cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

Abdulwekil’s official

Plan as your work, work as your plan

Більше
Рекламні дописи
207
Підписники
Немає даних24 години
+27 днів
Немає даних30 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

Repost from AASTU Muslims union
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ السلام عليكم ورحمة الله وبركاته 🔊🔊🍁የሙሓደሯ ጥሪ 🍁 ለአዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪች እና በዙርያው ለምትገኙ በሙሉ፡፡ ነገ ረቡዕ  13/09/2016 በአልነጃሺ መስጂድ በአይነቱ ልዩ የሆነ የዳዕዋ ኘሮግራም ተዘጋጅቶ ይጠብቃቿል፡፡ስለሆነም ለሁሉም የኣ.ሳ.ቴ.ዩ ተማሪዎች እና የእስታፍ አባላቶች እንዲሁም ለመላው የቂሊንጦ ማህበርሰብ ፕሮግራሙ ላይ እንድትገኙ ስንል የአክብሮት ጥሬያችንን ለማስተላለፍ እንወዳለን፡፡ 💎 ርዕስ፡- فاستقم كما أمرت ተጋባዥ እንግዳ:-የቀድሞው አሚራችን ወንድም ሙሀመድ ሱልጧን       ፕሮግራሙ 10:20(localtime)⏳ላይ  ስለመጀሚር አስር ሶላት በመስጂዳችን እንስገድ።                            ሊቀርም ሆነ ሊረፈድበት የማይገባው ፕሮግራም መሆኑ መረሳት የለበትም‼️
Показати все...
Show comments
ለጠቅላላ ዕውቀት እንዲሆናችሁ፦ ①) ከሺዓዎች መካከል በአንፃሩ የተሻሉ የሚባሉት ዓልይን ከአቡበከርና ዑመር የሚያስበልጡት ናቸው። ②) ሺዓዎች አቡበክርና ዑመር ካፊር ናቸው ይላሉ። አዑዙ ቢላህ! አቡበከር'ኮ "የርሱ ኢማንና የዚህ ኡማ ኢማን ቢመዘን የርሱ ይበልጣል!" ብለው ውዱ ነቢይ ﷺ የመሰከሩለት ነው! أفضل الخلق بعد الأنبياء! ታዲያ እንደት ነው እነዚህን ተራሮች ጭራሽ ካፊር የሚባሉት? በዚህ ማመንንም ሺዓህ ለመሆን እንደ ሸሃዳ ነው የሚያዩት። ③) ከአቡበከርና ከዑመር ባሻገር አጠቃላይ ሶሐቦችን ከእስልምና ያስወጣሉ። ከ7ቱ በስተቀር ሌሎቹ ሁሉም የነቢዩ ﷺ ሶሐቦች ነቢያችን ከሞቱ በኋላ ወደ ኩፍር ተመልሰዋል ብለው ያምናሉ። አዑዙ ቢላህ! ለመፃፍም ይሰቀጥጣል። ④) እናታችንን ዓኢሻን በዝሙት ወንጀል ይቀጥፉባታል። በቁርኣን ንጹሕነቷ የተረጋገጠ ሆኖ ሳለ ይህን ማለት ግልፅ ኩፍር ነው። ⑤) አሁን ላይ እጃችን ላይ ያለው ቁርኣን ኦርጂናሉ አይደለም ይላሉ። ይህም ግልፅ ክህደት ነው። ⑥) አኢማህ የሚሏቸውን ሰዎች ድንበር ያልፉባቸዋል፣ ለአላህ ብቻ የሚገባን አምልኮም አሳልፈው ይሰጧቸዋል። ⑦) በተቂያህ ያምናሉ። ካላቸው ውስጣዊ እውነታ በተቃራኒ ውጫዊ ማስመሰልን ይላበሳሉ። ⑧) ከቂያም ቀን በፊት ውዱ ነቢይ ﷺና ቤተሰቦቻቸው ወደ ዱንያ ይመለሱና፤ የዛኑ ጊዜ አቡበከር፣ ዑመር፣ ዑሥማን፣ ሙዓዊያህና ሌሎችም (በነርሱ እሳቤ አህለል በይቶችን ያስቸገሩ) ወደ ዱንያ ይመለሱና ከባድ ቅጣትን ያቀምሷቸዋል ብለው ያምናሉ። … በአጭሩ ሁሉም ሺዓህ ሙብተዲዕ ቢሆንም፤ ከነርሱ መካከል ቢድዓው ከእስልምና የሚያስወጣውና የማያስወጣው አለ። ቅርንጫፋቸው በጣም ብዙ ስለሆነ በአንድ ቅርጫት ውስጥ ብይናቸው ባይገባም ከላይ የተጠቀሱት ነጥቦች ግን ብዙዎቹ ያለ ምንም ማቅማማት ከእስልምና የሚያስወጡ ናቸው። copied
Показати все...
የብሔራዊ ምክክር ኮሚሽን ነገር ከዕለት ወደ ዕለት ይሻሻላል ብለን ብናስብም እየጠናበት መጥቷል። ለብዙዎቹ የሃገራችን ችግሮች መፍትሄ ያመጣል ተብሎ ተስፋ ተሰንቆለት የነበረው የምክክር ኮሚሽኑ፤ ገና ከዋናዎቹ መሪዎች ጀምሮ የሙስሊሙን ብዛት ታሳቢ ያላደረገ ሹመት ታይቶበታል። ይህ የሙስሊሙን ቁጥር ታሳቢ ያለማድረግ አባዜ በፌዴራል ደረጃ ብቻ ሳይሆን በክልል ከተሞችም ጭምር ነው። የፌዴራሉ መጅሊስ ጉዳዩ ስላሳሰበው በውይይት ለመፍታት ከኮሚሽኑ መሪዎች ጋር በተናጠል ውይይት ለማድረግ ቢጥርም ተገቢውን ምላሽ አልተሰጠኝም ብሎ በመግለጫ አሳውቋል። ባለፈ ጎንደር ላይ በዚህ ረገድ ሙስሊሙን ይወክላሉ ተብለው የተላኩ ሙስሊሞችን ወደ ስብሰባው እንዳይገቡ ከበር መልሷቸዋል። የአማራ ክልል መጅሊስ ትናንት ባወጣው መግለጫ፤ የብሔራዊ ምክክር ኮሚሽን ሙስሊሙን ያላማከለ እንቅስቃሴ መቀጠሉን አሳውቋል። ታዲያ ምንድን ነው የምንጠብቀው? ይህ ኮሚሽን እንኳን በሌሎች ክልሎች ሙስሊሙ በብዛት ባለባቸው አካባቢዎች ጭምር ሙስሊም ያልሆነ ሰው የሚመርጥ ነው የሚመስለው። የሃገራችን ሙስሊም ማኅበረሰብ ከግማሽ በላይ ስለሆነ፤ ከዋናዎቹ የፌዴራሉ ተሿሚዎች ጨምሮ በእያንዳንዱ ከተማ አስተዳደር፣ ክልል፣ ዞንና ወረዳ የሙስሊሙ ተወካይ ቁጥር የዚያን ህዝብ ብዛት የሚመጥን መሆን አለበት። ይህን ካላደረገ ይህ ተቋም አይወክለንም ብለን ከወዲሁ አካሄዱን ውድቅ ማድረግና ፈርሶ እንደ አዲስ በትክክል እንዲዋቀር ማድረግ የእያንዳንዱ ሙስሊም ግደታ ነው። ልብ በሉ! ባለፈ የመንግስትና የኃይማኖቶችን ግንኙነት በተመለከተ የወጣው በአንድ ርዕሰ ጉዳይ ረቂቅ አዋጅ ነው። ይህ ኮሚሽን ግን አስፈላጊ ከሆነ ህገ መንግስቱን እስከማሻሻል ደረጃ ድረስ አቅም የተሰጠው ነውና ከወዲሁ በሚገባ ካልተወልን እንጨቆናለን። ይታሰብበት‼ || @MuradTadesse
Показати все...
Repost from N/a
ስራዎት የህዝብ ትራንስፖርት ላይ ነው? ወይም ቢዝነሱን መጀመር አስበዋል? እንደዛ ከሆነ 👇🏻👇🏻👇🏻 Hyundai bus Year :-2010 የመጫን አቅም (ወንበር ):- 60 ሰው ይዞታው:- አሪፍ ነው ምንም አይፈለግም ገዝተው ቶሎ ወደስራ ይግቡ  💰 Price: 4,000,000 ብር Commission:-2% ብቻ   📞 +251 954 692 595 📞+251 970 161 787 https://t.me/Lebeyktotalbrokerage https://t.me/lebeykgeneraltradingplc01 https://m.facebook.com/groups/456742547026386/?ref=share&mibextid=S66gvF https://m.facebook.com/groups/1512424049354360/?ref=share&mibextid=S66gvF
Показати все...
👍 1
ሞራል መጠበቅ የሚባል ነገር እንወቅ! ~በዲናችንኮ ይሄም ቦታ ተሰጥቶታል።በበድር ጦርነት አቡ ጀህልን  የገደለው ማን ነው ሲባል ሁለቱ ሙዐዞች(ረዲየሏሁ ዓንሁማ)እኔ እኔ አሉ። ሁለቱም ሰይፋቸውን እንድያሳዩ ተደረጉ።ሁለቱም ሰይፍ ላይ ደም አለ። ነብዩ(ሰለሏሁ ዓለይሂ ወሰለም) ሁለታችሁም ናችሁ የገደላችሁት ብለው አስደሰቷቸው።እውነታው ግን አቡ ጀህልን በደንብ የጎዳውና ገደለው ሊባል የሚችለው አንደኛው ነው።ሌላኛው ብዙም ሚና አልነበረውም።ግን እኔ ነኝ የገደልኩት ብሎ እየተከራከረ አንተማ አይደለህም ብለው ሞራሉን አልጎዱትም።የገደለውን ጀግና ሚናም አላናናቁም። ይልቁኑ አቡጀህል ላይ የተገኙ ማንኛውም አይነት ንብረቶች ሁሉ ለሙዐዝ ቢን ጀሙህ እንድሰጥ ወሰኑ። ስለ ሰው የምትናገረው ሀቅ የሆነን ነገር ቢሆንም ሞራል መጠበቅ የሚባል ባህል ተላበስ። እንደምሳሌ…መልከኛ አለመሆኑን ብታውቅም መልከኛ ነኝ ብሎ የቀረበን ሰው አላህ እንዴት አሳምሮ ፈጥሮሃል ብለህ ጀምርና ከዚያም  ጉዳይህን ቀጥል።ጎበዝ ነኝ ብሎ የሚያምንን ወንድምህን ያንተ ጉብዝናማ የተለዬ ነው ግን ...! ይህም ከ አደብ ነውና ይልመድብን። =t.me/AbuSufiyan_Albenan
Показати все...
📌 አላህ ሱብሀነሁ ወተአላ ስለ ነብዩላህ ዩስፍ ሲናገር እንዲህ ይላል ፦ { وَرَفَعَ أَبَوَيْهِ عَلَى ٱلْعَرْشِ} 【 ወላጆቹን በዙፋኑ ላይ አወጣቸው 】 💥 ወደ ስኬት መሰላል ከፍ ባልክ ቁጥር ከአላህ ቀጥሎ ትልቅ አስተዋፅኦ ያላቸው ወላጆችህ እንደሆኑ አስታውስ 👍 اللهم ارحَم والدِينا واغفِر لهُما كما رَبَّونا صِغارا.        🤲 اللهم آمين يارب العالمين        ┏━ 🍃 ━━━━ 🍃 ━┓       Tolehaahmed ┗━ 🍃 ━━━━ 🍃 ━┛ 
Показати все...
Repost from AASTU Muslims union
☁️🌟🌟🌟☁️                 👉ለአንድ ፈቂህ የጂሀድ ባብ(አህካም)  ከሌሎች አህካም መጨረሻ ለምን ተደረገ ተብለው ተጠየቁ⁉️ 💥 ስለ ጠሀራ ያልተማረ ሰው ስለ        ጂሀድ እንዳያወራ ተብሎ ነው        ብለው መለሱ።      ለገባው ጉድ ያለው መልስ ነው የመለሱት
Показати все...
Show comments
ርብርብ ለጋራ ግብ ~ السلام عليكم ورحمة الله وبركاته በዚህ የብዙ ሴቶች አለባበስ በተበላሸበት ዘመን ጂልባብ እና ኒቃብ መልበስ እየፈለጉ በችግር ምክንያት ያን ማድረግ ካቃታቸው እህቶች ጎን መቆም ድንቅ ስራ ነው። ችግሩን ለመቅረፍ የበኩላችንን እንወጣ ዘንድ ይመለከተኛል የሚልን በሙሉ አካታች የሆነ ሰፊ ሀሳብ ይዘንላችሁ መጥተናል። ይህም የጂልባብ እና የኒቃብ ባንክ መክፈት ነው። ስራዉን በሚሰሩ ወይም በሚመለከታቸዉ እህቶች ስም የባንክ አካውንት የተከፈተ ሲሆን   1. ገንዘብ በማሰባሰብ ኒቃብና ጅልባብ መግዛት፣ 2. ቅያሪ ኒቃብና ጅልባብ ኖሯቸዉ መስጠት ለሚፈልጉ እህቶች ያሉበት ሰፈር ድረስ ሄዶ በመቀበል ለተቸገሩ እህቶቻችን ማድረስ ናቸው። የድርሻችንን እንወጣ። በችግር ምክንያት መልበስ ላልቻሉ እህቶቻችን እንድረስላቸው። የኢትዮጲያ ንግድ ባንክ ➛ 1000588690486 Hikma and/or Ahlam and/or Muhiba ለየትኛውም ሀሳብ፣ አስተያየት፣ ጥቆማና ጥያቄ እነዚህን አማራጮች መጠቀም ትችላላቹ። እህቶች በዚህ👇 @AhluYeWereilua @nikab_new_wbetea  ወንድሞች በዚህ👇 @FuadBezu @red_one1212 ስልክ 0913666695          0903939033 የቴሌግራም  ቻናላችን👇 t.me/NikabJilbab የቴሌግራም  ግሩፓችን 👇 t.me/nikab_jilbab_group
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
▪️︎العلم ما كان فيه قال حدثنا ... وما سوى ذاك وسواس الشياطين قال ابن القيم رحمه الله: (ومَن أحالَكَ عَلى غَيْرِ أخْبَرَنا وحَدَّثَنا فَقَدْ أحالَكَ: إمّا عَلى خَيالِ صُوفِيٍّ، أوْ قِياسِ فَلْسَفِيٍّ، أوْ رَأْيِ نَفْسِيٍّ، فَلَيْسَ بَعْدَ القُرْآنِ وأخْبَرَنا وحَدَّثَنا إلّا: شُبَهاتُ المُتَكَلِّمِينَ. وآراءُ المُنْحَرِفِينَ، وخَيالاتُ المُتَصَوِّفِينَ، وقِياسُ المُتَفَلْسِفِينَ، ومَن فارَقَ الدَّلِيلَ، ضَلَّ عَنْ سَواءِ السَّبِيلِ. ولا دَلِيلَ إلى اللَّهِ والجَنَّةِ، سِوى الكِتابِ والسُّنَّةِ. وكُلُّ طَرِيقٍ لَمْ يَصْحَبْها دَلِيلُ القُرْآنِ والسُّنَّةِ فَهِيَ مِن طُرُقِ الجَحِيمِ، والشَّيْطانِ الرَّجِيمِ) #مدارج_السالكين (٣/ ٢٧٩)
Показати все...
1
ከወራቤ ዩንቨርስቲ ሙሊም ተማሪዎች የቴሌግራም ቻናል 👇👇👇 🌹🌹ሙስሊሙ ወንድሜ🌷🌷🌹 🪻🪻🪻🪻🪻🪻🪻🪻🪻🪻        🌨🌨🌨🌨🌨🌨🌨🌨🌨🌨 አንተ የኔ ወንድም በጣም የምወድህ፤ በሂወት መንገድ ላይ ድንገት ያገኝሁህ፤ አንተን ተላምድኩኝ ብዬ ሳላበቃ፤ ቀጠሮው ደረሰ ልለይህ ነው በቃ? """ደረሰ አሉኝ ቀኑ ያ የመለያያው""" ሙስሊሙ ወንድሜ አንተ የሱና አርማ፤ አላህ ወስኖጂ ሲለዩህ አቶድም አውቃለሁ እሱማ፤          ""እናማ ወንድሜ እኔንም ተረዳኝ"" ላንተ ያልነገርኩህ እልፍ ፍቅር አለኝ፣ ቀና ብዬ ሳይህ  ሆዴን ባር ባር አለው፤ አንተን ትቶ መሄድ ለኔም  ዱብዳ ነው፤ የዱንያ ባህረዋ ሆነና ልማዷ፤ ስንቱ ተለያየ ሳይራራልን ሆዷ፤ መለየቱንማ ድሮም አውቀዋለሁ ትተውን ሲሄዱ፤ ምነው አድስ ሆነ ዘንድሮ በኔ ላይ ስሜት የመሄዱ፤!? ብዬ ስጠይቀው እራሴን በድንገት፤ ዛሬ ግልጽ ሆነልኝ የስሜቱ ጥልቀት፤   ከሚያምረው ጀመዓ ከዚህ ውብ አንድነት፤ ከወጣት ስብስብ ከጀመዓው ድምቀት ፤ ማሰብም ይከብዳል እንኳንስ መለየት፤ የአላህ ፍርድ ሆነና አምነን ተቀበልን፤ ልንሄድ ነው መሰለኝ ሳናስብ መሄድን፤ "ግናማ ወንድሜ " ግናማ ወንድሜ ትላንት ሸኚ ከሆንክ ዛሬ ትሸኛለህ፤ እውነታው ይሄነው ወዴት ትሸሻለህ፤ አንተግን ሁልጊዜ ትተህን ልቴድ ነው ለምን ትለኛለህ ፤ ግድ ሆኖብኝጂ ፈልጌ እንዳልሆነ አንተኮ ታውቃለህ ፤ እኔም መልስ አጣሁኝ አፌ ተያይዞ፤ የመለየት ቃታ በኔ ላይ  ተመዞ፤ እንዴት አወ እላለሁ ልቤ ባንተ ፈዞ፤ መልሴን  አትጠብቀኝ እኔ መልስ የለኝም፤ የመለየት ባህር ጠልቆ ቢያሰምጠኝም፤ አወ ልለይህ ነው ብሎ የሚያወጣ አንደበት የለኝም፤ ሙስሊሙ ወንድሜ እኔ አንተን ሳገኝህ፤ አስቤም አላውቅም ከቶ እንደምለይህ፤ አካሌ ቢሄድም ካካልህ ርቆ፤ ልቤ ካንተ ጋ ነው ፍቅርህን ስንቆ፤ እስከምንገናኝ አላህ ባለ ለታ፤ በዱአህ አትርሳኝ  ባለህበት ቦታ፤ ይህን የሰማችሁ መልዕክቴን አድርሱ፤ ብርቅየዋ መስጂድ ወደ ዳሩል ሂጂራ ለሚመላለሱ ። ✍አቡ ሩመይሳ( አል ወለውይ) https://t.me/wru_ms_officialgroup
Показати все...
Werabe university muslim students official group

ይህ ግሩፕ ትክክለኛው የወራቤ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሲሆን፣ በግሩፑም፦ ➲ ሙስሊም ተማሪዎችን የተመለከቱ መረጃዎች ➲ በዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች መስጂድ ስለሚደረጉ ሀይማኖታዊ እንቅስቃሴዎች ለምሳሌ ➩ የዳዕዋ ፕሮግራም ➪ የቂርአት እንቅስቃሴ ➪ ሌሎችም ዝግጅቶች ሲኖሩ የሚለቀቁ ይሆናል።👇

https://t.me/wru_ms_officialgroup

t.me/WRU_MSJ_Official_channel

👍 1