HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
Відкрити в Telegram
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
Показати більше2 265
Підписники
+124 години
+57 днів
+2230 день
Архів дописів
ጥያቄ 3፡ በምስጢረ ሥላሴ ትምህርት "አባትነት" (ወላዲነት) የአብ ብቻ ባሕርይ ከሆነ፣ "መስረጽ" (መውጣት) የማን ባሕርይ (ግብር) ነው?
ሀ) የወልድ
ለ) የሥላሴ በጋራ
ሐ) የመንፈስ ቅዱስ
መ) የመላእክት
ጥያቄ 2፡ በቤተክርስቲያን አስተምህሮ መሠረት "ነፍስ" ስትፈጠር ከየት ነው የምትገኘው?
ሀ) ቀድማ በሰማይ ትኖርና ወደ ፅንሱ ትገባለች
ለ) በአባትና በእናት ዘር አማካኝነት (Traducianism)
ሐ) በእያንዳንዱ ፅንስ ጊዜ አዲስ ትፈጠራለች
መ) ነፍስና ሥጋ የተለያዩ ፍጥረታት አይደሉም
ጥያቄ 1፡ በቅዱስ ቁርባን ጊዜ "አሚን አሚን አሚን ወአአምን" (አምናለሁ አምናለሁ አምናለሁ) የሚለው የሃይማኖት ምስክርነት በካህኑ የሚነገረው ስንት ምስጢራትን ለመግለጥ ነው?
ሀ) ስለ ሥላሴ ሦስትነት ብቻ
ለ) ስለ ጌታችን መከራና ስቅለት ብቻ
ሐ) ስለ ሥጋ ወደሙ እውነተኛነትና ስለ መለኮትና ትስብእት ተዋሕዶ
መ) ስለ ገነትና ሲኦል መኖር
በዩቱብ ኮሜንት ላይ ለጻፋችሁት ህልምና ጥያቄ የተሰጠ ቀጥተኛ መልስ - ክፍል 3 \\ የሞላ የውሃ ጉድጓድን መሻገር በህልም ምንድነው?? #ህልም #ሕልም #ራዕይ https://youtu.be/-RQGMxZ4vCg
የሰማዕቱ ቅዱስ ቂርቆስ ተወዳጅ መዝሙር ስብስቦች 2026 || Kidus Kirkos Orthodox Mezmur Collections 2026 Nonstop https://youtu.be/7RHh_2Ay7DU
በዩቱብ ኮሜንት ላይ ለጻፋችሁት ህልምና ጥያቄ የተሰጠ ቀጥተኛ መልስ - ክፍል 2 \\ በተደጋጋሚ የሞቱ ሰዎችን በህልም ማየት ትርጉሙ ምንድነው! #ህልም #ሕልም https://youtu.be/3itpplDby5w
በዩቱብ ኮሜንት ላይ ለጻፋችሁት ህልምና ጥያቄ የተሰጠ ቀጥተኛ መልስ - ክፍል 1 \\ መኪና መጥፋት ወይም ጎማ ሲነቀል በህልም ማየት ምንድነው!! ህልምና ፍቺው https://youtu.be/9HbzX4D5bAc
ይኼንን ምልክት በራሳችሁ ላይ ካያችሁ እባካችሁ አሁኑኑ ይኼንን አድርጉ!! ሳትሰግዱ ሳትንበረከኩ በጭራሽ ከቤት አትውጡ!! https://youtu.be/9_PM5gKw3es
ይኼንን መዝሙር ከቤት ከመውጣታችሁ በፍት 7 ጊዜ ከጸለያችሁ ይኼን ያገኛሉ!! መተተኛን መልሶ የሚቀጣ ጸሎት ይኼው!! በቀልን አቁምና ይኼንን መዝሙር ጸልይ!! https://youtu.be/IxRJlSzit8U
6ኛ፡ መዝሙረ ዳዊት የቅዳሜ ጸሎት ክፍል 6 ከቁጥር 121 140 \\ ለአጋንንት እሳት የሆነው የመዝሙረ ዳዊት ጸሎት \\ መዝሙረ ዳዊት የዘወትር ጸሎት https://youtu.be/xBk_cnxLydo
5ኛ፡ መዝሙረ ዳዊት የአርብ ጸሎት ክፍል 5 ከቁጥር 101-120 \\ ለአጋንንት እሳት የሆነው የመዝሙረ ዳዊት ጸሎት \\ መዝሙረ ዳዊት የዘወትር ጸሎት https://youtu.be/vZrSLnK_erQ
በመምህር ግርማና በካድሬው መካከል የተፈጠረው እጅግ አስገራሚው ገጠመኝና ታርክ!! ነፍሰ በላውና ተስፋ አስቆራጩ አሾክሻኪ መንፈስና ሴራው!! #ጾም #ጸሎት https://youtu.be/9H6KHFf1x3U
#የእህታችን_ጥያቄ፡ (መምህር፤ ዕድሜዬ 24 ሲሆን በሕይወቴ እያጋጠሙኝ ስላሉት ውስብስብ መንፈሳዊና ሥጋዊ ፈተናዎች መፍትሔ ፍለጋ ይህንን ጥያቄ አቅርቤያለሁ። እናቴ እኔን ፀንሳ እስከምትወልድ ድረስ በሕመም ትሰቃይ ነበር፤ እኔም እንደተወለድኩ ጀምሮ በሕመም አድጌያለሁ። እናቴ እጅግ ተቆጣጣሪና በሐሳቧ ካልተመራሁ የማትስማማ (Narcissistic) ስትሆን፣ አባቴ ደግሞ ሰዎችን ለገዛ ፍላጎቱ የሚጠቀም (Manipulative) ነው። ይህ የቤተሰብ ድባብ በማንነቴ ላይ ትልቅ ጠባሳ ጥሏል። በዚህም ምክንያት ትምህርቴን አቋርጫለሁ፣ ሥራ አልሰራም፣ እንዲሁም ከወንዶች ጋር ያለኝ ግንኙነት የተቋረጠ ነው። ወንድ ሲቀርበኝ የመኮሳተርና የማግለል (Avoidant) ባሕርይ ይታይብኛል። ባለፈው ዓመት በጸበልና በእመቤታችን ምልጃ ከነበረብኝ የድብርት (Depression)፣ የጭንቀት (Panic attack) እና የተከማቸ የሥነ-ልቦና ስቃይ (PTSD) ተፈውሼ ነበር። ነገር ግን ፈውሱን ካገኘሁ በኋላ እግዚአብሔርን በማመስገንና በጸሎት ከመበርታት ይልቅ፣ መንፈሳዊ ሕይወቴን ችላ በማለት ረሳሁት። አሁን በጸበል ቦታ መስቀል ሆዴንና ጭንቅላቴን ሲነካኝ በውስጤ የሆነ ነገር ይንቀሳቀሳል፤ ያንቀኛል እንጂ አይወጣም። በተጨማሪም ሌሊት ላይ ነጭ አረፋ ያስመልሰኛል፤ ሰውነቴንም ይበላኛል። በዚህም ምክንያት መልኬ ተቀይሯል፣ ሰውነቴም እጅግ ከስቷል። ትልቁ ፈተናዬ "ግብረ አውናን" (Masturbation) ነው። ይህ ፈተና የሚበረታብኝ በተለይ በመንፈሳዊ ሕይወት ለመበርታት ስነሳ፣ ለመቁረብ ስዘጋጅ፣ ስዘንጥ ወይም ደስተኛ ሆኜ በዋልኩባቸው ቀናት ነው። ይህ የዝሙት መንፈስ ከደስታዬና ከመንፈሳዊ ጥንካሬዬ ጋር እየተጋጨ ሰላም አሳጥቶኛል። ንስሐ ገብቼ ወደ ቅዱስ ቍርባን ለመቅረብ ብፈልግም፣ የሰጡኝን ቀኖና ሳልጨርስ በዚሁ ኃጢአት ደግሜ እየወደቅኩ ተቸግሬያለሁ። ለቅዱስ ቍርባን ሳልበቃ በዚህ አዙሪት ውስጥ መቅረቴ እጅግ አስጨንቆኛል። ወንድሜ፤ ከዚህ መንፈሳዊ እስራት የምወጣበትንና የቀኖናዬን ጊዜ በትዕግሥት ጨርሼ ከጌታዬ ሥጋና ደም ጋር የምዋሃድበትን መንገድ በመንፈሳዊ ምክርዎና በጸሎትዎ ይርዱኝ።)
#ኦርቶዶክሳዊ_መልስ! በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ውድ እህቴ ሆይ፤ በመጀመሪያ ያለሽበትን እጅግ ፈታኝና ውስብስብ ሁኔታ በዝርዝር ስለገለጽሽልኝ አመሰግናለሁ። የደረሰብሽ መንፈሳዊና ሥነ-ልቦናዊ ጫና ከባድ ቢሆንም፣ ባለፈው ዓመት ከድብርትና ከጭንቀት በታምራት የፈወሰሽ አምላክ ዛሬም ካንቺ ጋር መሆኑን በፍጹም እንዳትረሺ። የገለጽሽው ሁኔታ በቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ትምህርት "የዝሙት መንፈስ" (ጋኔን) እና "የዓይነ ጥላ" ሴራ መሆኑን በግልጽ ያሳያል። ይህ መንፈስ አንቺ እንድትደሰቺ፣ እንድትዘንጪ፣ ትዳር እንድትመሰርቺና ወደ እግዚአብሔር እንድትቀርቢ አይፈልግም። ለዚህም ነው መንፈሳዊ ጥንካሬ ስታሳይ ወይም ስትደሰቺ በግብረ አውናንና በሕመም የሚፈትንሽ። በርቺ፣ በጭራሽ ተስፋ አትቁረጪ፤ የሚከተሉትን መንፈሳዊ መፍትሔዎች በጥንቃቄ ተግባራዊ አድርጊ፦
፩. የወደቅሽበትን ቦታ አውቀሽ ተነሺ (ምስጋናና ጸሎት)፦ ለፈው ዓመት ድንቅ ፈውስ አግኝተሽ ምስጋናና ጸሎት ማቆምሽ ለጠላት በር ከፍቶለታል። ጌታችን በመጽሐፍ ቅዱስ እንዳስተማረው፣ ጋኔን ከሰው ወጥቶ ሲመለስ ቤቱ ባዶ ሆኖ ካገኘው ሰባት የከፉ መናፍስትን ይዞ ይመጣል (ማቴዎስ ፲፪፥፵፫-፵፭)። ስለዚህ አሁኑኑ "ጌታ ሆይ ስለረዳኸኝ አመሰግንሃለሁ፣ ስለረሳሁህ ይቅር በለኝ" ብለሽ ወደ ጸሎት ተመለሺ።
፪. የግብረ አውናን (ሴራ) መቆራረጥ፦ ይህ መንፈስ አንቺን ከቅዱስ ቍርባን ለማራቅ የሚጠቀምበት መሣሪያ ነው። "ቀኖናዬን ሳልጨርስ እወድቃለሁ" ብለሽ ተስፋ አትቁረጪ። የንስሐ አባትሽ ጋር ሂጂና ሁኔታውን (በተለይ መንፈሳዊ ነገር ስትጀምሪ እንደሚመጣብሽ) በግልጽ ንገሪያቸው። ቆርበሽ መንፈሱን "በእሳት" ካልጠቆለሽው በቀር በራሱ አይለቅሽም። ስለዚህ "ብወድቅም ተነስቼ እቆርባለሁ" ብለሽ ጨክኚ።
፫. ጸበልና የቤተክርስቲያን አገልግሎት፦ ጸበል ስትሄጂ ሆድሽ ላይ የሚንቀሳቀሰውና የሚያንቅሽ ነገር መንፈሱ መውጣት ስላልፈለገ የሚያደርገው ትግል ነው። ነጭ አረፋ ማስመለስሽ የመንፈሱ መውጫ ምልክት ነው። ጸበሉን አታቋርጪ፤ ቢቻል ተረክበሽ (ተከታትለሽ) ተጠመቂ። በየቀኑ ጠዋትና ማታ ጸበል ጠጪ፣ ሰውነትሽን ተቀቢ።
፬. የቤተሰብ ተጽዕኖና ሥነ-ልቦናዊ ጥንካሬ፦ እናቴና አባቴ እንዲህ ናቸው ብለሽ ከመጨነቅ ይልቅ፣ አንቺ የራስሽን ሕይወት በእግዚአብሔር ላይ ለመገንባት ወስኚ። የእናንሽ መቆጣጠርና "ናርሲሲስት" መሆን አጋንንታዊ ተጽዕኖ ሊኖረው ስለሚችል፣ በጸሎትሽ "ከክፉ ነገር ሁሉ ሰውረኝ" ብለሽ ለራስሽ ጸልዪ። ከቤተሰብሽ ጋር ባለሽ ግንኙነት ውስጥ ለራስሽ ክብርና "ወሰን" (Boundary) ይኑርሽ።
=> ለትዳርና ለሰዎች ያለሽ አመለካከት፦ ወንድ ሲቀርብሽ የመኮሳተርሽና የመራቅሽ ምክንያት አንቺ ሳትሆኚ ያ "የዓይነ ጥላ" መንፈስ ነው። "ይህ እኔ አይደለሁም፣ ጠላቴ ነው" ብለሽ በማሰብ ራስሽን አታኩርፊ። ጸጋሽ ሲመለስና መንፈሱ ሲለቅሽ ፈገግታሽና ማህበራዊ ሕይወትሽ ይመለሳል።
=> ተግባራዊ ትእዛዛት፦ የማያቋርጥ ጸሎት፦ በየቀኑ ውዳሴ ማርያም፣ መዝሙር ፺፩ (91) እና መዝሙር ፳፪ (23) ድምፅሽን አውጥተሽ ጸልዪ። ስግደት፦ አቅምሽ በፈቀደ መጠን (ለምሳሌ ፵፩ ጊዜ) በየቀኑ ስገጂ። ስግደት የዝሙትን መንፈስ ያደክማል። ቅዱስ ቍርባን፦ የንስሐ አባትሽን አማክረሽ በቶሎ ለመቁረብ ተዘጋጂ። ጠላት የሚፈራው የክርስቶስን ሥጋና ደም ነው። ራስን መንከባከብ፦ ፀጉርሽና መልክሽ የተቀየረው በጭንቀትና በመንፈሱ ጫና ነው። መንፈሳዊ ፈውስ ስታገኚ ሥጋዊ ውበትሽም አብሮ ይታደሳል። እህቴ ሆይ፤ አትፍሪ! ሰባተኛ ቀን ላይ ያዳነሽ ወላዲተ አምላክ ዛሬም ካንቺ ጋር ናት። እሷን "እናቴ ሆይ አትተዪኝ" ብለሽ ሙጭጭ በይባት። ይህ ፈተና ያልፋል፣ ትምህርትሽንም ስራሽንም ትቀጥያለሽ።
እግዚአብሔር አምላክ በቸርነቱ ይጎብኝሽ፣ ወላዲተ አምላክ በምልጃዋ አትለይሽ። አሜን።
4ኛ፡ መዝሙረ ዳዊት የሐሙስ ጸሎት ክፍል 4 ከቁጥር 81-100 \\ ለአጋንንት እሳት የሆነው የመዝሙረ ዳዊት ጸሎት \\ መዝሙረ ዳዊት የዘወትር ጸሎት https://youtu.be/5T4AONEykvI
3ኛ፡ መዝሙረ ዳዊት የረቡዕ ጸሎት #ክፍል_3 ከቁጥር 61-80 \\ ለአጋንንት እሳት የሆነው የመዝሙረ ዳዊት ጸሎት \\ መዝሙረ ዳዊት የዘወትር ጸሎት https://youtu.be/DI8S9a_cQfk
አንተ የሰው ልጅ ሆይ፦ የሰው ዘመን አልቋል (ሰቆቃው)
አውሬነት እንደ ምንጭ - ከሰው ምድር ፈልቋል፤
ፍቅር እንደ ሠማይ - ከሰው ልጅ እርቋል፤
መተማመን ወድቆ - አንዱ አንዱን ነጥቋል፤
በማስመሰል ውሸት - ሰው ሀገሩን ሰርቋል።
ብዙ ዓይነት ሱስ - ትውልድ ላይ ወድቋል፤
ሰው በዘር ተቧድኖ - በሴራ ሸምቋል።
በአስማትና በሟርት - በመተት ተናንቋል፤
አምላኩን ሲተው - ሰይጣንን ጠይቋል፤
እንደ ባሕር ላይ ሞት - እምነትን ደፋፍቋል፤
ወገን ጠላት ሆኖ - ክህደትን አስፋፍቷል።
ውርደትን ለትውልድ - እርግማን ሰንቋል፤
ውስጡ እያሽሟጠጠ - በማስመሰል ፍቋል።
እምነትና ወጉን - ታሪኩንም ንቋል፤
ጊዜ እስከሚያገኝ - ሴራውን ደብቋል፤
መንፈሳዊውም አባት - ለጥፋት ተጨንቋል፤
ከውስጡ ተንኮል ለብሶ - በአልባሳት ደምቋል።
መኖርም መሞትም - ሁሉንም አሳቋል፤
ለግፍና ሴራ - መንፈሳዊው እረቋል።
ጽድቅ ተነጣጥሎ - እርግማኑ ጸድቋል፤
ጣረ ሞት ኃይሎ - ሁሉን አስጨንቋል፤
አንተ የሰው ልጅ ሆይ - የሠው ዘመን አልቋል። /፪/
ከ መልአከ ኃይል ቀሲስ ኃይለመለኮት ግርማ ወንድሙ
መተት በምስጥር ከተላከባችሁ እነዝህን 6 ወሳኝና አንቂ ህልሞችን ታያላችሁ!! ኦርቶዶክሳዊያን ይኼንን ህልም ካያችሁ ቶሎ መንቃት አለባችሁ!! https://youtu.be/g4UWt5fttUU
ጥያቄ 10፡ የመጨረሻው የሰው ልጅ ከፍታ (Theosis) ተብሎ የሚጠራው አስተምህሮ ትርጉሙ ምንድነው?
ሀ) ሰው ባሕርዩ ተለውጦ አምላክ ይሆናል ማለት ነው
ለ) ሰው በእግዚአብሔር ጸጋ የመለኮታዊ ባሕርይ ተካፋይ ሆኖ ቅድስናንና ዘላለምነትን ይወርሳል ማለት ነው
ሐ) ከመላእክት መበለጥ ማለት ነው
መ) መልሱ የለም
ጥያቄ 9፡ በመንፈሳዊ ውጊያ ውስጥ "የጠባቂ መልአክ" ኃላፊነት ምንድነው?
ሀ) ሰውን ከመከራ መጠበቅ ብቻ
ለ) ጸሎትን ወደ እግዚአብሔር ማሳረግና ነፍስን ከአጋንንት ውጊያ መከታ መሆን
ሐ) ኃጢአት እንዳንሠራ እጃችንን መያዝ
መ) መልሱ የለም
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
