uk
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Відкрити в Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Канал Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 15 371 підписників, посідаючи 5 616 місце в категорії Релігія і духовність та 2 192 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 15 371 підписників.

За останніми даними від 25 червня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на -4, а за останні 24 години на -1, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 20.07%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 8.16% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 3 085 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 1 254 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 17.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 26 червня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Релігія і духовність.

15 371
Підписники
-124 години
+357 днів
-430 день
Архів дописів
#አንኳን_አደረሳቹህ ኅዳር ፲፪፤ በዓለ ሢመቱ ለቅዱስ ሚካኤል "በእልፍ አእላፍ መላእክት ላይ የተሾመበትና #ወበዓለ_መራኄ_ፍኖቱ_ለቅዱስ_ሚካኤል_ሊቀ_መላእክት_፨ "እስራኤልን የመራበት ክብረ በዓል ነው፡፡" ፨፨፨ #Share ያድርጉ ኅዳር ፲፪ ለሰው ወገን የሚያዝንና የሚራራ፥ በእግዚአብሔር የጌትነት ዙፋን ፊት ሁልጊዜ ለምስጋና የሚቆም፥ ለፍጥረት ሁሉ የሚማልድ፥ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል በዓለ ሢመቱና እስራኤላውያንን በባሕረ ኤርትራ ያሸገረበት በዓል ነው፡፡ ፠ #፩ በዓለ ሢመቱ፤ ሚካኤል ማለት ማን እንደ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡ ከሌሎች መላእክት ጋር በእለተ እሑድ ካለመኖር ወደ መኖር አምጥቶ የተፈጠረ ሲሆን፤ እርሱም መጀመሪያ ከ100ው ነገደ መላእክት የ10ሩ ነገደ መላእክት (የኃይላት) አለቃቸው ነበር፤ በተጨማሪም ከሳጥናኤል ውድቀት በኋላ የኃይላት አለቅነቱን እንደያዘ የአጋእዝትን ነገድም (ሳጥናኤል/ሰማልያል/) ይመራቸው የነበሩትን 10 ነገዶችም በአለቅነት ደርቦ አለቃ ኾኗል፤ እንዲሁም በዛሬው ዕለት ለ100ውም(99ኙም) ነገደ መላእክት (ለእልፍ አእላፋት መላእክት) አለቃቸውም ቅዱስ ሚካኤል ኾኖ የተሾመበት ዕለት ነው፡፡ ልዑል ውእቱ ልዑለ መንበር ያሰኘውም ይኸው ነው፡፡ ቅ/ሚካኤል ለሰው ልጆች ምሕረትን ከኅዳር 12 (ከበዓለ ሢመቱ) ጀምሮ እስከ ኅዳር 13 (የአእላፍ መላእክት) በዓል ድረስ ከአምላኩ ለፍጥረታት ሁሉ ምሕረትን የሚለምንበት ዕለታት ናቸው፡፡ ፨፨፨ ፠#፪ እስራኤልን ከግብጽ ባርነት እየመራቸው ማውጣቱን የሚዘከርበት በዓል ነው፡፡ ይህም የሆነው ያዕቆብ በረሃብ 70 ኹኖ ወደ ግብፅ ከወረደ በኋላ ከ215 ዓመታት (አብርሃም ወደ ግብፅ በተሰደደ ከ430 ዓመታት) በኋላ፤ የዮሴፍን ዝና ያልሰማ፥ ዮሴፍን የማያውቅ ፈርዖን በግብፅ ነገሠ፡፡ እስራኤል ከእኛ ይልቅ በዝተዋል ጠላቶቻችን ቢነሱብን ከጣለቶቻችን ጋር ተደርበው ያጠፉናል በማለት አገዛዝ አጸናባቸው፥ ፍርድ አጓደለባቸው፡፡ የእስራኤል ሴቶች ልጅ ሲወልዱ ወንድ ከሆነ እንዲገደል በማድረግ መከራ አጸናባቸው፡፡ ለ215 ዓመታት በግብፅ በባርነት ከቆዩ በኋላ ከዕብራውያን ወገን የሆነችው ራሔል ጭቃ እያቦካች ምጥ በያዛት ጊዜ ከሥራዋ እንዲያሳርፏት ጠየቀች፤ ግብጻውያን ግን የሕፃናቱ ደም ጡቡን ያጠነክራል ርገጭ አሏት፡፡ ከማሕፀኗ የወጡ ሁለት መንትያ ልጆቿን እያየች ከጭቃ ጋር ረገጠች፤ ራሔልም መሪር ልቅሶን አለቀሰች፤ ስለ ልጆቿም መጽናናትን እንቢ አለች፡፡ የእስራኤል ንጉሥ ሆይ የሆነብንን እይ ስትል ራሷን ይዛ ታለቅስ ጀመር ፥ እንባዋንም ወደ ሰማይ ንጉሥ ወደ እግዚአብሔር ረጨች፡፡ የራሔል እንባዋ የሕዝበ እስራኤልን ሁሉ ጩኸት ፥ እሮሮ ይዛ ቅድመ እግዚአብሔር ደረሰች፡፡ “. . . ራሔል ስለ ልጆቿ አለቀሰች የሉምና ስለ ልጆቿ መጽናናት እንቢ አለች” /ኤር 31፥5፤ ማቴ 2፥17/ እንዲል፡፡ ከዚህ በኋላ እግዚአብሔር ሙሴን አስነሳና፤ በሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል መሪነት፤ 10 ተዓምራትን በምድረ ግብፅ በ11ኛ ተዓምር ደግሞ በኅዳር 12 (ፈርዖንን ከነሠራዊቱ በኤርትራ ባሕር አስጥሞ) ወደ ተስፋይቱ ምድረ መራቸው፡፡ ባሕረ ኤርትራን እስራኤላውያን እንደተሻገሩም የእስራኤል ልጆች የሙሴ የአሮን እኅት ማርያም ከበሮ እየመታች ‹‹ንሴብሖ ለእግዚአብሔር ስቡሐ ዘተሰብሐ ፤ እግዚአብሔር ተዋጊ ነው ስሙም እግዚአብሔር ነው እያሉ፡፡›› ጠላታቸውን የመታላቸውን ፥ እነሱንም በተአምራቱ ያሻገራቸውን ፥ ከጠላታቸው እጅ ያዳናቸውን እግዚአብሔርን አመሰገኑ፡፡ ከዚህ በኋላ መጋቤ ብሉይ ቅዱስ ሚካኤል እየመራቸው ፥ መና ከሰማይ እያወረደላቸው ፥ ውሃ ከጭንጫ እያፈለቀላቸው ፥ ቀኑን በደመና ፥ ሌቱን በብርሃን መርቷቸው አርባ ዘመን ተጕዘው የቃል ኪዳን አገራቸው ምድረ ርስት ከነዓንን (የዛሬዋ ኢየሩሳሌምን) ወርሰዋል፡፡ /ዘጸ. 15/ ከሙሴ በኋላ እስራኤልን የመራው ነቢዩ ኢያሱም እስራኤልን በሚመራበት ጊዜ ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል እስራኤልን ይረዳቸው ነበር፡፡ ከጠላቶቻቸው ጋር ሲዋጉም ሰልፉን ይመራ የነበረው ቅዱስ ሚካኤል ነበር፡፡ ለምሳሌ እስራኤላውያን ከኢያሪኮ አጠገብ በነበሩበት ጊዜ ቅዱስ ሚካኤል ተገልጦኢያሱን አነጋግሮታል፡፡ ኢያሱ በኢያሪኮ አጠገብ ሳለ ቀና ብሎ ሲመለከት የተመዘዘ ሰይፍ በእጁ የያዘ አንድ ሰው ከፊቱ ቆሞ አየ፤ ኢያሱም ወደ እርሱ ቀርቦ “ከእኛ ወገን ነህ ወይስ ከጠላቶቻችን?” ሲል ጠየቀው፡፡ እርሱም “አይደለሁም ነገር ግን የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ በመሆኔ መጥቻለሁ” ብሎታል /ኢያሱ 5፥13-15/፡፡ ይህ የተመዘዘ ሰይፍ ይዞ ከኢያሱ ፊት ለፊት የቆመው መልአክ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል (እንዲሁም መልአኩ ቅዱስ ራጕኤል) ነው፡፡ ይህን ለአብነት አነሣን እጅ እስራኤል በሚበድሉበት ጊዜ ሁሉ ወደ እግዚአብሔር የሚማልድላቸው ይህ ታላቅ መልአክ መጋቤ ብሉይ ቅ/ሚካኤል ነበር፤ እግዚአብሔር አምላክ በእደ መልአኩ ይጠብቀን፤ ከበዓሉ ረድኤት ፥ በረከት ይክፈለን፤ አሜን፨ ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡ #Share ያድርጉ ሥርዓተ ማኀሌቱ እስመ ለዓለሙን የሰንበትን በማድረግ ተጠቀሙ(ሰርዓ ለነ) በመዲና ከተማችን የሊቀ መልአኩ የቅዱስ ሚካኤል ክብረ በዓል የሚከብርባቸው ገዳማትና አድባራትን እንጠቁማችሁ፡፡ /ፎቷቸውን ያልለጠፍናቸውና ስማቸውን ያልጠቀስናቸውን እንድትልኩልን በሊቀ መልአኩ ስም እንጠይቃለን) 1) *የካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን (ሾላ፤ መገናኛ) 2) *አንቀጸ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል /ጭቁኑ/፤ ፈረንሳይ 3) *ደብረ መዊዕ ቅዱስ ሚካኤል (አዲሱ ሚካኤል)፤ አውቶብስ ተራ 4) *ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል፤ /ቦሌ/ 5) *ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ሚካኤል፤ /ላፍቶ/ 6) *ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል፤ (መካኒሣ) 7) *ኮተቤ ደብረ ጽባሕ ቅዱስ ሚካኤል /ሳጠራው/ (ቀድሞ ኮተቤ አሁን ሲምሲ) 8) *ደብረ ምሕረት ሚካኤል (ቀድሞ ወህኒ ቤት ሚካኤል) 9) *መካነ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል 10) *ገነተ አምባ ቅዱስ ሚካኤል 11) *ደብረ ኢዮር ቅዱስ ሚካኤል 12) *ካራ ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ሚካኤልና 24ቱ ካህናተ ሰማይ 13) *ሐያት ጨፌ ኢያሪኮ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን (በ1980ዓ.ም ጽላቱ ከነ ድርሳናቱ ተቀብሮ የተገኘበት) 14) *መንበረ ክብር ቅዱስ ሚካኤል ወአቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም /ኋላ ወቅድስት አርሴማ በሚል እየተጠራ የሚገኝ/፤ (በቀጨኔ በአዲሱ ገበያና በእንጦጦ መሃል ጉብታ ላይ የሚገኝ) እንዲሁም በድርብነት 15) *እንጦጦ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት 16) *መንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ (ስድስትኪሎ) 17) *ደብረ ሰላም ቅዱስ እስጢፋኖስ (መስቀል አደባባይ) 18) *ጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ቤ.ክ (ኋላ ጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል በሚል እየተጠራ የሚገኘው)፤ (ኢምግሬሽን አጠገብ) 19) *ደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ (ኋላ ወመካነ ጎልጎታ ቅድስት ድንግል ማርያም በሚል እየተጠራ የሚገኝ ) (ሰሜን ሆቴል አካባቢ)

#የክርስቶስ_አያት ኀዳር 11 በዚህችም ቀን ለጌታችን ለመድኀኒታችን ፣ፀሐይን እና ጨረቃን ለሚገዛ ፣ ሰውን በአርያውን በመልኩ ለፈጠረ ፈጣሪያችን አያት የሆነች ፣ ለእመቤታችን ለቅድስት ቅዱሳን ድንግል ማርያምም እናቷ የሆነች የተመሰገነች እና የከበረች ቅድስተ ሐና ዐረፋቷ ነው፡፡ #share ያድርጉ #ቅድስት_ሐና በኢየሩሳሌም ከሌዊ ነገድ ከካህኑ አሮን ትውልድ የሌዊ የሚልኪ ልጅ ለሆነው የማጣት ልጅ ናት፡፡ ____ #ማጣትም 3 ልጆች አሉት እነርሱም ፤ #የመጀመሪያይቱ ስሟ ማርያም ነው፤ አዋላጅ የነበረች ስትሆን ቅድስት ሰሎሜን ወልዳለች ፤ ሰሎሜም እመቤታችን መድኃኒታችንን ከወለደችው ጀምሮ በስደቷም ወራት ከአረጋዊ ዮሴፍ ጋር እመቤታችንን ያገለገለቻት ናት፡፡ #ሁለተኛይቱ ስሟ ሶፍያ ነዉ ፤ ይህቺ ቅድስተ ለመጥመቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ እናት የሆነችውን ቅድስት ኤልሳቤጥን ወለደች፡፡ #ሦስተኛይቱም ስሟ ሐና ነው፤ ይህች ቅድስት ሐና ከይሁዳ ነገድ ለሆነ ጻድቅ ስሙም ኢያቄም ከሆነ ጋር ተጋብታ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ወለደቻት፡፡ ሰሎሜና ቅድስት ኤልሳቤጥ የእመቤታችን እናት ለሆነች ለቅድስት ሐና እኀትማማች ናቸው፡፡ _ ቅድስት ሐና መካነ እያለች አምላክን ልጅ እንዲሰጣት እጅግ አብዝታ ትለምን ነበር፡፡ እግዚአብሔርም በእርሷ ለዓለም ሁሉ ድኀነት የተደረገባትን ይቺን የተባረከችን የከበረች ልጅን ሰጣት እርሷም አምላክን የወለደች እመቤታችን ድንግል ማርያም ናት፡፡ ጌታ የዘር ሐረግ ውስጥ የተቆጠሩ ሁሉ ክቡራን ናቸው የመጨረሻዎቹ አያቶቹ ደግሞ የመጨረሻው ክብር ይገባቸዋል እነርሱም ሐና እና ኢያቄብ ናቸው:: አምላካችንን የልጅ ልጅቻችን ነው ለማለት ተገብተዋልና፡፡ ቅድስት ሐና ከሴቶች ሁሉ የምትከብርና የምትበልጥ መሆኗን አምላክን ለወለደችልን ለቅድስት እናታችን ድንግል ማርያም እናት ሆና አይተናል፤ ከሴቶች ሁሉ የሚበልጥ ትሩፋትና ተጋድሎ ባይኖራት ይህ ጸጋ ባልተገባት ነበር፡፡ አባቶችም ታጋድሎዋ እጅግ ብዙ እንድሆነ ነግረውናል፡፡ ---ምልጃዋ አይለየን ፡፡ ሃገራችንን ቅድስት ኢትዮጵያን እና ቅድስት ቤተክርስቲያናችንን ትጠብቅልን አሜን! አርኬ ሰላም ለኪ ለጸሎተ ኵሉ ምዕራጋ፡፡ ከመ አስካለ ወይን ዲበ ሐረጋ፡፡ ሐና ብፅዕት ተፈሥሒ እንበለ ንትጋ፡፡ እስመ ረከብኪ ምገሰ ወአድማዕኪ ጸጋ፡፡ እምሔውተ አምላክ ትኵኒ በሥጋ፡፡ በቦታው ሄዳቹ በዓሉን ማክበር ለምትፈልጉ👇🏼 ፎቶዎቹ፤ በአ.አ. እና በሌሎች የሚገኙ የቅድስት ሐና አብያተ ክርስቲያናት ... ፠ ኮተቤ መካነ ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና ቤ/ክ ፡ ፠ ደብረ ንግስት መንዝ ቅድስት ሐና:: ፠ በድሬዳዋ ሀገረ ስብከት በደብረ መንክራት ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን በደባልነት ትገኛለች ሌሎች በዓሉ የሚከብሩባቸውን ቦታዎች ኮሜንት ላይ ያጋሩን /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #Share #like

፠ ይህ ቤተ ክርስቲያን ታላቅ ጕባኤ ቤትም ሲኖረው፤ ቀድሞ የ4ቱ ጕባኤያት ዋና ማስመስከሪያ ኹኖ ቆይቷል፤ ከአፄ ኀይለ ሥላሴ ዘመን ጀምሮ በኢትዮጵያ ደረጃ የመጻሕፍተ መነኰሳት ዋና ማስመስከሪያ ኹኖ ይገኛል፡፡ እጅግ የሚገረመው ደግሞ ደብረ ሲመሠረት ያገለግሉ የነበሩት ካህናት 318 መሆናቸው ነው እኚህም በሥነ መለኮትን ት/ት እጅግ ሊቅ የሆኑ ሲሆን መጻሕፍትን በመተርጕም እና ምሥጢር በመግለጥ አገልግለዋል በዙ ደቀ መዛሙርትንም አፍርተዋል ፡፡ ፠ በ900 ዓ.ዓ አካባቢ ከቀዳማዊ ምኒልክ ጋር የመጡት የብሉይ ኪዳን መምህራን ቁጥር 318 መሆኑን መጻሕፍት ይናገራሉ ፡፡እነዚህም ወንጌል እና ግዕዝ ቋንቋን ያስፋፉ ናቸው፡፡ ኦሪትም በሕዝቡ ልቡና እንዲቀር ያደረጉ ፣ መጻሓፍትንም ( ከዕብራይስጥ ወደ ግዕዝ )በመተርጐም አስተዋጾ ያደረጉ ናቸው ፡፡፡፡የኦሪቶቹ 318 ሊቃውንት ከአዲስ ኪዳኖቹ ሊቃውንት ቁጥር ጋር እኩል መሆናቸው እጅግ የሚያስገርም ታሪክ ነው ፡፡ /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #Share #like

ኅዳር ፱ (9)፤ የሠለስቱ ምዕት (318ቱ ሊቃውንት) ክብረ በዓል ነው፡፡ በዚህችም ቀን ዳግመኛ የሦስት መቶ ዐሥራ ስምነት ኤጲስ ቆጶሳት ሊቃውንት ስብሰባ በኒቅያ ከተማ በጻድቅ ንጉሥ በቈስጠንጢኖስ ዘመን ሆነ ፡፡ " ፠የተሰበሰቡበትም ምክንያት የሊብያው ሰው አርዮስ በእስክንድርያ በቄስነት ሲያገለግል ጌትነት ገንዘቡ የሆነ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን‹‹ወልድ በመለኮቱ ፍጡር ነው ብሎ ›› ክዷል ከዚያም: በጻድቁ ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ጥሪ: 2348 ምሑራን ከመላው ዓለም ተሰበሰቡ:: ፠ጥሪው የተላለፈው በወርኀ ሚያዝያ ሲሆን በመንገድ ችግር ሁሉም ተጠቃለው ኒቅያ የገቡት መስከረም 21 ቀን ነበር (በዚችም ዕለት በዓላቸው ይታሰበል ) :: ከተሰበሰበው ብዙ ሰው መካከል የአበውን ደቀ መዛሙርት ሳንቆጥር ሃይማኖታቸው የቀና: ምግባራቸው የጸና 318ቱ አበው ሊቃውንት ተገኙ:: ፠እነዚህ አባቶች 'ሊቃውንት' ሲባሉ እንዲሁ በእውቀት ብቻ የበሰሉ እንዳይመስሉን:: 318ቱ አበው እኩሎቹ በዘመነ ሰማዕታት እጅና እግራቸውን የተቆረጡና ለሃይማኖታቸው ብዙ ዋጋ የከፈሉ ናቸው:: ፠እኩሎቹ ደግሞ በገዳማዊ ሕይወት ያጌጡ: ፍቅረ ክርስቶስ በውስጣቸው የሚነድ: የመንፈስ ቅዱስ ቤት ናቸው:: የጥቂቶቹ 1.ቅዱስ ቶማስ ዘመርዓስ (በዓሉ በደብራችን ደብረሰላም የሚከበር(ነሐሴ 24) (በዘመነ ሰማዕታት ለ22 ዓመት ሲቆራርጡት ኖረው በጉባኤው ላይ የተገኘው ያለ እጅ: እግር: ጀሮ: ከንፈር: ቅንድብ ነው) ስለ ቅዱስ ቶማስ እዚህ አነብብ https://t.me/medihanaelem/6993 https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool/posts/2985127341805344 2.ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ (ስለ ቀናች እምነት ለ50 ዓመታት የተጋደለና ለ15 ዓመታት በስደት የኖረ ነው) 3.ቅዱስ እለእስክንድሮስ ሊቅ (ከሰማይ ብርሃን ይወርድለት የነበረ አባት ነው) 4.ታላቁ ቅዱስ ባስልዮስ (በጸሎቱ አጋንንትን ያንቀጠቀጠ: ነፍሳትን ከሲዖል የቀማና ከከዊነ እሳት የደረሰ አባት ነው) 5.ቅዱስ ጐርጐርዮስ ዘአርማንያ (ስለ ቀናች እምነት መጸዳጃ ጉድጉዋድ ውስጥ ለ15 ዓመታት ተጥሎ የኖረ ሰማዕት ነው) 6.ቅዱስ ኒቆላዎስ ዘሜራ (ከሕጻንነቱ የተቀደሰ: በበርሃ የተጋደለ: በዘመነ ሰማዕታት ብዙ መከራን የተቀበለ አባት ነው) 7.ቅዱስ ያዕቆብ ዘንጽቢን (በደግነቱ ሙታንን ያስነሳ: ወንዝን በጸሎቱ ያቆመ: በንጽሕና የተጋደለ አባት ነው) 8.ቅዱስ ሶል ዼጥሮስ (ቅዱሱን ንጉሥ ያጠመቀ: ቁስጥንጥንያን በወንጌል ያበራ ሊቅ ነው) 9.ቅዱስ ኤዎስጣቴዎስ (ስለ ቀናች እምነቱ ብዙ ግፍ የደረሰበትና በስደት ያረፈ አባት ነው) ፠ለአብነት እንዲሆኑን እነዚህን አነሳን እንጂ 318ቱም ሊቃውንት ስለ ቤተ ክርስቲያን ተግተው የተጋደሉ: ብዙ ዋጋም የከፈሉ አባቶች ናቸው:: ፠በወቅቱ ታዲያ ቤተ ክርስቲያንን የበጠበጡ ብዙ መናፍቃን ቢኖሩም የአርዮስ ግን ከመጠኑ አለፈ:: የእርሱ ኑፋቄ (ፈጣሪያችንን ፍጡር ነው ማለቱ) መነሻው ከእርሱ በፊት ነው:: መናፍቃን ከዘመነ ሐዋርያት ጀምሮ ቤተ ክርስቲያንን ሲያውኩ መኖራቸው ግልጽ ነው:: ፠በተለይ ደግሞ ቢጽ ሐሳውያንና ግኖስቲኮች የወለዷቸው እሾሆች አባቶቻችንን እንቅልፍ ነስተው ነበር:: የሚገርመው በዘመኑ እንደ ነበሩ መናፍቃን ኃይለኝነት የእኞቹ ከዋክብት ሊቃውንት ባይኖሩ ምን ሊፈጠር እንደሚችል ያሳስብ ነበር:: ፠ግን እግዚአብሔር ለሁሉ እንደሚገባ ያዘጋጃልና አበው ብርቱ መናፍቃንን በብርቱ መንፈሳዊ ክንድ እያደቀቁ ከጐዳና አስወገዷቸው:: የዛሬውን ደካማ ትውልድ ደግሞ የአርዮስ ልጆች 2 (3) ጥቅስ ይዘው ሲያደናብሩት ይውላሉ:: ፠ሐረገ መናፍቃን በርጉም ሳምሳጢ ዻውሎስ: በመርቅያንና በማኒ ይጀምራል:: በእርግጥ አርጌንስ እና የግብጹ ቀሌምንጦስም ተቀላቅለዋቸዋል:: ርጉም ሳምሳጢ ድያድርስን በኑፋቄ ወልዶታል:: ድያድርስ ሉቅያኖስን: ሉቅያኖስ ደግሞ አርዮስን ወልደዋል:: ፠ይህ አርዮስ እጅግ ተንኮለኛ በመሆኑ ልክ እንደ ዘመኑ መሰሎቹ ግጥምና ዜማ እየጻፈ በየመንገዱ እያደለ: በየቤቱ እየሰበከ ብዙዎችን በኑፋቄው በከለ:: በመጀመሪያ ተፍጻሜተ ሰማዕት ቅዱስ ዼጥሮስ (አስተማሪው) መከረው:: ባይሰማው ከአንዴም ሁለት ጊዜ አወገዘው:: ፠ቆይቶ ሰነፉ ዻዻስ አኪላስ ቢፈታውም ሊቁ ቅዱስ እለእስክንድሮስ እንደ ገና አወገዘው:: እንደ አርዮስ ሐሳብ መድኃኒታችን ክርስቶስ የባሕርይ አምላክ አይደለም (ሎቱ ስብሐት!!!) ማለት ክርስትናን ከሥሩ ፈንቅሎ መጣል ነው:: ፠ስለ ክርስቶስ እግዚአብሔርነት ብሉይም ሐዲስም እየመሰከሩ (ኢሳ. 9:6, መዝ. 46:5, 77:65, ዘካ. 14:4, ዮሐ. 1:1, 10:30, ራዕይ. 1:8, ሮሜ. 9:5) አርዮስና የዛሬ መሰሎቹ አንዲት ጥቅስ ይዘው ክርስትናን ከመሠረቱ ለመናድ መሞከራቸው በእርግጥም ከሰይጣን መላካቸውን ያሳያል:: ፠በወቅቱም በመወገዙ 'ተበደልኩ' ብሎ የጮኸው አርዮስ ከ2ቱ አውሳብዮሶች ባልንጀሮቹ (ዘቂሣርያና ዘኒቆምድያ) ጋር ሆኖ ወደ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ ሔዶ ከሰሰ:: ቅዱሱ ንጉሥም የጉዳዩን ክብደት ተመልክቶ የዓለም ሊቃውነት ይሰበሰቡ ዘንድ አዘዘ:: ፠ከሚያዝያ 21 እስከ መስከረም 21 ተጠቃለው ገቡ:: በ325 ዓ/ም (በእኛው በ318 ዓ/ም) ለ40 ቀናት የሚቆይ ሱባኤን ያዙ:: ሱባኤውን ሲጨርሱም በ4ቱ ፓትርያርኮች (እለእስክንድሮስ: ሶል ዼጥሮስ: ዮናክንዲኖስና ኤዎስጣቴዎስ) መሪነት: በእለእስክንድሮስ ሊቀ መንበርነት: በአትናቴዎስ ጸሐፊነት ጉባኤው ተጀመረ:: ፠በጉባኤው ሙሉ ስልጣን በሰማይ ከፈጣሪ: በምድር ከንጉሡ የተሰጣቸው አበው አርዮስን ተከራክረው ከነ ጀሌዎቹ ምላሽ አሳጡት:: ክርስቶስ አምላክ ወልደ አምላክ: ሥግው ቃል: ራሱም እግዚአብሔር መሆኑን አስረዱት:: በጉባኤው መጨረሻም:- 1.አልመለስም በማለቱ አርዮስን አወገዙ:: 2.ጸሎተ ሃይማኖትን "ለመንግስቱም ፍጻሜ የለውም" እስከሚለው ድረስ ተናገሩ:: 3.ፍትሐ ነገሥትን ሥጋዊና መንፈሳዊ ብለው አዘጋጁ፡፡ 4.ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን እንደሚገባ አደራጁ፡፡ 5.በስማቸው የሚጠራ አንድ ቅዳሴን ደረሱ፡፡ ፠ይህ ሁሉ ሲሆን መድኃኒታችን ክርስቶስ 319ኛ ሆኖ እና ገሊላዊ ዻዻስን መስሎ ሁሉን አከናውኖላቸዋል:: አባቶችም ሥራቸውን ከጨረሱ በሁዋላ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስን ባርከው ወደየ ሃገረ ስብከታቸው ተመልሰዋል፡፡ ፠በየዘመኑም ዐርፈው ለክብረ መንግስተ ሰማያት በቅተዋል:: እኛም እነሆ "አባቶቻችን: መምሕሮቻችን: መሠረቶቻችን: ብርሃኖቻችን: ምሰሶዎቻችን" እያልን እናከብራቸዋለን:: =>318ቱ ቅዱሳን ሊቃውንት በጸሎታቸው እኛንም: ቤተ ክርስቲያናችንንም ከክፉ ጠላት ይጠብቁልን:፡፡ በረከታችው ምልጃቸው አይለየን ፡፡ ------ የቤተ ክርስቲያኑ ፎቶ፤ ሐመረ ኖኅ ሠለስቱ ምዕት ቤ.ክ፤ በሃገራችን በሠለስቱ ምዕት (በ318ቱ ሊቃውንት ስም) ብቸኛ የሆነውና በአሁኑ ሰዐት ከ4ቱ የመጻሕፍት ጕበኤያት በኢትዮጵያ ደረጃ የመጻሕፍተ መነኰሳት ዋና ማስመስከሪያ የሆነ ነው፡፡ ፠ በሃገራችን በሠለስቱ ምዕት (በ318ቱ ሊቃውንት ስም) ብቸኛ የሆነውና ከ1700-1701 ዓመታት በፊት በአፄ ቴዎፍሎስ (ስመ መንግሥት አጽራር ሰገድ) ታንጾ የነበረ ሲኾን ንጉሡ ሲያንጹትም የሠለስቱ ምዕት የአእላፍ መላእክትና የነቢያት ቤተ ከርስቲያን አድርገው ነው፤ ድርቡሽ ጎንደርን በ1880 በወረረ ጊዜ ጠፍ ኹኖ ቆይቶ በ2007 ዓ.ም. ቤተ ክርስቲያኑ ድጋሚ ተሠርቷል፤

ሰላም ለክሙ አርባዕቱ እነስሳሁ ፡፡ ለእግዚአብሔር መናብርቲኁሁ ፡፡ እሳታውያን ናሁ ሠረገላሁ ፡፡ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እንዘ ይብሉ ይሄልሑ፡፡ አሐተ ሰዓተ እንበለ አጽርዖ በጽርሑ ፡፡ ሰአሉ ለነ ትጉሃን ሐራሁ ፡፡ **መልክአ አርባዕቱ እንስሳ፡፡ በኢትዮጵያ ሀገራችን የአርባዕቱ እንስሳ (ኪሩቤል) ዓመታዊ ክብረ በዓል የሚከበሩባቸው አድባራትና ገዳማት በጥቂቱ:- 1.#ቤተ ፬ቱ(አርባዕቱ) እንስሳ (ማዕከላዊ ትግራይ አክሱም ጽዮን አጠገብ) 2.#ደብረ ዓሣ አርባዕቱ እንስሳ (ማእከላዊ ትግራይ ተምቤን) 3.#አርባዕቱ እንስሳ ቤተክርስቲያን (ሰሜን ጎንደር፤ጎንደር ከተማ) 4.#ቤተ አርባዕቱ እንስሳ አለት ፍልፍል (ሰሜን ወሎ አንጎት አካባቢ) 5.#መካነ ትጉሐን አርባዕቱ እንስሳ ቤተክርስቲያን (ደቡብ ጎንደር ደብረ ታቦር) 6.#ደብረ ኪሩብ አርባዕቱ እንስሳ ቤተክርስቲያን (ምዕራብ ሐርጌ መኢሶ አካባቢ) 7.#ዝቋላ አርባዕቱ እንስሳ ቤተክርስቲያን (ምሥራቅ ሸዋ ዝቋላ) *በኤርትራ* 8.#አርባዕቱ እንስሳ ቤተክርስቲያን (ሃዞሞ የሚባል አካባቢ) 9.#ራቂት(ዓዲ ናላ) አርባዕቱ እንስሳ ቤተክርስትያን (በራቂት/ዓዲ ናላ) ****በደባልነት ያለ በአዲስ አበባ የሚከበርባቸው ቦታዎች*** 9.#ደብረ ጽጌ ቅድስት ማርያም (አዲስ አበባ፣ አደይ አበባ) 10.#ቅዱስ በዓለ ወልድ ቤተክርስቲያን (አዲስ አበባ፣አራት ኪሎ) https://youtu.be/KrUaSIJ9_98 /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #Share #like

#እንኳን ለበዓለ ‹‹ኪሩቤል›› አርባዕቱ እንስሳ በሰላም አደረሳቹህ:: ኅዳር ፰፤ አርባዕቱ እንስሳ (ኪሩቤል) | አራት ኪሎ ቤ.ክ በዓሉ በድምቀት ይከብራል :: *በኢትዮጵያ ሀገራችን የአርባዕቱ እንስሳ (ኪሩቤል) ዓመታዊ ክብረ በዓል የሚከበሩባቸው አድባራትና ገዳማት በጥቂቱ:- ከታች ይመልከቱ :: #share ያድርጉ ----- ከእግዚአብሔር በቀር የሚቆጥራቸው የሌለ የብዙ ሠራዊተ መላእክት በሰማይ ያሉ ሲሆን በዙውን አንድ እያልን በነገዳቸው እንቆጥራል፡፡ ስንቆጥርም የመጀሪያዎቹ ኪሩቤል (አርባዕቱ እንሳሣ )ናቸው ፨ ኪሩቤል ቃሉ ከአካድ/ጥንት ባቢሎናውያን ቋንቋ / የተወረሰ ሲሆን ትርጉሙም አማላጅ፣ኃያል፣ታላቅ ማለት ነው፡፡በአራቱ እንስሣ አምሳል የተገለጹ ጸውርተ መንበሩ ኪሩቤል ናቸው ፡፡ #ኪሩቤል የብዙ ቁጥር ሲሆን በነጠላ #ኪሩብ ይባላል፡፡ ፨ መላእክት ሆነው ሳለ ‹‹አርባዕቱ እንስሳ›› የተባሉበት ምክንያት ለቅዱሳን ነቢያትና ሐዋርያት በእንስሳት አምሳል በመገለጻቸው ነው፡፡ ፨ ኪሩቤል ከመቶው ነገድ መላእክት የአስሩ ነገድ መጠሪያ ስም ነው ፨ ከ3ቱም ሰማየ መላእክት በመጀመሪያይቱ በኢዮር ላይ ከአጋዕዝት በታች በ2ኛይቱ ከተማ የሰፈሩ ናቸው፡፡ ፨ ከእግር እስከ ራሳቸው በዓይን ተሸልመዋል - ዓይናቸውን እንደ ነብር ለምድ ዥንጉርጉር ነው፤አንድም እንደ መስታወት ስድ ነው ፤ ይኸውም ኪሩቤል ኃላፊያትንና መጻእያትን የማወቅ ክሂል ከልዑል አምላክ መቸራቸውን ያሳየናል ፤ ይህም የእግዚአብሔር ስራ ገደብ የማይጣልለት የቸርነት ሥራ ነው፡፡ መዝ 87፥ 35 ፨ነቢዩ ሕዝቅኤል እንደተመለከታቸወ ‹‹ ኪሩባውያን አፍራሱ ፤ ፈረሶቹ ናቸው ሲል ይገልጻቸዋል፡፡ ግብራቸውም ዙፋኑን ተሸክመው ሥላሴ ለወደዱት መገለጽ ነው፡፡ ይህ ማለት ግን ዙፋኑን ተሸክመው ይዘዋወራሉ ማለት አይደለም፡፡ እግዚአብሔር መገለጽ ሲፈልግ ዙፋኑን በዘፈቀደ ተሸክመው ስለሚታዩ ነው ፡፡ ፨ከአራቱ ኪሩቤል አንዱ ‹‹ ባራ ማራ ›› የሚባል ነው አንደኛነቱ የቁጥር እንጂ የክብር መበላለጥ አይደልም፡፡ ትርጕሙም ባራ ማለት በራ ማለት ነው ፡፡ በተፈጥሮ በራነት እንዳለ በመሸከምም በራነት ይኖራል ፡፡ ጸዋሬ መንበርነቱን ሲመለከትም ‹‹ ባራ ማራ መሊጦን ›› ብሎ ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በምድራዊ ግሥ ገልጾታል፡፡ ፊቱም በአንበሣ ምስል ይገለጻል፤ ‹‹ ወቀዳሚ ይመስል አንበሳ ፤ የመጀመሪያው አንበሣን ይመስላል ›› እንዲል ራዕ 4፡፡ አንበሣ የአራዊት ንጉሥ ነውና በአለቃቸው ተመሰለ፡፡በአንበሣ መገለጹ ኃያልነቱን ሲያሳይ ነው ፍጻሜው ግን ‹‹ ሞዓ አንበሣ ዘእምነገደ ይሁዳ ›› የተበላው ክርስቶስ ይገለጣል ነው፡፡ ግብሩ ለአራዊት መለመን ሲሆን በሐዋርያው ቅዱስ ማርቆስ መመሰሉም የጌታን ሃያልነት ገልጾ ከማስተማሩ ጋር እና በአምሳለ አንበሳ የተሰሩ የግብፅ ጣዖታትን ቀጥቅጦ በማጥፋቱ ነው ፡፡ ፨‹‹መሊጦን መልአክ ›› ይህ ደሞ ሁለተኛው ሲሆን ሁለተኝነቱ የቁጥር እንጂ የክብረ መበላለጥ አይደልም፡፡ ትርጉሙም ዓምዳዊ ዘዐምድ እንደማለት ነው ዙፋኑን ተሸክሞ ‹‹ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ›› ብሎ ማመስገኑን ያሳያል ይህም መላእክት የሰማይ አምድ ናቸው ማለት ሳይሆን ግብራቸውን ያሳያል ፡፡ ቅዱስ ያሬድም ባራ ማራ .. መሊጦን ሲል ያዜማል፡፡‹‹ወካልዑ ይመስል ከመ ላሕም ››ሁለተኛውም ላም ይመስላል እንዲል ›› ራዕ እንዲል በላሕም ተመስሏል፡፡ በዚህም የተመሰለው ሉቃስ ሲጽፍ ‹ ‹ያን ላም አምጡት አርደን አወራርደን እንብላው ›› ሉቃ 15 ሲል ምሥጢረ ቁርባንን ጸፏል ፤ መሰየሙም ለዚህ ምክንያት ነው ፡፡ ፨‹‹እግረ ማጣ›› መልአክ ደግሞ አንዱ ነው ፡፡ቅዱስ ያሬድ ጸወርተ መንበር ብሎ በአንድነት ገልጻቸዋል፡፡ አምላካችንን በንጉሥ ፣ መንበረ ምንግሥቱን በኮር ፣ ሰማይ ውዱድን በአልጋ ፣ ኪሩቤልን በአራቱ እግሮቹ መስሎ ነው ፡፡ ይህ ከኪሩቤል አንዱ የሆነው መልአከ ፊቱ የሰው ልጅን ይመስላል ‹‹ወሣልሱ ይመስል ከመ ገጸ እጓለ እመ ሕያው ›› እንዲል ራእ 4 ፡፡ ይህ የሰው ፊት ያለው በማቴዎስ ይመሰላል ማቴዎስ ከአብርሃም ጀመሮ እስከ እመቤታችን ድረስ ልደተ አበውን ጸፏልና ፡፡ ፨‹‹ሱርትዮን መልአክ›› ይህ ደግሞ ትርጓሜው አገልጋይ ማለት ነው ፡፡ እሱም ዙፋኑን ተሸክሞ ሲያመሰግን ይኖራል ፡፡ገጹም ገጸ ንሥር ነው፤፤ ‹‹ወራቡዑ ይመስል ከመ ገጸ ንሥር›› እንዲል ራዕ 4፡፡ይህም ወንጌላዊውን ዮሐንስ የሚመስል ሲሆን ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌሉን ሲጽፍ አመሣጥሮ ስለሚጽፍ ንሥር ደግሞ ከፍ ብላ ሌሎች አዕዋፍ የማይደርሱበትን ሰለምታይ እሱም እንዲሁ በ ንሥር ተመስሏል ፡፡ ፨ኪሩቤል (4ቱ እንሰሳ ) ለተወከሉበት መልክእ ቅድም እግዚአብሔር ጸሎት ያደርጋሉ #የሰው መልክ ያለው ኪሩብ ‹‹እግረ ማጣ›› #ለሰው ልጅ፣ #የአንበሳ መልክ ያለው ኪሩብ‹‹ ባራ ማራ ››#ለአራዊት፣ #የላሕም መልክ ያለው ኪሩብ ‹‹መሊጦን መልአክ ›› #ለቤት እንስሳት፣#የንስር መልክ ያለው ኪሩብ ‹‹ሱርትዮን›› ደግሞ #ለአእዋፍ ሁሉ እየጸለየ ሲጠብቃቸው ይኖራል፡፡ ይህ ማለት ግን ምልጃቸው ገደብ አለው ማለት አይደለም አንዱ ለሌላኛው አንዱም ለሌላው መጸለይ መለመን ይችላሉ ማለት ነው፡፡ ፨የሰው ፊት ያለው ዕውቀታቸውን ፣ የአንበሣ ፊት ያለው ግርማ ሞገሳቸውን ፣ የንስር ፊት ያለው ተመሥአቸውን ( ሲመሰጡ ሰማየ ሰማያት ይደርሳሉ )፡፡ ትህትናቸው የፍርሃት ምልክት ሲሆን ምድር ምድር የመለከታሉ ይህም ፊቱን ማየት ባሕርዩን መመርመር አይቻለንም ሲሉ ነው ፡፡ ግርማቸው ነበልባል ሲሆን እንደ እሳት ለተልእኮ ይፋጠናሉ ፡፡ አእምሮአቸው ግሩም ሲሆን በእውቀት ከሁሉ በላይ ናቸው ፡፡ አራት ፊትም ስላላቸው ለተልዕኮ አቅጣጫ አይቀይሩም ያለምንም ተፋልሶ ባለቡት ይቀጥላሉ እንጂ ‹‹ ሕዝ 1›› ለእያንዳንዳቸው አራት ክንፍ አላቸው ይህም በአጠቃላይ 16 ይሆናል ፡፡ ክንፋቸውስ 6 ነበር ነገር ግን በሰው አምሳል ስለተገለጡ ሁሉቱ እጃቸው ነበር ፡፡ እንጂ ያው ስድስት ክንፍ ነው ያላቸው ፡፡ ሁለቱ ክንፋቸውን ፊታቸውን ይሸፍኑበታል( ባህሪያን መመርምር አይቻለንም ሲሉ ) ሁለቱን ደግሞ እግራቸውን ይሸፍኑበታል( ከፊትህ ጸንቶ መቆም አይቻለንም ሲሉ ) ፣ ሁለቱን ደግሞ አንዱን ወደ ታች አንዱን ወደ ላይ ይዘረጋሉ( ቢወጡ ቢወረዱ አትመረመርም ሲሉ ) ፡፡ ፨የክንፋቸውም ጅግጅታ እንደ ፏፏቴ ከሩቅ ይሰማል ፡፡ ለመላእክት 6 ክንፍ ሲኖራቸው ለእንያንዳንዳቸው ኪሩቤል 16 ክንፍ በጠቅላላው 64 ክንፍ አላቸው ፡፡ ከዚኅ ጋርም ተያይዞ ‹‹ ከኪሩቤል እና ከሱራፌልም እሳ ትበልጣለች ›› የተባለቸው እመቤታችን እንዲዚህ መባሏ አንድም ኪሩቤል በክንፋቸው ጋርደው አምላከ ምሕረት ክርስቶስን ሲያመሰግኑባት አይቶ ነው ፡፡ ምልጃቸው አይለየን ፡፡ አሜን ! ---- በቅዱስ በዓለ ወልድ

ኅዳር 7 ( ፯ ) የሊቀ ስማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቅዳሴ ቤቱ ነው ። ፠ኅዳር 7 ከ፯ቱ ቅዱሳን ዘጋሥጫ አንዱ የኾኑት፤ #አቡነ_ገብረ_እንድርያስ_በዓለ_ዕረፍታቸው_ነው፨ ------- መክብበ ሰማዕት ፥ ሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ፤ ኰከበ ልዳ፥ ፀሐየ ፋርስ፤ ቅዱስ ጊዮርጊስ፤ የኢትዮጵያ ገበዝ፤ ከአውሎ ነፋስ ይልቅ ፈጥኖ የሚደርስ ፈጥኖ ደራሽ ሰማዕት፤ እንደ እናቱ (እኅቱ) ቅድስት ማርያም ርኁሩህ የኾነ፡፡ ኅዳር 7 ቅዳሴ ቤቱ (ለመጀመሪያ ጊዜ የተሠራው ቤ.ክ የተመረቀበትና ቅዳሴ የተከናወነበት ክብረ በዓል) ነው፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሚያዚያ 23 ቀን በሰማዕትነት ከሞተ በኃላ አጋልጋዮቹ እጅግ የከበሩ ልብሶችና ያማሩ ሽቶዎች አዘጋጁ በከበረ አገናነዝም ገነዙት በመርከብም ጭነው ወደ ትውልድ አገሩ ልዳ አመጡት ነገር ግን ቤተሰቦቹ በሙሉ ማለትም አባቱ ዘሮንቶስ እናቱ ቴዎብስታ እህቶቹ ማርታና እስያ እንዲሁም አጭተውለት የነበረች እጮኛው ሁሉም ሞተው አገኙዋቸው፤ እንድርያስ የሚባል አጎት ነበረው ስጋውን ተቀበላቸው አገሬው ተሰበሰበ የእየሩሳሌሙ ሊቀ ጳጳስ አባ ቴዎድሮስ ተጠርቶ መጣ ቤተክርስቲያኑን አነጹለት ስጋውንም በዚያ በክብር አኖሩት፤ በዚህች ቀን እጅግ ብዙ የሆነ ድንቅ ታአምራትና ታላላቅ ኃይላት ተደረጉ፤ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ቤተክርስቲያን ይህንን ቀን ታከብረዋለች። ታላቁ ንጉሳችን እምዬ ምኒሊክ አራዳ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያንን ሲሰሩ ከዚሁ ከልዳ የቅዱስ ጊዮርጊስ መቃብር ካለበት አፈሩን በመርከብ ከዚያም በበቅሎ አስጭነው አምጥተው ለቤተክርስቲያኑ መሰረት እንዳደረጉት እና ቅጥሩን ዙርያውንም እንደነሰነሱት መጻሕፍት ይናገራሉ ፡፡ ፠ ፠ በዓሉ በድምቀት በገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ.ክ (በአራዳ ጊዮርጊስ) ይከበራል ———- ፨ ኅዳር ፯፤ (የአቡነ ገብረ እንድያስ በዓለ ዕረፍትና ነው)፨ ፠ ዕፁብ ድንቅ የኾነ ተዓምራትን የሚሠሩት እንጨቱ ጸበላቸው_=ውስጥ ሲገባ መቊጠሪያ የሚያደርጉት ፤ (በፎቶ የምታዩት)፤ ፠ በጠበላቸው ድንቅ ድንቅ የሆኑ ተዓምራትን የሚያደርጉት ፠ ፻ ትውልድ የሚያስምሩት፤ ፠ በደንጊያ ሠረገላነት የሚጓጓዙት፤ ፠ ከ፯ቱ ቅዱሳን ዘጋሥጫ አንዱ የኾኑት፤ #አቡነ_ገብረ_እንድርያስ_በዓለ_ዕረፍታቸው_ነው፨ ቦታቸውን ክርስቲያን የኾነ ኹሉ ሊያየው የሚገባ የተዓምራት ቦታ ነው፤ ✤✣✤ #ጻድቁ_አቡነ_ገብረ_እንድርያስ_ዘወለቃ_ወዘደብረ_ቆዘት_፤ ✤አባታቸው ተንሥአ ክርስቶስ፥ እናታቸው አርሴማ ሲባሉ፥ የትውልድ ሀገራቸው ወሎ፥ ቦረና፥ ጋሥጫ ሲኾን፤ የቀድሞ ስማቸው ንፍታሊም ይባል ነበር። ✤ ለትምህርት ሲሄዱ መምህራቸው ብዙኃኑን የምታድን ጻድቅ ትሆናለህ ብለው ትንቢት የተናገሩላቸው ሲኾን፤ የመጻሕፍትን ትርጓሜ በደንብ ካስተማሯቸው በኋላ ንፍታሊም ይባል የነበረውን የቀድሞ ስማቸውን ለውጠው ገብረ እንድርያስ አሏቸው። ✤ ጻድቁ በአቡነ ከማ ገዳም ለረጅም ጊዜ በታላቅ ተጋድሎ አገልግለዋል፤ ብዙ አባቶች ሱባኤ በሚይዙበት በስኮሩ ሥላሴ ቤተክርስትያን ጸሎት ሲያደርጉ ቅዱስ ዑር(ራ)ኤል በወርቅ ጽዋ ማየ ሕይወት አጠጥቷቸዋል። ✤ ጻድቁ አባታችን ሙታንን በማስነሳትና ድውያንን በመፈወስ ብዙ ተአምራትን ሲያደርጉ ኖረዋል። ✤ ጻድቁ ዐርብ ፥ ዐርብ የጌታችንን ቅዱስ ሥጋውን ና ክቡር ደሙን ለመቀበል ወደ ኢየሩሳሌም ይመላለሱ የነበረው በአየር ላይ ድንጋዩን እንደ ሰረገላ ፥ ዋርካውን እንደ ጥላ እየተጠቀሙበት ነበር። ይህ ሰረገላ የሆነው ድንጋይ በገዳማቸው ዛሬ ድረስ ይገኛል። (ፎቶውን ይመልከቱ) ✤ ጻድቁ አባታችን እግዚአብሔር ኀጥአንን እንዲምርላቸው ርቀት ወንዝ ከተሰኘው ቦታ በአንገታቸው ላይ በጣም ትልቅ ድንጋይ እየተሽከሙ ይጸልዩ ነበር። በዚህም ይጸልዩበት በነበረው ወንዝ ውስጥ በተአምራት መቊጠርያ የሚሰራ ጸበል ፈለቀላቸው፤ ጠበላቸው ውስጥም እንጨት ሲነከርበት እንጨቱ በተአምራት መቊጠርያ ሆኖ ይወጣል፤ ይኸውም መቊጠሪያ ለብዙ ሕመሞች መድኀኒት ነው፡፡ (ፎቶውን ይመልከቱ) ✤ ✤ ✤ አቡነ ገብረ እንድርያስና ሊቀ ሰማዕቱ ስለ ሃገራችን በተቀበሉት ቃል ኪዳን ሰላምና ጤና ያውርዱልን፤ ጠላታችንን ከሃገራችን ያባርሩልን፨ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #Share #like