HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
Відкрити в Telegram
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
Показати більше2 269
Підписники
+224 години
+177 днів
+2930 день
Архів дописів
አጋንንት የሚፈሯቸው 12ቱ የመጽሐፍ ቅዱስ ኃይለኛ ጥቅሶችና ቃላቶች!! ሁሉም ክርስቲያን ማወቅ የሚገባው የመናፍስት ውጊያ መረጃ! #አጋንንት #ሰይጣን #ጸሎት https://youtu.be/lNDWIH1Gh2s
ይኼንን ትምህርት ሰምታችሁ አሁኑኑ እራሳችሁንና ቤታችሁን ፈትሹ ታተርፋላችሁ!! ቤተክርስቲያን ጎበዝ ዘማሪ ሰፈራችን ደግሞ አስጨፋሪ! 4ቱ ከባባድ ልምምዶችና መርዝ እህታችን የረጨችው!
https://youtu.be/BpwkdyiZ2_Q?si=xpmDp-Ny6BPIXeKp
የመከራና የፈተና ምንጩ አጋንንትና ሰይጣን አይደሉም ነጻ ፍቃዳችን እንጂ!! ማንያዘዋል አስተምሮ ያስመረቃት ያልነቃች አንቂና ስህተቷ! የዲያቆን ሄኖክና መምህር ግርማ ድንቅ ትምህርት! https://youtu.be/Olzy-OD-jcA
ጨነቀኝ ከበደኝ ከጀርባዬ የሆነ ነገር የቆሜ ይመስለኛል ብላችሁ ለምትጨነቁ!! ደጋ ላይ የወደቀው ሰይጣንና አጋንንት! ክፉ መናፍስትና የጥቃት አቅጣጫው ክፍል 4 https://youtu.be/g2rAbYkINP4
የአየር አጋንንት የጥፋት አቅጣጫዎቹና ማወቅ የሚገቡን እውነቶች! ክፉ መናፍስት እና የጥቃት አቅጣጫዎቻቸው ክፍል 3 | 3ቱ የአየር አጋንንት የአያያዝ ስልቶች! https://youtu.be/PG020k9mJsI
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
https://www.youtube.com/@estifo2239
ክፉ መናፍስት እና የጥቃት አቅጣጫዎቻቸው #ክፍል_2 መናፍስት ለምን አጋንንትና ሰይጣን ተብለው ይጠራሉ? መናፍስት እኔን አያጠቁኝም የምትሉ አዳምጡ!!
https://youtu.be/0OOV8_VrHWw
ክፉ መናፍስት እና የጥቃት አቅጣጫዎቻቸው ክፍል 1 | የሁሉም መናፍስት 5ቱ ዋና ዋና ባሕሪያቶች ሰይጣን ለምንድነው እንዲህ አጥብቆ የሚፈትነን? https://youtu.be/v8reiuQE26w?si=ggD0tOLKxJKiRrrQ
የቀሲስ ሄኖክን #መጽሐፍ የጻፈው #የዓይነጥላ #መንፈስና የሆነውን ጉድ ተመልከቱ!! በጸሎታችን ዘወትር ልናካትተው የሚገባ ወሳኝ ነገር!! #አጋንንት #መናፍስት https://youtu.be/3m255yVqX0M?si=eqTpKrRxNs9HJm0W
«የዕለቱን ወንጌል እናንብብ» ነሐሰ 24
(የማቴዎስ ወንጌል 10፡1-42)
«ሥራ ሁለቱን ደቀ መዛሙርቱን ወደ እርሱ ጠርቶ፥ እንዲያወጡአቸው በርኩሳን መናፍስት ላይ ደዌንና ሕማምንም ሁሉ እንዲፈውሱ ሥልጣን ሰጣቸው። የአሥራ ሁለቱም ሐዋርያት ስም ይህ ነው፤ መጀመሪያው ጴጥሮስ የተባለው ስምዖን ወንድሙ እንድርያስም፥ የዘብዴዎስ ልጅ ያዕቆብም ወንድሙ ዮሐንስም፥ ፊልጶስም በርተሎሜዎስም፥ ቶማስም ቀራጩ ማቴዎስም፥ የእልፍዮስ ልጅ ያዕቆብም ታዴዎስም የተባለው ልብድዮስ፥ ቀነናዊውም ስምዖን ደግሞም አሳልፎ የሰጠው የአስቆሮቱ ይሁዳ። እነዚህን አሥራ ሁለቱን ኢየሱስ ላካቸው፥ አዘዛቸውም፥ እንዲህም አለ። በአሕዛብ መንገድ አትሂዱ፥ ወደ ሳምራውያንም ከተማ አትግቡ፤ ይልቅስ የእስራኤል ቤት ወደሚሆኑ ወደ ጠፉት በጎች ሂዱ እንጂ። ሄዳችሁም። መንግሥተ ሰማያት ቀርባለች ብላችሁ ስበኩ። ድውዮችን ፈውሱ፤ ሙታንን አስነሡ፤ ለምጻሞችን አንጹ፤ አጋንንትን አውጡ፤ በከንቱ ተቀበላችሁ፥ በከንቱ ስጡ። ወርቅ ወይም ብር ወይም ናስ በመቀነታችሁ፥ ወይም ለመንገድ ከረጢት ወይም ሁለት እጀ ጠባብ ወይም ጫማ ወይም በትር አታግኙ፤ ለሠራተኛ ምግቡ ይገባዋልና። በምትገቡባትም በማናቸይቱም ከተማ ወይም መንደር፥ በዚያ የሚገባው ማን እንደ ሆነ በጥንቃቄ መርምሩ፤ እስክትወጡም ድረስ በዚያ ተቀመጡ። ወደ ቤትም ስትገቡ ሰላምታ ስጡ፤ ቤቱም የሚገባው ቢሆን ሰላማችሁ ይድረስለት፤ ባይገባው ግን ሰላማችሁ ይመለስላችሁ። ከማይቀበላችሁም ቃላችሁንም ከማይሰሙ ሁሉ፥ ከዚያ ቤት ወይም ከዚያች ከተማ ስትወጡ የእግራችሁን ትቢያ አራግፉ። እውነት እላችኋለሁ፥ በፍርድ ቀን ከዚያች ከተማ ይልቅ ለሰዶምና ለገሞራ አገር ይቀልላቸዋል። እነሆ፥ እኔ እንደ በጎች በተኵላዎች መካከል እልካችኋለሁ፤ ስለዚህ እንደ እባብ ልባሞች እንደ ርግብም የዋሆች ሁኑ። ነገር ግን ወደ ሸንጎ አሳልፈው ይሰጡአችኋል፥ በምኩራቦቻቸውም ይገርፉአችኋልና ከሰዎች ተጠበቁ፤ ለእነርሱና ለአሕዛብም ምስክር እንዲሆን፥ ስለ እኔ ወደ ገዥዎች ወደ ነገሥታትም ትወሰዳላችሁ። አሳልፈውም ሲሰጡአችሁ፥ የምትናገሩት በዚያች ሰዓት ይሰጣችኋልና እንዴት ወይስ ምን እንድትናገሩ አትጨነቁ፤ በእናንተ የሚናገር የአባታችሁ መንፈስ ነው እንጂ፥ የምትናገሩ እናንተ አይደላችሁምና። ወንድምም ወንድሙን፥ አባትም ልጁን ለሞት አሳልፎ ይሰጣል፥ ልጆችም በወላጆቻቸው ላይ ይነሣሉ ይገድሉአቸውማል። በሁሉም ስለ ስሜ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ፤ እስከ መጨረሻ የሚጸና ግን እርሱ ይድናል። በአንዲቱ ከተማም መከራ ቢያሳዩአችሁ ወደ ሌላይቱ ሽሹ፤ እውነት እላችኋለሁና፥ የሰው ልጅ እስኪመጣ ድረስ የእስራኤልን ከተማዎች አትዘልቁም። ደቀ መዝሙር ከመምህሩ፥ ባሪያም ከጌታው አይበልጥም። ደቀ መዝሙር እንደ መምህሩ፥ ባሪያም እንደ ጌታው መሆኑ ይበቃዋል። ባለቤቱን ብዔል ዜቡል ካሉት፥ ቤተሰዎቹንማ እንዴት አብዝተው አይሉአቸው! እንግዲህ አትፍሩአቸው፤ የማይገለጥ የተከደነ፥ የማይታወቅም የተሰወረ ምንም የለምና። በጨለማ የምነግራችሁን በብርሃን ተናገሩ፤ በጆሮም የምትሰሙትን በሰገነት ላይ ስበኩ። ሥጋንም የሚገድሉትን ነፍስን ግን መግደል የማይቻላቸውን አትፍሩ፤ ይልቅስ ነፍስንም ሥጋንም በገሃነም ሊያጠፋ የሚቻለውን ፍሩ። ሁለት ድንቢጦች በአምስት ሳንቲም ይሸጡ የለምን? ከእነርሱም አንዲቱ ያለ አባታችሁ ፈቃድ በምድር ላይ አትወድቅም። የእናንተስ የራሳችሁ ጠጉር ሁሉ እንኳ ተቈጥሮአል። እንግዲህ አትፍሩ ከብዙ ድንቢጦች እናንተ ትበልጣላችሁ። ስለዚህ በሰው ፊት ለሚመሰክርልኝ ሁሉ እኔ ደግሞ በሰማያት ባለው በአባቴ ፊት እመሰክርለታለሁ፤ በሰው ፊትም የሚክደኝን ሁሉ እኔ ደግሞ በሰማያት ባለው በአባቴ ፊት እክደዋለሁ። በምድር ላይ ሰላምን ለማምጣት የመጣሁ አይምሰላችሁ፤ ሰይፍን እንጂ ሰላምን ለማምጣት አልመጣሁም። ሰውን ከአባቱ፥ ሴት ልጅንም ከእናትዋ፥ ምራትንም ከአማትዋ እለያይ ዘንድ መጥቻለሁና፤ ለሰውም ቤተ ሰዎቹ ጠላቶች ይሆኑበታል። ከእኔ ይልቅ አባቱን ወይም እናቱን የሚወድ ለእኔ ሊሆን አይገባውም፤ ከእኔ ይልቅም ወንድ ልጁን ወይም ሴት ልጁን የሚወድ ለእኔ ሊሆን አይገባውም፤ መስቀሉንም የማይዝ በኋላዬም የማይከተለኝ ለእኔ ሊሆን አይገባውም። ነፍሱን የሚያገኝ ያጠፋታል፥ ነፍሱንም ስለ እኔ የሚያጠፋ ያገኛታል። እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል፥ እኔንም የሚቀበል የላከኝን ይቀበላል። ነቢይን በነቢይ ስም የሚቀበል የነቢይን ዋጋ ይወስዳል፥ ጻድቅንም በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ ይወስዳል። ማንም ከእነዚህ ከታናናሾቹ ለአንዱ ቀዝቃዛ ጽዋ ውኃ ብቻ በደቀ መዝሙር ስም የሚያጠጣ፥ እውነት እላችኋለሁ፥ ዋጋው አይጠፋበትም።»
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
https://www.youtube.com/@estifo2239
Do Orthodox Christians Believe Saint Mary Can Save Us? Ethiopian Faith Explained! #orthodox #faith https://youtu.be/nZB0fVC4kH0
«የጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለ ሐይማኖት የዕረፍታቸው መታሰቢያ በዓል ነሐሴ 24»
ወተቀበልዎ መላእክት በስብሐት ወበማሕሌት፣ ወአብዕዎ ኢየሩሳሌም ሰማያዊተ
አብዕዎ ለተክለሃይማኖት፤
አቡነ ተክለ ሃይማኖት የዕረፍታቸው ጊዜ መቃረቡን ባወቁ ጊዜ የመንፈስ ልጆቻቸውን ጠርተው ጌታችን የነገራቸውን ዅሉ አስረድተው አባታዊ ምክርና ተግሣፅ ከሰጧቸው በኋላ ነሐሴ ፳፬ ቀን ከዚህ ዓለም ድካም ዐርፈዋል፡፡
የመንፈስ ልጆቻቸውም ለአንድ ቅዱስ አባትና ካህን በሚገባ ሥርዓት በማኅሌት፣ በዝማሬና በምስጋና ቀብረዋቸዋል፡፡ ጌታችንም ከእመቤታችንና ከቅዱሳን መላእክት ጋር ተገልጾላቸዋል፤ ነፍሳቸውንም ‹‹የጠራሽ፣ ንጽሕት ነፍስ ሆይ ወደ እኔ ነዪ›› ብሎ በክብር ተቀብሏታል፡፡ በመጽሐፈ ገድላቸው እንደ ተጠቀሰው አቡነ ተክለ ሃይማኖት በዚህ ዓለም የኖሩበት ዕድሜ ዘጠና ዘጠኝ ዓመት ከዐሥር ወር ከዐሥር ቀን ነው።
በእናት አባታቸው ቤት ፳፪ ዓመት፤ በከተታ ፫ ዓመት፤ በይፋት ፱ ወር፤ በዳሞት ፲፪ ዓመት፤ በአማራ ፲ ዓመት፤ በሐይቅ ፲ ዓመት፤ በደብረ ዳሞ ፲፪ ዓመት፤ በትግራይና በኢየሩሳሌም ገዳማት ፩ ዓመት፤ ዳዳ በሚባል አገር ፩ ወር፤ በደብረ አስቦ ገዳም ፳፱ ዓመት ከ፲ ቀን መቆየታቸውን መጽሐፈ ገድላቸው ይናገራል (ገ.ተ.ሃ ፶፱፥፲፬-፲፭)፡፡
ወተቀበልዎ መላእክት
በስብሐት ወበማሕሌት፣
ወአብዕዎ ኢየሩሳሌም ሰማያዊተ
አብዕዎ ለተክለሃይማኖት፤
አባ አባ ጸሎትከ ትባርከኒ ወትረ፣
ንበር ምስሌየ በኩሉ መዋዕልየ።
🙏🏾 የጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለ ሐይማኖት ረድኤት በረከታቸው አይለየን 🙏🏾
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
https://www.youtube.com/@estifo2239
ተጠንቀቁ!! ትዳር ወንጌል በሕይወት የሚሰበክበት ቅዱስ መንገድ ነው!! መማርና ማወቅ ወደ ቅዱስ ቁርባን ማደግ እንዲህ ነው!! ለሰይዶ ማርሻል የተሰጠ መልስ!! https://youtu.be/27r6Fx_6r-Y
3 Christological Heresies That Ethiopians Rejected https://youtu.be/0N44-hhRvnk?si=NO7x8ImhsFq7NR-8
What People Don’t Know About Oriental Orthodoxy #ethiopia #orthodoxfaith #christianreligion #faith https://youtu.be/t_LFxBzfgiM
ከአዚምና ከድንዛዜ መንፈስ መላቀቂያ ጊዜ አሁን ነው እባካችሁ ተጠንቀቁ!! 3ቱ የየዋህነት ደረጃዎችና ማወቅ የሚገቡን ነገሮች! ወላጆች ልጆቻችሁን ጠብቁ አደራ! https://youtu.be/u_up6PwXzo0
በጸሎታችን ወቅት ይኼንን ማሰብና መረዳት እጅግ አስፈላጊ ነው!! ኦርቶዶክስን ሳታውቁ ጴንጤ የሆናችሁ ይኼንን በደንብ አዳምጡ!! #ጸሎት #ስግደት #መቁጠሪያ https://youtu.be/pLwbwm8Hgbg
መዝሙረ ዳዊትን በዚህ መንገድ ብትጸልዩ ብዙ ምስጥሮች ይገለጹላችኋል!! የመምህር ግርማ ልብን የሚነካ መልዕክትና ተግሳጽ!! ያልተረዳነው የአጋንንት ፈተና!! https://youtu.be/XEVtmvojKPg
«የዕለቱን ወንጌል እናንብብ» ነሐሴ 20
(የማቴዎስ ወንጌል 22፡23-34)
«በዚያን ቀን። ትንሣኤ ሙታን የለም የሚሉ ሰዱቃውያን ወደ እርሱ ቀረቡ፥ እንዲህም ብለው ጠየቁት። መምህር ሆይ፥ ሙሴ አንድ ሰው ልጅ ሳይወልድ ሲሞት ወንድሙ ሚስቱን አግብቶ ለወንድሙ ዘር ይተካ አለ። ሰባት ወንድማማች በእኛ ዘንድ ነበሩ፤ ፊተኛውም ሚስት አግብቶ ሞተ፥ ዘርም ስለሌለው ሚስቱን ለወንድሙ ተወለት፤ እንዲሁ ደግሞ ሁለተኛው ሦስተኛውም፥ እስከ ሰባተኛው ድረስ። ከሁሉም በኋላ ሴቲቱ ሞተች። ሁሉ አግብተዋታልና በትንሣኤ ቀንስ፥ ከሰባቱ ለማናቸው ሚስት ትሆናለች? ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው። መጻሕፍትንና የእግዚአብሔርን ኃይል አታውቁምና ትስታላችሁ። በትንሣኤስ እንደ እግዚአብሔር መላእክት በሰማይ ይሆናሉ እንጂ አያገቡም አይጋቡምም። ስለ ትንሣኤ ሙታን ግን። እኔ የአብርሃም አምላክ፥ የይስሐቅም አምላክ የያዕቆብም አምላክ ነኝ የሚል ከእግዚአብሔር ዘንድ ወደ እናንተ የተባለውን አላነበባችሁምን? የሕያዋን አምላክ ነው እንጂ የሙታን አይደለም። ሕዝቡም ይህን ሰምተው በትምህርቱ ተገረሙ። ፈሪሳውያንም ሰዱቃውያንን ዝም እንዳሰኛቸው በሰሙ ጊዜ አብረው ተሰበሰቡ።»
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
ነሐሴ ፳ /20/በዚችም ቀን በከሀዲው ንጉሥ ዳኬዎስ ዘመን የነበሩ ከኤፌሶን ሀገር ሰባቱ ደቂቅ አረፉ። እሊህም ሰባቱ ደቂቅ በንጉሥ ዳኬዎስ ዘመን የንጉሱ አገልጋይ ነበሩ። ለጣዖት ባለመስገዳቸው ታሰሩ ንጉሱ ወደ ሌላ ሀገር ሲሔድ ግን ለቀቃቸው። ከዚህም በኋላ እሊህ ቅዱሳን ለረከሱ ጣዖታት እንዳይሰግዱ የጭፍራነት ሥራቸውን ትተው በተራራ ውስጥ ወደአለ ዋሻ ሒደው በዚያ ተሠወሩ። ምግብ ሲያልቅባቸው አንዱ ወደ ከተማ ሔዶ ይገዛ ነበር። እሊህም ቅዱሳን በእግዚአብሔር ትእዛዝ ሦስት መቶ ሰባ ሁለት ዘመናት አንቀላፉ ዳኬዎስም ሙቶ እስከ ቴዎዶስዮስ ብዙ ነገሥታት ነገሡ። ከዚህም በኋላ ከእርሳቸው አንዱ ምግባቸውን ሊገዛ ከዋሻው ወጣ በገበያ ላይም ከነጋዴው ጋር በያዘው ገንዘብ ምክንያት ተጣሉ። በዚህም ምክንያት ወደ ንጉሱና ኤጲስ ቆጶሱ ወሰዱት። በዚያም የሆነውን ሁሉ ተናገር። እውነት መሆኑንም ለማጣራት ወደ ዋሻው ሔዱ። ንጉሡና ኤጲስቆጶሱ ከሕዝቡ ሁሉ ጋር የሆነውን አይተው አደነቁ ምስጉን እግዚአብሔርንም አመሰገኑት ትንሣኤ ሙታን የለም የሚሉትም ይህን ድንቅ ሥራ አይተው ትንሣኤ ሙታን እንዳለ አመኑ። እሊህ ሰባቱ ደቂቅንም በጠየቋቸው ጊዜ ከእርሳቸው የሆነውን ሁሉ ነገሩአቸው። ከዚህም በኋላ ተመልሰው ተኙ። ነፍሳቸውንም በእግዚአብሔር እጅ ሰጡ። ንጉሥም የወርቅ ሣጥን ሠራላቸው በሐር ልብሶችም ገንዘው በመልካም ቦታ አኖሩዋቸው። ከሥጋቸውም ብዙዎች ድንቆችና ተአምራት ተገለጡ። ስማቸውም:- መክሲማኖስ፣ ታሙኪሮስ፣ መርዳዲሞስ፣ ዮሐንስ፣ ቈስጠንጢኖስ፣ አዝሚና ዲዮናስዮ ነው። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
