❤የፍቅር እውነታ❤
Відкрити в Telegram
❤️ የፍቅር ግጥሞች ❤️የፍቅር ጥቅሶች ❤️ የፍቅር ደብዳቤዎች ❤️ የፍቅር መልእክቶች ፍቅርን💓 የመሰለ ምን አለ! 🚩 አስተማሪ እና አዝናኝ ገጠመኝ እዚ ይገኛል 🔴 የፍቅር ጉዋደኛ ፣ ❣ወርቃማ የሆኑ የፍቅር አባባሎች ✅ @yefkl_eweneta Contact 👇👇 @BAMII213 @ferid69 . . . . . . . . @AFEKARIWE
Показати більшеКраїна не вказанаКатегорія не вказана
1 998
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
+230 днів
Архів дописів
1 998
ወረሃ ሚያዚያ። ነፋሱ አፉን አሞጥሙጦ ያፏጫል። አቧራውን እያቦነነ መንገደኞችን
ያበሳጫል። ዛፎች ተደናግጠዋል፤ ነፋሱ ሊደፍራቸው ያሰበ ይመስል ያስጎነብሳቸዋል። ይሄ
ነፋስ ባልጓል። ይሄ ነፋስ ከአበቦች ገላ ቅጠል ይሰርቃል። ከሰብሎች አካል ፍሬ ያጎድላል።
የሚከሰው ስላልተገኘ እንደልቡ ነው የሚሆነው። የሚፈርድበት የለም።
ከሳሽ የለም አንድስንኳ ...
ትንቅንቅ ነው።
የማይወደድ።
የተከፋ ዘመን ነው። እንደ ሐምሌ አልቅሶ የማይወጣለት፣ ፊቱን አክብዶ የሚያመሽ ... ንጋት
እንኳ ተስፋ ኾኖ እንዳይቀር የሚሰጋበት ፅልመታም ዘመን። (አንፖል ታቅፎ ጨለማ
የሚለግስ አረመኔ ዘመን)
👑BAMII👑
1 998
ይቀፋል ... ቀኑ። የሰማይ ደማቅ ቀለማት ጠይመዋል። የሆነ ትከሻ ላይ ተከምሮ ቁልቁል
የሚገፋ ጋግርት ነበረው። በጎዳናው ላይ የሚርመሰመሱ ሰዎች ገፅታዎች በሙሉ ከከባድ
ዶፍ በፊት ያለውን የሐምሌ ሰማይ ይመስላሉ። በደራረቡት ሹራብ፣ ጃኬትና ካፖርት ስር
ጭብጥ ፣ ኩርምት እንዳሉ ... ወደ ዕለት ግብራቸው ይጣደፋሉ። ቅዳሜና እሁድ ፍኩ
የእረፍት ቀናቸው ያልበረከተላቸው ... ምስኪን የሰኞ ማለዳ ተጓዦች!።
👑BAMII👑
1 998
💡አስተማሪ ነው ይነበብ !!
-------------''------------
ሰውየው አስር ክፍል ቤት ሠርቶ ብቻውን ሲኖር አንድ
ቀን በሩ ተንኳኳ ሲከፍት ጌታ ነው፡፡ "ውይ አምላኬ
ጌታዬ አንተ እኔ ቤቴ መጣህ?" ብሎ በደስታ
ተቀብሎት አንድ ክፍል ቤት ሰጥቶት መኖር ጀመሩ፡፡
በሌላ ጊዜ በሩ ተንኳኳ፣ ሲከፍት ሰይጣን ነው፡፡
ተበሳጭቶ ይዘጋና "ጌታዬ ሆይ አንተ እኔ ቤት እያለህ
ሰይጣን የእኔን ቤት እንዴት ያንኳኳል?" አለው፡፡
ጌታም "ቤቱ የአንተ እንጂ የእኔ አይደለም " አለው፡፡
ሰውየውም ተሰምቶት ሁለት
ክፍል ቤት ለጌታ ጨምሮለት እርሱ ሰባት ክፍል ይዞ
መኖር ቀጠሉ፡፡ በሩ ተንኳኳ ሲከፈት ሰይጣን ነው፡፡
ተበሳጭቶ ይዘጋና "ጌታዬ ሆይ አንተ እኔ ቤት እያለህ
ሰይጣን የእኔን ቤት እንዴት ያንኳኳል? " አለው፡፡
ጌታም " ቤቱ የአንተ እንጂ የእኔ አይደለም " አለው፡፡
ሰውየውም ተሰምቶት ከጌታ
ጋር እኩል ለእኩል ተካፈለ፡፡
ነገር ግን ቤቱ ከቀድሞ ይልቅ ተንኳኳ ፡፡ አዝኖም
ይዘጋና ጌታ ሆይ አለው፡፡ ጌታም የቀድሞውን መልስ
ሰጠው፡፡
በዚህ ጊዜ ሰውየው ለራሱ አንድ ክፍል ቤት ይዞ
ዘጠኙን ክፍል ቤት ለጌታ ሰጠው፡፡ ነገር ግን
ከቀድሞው ይልቅ በጣም ተንኳኳ፡፡ ቢከፈት ሰይጣን
ነው፡
በሩን ይዘጋና ወደ ጌታ ሄዶ " ጌታ ሆይ ምሥጢሩ
ምንድን ነው? " አለው፡፡ "ጌታ ግን ቤቱ የአንተ እንጂ
የእኔ አይደለም "አለው፡፡
በዚህ ጊዜ ዐሥሩንም ክፍል ለጌታ አስረከበ፡፡ ጌታም
አንድ ክፍል ቤት ለሰውየው ሰጠው፡፡ በሩም ተንኳኳ
፡፡ ጌታም ሊከፍት ተነሣ፡፡ ሲከፍት ሰይጣን ነው፡፡
ሰይጣንም " ይቅርታ የአንተ ቤት መሆኑን አላወቅሁም
" ብሎ ሄደ፡፡ ከዚያን ቀን ጀምሮ መንኳኳት ቆመ፡፡
ሁሉንም የሕይወታችንን ክፍል ለጌታ እግዚአብሔር
ካላስረከብነው መንኳኳት አይቆምም፡፡ 1ዐ% ስንሰጥ
ይንኳኳል፡፡ 30% ስንሰጥ ይንኳኳል፡፡ 50% ስንሰጥ
ይንኳኳል፡፡ 99% ስንሰጥ ይበልጥ ይንኳኳል፡፡ 100%
ስንሰጥ መንኳኳት ይቆማል፡፡ እኛ ከከፈትን ሰይጣን
ይገዳደረናል፡፡ ጌታ ሲከፍት ሰይጣን " ይቅርታ የአንተ
ቤት መሆኑን አላወቅሁም " ብሎ ይሄዳል፡፡
እግዚአብሔር ሰማይን የደስታ አገር ያደረጋት ሙሉ
በሙሉ የእግዚአብሔር ፈቃድ የጸናባት በመሆኗ ነው፡፡
ባንተም ሕይወት የሰማይ ደስታ የሚመጣው
የእግዚአብሔር ፈቃድ በሕይወትህ ሙሉ በሙሉ
ሲፈጸም ነው፡፡ ስለዚህ፡-
· እግዚአብሔርን እረኛህ አድርገው፡፡
· በፍጹም ልብህ ተከተለው፡፡
· የሚያስፈልጉህ ነገሮችም አንተን ይከተሉሃል፡፡
"ሙሉ ሕይወታችንን ለእግዚአብሔር እናስረክብ።"
መልካም ምሽት🥰
1 998
❤️
አንዲት ልጅን አፈቀርኩኝና እሷን ለማጨት ወደ ቤተሰቦቿ ሄድኩኝ ከቤተሰቦቿ ጋር
ተቀምጬ ሳለሁ ታናሽ እህቷን ተመለከትኳት ከታላቋ(ከማጫት ሴት) የበለጠ በጣም ቆንጆነበረች ::
ታናሽየዋን ባየዃት ቁጥር ወደኔ ታያለች አልፋም በአይኖቿ ትጠቅሰኝ ጀመር ::
ከሁለት ቀናት በኋላ ታናሽ እህቷ ደውላ ለአስቸኳይ ጉዳይ እንደምትፈልገኝ እና አሁኑኑ እንድመጣ ነገረችኝ ሄድኩኝ ስደርስ በጣም የሚስብ(ለወሲብ የሚጋብዝ ) ልብስ ለብሳ ነበር ::
ምንድነው ስል ጠየኳት እሳም 200 ዶላር ስጠኝና የፈለከውን አድርግ አለቺኝ:: ጥያት ወጥቼ ወደ መኪናዬ ጋ ስደርስ ከኋላ የሆነ ሰው ጠራኝ ስዞር አባቷ ነበር እንኳን ደስ አለህ ፈተናውን በሚገባ አልፈሀል ልጄን ሰጥቼኻለሁ አለኝ ::
አሁን ይሄ ከተፈጠረ ሀያ ዓመታት አልፈዋል ማንም ግን ወደ መኪናው የሄድኩት 200 ዶላሩን ለማምጣት
እንደነበር አያውቅም.....
#ማስታወሻ:- ምን ለማለት መሰላቹ...? ፈልጋቹ ድረሱበት!
1 998
ሳምሶን ከሚስቱና ከሚስቱ እናት ጋር እየኖረ... ሁሌ ከሚስቱጋ ይጣላና እንዲያስታርቀው ያገባ ጏደኛውጋ ይመጣል
ሳምሶን፡- "ሰው የገዛ ባሉን እንዴት ሰ….ቀጫን! ብሎ ይሰድባል?" ይላል ብክንክን ብሎ
ጏደኛው ፡- "ሰቀጫን?.... ምን ማለቷ ነው?"
ሳምሶን፡- "እሱማ ስግብግብ፣ ቆንቋና እንደማለት ነው፡፡"
የጏደኛው ሚስት፡- "ሆ!! ....ምን ብታደርጋት ነው ቆይ ሰ…ቀጫን ያለችህ?"
ሳምሶን ፡- "እሱማ እ…. እንትን … እንጀራ ስቆጥር እናቷ አይተው ነገሯትና …"
ጏደኛው ፡- "በስመአብ !! ......ቱ !!!!......አንተ?"
ሚስትው፡- "አበስኩ ገበርኩ!!!"
ሳምሶን ፍጥን ብሎ ፡- "ለጥቂት እኮ ነው ... እንጀራው ትኩስ ሆኖ እየተደራረበ አልሄድ ብሎኝ (የደብተር ገፅ እንደመግለጥ በእጁ እየቆጠረ )እንጂ እኮ ለጥቂት ልጨርስ ነበር::"
ጏደኛው ፡- "ሂድ!!.... ሂድ አንተ!!!!!......... ሰ…ቀጫን!!!.............. አሁን እንጀራ ስትቆጥር ተይዘህ አስታረቅኩህ በኋላ ስኳር ስትቆጥርስ?"
ሳምሶን(ከአፉ ቀበል አድርጎ)፡- "ማን ?....እኔ?....... ኸረ አይለመደኝም!!!! ሁለተኛ……….. በእርሳቸው ፊት ልቆጥር ?.......አላደርገውም!!"🤣🤣🤣🤣
*ትዳር ሲታጠን
1 998
ኢትዮዽያ መኪና ነድቼ አላውቅማ ... ራሴ ነዳለሁ ብዬ መኪናውን ልከራይ የቀጠርኩት ሰውዬ ...
"አይከብድሽም? እርግጠኛ ነሽ? ረዥም አመት እንኳን ውጪ የነዱትኮ እዚህ ይፈራሉ .... (ሲያስፈራራኝ ከቆየ በኃላ ) ለማንኛውም እስኪ አብረን ሆነን ልይሽ" ብሎ ከኃላ ተቀምጦ ስንዳ ... ሲኖትራክ ሲንቀለቀል መጣ ...
"ውይይ ይለፍ ቆይ ያስፈራል" አልኩት ...
"ገና እሩቅ ነውኮ .."
"አይ ቢሆንም አመጣጡን እየው ያስፈራል::" እለዋለሁ:: ምን ቢለኝ ጥሩ ነው?
"በዚህ አያያዝሽ ሹፌሩ ወርዶ ሁላ እለፊ ቢልሽ...'በማርያም ሞተሩንም አጥፋውና ነው የማልፈው' ትያለሽ::"
ወዮዮዮዮዮዮዮ 🙆🏻♀️🙆🏻♀️🙆🏻♀️🙆🏻♀️🙆🏻♀️🙆🏻♀️🙆🏻♀️🙆🏻♀️
ውብ ቀን ውብኛ አዋዋል ዋሉማ❤️❤️❤️❤️
1 998
በአንድ ጫካ ውስጥ አንበሳና ድኩላ ይጮኸሉ፡፡ ሁለቱም የነበሩበት ቦታ የተራራቀ ከመሆኑም በላይ አካባቢው ጥቅጥቅ ያለ ጫካ በመሆኑ በድምፅ ካልሆነ በስተቀር አይተያዩም ነበር፡፡ የሁለቱም ጩኸት ታዲያ ለፈጣሪያቸው የሚያደርሱት ጸሎት ነበር፡፡ አንበሳው ‹‹እባክህ አምላኬ ለዛሬ የሚሆን ምግብ ፍጠርልኝ፡፡›› እያለ ጮክ ብሎ ይጸልያል፡፡ ድኩላውም በበኩሉ ‹‹ፈጣርዬ ሆይ አንበሳና ነብር ከመሳሰሉ ጠላቶቼ ጠብቀህ በሰላምና በሕይወት አውለኝ›› በማለት ጸሎትን ያሰማል፡፡
በመካከሉ አንበሳው መጮኹን አቁሞ የድኩላው ድምፅ ወደ ሰማበት አቅጣጫ መጓዝ ጀመረ፡፡ ድኩላው የአንበሳውን ድምፅ መጥፋት ባወቀ ጊዜ ይኼኔ አንበሳው ወደኔ እየመጣ መሆን አለበት በማለት ፈራ፡፡ የፈራውም አልቀረ አንበሳ እየተሽሎከሎከ ድኩላው ካለበት ደረሰ፡፡ በዚህን ጊዜ ድኩላው ባለ በሌለ ኃይሉ እግሬ አውጭኝ በማለት መሮጥ ጀመረ፡፡ አንበሳ ፍጥነቱን በመጨመር ድኩላውን ለመያዝ ይወረወር ጀመር፡፡
በዚህ መካከል ግን አንድ አጋዘን ሣሩን በልቶ፣ ውሃውን ጠጥቶ፣ ያለ ሐሳብ ተኝቶ ያመነዥካል፡፡ አንበሳው ድኩላውን ለመያዝ ትንሽ ሲቀረው ድንገት ሳያስበው ከተኛው አጋዘን ዘንድ ደረሰ፡፡ በዚህን ጊዜ ድኩላውን ማሳደድ ትቶ ያልታሰበ ሲሳዩን ያጣጥም ጀመር፡፡ ይኼኔ ታዲያ፡-
"አውጣኝ ያለም ወጣ
አብላኝ ያለም በላ፣
ያልጸለየ አጋዘን ተበላ፤" ተባሎ ተገጠመ፡፡
ጠዋት ስትወጣ ፀልይ፤ ማታ ስትገባ አመስግን እንደወጣክ ባለመቅረትህ፡፡
ሰናይ ምሽት!!!
@yefkl_eweneta
1 998
የማያልፍ ይመስላል ፥ ቀን አጉል ሲረዝም
ሲያደክም፣ ሲያዝለን ፥ ለከንቱ ስንቆዝም፤
ከደስታ ከሳቁም
ከናፍቆት ፀፀቱም
ከመዋል ካ'ዳሩም
በጥቂት በጥቂት እየጨላለፍኩት
እየቀማመስኩት
ላልኖር የመሰለኝ ፥ ይኸው ኖሬ አየሁት።
ከሁሉ ከሁሉ ፥ የቸገረኝ ነገር
የፍቅር የመውደድ
የሴት ልጅ ልኬን
እንዳይደርሱት አርገሽ ፥ ባትሰቅይው ምን ነበር።
👑BAMII👑
1 998
አንዳንዴ ተስፋ መቁረጥ ጥሩ ነው::
በተስፋ አለመቁረጥና በትእግስት ብዙ ነገር እንደሚሳካ አምናለሁ:: አንዳንዱ ነገር ግን በቃ አይሆንም .... ከብርትኳን ዛፍ ላይ በየዓመቱ እያፈጠጥክ ማንጎ መጠበቅ ... አይሆንማ!!!...
ወይ ማንጎ ተክለህ ጥበቃህን ትክክለኛ ቦታው ላይ አድርግ ወይ አርፈህ ብርትኳንህን እየቀጠፍክ አጣጥም..... ወይ በእምነት መንጎ ነህ ብያለሁ መንጎ ነህ ብለህ ግግም 🤣🤣🤣🤣
የተዋበ ቀን ዋሉማ❤️❤️
1 998
ስትጀምር ይንቃሉ፡፡ስትሳሳት "ብለን አልነበር!" ይላሉ፡፡መሐል ስትደርስ ወደ ኋላ ይጎትታሉ፡፡ወደ መጨረሻው ስትቃረብ መንገድ ይዘጋሉ፡፡እንደምንም ስታሳካው ግን መግቢያ ያጣሉ፡፡ወዳጅ መስለው ወደ አንተ ይመጣሉ፡፡"እንኳን ደስ ያለህ!" ይላሉ፡፡አንተ ግን ስትጀምርም አትስማቸው፡፡ስትጨርስም አትስማቸው፡፡ራስህ ላይ እና ስራህ ላይ ብቻ አተኩር፡፡ስኬት ሲመጣ ወደ አንተ የማይመጣ የለም፡፡መጀመርያ ስኬታማ ሁን፡፡
1 998
ራሷን እንደ ድስት ትቆጥረዋለች፤ የፍቅር ሽንኩርት ተቁላልቶ የሚከሸንበት ድስት። ሁል ጊዜ
እሷ ስር ምን አለ? እሳት! የሚጨልም የማይመስል የመውደድ ብርሃን! ሁሌም በፍቅር
ፍም እንደሞቀች ነው።
ግና ቀረብኳትና ቀየርኳት። ቀረብኩና ልቧን ወሰድኩት። አሸነፍኳት። እጇን ሰጠችኝ።
እጇን ሰጠችና -
የሰው ገላ እንደ ሽንኩርት ነው። በላጥከው ቁጥር አዲስ ገላ ይሆንብሃል´ ማለቷን
ተወችው።
ትኩስ ውበት ለመዳሰስ፣ አዲስ ጠረን ለመታጠን መጓጓቱ ምኑ ላይ ነው ነውሩ?´ ማለትን
አቆመች።
አቆመችና የኔ ብቻ ሆነች። ቀስ በቀስ - ቀስ በቀስ ግን ቅናት መጣና ፍቅራችንን
አቆሸሸው። ገባት። የፍቅርን ሽንኩርት ሲልጡት ዐይንን ቆጥቁጦ እንደሚረብሽ ...
✍Abbi koche1 998
በፈጣሪ እምናለው ብሎ ያስባል::ነገር ግን ስለፈጣሪ ከሚያስበው በላይ ስለችግሩ አብዝቶ ያስባል::ከአንደበቱ የሚወጣው ምስጋና ሳይሆን ማማረር ነው::በአገሪቱ ፈጣሪ ከሚያደርገው ገደብ አልባ በጎ ነገሮች በላይ ስይጣን ያደረጋትን ጥቂት ክፉ ነገር በማህበራዊ ሚዲያ ሲያንሸራሽር ይውላል::የአምላክን እርዳታ እና የህይወት በረከት አይመለከትም::እምነቱ ለስም ነው::የመንፈስ አይደለም::በአምላክ የእውነት እምነት ያለው ሰው በሚሆነው ነገር አያለቃቅስም::የሚሆነው ነገር ሁሉ ለበጎ እንደሚሆን ያምናልና::እንዲስተካከል የሚፈልገው ነገር ካለ በፍጹም እምነት አምላኩን ይጠይቃል::በራሱ ማድረግ ያለበትን ነገር ሁሉ ያደርጋል::በህይወቱ ለሆኑ ነገሮች ማንንም አይወቅስም::በአገሩ ለሚፈጠረው ስቃይ ጣት አይጠቁምም::ምክንያቱም የሚሆነው ነገር ሁሉ የሚሆነው ለበጎ እንደሆነ ያውቃል::በእርግጥ የእርሱ ደስታ ትልና ብል በሚበላበት በምድር ስኬት አይደለም::ደስታው ትልም ብልም በማይበላው በሰማይ ባለው አምላክ ነው::ፈጣሪ ደግሞ ሁሌም ፍጹም ነው::ገንዘብ ባይኖር....የአገሩ ፓለቲካ ቢበላሽ...ኑሮው ቢወደድ...ታመን ብንተኛ...ስራ ብናጣና ምንም ነገር ቢሆንብን አምላክ ሙሉ ነው::በገንዘብ: በፓለቲካ መረጋጋት ወይም በየትኛውም የአለም ነገር የማናገኘውን እርካታ በእምላክ ማግኘት እንችላለን::የትም ብንሆን ማንም ብንሆን ይህ የአምላክ መንፈስ ነጻ ነው::ይህን ውሳጣዊ እርፍት ያላገኘ እምንቱ የውሸት ነው::እውነተኛ አማኝ እያንዳንዱ ሁኔታ ወደ አምላኩ እንዱያቀርበው ያደርጋል::በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ እንደ ጸሐይ ያበራል::ምክንያቱም ከ10ሺ ጸሐይ አብልጦ የሚያበራው የአምላክ መንፈስ በውስጡ እንዳለ ያውቃል::
1 998
አባትህን 1ሺህ ብር ጠየቅከው፤እሱም ጠዋት ለስራ ከመውጣቱ በፊት እሰጥሀለሁ
ይልሃል። አባትም ማታ እያሰላሰላ ሳይተኛ ያድርና ሲነጋ ገንዘቡን ከመስጠቱ በፊት ጠርቶህ
የተለያዩ ጥያቄዎችን ይጠይቅሀል፤ብቻ ጥያቄዎቹ የሚያናድዱ ናቸው።.."ገንዘቡን ምን
ልታደርግ ነው? ለዚህች ፕሮግራም ይሄ ሁሉ ገንዘብ ምን ይሰራል?.." ወዘተ ሲል
ከጨቀጨቀህ በኋላ 100 ብር ቀንሶ 900 ብር ይሰጥሃል።
አንተም እያጉረመረምክ.. ''ሙሉ አይደለም ግን አመሰግናለሁ'' ብለህ ትቀበለዋለህ።
ይህንን ያየችው እናትህ ወደ ክፍልህ ትመጣና "በርሱ ድርጊት አትናደድ እንካ የጎደለህን
በዚህ ሙላ ብላ" 200 ብር ከሷ ገንዘብ ላይ ትሰጥሃለች።አንተም ወደ FB ትመጣና "እናቴ
ትለያለች".."የኔ እናት አይነት ምድር ላይ አልተፈጠረችም" ትለናለህ።አባትህ ግን ባንተ
ምክንያት የትራንስፓርት አጥቶ በእግሩ ነበር ወደ ስራ ቦታ የሄደው፤ለምሳም ወደ ቤት
አልመጣም ነበር ምክንያቱም በእግሩ መጥቶ ለመመለስ ስለሚርቅበት። ከስራም ደክሞት
አምሽቶ ሲገባ ትንሿ ልጅ ትመጣና "ዳዲ እኛን አትወድም ከኛ ጋር መዋል አትፈልግም ወደ
መጫወቻ ቦታ ሁሌ የምትወስደን ማሚ ብቻ ናት" ትለዋለች...በዚህ ሁሉ ግን አባትህ
በምን ውስጥ እያለፈ እንደሆነ እንዲታወቅበት አይፈልግም ምክንያቱም አባት ነውና።
# ትምህርት ለኛ ብለው በብዙ ውጣ ውረድ እያለፉ ያሉ አባቶቻችን ጊዜው ሳይረፍድብን
በህይወት እያሉ ሊመሰገኑ ይገባል።አጠገብህ አልዋለም ማለት አያስብልህም ማለት
አይደለም። ለወላጆቻችን እኩል ፍቅር ሊኖረን ይገባል ወደ አንዱ ያጋደለ [one sided love]
አደገኛ ነው።
እናት ከልጆች አጉል ክብር ለማግኘት ብላ ከልጆች ጋር ሚስጥራዊ ግኑኝነት ሊኖራት
አይገባም አባት ያላወቀውን ገንዘብ በድብቅ መስጠት ተገቢ አይደለም፤አባታቸው የሷን
ያህል እንደማይጨነቅላቸው ማስተማርም ጥሩ አይደለም!! ክብር ለአባቶች ይሁን!!
