበቅ እግዚአብሔርን ከአገለገለ በኋላ ሔደ። ጸሎቱ በረከቱ ከእኛ ጋር ለዘላለሙ ትኑር አሜን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
🛑የልብሷን ጨርቅ እንደ መቁጠሪያ የተጠቀመች ብርቱዋና ጠንካራዋ ሴት!! #ethiopia https://youtu.be/7K9IyGn5hOM
🛑በመንፈሳዊ ውጊያ እንዲህ ከበረታን አጋንንትና ሰይጣን አቅም ያጣሉ!! ልጆቻችሁን ከወደዳችሁ በዚህ መንገድ አሳድጓቸው!! በተለካና በተመጠነ ሕይወት መኖር!! https://youtu.be/SSYoBYw6IU0
🛑መምህር ተስፋዬን ያስለቀሰው ጉዳይ ምንድነው?? ክርስትናን በተግባር የተፈተነች ነፍስ!! https://youtu.be/gGOM80P5rpk
#የግላስኮ_ደብተራዎች_ቀሲስ_ሄኖክ_ወልደማሪያም_ላይ_ያሴሩት_ሴራና_ተንኮል!! ቅድሜ ጋብቻ መልከስከስ በትዳር ላይ ያለው ከባድ ፈተና!! #ethiopia #hdr https://youtu.be/yNboxoeqGu4
መጋቢት ፳፱ /29/በዚችም ዕለት ደግሞ በመድኃኔታችን በከበረችና ልዩ በሆነች ትንሣኤው የዓለም ድኅነት ሆነ። በረቀቀ ጥበቡ ሠላሳ ሦስት ዓመት ያህል በምድር ላይ ሥራውን ሠርቶ በፈጸመ ጊዜ በፈቃዱ ሕማማተ መስቀልን ተቀብሎ ሙቶ ከተቀበረ በኋላ በሦስተኛው በዚች ቀን በሃያ ዘጠኝ ከሙታን ተለይቶ ተነሥቷልና። በዚች ቀን አስቀድሞ ደጅ ለሚጠኑት በዓለም ላሉ ሰዎች ሰው በመሆኑ ድኅነታቸውን አበሠራቸው እንዲሁም ደግሞ በዚች ዕለት ከሲኦል በመዳን ሙታንና ሕያዋን ደስ አላቸው። በዚህም በጌታችንና በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ መነሣት መነሣታቸውን አረጋገጡ። የከበረ ጳውሎስ በመነሣቱ ክርስቶስ የሙታን በኵር ሆነ እንዳለ እርሱ ለሙታን በኵራቸው ነውና። ለእርሱም ክብር ምስጋና ለዘላለሙ ይሁን አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
"ለችግረኛና ለምስኪን የሚያስብ ምስጉን ነው፤ እግዚአብሔር በክፉ ቀን ያድነዋል።" መዝሙር 41:1
ሙዳይ በጎ አድራጎት ማህበር የነበረን ቆይታ እንደ እግዚአብሔር ፍቃድ መልካምና በጎ ሆኖ ከቤተሰቦቻችን፣ ከሕጻናቱ ገር ጥሩ ጊዜ አሳልፈናል። እግዚአብሔር ይመስገን።
እህታችን ወለተ ሚካኤል ለዚህ የበጎ አድራጎት መሳካት ትልቁን ድርሻ ወስዳ እሷ ለበረከት ይሁንልኝ ብላ በላከችው ገንዘብ ይሄው እንዲህ ከሙዳይ ቤተሶች ጋር ምሳ በማብላትና በመጎብኘት አሳልፈናል።
በዚህ የበረከት ሥራ ላይ የተሳተፋችሁ እህቶቼ ቤተሰቦቼ ወንድሞቼም ጭምር እግዚአብሔር አምላካችን ረጅም እድሜን ያድልልን። ሁላችንም በተቻለን አቅም በበጎ ሥራ ላይ መሳተፍን ዘወትር ቅደሚያ የምንሰጠው ጉዳይ ልሆን ይገባል።
እህታችን ወለተ ሚካኤል እግዚአብሔር አምላካችን መሻትሽን፣ ጉድለቶችሽን ይሙላልሽ። ቤትሽ በበረከት ይትረፍረፍ። የሙዳይ ቤተሰቦችን እንዳስደሰትሽና ያለሽን እንዳካፈልሽው እግዚአብሔር በቤትሽ ይገባ፣ ሰላም በቤተሽ ይግባ፣ ፍቅርና ደስታ በቤትሽ ይግባ። በርቺ
መልካም ቀን ለሁላችን 🙏
የዲጄ ሊ አወዛጋቢው ንግግርና የቡዳ ዛር መንፈስ እንዳሉባት ምልክቶቹ!! ጸሎት ስንጸልይ ሐሳባችን እየተበተነ ለተቸገርን!! መንገድ ዳር የወደቀ ትውልድ!! https://youtu.be/dMj1Po9KHic
‹‹ዓለም ቢጠላችሁ፡ አስቀድሞ እኔን እንደጠላኝ ዕወቁ፤ እናንተስ ከዓለም ብትኾኑ፡ ዓለም በወደዳችሁ ነበር፤ ዓለም ወገኖቹን ይወዳልና፤ ነገር ግን፡ እኔ ከዓለም መረጥኋችሁ እንጂ፡ እናንተ ከዓለም አይደላችሁምና፡ ስለዚህ ዓለም ይጠላችኋል። (ዮሐ 15፥ 18-19)
ዓለም የጠላቻችሁ (ማለትም፦ ሹመት፥ ሀብት፥ ዝና፥ የቲፎዞ ብዛት፥ ወዘተ... የሌላችሁ)፥ የክርስቶስ እውነተኛ ተከታዮች የኾናችሁ፥ ከክርስቶስ መስቀል በቀር ሌላ ምርኩዝና መመኪያ የሌላችሁ፡ የእግዚአብሔር ምርጦቹ ኹሉ፤
እንኳን ለመድኃኔዓለም ዓመታዊ ክብረ በዓሉ አደረሳችሁ።
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
ዲያብሎስ ዘወትር በእነዚህ ነገሮች ላይ ከባድ ጥንቃቄ ያደርጋል! 5ቱ ወሳኝ የመንፈሳዊ የሕይወት መሪህዎችና በረከታቸው!! መምህር ግርማ ወንድሙ #ethiopia https://youtu.be/kS19lAuvNCw
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
