uk
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Відкрити в Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Канал Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 15 391 підписників, посідаючи 5 586 місце в категорії Релігія і духовність та 2 200 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 15 391 підписників.

За останніми даними від 01 липня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 22, а за останні 24 години на -7, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 21.30%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 10.19% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 3 278 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 1 569 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 17.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 02 липня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Релігія і духовність.

15 391
Підписники
-724 години
+227 днів
+2230 день
Архів дописів
#ማክሰኞ ዕለት በ15/10/2013 ዓ.ም ፤ ለ2013 ዓ.ም ተከታታይ መንፈሳዊ የክረምት ኮርስ ተማሪዎች የመከፈቻ መርሃ ግብር ተካሄዷል፡፡ በመርሃ ግብሩ ላይ በመምህር ዘካርያስ ትምህርት የተሰጠ ሲሆ
+3
#ማክሰኞ ዕለት በ15/10/2013 ዓ.ም ፤ ለ2013 ዓ.ም ተከታታይ መንፈሳዊ የክረምት ኮርስ ተማሪዎች የመከፈቻ መርሃ ግብር ተካሄዷል፡፡ በመርሃ ግብሩ ላይ በመምህር ዘካርያስ ትምህርት የተሰጠ ሲሆን በትምሕርት ክፍሉ ጸሐፊ መ/ር ኪሩቤል ጀቤሳ ደግም አጠቃላይ የትምሕርቱን ሂደት የሚዳስስ መግለጫ ( orientation ) ተስጥቷል ፡፡ ትምሕርቱ ዛሬ ሐሙስ በ 17 የሚጀምር ሲሆን መመዝገብ ለምትፈልጉ ሁሉ እስከ ዓርብ ድርስ በድረ ገጻችን መመዝገብ እንደምትችሉ ልናሳውቅ እንወዳልን፡፡ #የመመዝገቢያ አድራሻ https://finotehiwotsundayschool.com/#Register/ ወይንም 0921056056 | 0922851374 ወስብሐት ለእግዚአብሔር ꔰ ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ꔰ Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool https://finotehiwotsundayschool.com/#Register/

ሰኔ ፲፯፤ በዓለ አባ ገሪማ (ይስሐቅ) ዘመደራ፡፡አባ ገሪማ የተሠወሩበት( ሰኔ ፲፯) #በዓለም ላይ በእድሜ ረጅም ዓመታት (ከ1500ዓመታት በላይ) ያስቈጠረውን የብራና ወንጌል ጽፈው ያቆዩልን፤ #ዓድዋ የሚለውን ስያሜ ያወጡ፤ #አሁንም ድረስ ከደረቅ ዓለት ላይ ጠበል እንዲፈልቅ ቃል ኪዳን የተሰጣቸው፤ ሂዳችሁ እዩ!! #በአንድ ቀን ዘርተው ለ9 ሰዓት ቅዳሴ መሥዋዕት ያደረሱ፤ በዚህና በሌሎች ምግባሮቻቸው ወንድሞቻቸው የሚኾኑ ቅዱሳን ሳይቀር ገሪማ ገረምከን ብለው የመሰከሩላቸው፤ *#የኢትዮጵያ ታሪክን የያዘ ታላቁን መደራ ገዳም የመሠረቱ፤ የታላላቅ የአድዋ ጀግኖቻችን መሪያቸው ራስ አሉላ አባ ነጋን ጨምሮ አጽማቸው ያረፉበት ነው፡፡ (ክብረ በዓላቸው በዓድዋ በሚገኘው ገዳማቸው፣ በጎንደር ተክለሃይማኖት፣ በአዲስ አበባ ካራአሌ መድኀኔዓለም ወአቡነ ገሪማ ገዳም) #አባ_ገሪማ_(ይስሐቅ)#ዘመደራ በአልአሜዳ ዘመነ መንግሥት በ፬፻፹ ዓ.ም ወደ አገራችን ወደ ኢትዮጵያ በሃይማኖት ምክንያት ከሶርያና ከታናሽ እስያ ተሰደው ከመጡት ተስዓቱ (ዘጠኙ) ቅዱሳን መነኮሳት (አባ አሌፍ፣ አባ አረጋዊ፣ አባ አፍጼ፣ አባ ሊቃኖስ፣ አባ ገሪማ፣ አባ ጉባ፣ አባ ይምአታ፣ አባ ጰንጠሌዎን እና አባ ጽሕማ) መካከል በትምህርታቸው የላቁ፣ ቅዱስ ያሬድ በድጓው (በመዝሙር)፣ በዝማሬና በመዋሥዕት ድርሰቱ ውስጥ ‹‹ገሪማ ገረምከኒ አስኬማከኒ አልባቲ ሙስና፤ አባ ገሪማ አስገረምኸኝ፡፡ ለምንኵስናህም እንከን የለባትም›› በማለት የደረሰላቸውና አድዋ የሚለውን ስያሜ የሰየሙ፣ በዓለማችን ላይ እስካሁን ከተገኙት የብራና ወንጌሎች መካከል በእድሜው ረዥሙንና ባለሠንጠረዡን /ከ1400ዓመታት በላይ/ የጻፉ፣ እስከ አሁንም ድረስ የሚያስደንቅ ከደረቅ ዓለት ላይ እንደ እንባ የሚወጣው ፈዋሽ ጠበል ያፈለቁ አባ ገሪማ ዘመደራ ናቸው፡፡ እነዚህ ዘጠኙ ቅዱሳን በመላው ኢትዮጵያ ተዘዋውረው ወንጌልን ሰብከዋል፤ በወቅቱ ብሔራዊ ቋንቋ የነበረዉን ግእዝን በሚገባ አጥንተው ቅዱሳት መጻሕፍትን ከሱርስትና ከጽርዕ ቋንቋዎች ወደ ግእዝ ተርጕመዋል፡፡እንደዚሁም ገዳማትንና አብያተ ክርስቲያናት አሳንጸዋል፡፡ ቤተ ክርስቲያናችንም ከፈጸሟቸው መንፈሳውያን ተልእኮዎች፣ ካደረጓቸው ተአምራትና መልካም ሥራዎች አኳያ ቅዱሳን በሚል መዓርግ ትጠራቸዋለች፤ በስማቸውም ጽላት ቀርፃ በዓላቸውን ታከብርላቸዋለች፡፡ የአባ #ገሪማ አባት መስፍንያኖስ የሮም አገር ንጉሥ ነበረ፤ ሚስቱም ሰፍንግያ ትባላለች፡፡ መካን ስለነበረች በቅድስት #ድንግል_ማርያም ስም በመማጸን ልጅ እንዲሰጣት እግዚአብሔርን ስትለምን ከኖረች በኋላ ወንድ ልጅ ወለደች፤ስሙንም ይስሐቅ አለችው፡፡ የያን ጊዜው ይስሐቅ የኋላው አባ ገሪማ በመንፈሳዊ ሥርዓት ካደገ በኋላም የቤተ ክርስቲያን ትምህርት ተምሮ በዲቁና ማገልገል ጀመረ፡፡ ይስሐቅ ወላጅ አባቱ ሲሞትም በአባቱ ዙፋን ተተክቶ ለሰባትዓመታት ሮምን በንጉሥነት ሲያስተዳድር ከቆየ በኋላ በዋሻ ይኖሩ የነበሩት አባ ጰንጠሌዎን ዘጾማዕት ‹‹ይስሐቅ ሆይ፣ ሙታኖቻቸውን ይቀብሩ ዘንድ ሙታንን ተዋቸውና የማያልፈዉን የክርስቶስን መንግሥት ትሻ ዘንድ ወደ እኔ ና›› ብለው መልእክት ላኩበት፡፡ መልእክቱ እንደ ደረሰውም መንግሥቱን ትቶ በሌሊት ወደ አባ ጰንጠሌዎን ሲሔድ ቅዱስ ገብርኤል ተገልጾ በብርሃናውያን ክንፎቹ ተሸክሞ ዐሥር ወር የሚወስደዉን መንገድ በሦስት ሰዓታት አስጉዞ ከአባ ጰንጠሌዎን በዓት አደረሰው፡፡አባ ይስሐቅ (አባ ገሪማ) በአባ ጰንጠሌዎን እጅ ከመነኰሱ በኋላ በጾም፣ በጸሎትና በስግደት ተጠምደው ቆዳቸው ከዐፅማቸው እስኪጣበቅ ድረስ ተጋድሎ ሲፈጸሙ ቆዩ፡፡ ከዚያ በኋላ ወደ መደራ ሔደው በእግዚአብሔር ኃይል ድንቆችንና ተአምራትን እየያደረጉ፣ በሽተኞችን እየፈወሱ፣ አጋንንትን እያስወጡ ብዙ ዓመታት ኖሩ፡፡ ካደረጓቸው ተአምራት መካከልም በጠዋት ሥንዴ ዘርተው፣ በሠርክ ሰብስበው መሥዋዕት ካሳረጉ በኋላ በማግሥቱ ከግራር ዛፍ ላይ በሬዎችን አውጥተው ሥንዴዉን አበራይተው ሰባ ሰባት የእንቅብ መሥፈሪያ መሰብሰባቸው አንደኛው ሲኾን፤ በዓለት ላይ የተከሏት ወይን ወዲያው በቅላ፣ አብባ ፍሬ እንድታፈራ ማድረጋቸውና በወይኑም መሥዋዕት ማሳረጋቸው ደግሞ ሌላኛው ተአምር ነው፡፡ #አባ ገሪማ መጽሐፍ እየጻፉ ሳሉ #ፀሐይ ሊጠልቅ በተቃረበ ጊዜ ጸሎት አድርሰው ጽሕፈታቸዉን እስኪፈጽሙ ድረስ እንደ ኢያሱ #ፀሐይን_በቦታው እንዲቆም ማድረጋቸውም በመጽሐፈ ስንክሳር ተመዝግቧል፡፡ ከእጃቸው የወደቀው ብርዕ ወዲያው በቅሎ፣ አቈጥቍጦ እንደ አደገ፤ ምራቃቸዉን ትፍ ያሉበት ሥፍራም እስከ ዛሬ ድረስ ሕሙማንን እንደሚፈውስ መጸሐፈ ስንክሳር ይናገራል፡፡ በአንዲት ዕለትም መቅኑናቸውን ተቀብለው ከመነኮሳት ጋር ሲሔዱ መንገድ ላይ ቤተ ክርስቲያን አግኝተው ሲጸልዩ ካህናቱ ቅዳሴ እንዲያሟሉላቸው ጠየቋቸው፡፡ በዚህ ጊዜ ሌሎቹ ምግብ በልተው ነበርና ‹‹አንችልም›› ሲሉ አባ ይስሐቅ ምግብ አልተመገቡም ነበርና መቅኑናቸዉን አስቀምጠው ቅዳሴውን አሟሉ፡፡ ባልንጀሮቻቸው ግን በልተው የቀደሱ መስሏቸው ወደ አባ ጰንጠሌዎን መጥተው ‹‹ቀሲስ ይስሐቅ ከበላ በኋላ ቀደሰ›› ብለው ከሰሷቸው፡፡ አባ ጰንጠሌዎንም አባ ይስሐቅ ሲመለሱ ‹‹የምጠይቅህ ምሥጢር ስላለኝ ሰዎችን ከአጠገብህ ገለል አድርጋቸው›› ሲሏቸው አባ ይስሐቅም ‹‹ሰዎች ብቻ ሳይኾኑ ዕንጨቶችና ድንጋዮችም ገለል ይበሉ›› ብለው መለሱላቸው፡፡ ወዲያዉኑም ዕንጨቶችና ድንጋዮች አንድ ምዕራፍ ያህል ከቦታቸው ሸሹ፡፡ በዚህ ጊዜ አባ ጰንጠሌዎን ‹‹ኦ ወልድየ ይስሐቅ ገረምከኒ፤ ልጄ ይስሐቅ ሆይ! ገረምኸኝ›› እያሉ አደነቋቸው፡፡ አባ ገሪማን ሳያዉቁ የከሰሷቸው መነኮሳትም ይቅርታ ጠይቀዋቸዋል፡፡ አባ ገሪማ ተብለው መጠራት የጀመሩትም ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ነው፡፡ ይህንን መሠረት በማድረግ ‹‹#ገሪማ_ገረምከኒ_አስኬማከኒ_አልባቲ_ሙስና፤ አባ ገሪማ አስገረምኸኝ፡፡ ለምንኵስናህም እንከን የለባትም›› በማለት #ቅዱስ_ያሬድ በመዝሙሩ አመስግኗቸዋል፡፡ ከዚያም በትግራይ ክፍለ ሀገር ልዩ ስሙ መደራ ከሚባል ቦታ ገብተው በዓት ሠርተው ለ፳፫ ዓመታት በትኅርምት ኖረው መልካም ተጋድሏቸውንና የቀና አካሔዳቸዉን በፈጸሙ ጊዜ ክብር ይግባውና ጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰኔ ፲፯ ቀን ተገልጦ ስማቸውን የሚጠሩትን፣ መታሰቢያቸዉን የሚያደርጉትን፣ ገድላቸዉን የሚጽፉ፣ የሚያነቡና የሚተረጕሙትን፣ ቤተ ክርስቲያን የሚያንጹትንና የሚያገለግሉትን ስማቸውን በሕይወት መጽሐፍ እንደሚጽፍላቸው ቃል ኪዳን ሰጥቷቸዋል፡፡ አባ ገሪማም ይህንን ታላቅ ሀብት የሰጣቸዉን እግዚአብሔርን አመስግነው ከተደሰቱ በኋላ በብርሃን ሠረገላ ተነጥቀው #ብሔረ_ሕያዋን ገብተዋል፡፡ በቤተ ክርስቲያናችን በተለይ በገዳማቸው በመደራ አባ ገሪማ የተሠወሩበት ሰኔ ፲፯ ቀን በየዓመቱ በድምቀት ይከበራል፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይኹን፡፡ እኛንም በጻድቁ ጸሎት ይማረን፤ በረከታቸዉም ከእኛ ጋር ትኑር፤ ለዘለዓለሙ አሜን፡፡ ሰአል ለነ አባ ገሪማ፤ ꔰ ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ꔰ Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem www.Finotehiwotsundayschool.com

«ከእስትንፋስህ ጋራ ለተዋሀደ የከበረ ቃልህና ከወይንም ይልቅ የክርስቶስ ጣዕመ ፍቅሩን ለቀመሰ ጕሮሮህ ሰላምታ የሚገባህ ትሩፈ ምግባር ነቢየ ሴሎ ዮሐንስ #አረጋዊ ሆይ በሰማይ የአለ የአየኸውን ኅቡእ ሚስጢራት እስኪ ንገረኝ ግለጽልኝ፡፡» ዝማሜ | ዘእምደብረ ደናግል | በዩቲዩብ ቻናልቻን ያድምጡ https://youtu.be/8TaHMwbZ-KQ YouTube

ሰላምንና ፍቅርን የተመላህ የከበርህ መምህር አባታችን አረጋዊ ሆይ የእስራኤላውያንን እግር ከታሠረበት የባርነት ማሠሪያ ፈትቶ ከግብፅ የነፃነት መንገድን በመራው እግዚአብሔር ስም አምኜ የፅድቅህን ዜና እነግር ዘንድ አንደበቴን አከናውን፡፡ ልቡናየንም ከሀኬት አንቃው፡፡ ወረብ | ብፁአን አበዊነ አረጋዊ በዩቲዩብ ቻናልቻን ያድምጡ https://youtu.be/3o4wj7Qqcaw

የአቡነ አረጋዊ እና የገብረ ክርስቶስ ወረብ ወረብ | ብፁአን አበዊነ አረጋዊ .. | በደብረሰላም ሊቃውንት ዝማሜ ※ጥቅምት14፤2013 ዓ.ም በዓለ አቡነ አረጋዊ ወገብረክርሰቶስ ወሙሴ ብእሴ በዩቲዩብ ገጻችን ላይ ይመልከቱ በሕጻናት——-> https://youtu.be/3o4wj7Qqca ዝማሜ | ዘእምደብረ ደናግል | በዩቲዩብ ቻናልቻን ያድምጡ https://youtu.be/8TaHMwbZ-KQ https://youtu.be/3o4wj7Qqcaw

#ጾመ_ሐዋርያት ꔰበየዓመቱ በዕለቱ ሰኑይ የሚጀምሩ ሶስት አጽዋማት ብቻ አሉ ፡፡ ከእነርሱ መካከል አንዱ ጾመ ሐዋርያት ነው ፡፡ ቅበላው በዕለተ እሑድ ይሆንና ጾሙ ሰኞ ይውላል ፡፡ የ2013 ዓ.ም ጾመ ሐዋርያት ሰኔ 14 ይገባል ፡፡ ꔰይህ ጾም እራሱ ጌታቸን ኢየሱስ ክርቶስ ትንቢት የተናገረለት ጾም ነው፡፡ ꔰይህ ታላቅ ጾም የዛሬ 1900 ዓመት በፊት በራሳቸው በቅዱሳን ሐዋርያት የተጀመረ ጾም ነው ፡፡ ከሰባቱ አጽዋማት መካከልም አንዱ ነው ፡፡ ይህ ጾም እራሱ ጌታቸን ኢየሱስ ክርቶስ ትንቢት የተናገረለት ጾም ነው፡፡ ꔰፈሪሳውያ ጌታችንን ደቀ መዛሙርትህ አይጾሙም ብለው በጠየቁት ጊዜ እርሱም ‹‹ ሚዜዎች ሙሽራ ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ ይችላሉን ? ነገር ግን መሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራት ይመጣል ፤ በዚያ ጊዜም ይጾማሉ ፡፡ በአረጀ ልብስ አዲስ እራፊ የሚያኖር የለም ፤ መጣፊያው ልብሱን ይቦጭቀዋልና ፤ መቀደዱም የባሰ ይሆናል ፡፡ በአረጀ አቁማዳ አዲስ የወይን ጠጅ የሚያኖር የለም ፤ ቢደረግ ግን አቁማዳው ይፈነዳል የወይን ጠጁም ይፈሳል ፡፡አቁማዳው ይጠፋል ፡፡ ነገር ግን አዲሱን የወይን ጠፉ በአዲስ አቁማዳ ያኖረዋል ሁለቱም ይጠባበቃሉ ፡፡›› ማቴ 9 – 14-17 ፡፡ አላቸው ይህ ቃለ ጌታችን ራሱ ስለ ጾመ ሐዋርየት የተናገረው ትንቢት ነው ፡፡ ꔰ‹‹#መሽራው_ከተወሰደ በኃላ›› ማለት ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሰማይ ካረገ በኃላ ማለት ሲሆን ይህን ጾም ከዕረገት በኃላ የምንጀምረው ይህን ምሳሌ በማድረግ ነው ፡፡ አስር ቀን ዘግይቶ መጀመሩም የሐዋርያት ሰውነት ለጾሙ መዘጋጀት ነበረበትና ነው ፡፡ የዚህን ማብራርያ በቀጣይ ጽሁፋችን እንመለስበታልን፡፡ ꔰይህ ጾም በአላዋቂዎችን እና በቤተክርስቲያን ጠላቶች የሽማሌዎች ጾም እየተባለ ምዕመናን እንዳይጾሙት ብዙ ተለፍቷል ልናውቅ የሚገባው ነገር ግን ሐዋርያት ዓለምን ዞረው ከማስተማራቸው በፊት ይህን ጾም ጾመዋል ፡፡ በዚህም ጌታችን የተናረው ተንቢት ተፈጽሟል፡፡ ከሰባቱ አጽዋማትን አንዱ ነው ፡፡ በዚህ ምክንያት ይህን ጾም ታላቅ እና ልዩ ያስብለዋል ፡፡ ይህንን አውቀን ሁላችንም ልንጾመው ይገባል ፡፡ ይቀጥላል ………. ꔰ ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ꔰ Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem www.Finotehiwotsundayschool.com ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ

⨳ ዝክረ ቅዱስ ያሬድ #ዘወርኀ_ሰኔ እንዲሁም ሳምንታዊው የዓርብ ጉባዔ በመምህር #መጋቤ_ሐዲስ_የኔታ_ወልደትንሣኤ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ የሐዲሳት መምህር ፤ እጅግ ግሩም በሆነ ቃለ ወንጌል
+2
⨳ ዝክረ ቅዱስ ያሬድ #ዘወርኀ_ሰኔ እንዲሁም ሳምንታዊው የዓርብ ጉባዔ በመምህር #መጋቤ_ሐዲስ_የኔታ_ወልደትንሣኤ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ የሐዲሳት መምህር ፤ እጅግ ግሩም በሆነ ቃለ ወንጌል እና #በዘማሪት ሲስተር ሕይወት ጣፋጭ ዝማሬ አልፉል ፡፡ ባርከነ አምላከ ቅዱስ ያሬድ ለዘአብጽሃነ እስከ ዛቲ ሰዓት ፡፡ …ለወሩ ያድርሰን ፤ አሜን፡፡ ትምህርቱን በዩቲዩብ ገጻችን የምንለጥፍ ይሆናል ፡፡ ጉባዔዉ ሳምንት ዓርብ ይቀጥላል። https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

ዝክረ ቅዱስ ያሬድ ዘወርኀ ሰኔ በመምህር መጋቤ ሐዲስ የኔታ ወልደ ትንሣኤ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ የሐዲሳት መምህር ፤ እጅግ ግሩም በሆነ ቃለ ወንጌል እና በዘማሪት ሲስተር ሕይወት ጣፋጭ ዝማሬ አልፉል ፡፡ ባርከነ አምላከ ቅዱስ ያሬድ ለዘአብጽሃነ እስከ ዛቲ ሰዓት ፡፡ …ለወሩ ያድርሰን ፤ አሜን፡፡ ትምህርቱን በዩቲዩብ ገጻችን የምንለጥፍ ይሆናል ፡፡

https://youtu.be/_mfJ4ltt80A የቅዱስ ሚካኤል ወረብ ፤ ባሕራንኒ ይቤ ፤ በደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ቤተክርስቲያን ሊቃውንት:: ወረብ ባሕራንኒ ይቤ ዘነገደ ባሕረ፤ ርኢክዎ ለሚካኤል ወስዕንኩ ጠይቆቶ ስዕንኩ፡፡ ꔰ ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ꔰ Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem www.Finotehiwotsundayschool.com ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ https://youtu.be/_mfJ4ltt80A

የቅዱስ ሚካኤል ወረብ ፤ ባሕራንኒ ይቤ ፤ በደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ቤተክርስቲያን ሊቃውንት:: ወረብ ባሕራንኒ ይቤ ዘነገደ ባሕረ፤ ርኢክዎ ለሚካኤል ወስዕንኩ ጠይቆቶ ስዕንኩ፡፡ ꔰ ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ꔰ Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem www.Finotehiwotsundayschool.com ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ https://youtu.be/_mfJ4ltt80A