cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

ጦቢያ የግጥም መድብል

አማራ ነኝ ያውም ትግሬ እንደ ሮሃ ተፈልፍዬ፣ልክ እንደ አክሱም ተገትሬ ምጠብቅሽ እልፍ ዘመን፣በጣይ እና በጨረቃ ስቀልድ ነው ኦሮሞ ነኝ፣ከተናገርኩ በሀቂቃ እንደውም ሁሉን ብሔር ነኝ፣ዘረኝነትን የምደቃ ዘሬ ሰው ነው፣ብሔሬም ሰው፣ሰው ነኝ በቃ ።።።።።።።።።። @WAS143 ይጎብኙ @WAS143 @WAS143 በቀጥታ ለማግኘት @WASYA @WASYA ማንኛውንም መልዕክት ለመላክ @WASYA

Більше
Ефіопія4 453Амхарська3 357Категорія не вказана
Рекламні дописи
4 349
Підписники
+424 години
+157 днів
+2330 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

ምሽት በረንዳ ላይ (በእውቀቱ ስዩም) አገር ምድሩ መሽቶ ሌቱ ምጣድ ሆኖ ፥ በኮከብ ተሟሽቶ የጎዳናው መብራት ፥ጨለማው ላይ ሲገን ከመስኮት አምልጦ ፥የወጣ ወጋንን ሳር ቅጠሉን ሲያሳይ አጥብቄ ስፈልግ ፥የእለት ያይኔን ሲሳይ የሌት አይኔን ሲሳይ በኩርማን ገላዋ፤ እራፊ ደርባ የራሷ ሻጭ ሆና ፤ለሸመታ ቀርባ በሌት ይፋ ሆና፥ በቀን ልትደበቅ ያልቀጠረችውን ፥የምትጠባበቅ አንዲት ሴት እያየሁ አሰላስላለሁ ፤ “ አብረዋት ያደጉ፤ ብጤዎቿ ሁሉ በድሜና በውበት እሷን የሚያክሉ ተድረው እንደ ሴት፥ ተከብረው እንደ ሰው የባሎቻቸውን ደረት ተንተርሰው ፍቅር ሲያጣጥሙ ወይ በንቅልፍ ሲሰጥሙ ይች ወገን አልባ የሌሊት አበባ በቀትር ተኝታ ለውድቅት የነቃች የቱን ፍሬ በልታ ለዚህ ፍዳ በቃች ?” እያልሁ አስባለሁ፥ ደሞ ከደጃፌ ትንሽ ማዶ ርቆ የመሸበት ለማኝ ፤ መንገዱ ዳር ወድቆ በግልጥ ይታየኛል “ ረፍትን ላክልኝ ፥ወይ እንጎቻህን ጣል በራብ እና በንቅልፍ ሰው እንዴት ይቀጣል" የሚል ይመስለኛል ፤ በረንዳ ላይ ቆሜ፥ በሌሊት ስምሪት ከመስኮት በወጣ፥ የብርሀን ቅሪት አይቼ ማልዘልቀው ያገሬ ጎዳና የት ላይ ነው የሚያልቀው መከራና ውበት የሚያፈራርቀው:: @WAS143 @WAS143
Показати все...
14👍 7🕊 2🥰 1
ቀጣዩ ‘ስቴፕ” (በእውቀቱ ስዩም) እንደ ቀነኒሳ አይነት ልእለ-ሰብ ሰዎችን ስታይ የእድሜ መገስገስ አያስፈራህም፤ እድሜ ሆይ መውጊያህ ወዴት አለ? ብለህ ትፎክራለህ ፤ “ ቀነኒሳ አንበሳ “ ይላል ጀግና አሞጋሹ ጀግና ቴዲ አፍሮ፤ አንበሳ በምን እድሉ ነው ቀነኒሳን የሚስተካከለው ? አንድን አንበሳ በሀያ አመቱ በአጸደ ስጋ አታገኘውም፤ ካገኘኸው ጭርጭስ ብሎ፥ ጎብጦ ቁርበቱን እየላሰ ተኝቷል፤ ቀነኒሳ ግን በአርባ ሁለት አመቱ ማራቶን ያሸንፋል፤ ዋናው ጥያቄ- ለእድሜ ትገብራለህ ወይስ እድሜን ታስገብራለህ?” የሚል ነው፤ ርግጥ ነው እኔ በዚህ እድሜየ እንኳን ማራቶን ልሮጥ ውድድሩን በቲቪ ጨርሶ ለማየት ራሱ አቅምና ትግስት የለኝም፤ አንዳንድ ቀን፥ ከባለንጀሮቼ ጋር ኳስ ለማየት እቀመጣለሁ፤ በተቀመጥኩበት ሶፋ ላይ አራት ዙር ግልገል እንቅልፍ (ናፕ ) እተኛለሁ፤ በቀደም ከስንት ጊዜ በሁዋላ ጂም ሄድኩ፤ አሰልጣኙ ተቀብሎ ገና የስነልቦና ምክር እንኳ ሳይሰጠኝ “ ሀያ ጊዜ ቁጭ ብድግ ስራ “ አለኝ ፤” ቁጭ ማለቱ ላይ ችግር የለብኝም ብሮ ! ብድግ ማለቱ ላይ ግን እገዛህን እሻለሁ “ ብየው ፥ ትንሽ ወልመጥ ወልመጥ አልሁ ፤ ቀጠለና አስር ፑሽ አፕ አዘዘልኝ፤ አምስቱን ወገቡን እንደተመታ እባብ እየተቅመደምድሁ ሰራሁ፤ በተረፈች፥ ጉልበቴ ምንጣፉን እየሳምኩ ተነሳሁ፤ በመጨረሻ ሳልፈልግ ፥በርከክ ብየ ለወጫጫ ተራራ ሰገድሁ፤ ማጠቃለያው ላይ፥ አምስት ኪሎ ድምቤል አሸከመኝ፤ ከዚያ መስታውት ፊት ቆሜ ፥ ከክርኔ በላይ ያለውን ክንዴን ክፍል እየዳበስኩ ገመገምኩት፤ ብዙም ሳይቆይ አሰልጣኙ ከተፍ አለና፥ “አሁን አሟሙቀሀል፤ ቀጣዩ ስቴፕ ምን እንደሆነ ታውቃለህ? ” ሲል ጠየቀኝ፥ “ ቀጣዩ “ ስቴፕ”ማ ንቅሳት እሚሰሩ ሰዎችን ማፈላለግ ነው ዠለስ“ @WAS143 @WAS143
Показати все...
🤣 6👍 2👌 1
የክረምት መባቻ ወግ (በእውቀቱ ስዩም) ወንድ ልጅ ግን በክረምት ገንዘብና ጺም አይጣ! በነገራችን ላይ፥ ንግድ ባንክ ባለፈው ብር እንደ መስኖ ጠልፈው ያስቀሩ ሰዎችን ፎቶ መበተኑ በቂ አይደለም ፤ በፎቶው ላይ የሚታዩ ሰዎችን ለምንጠቁም ሰዎች የክረምቱን የሚያወጣ ጉርሻ ቢለቅልን አሪፍ ነው፤ ህግ የማስከበር ዘመቻውንም ያቀላጥፈዋል ! ይህ በእንዲህ እንዳለ፥ ጃንጥላ እሚይዝ ወንድ ፋራ ነው ብሎ ያወጀው ዠዝባ ማን ነው? ባለፈው ጃንጥላ ልገዛ ስጠይቅ ፥ ሻጩ “ለእናትህ ነው ለሚስትህ ?” ብሎ ጠየቀኝ ፤ " ለአናቴና ለሚስቴ በህየወት እንድቆይላቸው እሱን አራት ሄክታር ጃንጥላ ስጠኝ ፤ ሰገጤ ላለመባል የተነከረ ባቄላ መስየ ቤቴ እንድገባ ፈልገህ ከሆነ ትልቅ ስተት ሰርተሀል ፤ ቢመቸኝ ፥ እንኩዋን ጃንጥላ እጀታ ያለው ድንኩዋን እዘረጋለሁ ፤ “ልለው ፈልጌ ተውኩት፤ እሚገርመው፥ የሆነ ዘመን እርድና በሌላው ዘመን ላይ ስግጥና ይሆናል፤ ነዋይ ደበበ ’ ጥላ ይዤ ልከተልሽ?” የሚል ሁሉ ዘፈን ነበረው፤ እኔ ሲመስለኝ ወንዶች ጃንጥላ መያዝ የለባቸውም ብሎ የደነገገው ሰውየ “አስጠልይኝ “ በሚል ሰበብ ከሴቶች ጋራ መተሻሸት የሚፈልግ ይመስለኛል ፤ ጃንጥላ በመያዝ ራሳችንን ችለን እንቁም! ሳይፈቀድልን በሴቶች ራዳር ውስጥ አንግባ! አመሰግናለሁ! ክረምት መባቻ ላይ ትዝ እምትለኝን የወዳጄን ገጠመኝ አካፍየ ምሳየን ላብስል፤ ከአያሌ አመታት በፊት ጌትነት እንየውና ጉዋደኞቹ ለአንድ የገጠር ቀበሌ ህዝብ መስክ ለይ ተውኔት ያሳያሉ፤ ህዝቡ መስኩን ከበብ አድርጎ ያያቸዋል፤ ተውኔቱ የታሪኩ አማካኝ ላይ ሲደርስ ዝናብ ማካፋት ጀመረ፤ ግማሹ ተመልካች ከተቀመጠበት ፥ተነስቶ እየተግበሰበሰ፥ ባቅራቢያ በሚገኘው ዋርካ ዛፍ ስር ተጠለለ፤ የኪነጥበብ ፍቅራቸው የዝናቡን ያስረሳቸው ሰዎች ብቻ ሜዳው ላይ ቀሩ፤ ትንሽ ቆይቶ በረዶ ብቻ ሳይሆን በራሪ ኮከብ የቀላለቀለ ዝናብ አካባቢውን ይወቅጠው ጀመር ፤ ተዋናዮች ከዚህ በላይ ለኪነጥበብ መስዋእትነት መክፈል አልፈለጉም፤ እየሮጡ ዋርካው ስር የተጠለሉትን ሰዎች ተቀላቀሉ፤ ከተጠለሉት ተመልካቾች መካከል አንድ ወዝ የጠገበ ከዘራ የያዘ ጎረምሳ ወደ ተዋናዮች እያየ “ ጎበዝ ! ዛሬ ሰንጢ ይዘንባል እንጂ አምስት ብራችንን የከሰከስንበትን ትያትር መጨረሻ ሳናይ አንሄድም” ይሄኔ ጌትነት እንዲህ አለ፤ “ በመጨረሻ! ሙሽራውና ሙሽራይቱ ወንድምና እህት መሆናቸውን ይደርሱበታል፤ አሁን በሰላም ወደ ቤታችሁ መሄድ ትችላላችሁ “ @WAS143 @WAS143
Показати все...
👍 7 6👌 1
ያንድ ምሽት ሀሳብ (በእውቀቱ ስዩም) ልማድ ሆኖበት፥ ሌቱ ቢገፋ ምን ሊጠቅመኝ፥ ነው የማንቀላፋ ህልም ሸክም ነው፥ ፈቺው ከጠፋ፤ ሳይጎድለኝ ለዛ ሳያንሰኝ ውበት የቀን ጨረቃ፥ ላይንሽ ሆኘበት፥ ቀልብን የማይስብ፥ የሳር ቀለበት መወደዴ ብላሽ ምኞቴ ዘበት፤ የአሻንጉሊት ላም፥ ጡት እንደማለብ የፈረስ ሀውልት፥ እንደመጋለብ ሲሳይሽ ፈልቆ፥ ጣት አያርስም የትም ብትኖሪ፥ የትም አልደርስም፥ የሚፈሰውን አልፎ ገደቤን -እንባየን ልሼ ደረቴን ሰብሮ ፥ የሸሸ ልቤን ቦታው መልሼ በፍቅር ፈንታ ፥እረፍት ሸመትሁኝ ቁርጤን አወቅሁኝ ፤ ለካ ሰው ቢማር፥ ከሊቅ፥ ከመጻፍ፥ ከኑሮ ከእድሜ ቁርጥን ማወቅ ነው የእውቀት ፍጻሜ;: @WAS143 @WAS143
Показати все...
👍 10 3😍 3
ነገረ አድዋ (ቁጥር 1) (በእውቀቱ ስዩም) በቀደም ጳውሎስ ኞኞ ስለ አድዋ የጻፈውን ስገርብ እንዲህ እሚል አንቀጽ አገኘሁ፥ “የአድዋ ጦርነት የተካሄደው በገናና በሁዳዴ ጾም ጊዜ ነው፤ ክርስትያን ዘማች በዚያንጊዜ እንደነበረው አጽዋጽዋም እስከሚቀጥለው ጀንበር መጥለቅ ድረስ ምንም አይቀምስም፤ ውሀ እንኳን አይጠጣም ነበር፤ ይህንን የተገነዘቡት አጤ ምኒልክ ጳጳሱን አቡነ ማቴዎስን “ጦርነት ላይ መሆናችንን ያውቃሉ፤ ሰራዊቱ በጦርነትም በጦምም ተደራራቢነት ጉዳት እንዳይደርስበት ያገኘውን እየበላ እንዲዋጋ ይፍቱት ፤ ቢፈለግ ከጦርነት መልስ እጾማል ቢሏቸው “ አቡኑ ግብጻዊ ነበሩና የኢትዮጵያ ጉዳይ ጉዳያቸው ስላልሆነ “አልፈታም “ ብለው እምቢ አሉ፤ ምኒልክም በዚህ አዝነው “እግዚአብሄር የየዋህ አምላክ ይፈርዳል “ አሏቸው፤" (ጳውሎስ ኞኞ፥ አጤ ምኒልክ፥ ገጽ 172) እስቲ በዚች አንቀጽ ትንሽ እንቆዝም! ጳውሎስ ኞኞ በሀገር ፍቅር ስሜት የተቃጠለ ጸሀፊ መሆኑ ጥርጥር የለውም፤ ይሁን እንጂ ለአቡነማቴዎስ በትክክል የፈረደላቸው አይመስለኝም፤ አቡኑ በትውልድ ግብጻዊ ቢሆኑም ታማኝነታቸው ለሀይማኖታቸው እና ለኢትጵያ ንጉስነገስት መንግስት ነበር፤ ያም ሆኖ፥ ባጋጣሚ፥ ከሀይማኖታቸውን ሚቃረን የመንግስት ሀሳብ ቢገጥማቸው ለሀይማኖታቸው ማድላታቸው የመርህ ሰው ያስኛቸዋል እንጂ ከሀዲ አያስብላቸውም ፤ ስለዚህ ፥“የኢትዮጵያ ጉዳይ ጉዳያቸው ስላልሆነ” የሚለው የጳውሎስ ኞኞ ክስ ምንም መሰረት የለውም፤ በንጉሰነገስቱና በፓትርያርኩ መካከል ልዩነት አለ፤ ንጉሱ ካለው ሁኔታ አንጻር የሚያዋጣውን የሚመርጡ” ፕራግማቲስት” የፖለቲካ ሰው ናቸው፤ ሐቀኛ የሀይማኖት መሪ ከሆንህ ግን ሁኔታው ተለወጠ ብለህ የምትለውጠው አይኖርም! በጊዜው ንጉሱ ሰይፍ ታጥቂያለሁ ብለው “ አንተ የምስር ነጫጭባ ! ትፈታለህ ብያለሁ ትፈታለህ ? “ ብለው አለመሳፈጣቸው እርፍና ይመስለኛል ፤ ቤተመንግስት በሰራዊቱ ተማምኖ በቤተክሀነት ውስጥ አለመግባቱ ስልጣኔ ነው፤ አጼ ምኒልክም ሆነ ተራኪው ጳውሎስ የበላ ወታደር ከጾመ ወታደር የተሻለ ይዋጋል የሚል አስተሳሰብ ነበራቸው ፤ ዘመናዩ ሳይንስ ግን ጾም የተሻለ ጉልበት እንደሚያጎናጽፍ ደርሶበታል፤ ስትጾም ለጽሞና፥ ለእርጋታ የሚያግዙ ሆርሞኖችን ማምንጨት ትችላለህ! አንዱ የምግብ ምርምር ሊቅ በቅርቡ ሲናገር እንደሰማሁት፤ “ ተራበ ተኩላ እና የጠገበ አንበሳ ቢታገሉ ተኩላው ያሽንፋል፤ የተራበ ተኩላ በሙሉ ሀይልና ቁርጠኝነት ነው የሚፋለመው፤ የጠገበ አንበሳ ግን ማረፍ እና መተኛት ነው የሚፈልገው “ ምናልባት የአድዋ ላይ አርበኞች፥ ከጠላቶቻቸው በሚልቅ ጉልበት እና ወኔ የተዋጉበት ምክንያት ስለጾሙ ይሆን? እንዲያ ከሆነ ደሞ አቡነ ማቴዎስም( ባለማወቅም ቢሆን) ለአርበኞች ተጨማሪ ጉልበት አለፋፍለዋል ማለት ነው፤ @WAS143 @WAS143
Показати все...
👍 15 3👎 1🕊 1
እማማ አፀደ የሚባሉ ጎረቤት አሉን የእናቴ ጓደኛ ናቸው። እማማ አፀደ አመም አድርጓቸው ህመማቸው በባሰ ቁጥር እናቴን ጠሏት። ይሰድቧታል ሌባ ናት ይላሉ። መሰሪ ናት ይላሉ። ልትገለኝ ትፈልጋለች ይላሉ። መርዝ አበላቺኝ ይላሉ ። አትምጣብኝ ብለው ስሞታ ይናገራሉ ሌሊት እቤቴ ልትገባ ነበር ይላሉ ። ሰው እንዳትመስላችሁ ይላሉ ። እናቴ ቤታቸው መሄድ አቆመች ። ከቤት መውጣት እያቆሙ ግቢያቸው መዋል ጀመሩ .... እናቴ እሷ መሆኗን አትንገሩ ብላ ፤ ምግብ ትልክላቸዋለች ። በእህታቸውን ልጅ ፤ ምን ጎደለ ጤናቸው እንዴት ነው እያለች ትሰልላቸዋለች... ንዴት ሊገድለኝ ይደርሳል ። እቆጣታለሁ << ስምሽን እያጠፉሽ እየሰደቡሽ እየጠሉሽ አትተያቸውም ወይ?>> እላታለሁ!! <<ጭንቅላታቸው እጢ ወጥቶባቸዋል እሱ ነው ትንሽ ቀየር ያደረጋቸው እንጂ ፤ እሳቸው እንኳን ሳልበድል ብበድላቸው እንኳን በክፉ አያነሱኝም>> ትለኛለች። ምግብ ትልክላቸዋለች ። በእህታቸው ልጅ በኩል የሚያስፈልጋቸውን መድኃኒት መግዣ ከኛ ወስዳ ... ተበድራም ቢሆን ትገዛላቸዋለች ። እሳቸው ያቺ ምናምንቴ ፣ ድግምታም ያቺ ነጠላ እያሉ ጮክ ብለው እናቴን ሲሰድቧት ይውላሉ ። ጠላኋቸው !! አንድ ቀን ለምን ግን እንዲ ስምሽን እያጠፉ እየጠሉሽ እያልፈለጉሽ አልጠላሻቸውም? ብዬ እናቴን ጠየቅኋት። <<ጓደኛዬ ናቸው! እዚህ ሰፈር ስመጣ እሳቸው ናቸው ያለመዱኝ ። እድር ያስገቡኝ ፥ የሌለኝን እቃ ያዋሱኝ ፥ የተቆረቆሩልኝ ፥ የአረሱኝ ፣የመከሩኝ... እንዲህ አይባልም እያሉ መንገድ ያሳዩኝ እርሳቸው ናቸው ። ድንገት ታመው ነው የተቀየሩት ።ከሁሉም ጋር ነው መጣላት የጀመሩት እኔ ላይ ትንሽ ጠንከር አሉ እንጂ ... በክፉ ግዜ እንኳን ወዳጅ ላይ ጠላት ላይ አይጨከንም!! የጨዋ ሰው ልክ የሚታየው ሲጣሉት ነው ። በፍቅር ግዜ ሰው አይመዘንም ክፉ ግዜ ነው ሰው የሚያጠለው .... አፀዱ እንዴት አይነት ጥሩ ሰው መሰሉህ ዛሬ ህመም ተጣብቷቸው እን'ጂ ። ስንት ቀን መሰለህ እጦት በሳቸው ሳብያ ከቤታችን የተባረረው ። አፀደ ደግ 'ሩህሩህ ናቸው... እናንተ ሳትወለዱ ማንም ሳይኖረኝ ነው ከኔ ጋር የነበሩት... የአፀደ ውለታ አለብኝ !>> © Adhanom Mitiku @WAS143 @WAS143
Показати все...
👍 11 7👌 1😍 1
ሴት አይቅናው ! ሄዱ አብረው ጊዜና እሱ ወዴት ቆሙ የት ደረሱ ? ማን ተጠጋው ? ማን አወጋው? ማን አለፈው ? ማን አቀፈው ? ይጨንቀኛል .... የለሁበት በህይወቱ የለሁበት በመንገዱ ይቃዠዋል ልቤ እብዱ ምን ቤት ቤቴ ? ምን ቤት ጣሪያው? የሚስለው ዙሪያ ገባው ለሄደ ሰው ምን አገባው ምን ቤት ልቤ ምን ቤት አይኔ እየሳቡ የሚያመጡት ምን ይገዳል ምንስ ቢሆን ከእጅ ያወጡት?? እንጃ..!! ብቻ.. የተኛበት እንዳይሞቀው እመኛለሁ ሴት ባያውቀው እመኛለሁ ሴት ባያቅፈው ሄዋን ሳያውቅ እድሜ ቢያልፈው እመኛለሁ ባይዳበስ እመኛለሁ ባይታበስ እመኛለሁ ለፍቅር ያለው ባይሳካ እንኳን ገላው የፀጉሩ ጫፍ ባይነካ ይጨንቀኛል ... ቁርጥ አርጎ ለሄደ ሰው ልቤን ሐሳብ እየጠናው እመኛለሁ በደፈናው እመኛለሁ ሴት ባይቀናው... . . . ሴት አይቅናህ ..... 😞 ሊና አርጋው ✍️ @WAS143 @WAS143
Показати все...
13👍 4👌 3😍 1
ግብይት (በእውቀቱ ስዩም) ሰሞኑን ለዲያስፖራ ወገኖቻችን አገራቸውን እንዲጎበኙ ጥሪ ተደርጓል፤ እኔ ለዲያስፖራ ወገኖቻችን ቦታ ለመልቀቅ ብየ ወደ አሜሪካ መጣሁ፤ ሰልስትና (ከሶስት ቀን በፊት) ዲሲ በእግሬ እየተወዘወዛለሁ፤ ዋይታውስ አጠገብ ስደርስ በብዙ ያለም ቋንቋዎች መሀል ጎልቶ የሚታይ የአማርኛ ጽሁፍ ተመለከትኩ፤ “ ፕሬዚዳንት ባይደን ሆይ ! የሚደረግብንን እያየህ ስለምን ዝም ትላለህ! “ የሚል መፈክር ነበር የጠበቅሁት፤ ጠጋ ብየ ሳየው “ የአላባ በርበሬ እዚህ ይገኛል “ የሚል ማስወቂያ ነው፤ ወደ ሱቁ ገባሁና ፥ “ደና ዋላችሁ?” “I am good” አለኝ ፥ አንድ በደብረ ብርሀን ብርድልብስ ላይ የሳይቤሪያ ቡሉኮ የደረበ አበሻ፤ “ እስቲ ወደ ኢትዮጵያ የሚሄድ አንድ ፈረሱላ በርበሬ መዝኑልኝ “፤ ---------- መንግስቱ ሀይለማርያም " ሰው በላው ካፒታሊዝም " ቢልም እንኳ ያሜሪካ ካፒታሊዝም የቸርነት ገጽታም አለው፤ የሚበዘብዝህን ያህል እንድትበዘብዘው እድል ይሰጥሀል! ለምሳሌ የሆነ ልብስ ከሱቅ ገዝቼ አንድ ሳምንት ዘንጨበት ሳበቃ ፥ አልመጠነኝም ብየ ለሻጮች መመለስ እችላለሁ፤ ሳያንገራግሩ ገንዘቡን ይመልሱልኛል ፤ ይሄ አሰራር ኢትዮጵያ ውስጥ የሚጀመረው መቼ ነው? ከጥቂት ጊዚያት በፊት ሽሮ ሜዳ ፎቅ ላይ ወደሚገኝ የባህላዊ ልብስ መሸጫ ሱቅ ጎራ ብየ ነበር፤ “ምን ነበር?” አለኝ ሻጩ! “አንድ ጓደኛየ ከዚህ ቤት ቆንጆ የዶርዜ ሸሚዝ ገዝቶ ስጦታ ሰጥቶኝ ነበር” “ የተባረከ ጓደኛ ነው ያለህ " ” “ ምን ዋጋ አለው፤ ሰሞኑን ትንሽ ወፈር ስላልሁ ጠበበኝ “ “ ምንችግር አለው ታድያ !” አስቀምጠውና ስትከሳ ትለብሰዋለህ” ሲል መለሸ ሻጩ፤ “ መመለስ አልችልም?” “ ምኑን ነው እምትመልሰው?” “ልብሱን ነዋ” “ ያንተን አንጋፋ ላብ የጠገበ ልብስ ተቀብየ ልሸጠው ነው ሙዝየም ላስቀምጠው?” ሰውየው አንባረቀብኝ ፤ በጣም ተናድጄ ከሱቁ ወጥቼ አምስት ፎቅ ወረድኩ ፤ ታች ከደረስኩ በሁዋላ ሰውየው በረንዳው ላይ ሆኖ በፉጨት ጠራኝና ስዞር ፥ “ ተነጋግረን አልጨረስንምኮ “ አለኝ’ ከምኔው ሀሳቡን ቀየረ ብየ ወደ ላይ መወጣት ጀመርኩ፤ ፎቁ ሊፍት እንደሌለው ልብ ያልሁት አሁን ነው፤ በርግጥ ባህላዊ ልብስ ሻጩ ባህላዊ ፎቅ መምረጡ አግባብ ነው፤ እያንዳንዱን ደረጃ በምጥ እና በመራራ ትግል ከወጣሁ በሁዋላ እንደገና ሱቁ በር ላይ ተገተርኩ፤ “ እኔ እምልህ” አለ ሻጩ፥ “ እህ” “ እህቴ የሚያከሳ አረቄ ትሸጣለች ፤ ቀብድ ከከፈልህ ላስመጣልህ እችላለሁ” @WAS143 @WAS143
Показати все...
9👍 6😁 1
ስፍራው እዚህ ላይ ነው ( በእውቀቱ ስዩም) የተገናኘነው ስፍራው እዚህ ላይ ነው፤ በጋዜጣ ቅዳጅ፥ መታ መታ አድርገን አቧራውን ጠርገን ከሰፈ ጀርባው ላይ የተቀመጥንበት፤ አረጋዊ ድንጋይ አካሉ በከፊል ፤ ወደ መሬት ሰጥሞ እንደነበር አለ፤ የሳር ሻሽ ጠምጥሞ ላልፎ-ሂያጅ ተመልካች፥ ፍቅር ለጎደለው ምንም ነገር የለው፥ ቀልብን የሚያሸፍት በሀያል አድናቆት፥ አፍን የሚያስከፍት ፤ በግርማ ሞገሱ ፥ተሪስት የሚጠራ ጥንታዊ ሰገነት፥ አለት -ለበስ ጣራ ተምዘግዛጊ ውሀ፤ ረጅጅጅም ተራራ አቤት የሰው ጥበብ አቤት የግዜር ስራ የሚያሰኘ ድንቃድንቅ ፥ የለም ከዚህ ስፍራ፤ ለኔ መሳዩ ግን ላንድ የፍቅር መናኝ ወርቅ የሚሆንለት፥ ትቢያውን ቢዘግን አንዲት የሳር ብናኝ አንዲት ያፈር ቅንጣት አመት የሚያወጉት፥ ታሪክ ነው ሚወጣት ፤ በምነት የተመካ ተጓዥ ያገሬ ሰው ወደ ኢየሩሳሌም፥ ወይም ወደ መካ ቀን ቆርጦ ሲሳፈር፥ ወደ ተቀደሰው እኔ ግን እዚህ ነው የምመላለሰው :: @WAS143 @WAS143
Показати все...
7👍 4👌 3👏 1
ወላጅ እናትህ - ድንገት ብትከዳህ ያፀድቃል ያልከው - ሲኦል ቢነዳህ ለፈውስ የዋጥከው - አጉል ቢጎዳህ የእስካሁን ውሎህ የእስካሁን ኑሮህ ቅዠት ነው ቢባል አስበኸዋል ? አለህ ወይ ትከሻ ? አለህ ወይ መሸሻ - ህመም ማስታገሻ ? አለህ ወይ "ምናልባት" ማረፊያ ምትሆንህ በዚያ ጭንቅ ሰአት ? ሙሉ አለም አትስራ ፥ አበጅለት ክፍተት ልክ ሆነህ አትኑር ... አክልበት ስህተት ነፍስህ ይደናበር ዝግ ልብህን ስበር አፍርስ ግዳግዳውን ለመስኮትና በር ህይወት ፀጋ ስትቸር ያኔ እንድትቀበል ። @WAS143 @WAS143
Показати все...
👍 8 6🥰 1😍 1
Оберіть інший тариф

На вашому тарифі доступна аналітика тільки для 5 каналів. Щоб отримати більше — оберіть інший тариф.