uk
Feedback
GLOW KG AND PRIMARY SCHOOL ADDIS ABABA ETHIOPIA.

GLOW KG AND PRIMARY SCHOOL ADDIS ABABA ETHIOPIA.

Відкрити в Telegram

Always strive for Excellence❤!!

Показати більше
1 431
Підписники
+824 години
+127 днів
+730 день
Архів дописів
> Sis: በፈተና ጊዜ የሚፈጠርን ጭንቀት ወይም ቴንሽንን ልንቆጣጠር የምንችልባቸው ዘዴዎች! ======================== 👉ፈተና የመፈተኛ ጊዜ ሲቃረብ ሁላችንም በመጠኑ መጨነቅ እና ከወትሮው ከፍ ባለ መጠን ውጥረት ውስጥ መግባታችን የተለመደ ነገር ነው::ይህን አይነቱን ከፍተኛ ውጥረት መቆጣጠር የምትችሉበትን መንገድ አንድ በአንድ እንመልከት፤ ከፈተና በፊት ማድረግ የሚገባን ዘዴዎች፤ ------------------------------------------------ ☝️ ፈተና ሲመጣ መጠነኛ ውጥረት እና ጭንቀት ተፈጥሮአዊ እና ሁሉም ተፈታኝ ተማሪ እንደሚያጋጥመው መረዳት። ☝️ ለፈተና ስንዘጋጅ አዎንታዊ እና በጎ ሀሳቦችን ማሰብ፡፡ 👌ፈተና ማለት ከዚህ ቀደም ከተማርነው ነገር የተረዳነውን እና የቀሰምነውን እውቀት የምንለካበት መመዘኛ እንጂ የኛ የህይወት ምዕራፍ ማብቂያ ወይም አጠቃላይ ችሎታችንን የሚያመላክት አይደለም ። ☝️ማወቅ ያለብን አንድ ነገር ቢኖር መሳሳትን አለመፍራት እና ሁሌም ለማወቅ እና ራስን ለማሻሻል ዝግጅ መሆንን ነው ። እንዲሁም አሁን የምንፈተነው ፈተና እንዳሰብነው እንኳን ውጤቱ ባያስደስት ለቀጣይ ማስተካከል እና ማሻሻል እንደሚቻል ማመን። ☝️ ከጓደኞቻችን ጋር ያጠናነውን ነገር በጋራ ሆነን መጠያየቅ እና እርስ በርስ ያወቅነውን ነገር መለዋወጥ፡፡ ይህ ዘዴ ይበልጥ የማስታወስ ብቃታችንን እንደሚጨምር እና የተጠያየቅነው ነገር እንዳይረሳን ያረጋል ። ከዚህም በተጨማሪ የተሳሳትነውን ነገር ድጋሚ እንድንከልስ እና እርማት እንድናረግ ያግዘናል። ☝️ የፈተና ቀን ሲቃረብ እንደ ወትሮው ዘና ማለት እና በቂ እረፍትና በቂ እንቅልፍ መተኛት ። ይህም ጭንቀትን ይቀንስልናል፣ እንዲሁም ተረጋግተን ያጠናነውን ነገር አስበን እንድንሰራ ይረዳናል። ፈተና ከጀመርን በኋላ ማድረግ የሚገቡን ነገሮች (ፈተና ላይ እያለን)፤ 👉 ወደ ፈተና ከመሄዳችን ቀደም ብለን ለፈተና የሚረዱንን መሳሪያዎች እና የመፈተኛ ቁሶችን ማዘጋጀት። 👉አብዝተን ፈተናን እና የምናመጣውን ነጥብ ስሌት አለመገመት ። 👉ፈተና ስንጨርስ የተሳሳትነውን ጥያቄ አብዝቶ ማሰብ እና ሌላ ተማሪ መጠየቅ ጭንቀት ውስጥ ስለሚከተን ከዚህ ይልቅ ቤት ሄደን እረፍት ማድረግ እና ለቀጣይ ፈተና መዘጋጀት ። 👉 በፈተና ጊዜ ድንገተኛ ጭንቀት እና ድንጋጤ ከገጠመን ወዲያው የምንሰራውን ገታ አድርገን በጥልቀት አየር በአፍንጫችን ስበን ወደ ሳንባ እያስገባን መልሰን ማስወጣት ይህንንም እስክንረጋጋ መደጋገም ። ከዚህ በመቀጠል የማረጋጊያ ቃላትን ለራስዎ መንገር:: 👉 ፈተና በምንሰራ ጊዜ ግራ ያጋባንን እና እርግጠኛ ያልሆንበትን ጥያቄ በይለፍ ማቆየት እና ወደ ቀጣዩ ጥያቄ መሄድ ይህም ጊዜያችንን በአግባቡ እንድንጠቀም ይረዳናል። ነገር ግን ምልክት አድርገን ማለፍ፤ 👉በተመሳሳይ እርግጠኛ ያልሆልንበትን መልስ ላይ ተደናግጠን መሰረዝ እና መደለዝን መቀነስ ይህም ስንደነግጥ እና ስንጨነቅ የምናውቀውን መልስ ትተን ወደ ሌላ መልስ እንድሰጥ ስለሚያረግ መሰረዝና መደለዝን መቀነስ ። 👉ፈተናውን ወደ ማገባደድ ስንደርስ በይለፍ ያስቀመጥናቸውን ግራ ያጋቡንን ጥያቄዎች ጥቂት አስበንበት መልስ መስጠት ፤ ካልሆነም ደግሞ ብልሀት ተጠቅመን የግመታ መልስ ሰጥተን ወደ ቀጣዩ ጥያቄ መሄድ ። 👉በተደጋጋሚ ሰአትን አለመመልከት ወይም ሰአት በቃን አልበቃን እያልን አለመጨነቅ። 👉መጭው ወቅት የፈተና ወቅት ነውና ለተፈታኞች በሙሉ መልካም ጊዜ ተመኘን👏👏👏👏

📝ሰሞነኛ 📝 ልጆችና👧🧒 ዝናብ🌧 ልጆች በዝናብ እንደመጫወት በውሀ እንደመንቦራጨቅ የሚያስደስታቸው ነገር የለም አልፈንበታልና መቼም ሁላችንም እናውቀዋለን ግን ምን ያደርጋል የሚያስደስት ሁሉ መልካም አይደለም አደጋ አለው እናም ጥንቃቄዎችን ለኛም ለልጆቻችንም እናድርግ። "አይሆንምን ትተሽ ይሆናልን ያዢ" 👵ትለኝ ነበር አያቴ ምክሩ ቀላል ይመስላል ብዙዎቻችን ምንም አይመጣም ችግር የለውም ብለን የምናልፋቸው ነገሮች ደርሰው ጎድተውናልና ቅድመጥንቃቄን መተግበር መልካም ነው ስለዚህ?ስለዚህ... ⛈ የአየሩን ሁኔታ አይቶ ለልጆች ከደንብ ልብስ (ከዮኒፎማቸው)ስር የሚሞቁ ልብሶችን ማልበስ🧥🥼 ⛈ በዝናብ ውስጥ እንዳይሯሯጡ እና በውሀ እንዳይንቦራጨቁ መምከር። ⛈ በዝናብ ወቅት የተቆፈረ ወይም ያልተደፈነ ጉድጓድ በውሀ ስለሚሸፈን ልጆቻችን ከእጃችን ሳይወጡ ግልፅ ሆኖ በሚታይ መንገድ መጓዝ ይኖርብናል። ⛈ እንደሚታወቀው ዝናብ ለመኪናም አስቸጋሪ ስለሆነ ስናሽከረክርም🚗 በጥንቃቄ እግረኛም ከሆንን ልጆቻችንን እጃቸውን ይዘን እራሳችን ብንወስዳቸው ይመረጣል። ⛈ ዝናቡ አባርቶ እንኳን ከሌላ ቦታ በዘነበ ዝናብ ምክንያት ጎርፍ ሊከሰት ስለሚችል ልጆችን በቤት ውስጥ ማቆየት ⛈ ከዚህ በፊት በምናውቀው በዝናብ ወቅት ድንገት የኤሌትሪክ መቋረጥ፣ የኤሌትሪክ ⚡️ገመድ መርገብ፣ የኤሌትሪክ እንጨት መውደቅ፣ በገመዶቹ መነካካት የሚፈጠር እሳት🔥 እና ሌሎችም አደጋዎች ስለሚኖሩ በዚህም ጉዳይ የተቻለንን ጥንቃቄ ማድረግ መልካም ነው። የልጆቼ ወላጆች👨‍👩‍👧‍👦 አይሆንምን ትተን ይሆናልን እንያዝ ጨርሻለሁ። ት/ቤትዎ

✍የ2015 ትምህርት ዘመን  2ኛው ሴሚስተር   አጋማሽ  ፈተና ፕሮግራም ከላይ የተያያዘ ሲሆን ልጅችዎ በፕሮግራሙ መሰረት እንዲያጠኑ እገዛ ያድርጉላቸው፡፡ # ስለሚደረገው ክትትልና ድጋፋ እናመሰግናለን!!👍👍👍👍👍                             ት/ቤትዎ

የ2015 ትምህርት ዘመን 2ኛው ሴሚስተር አጋማሽ ፈተና ፕሮግራም ከላይ የተያያዘ ሲሆን ልጅችዎ በፕሮግራሙ መሰረት እንዲያጠኑ እገዛ ያድርጉላቸው፡፡ # ስለሚደረገው ክትትልና ድጋፋ እናመሰግነለን!! ት/ቤትዎ

ሚያዚያ 19/ 2015 ዓ.ም የተከበራችሁ የትምህርት ቤታችን  ወላጆች # ከነጌ ሚያዚያ 20 - 21/2015 ዓ.ም በመምህራን ስልጠና ምክንያት ትምህርት የማይኖር መሆኑን እና # ሚያዚያ ሰኞ 23/2015 ዓ.ም የላብ አደሮች ቀን ታስቦ ስለሚዉል ትምህርት አይኖርም። # ሚያዚያ ማክሰኞ 24/2015 ዓ.ም መደበኛ ትምህርት ይቀጥላል። ለ1444ኛዉ ኢድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ ። ግሎው ት/ቤት

Eebla 12/2015 ALH Maatiiwwan manan barumsaa keenya hundaaf / Maraaf Duran dursa hordoftoota Amantaa Musliimota maraaf baga ayyaana waggaa 1444ffaa IId Alfaxiriif isin gahe Jenna. Haa ta’u malee sababa ayyaana kanaan walqabatee Eebla 13/2015 ALH manni barumsaa cufaa ta’uu isaa isin beeksifna. Dabalataanis Sambata Eebla 14/2015 ALH sababa ayyaana kanaan barumsi gargaarsaaf/ Tutor Class/ kennamu kan hin jiraanne ta’uu isaa isin beeksifna. Wixata Eebla 16/2015 ALH barnootni idilee guyyaa guutuu itti fufa. Mana Barumsaa Glow

ሚያዚያ 12/ 2015 ዓ.ም የተከበራችሁ የትምህርት ቤታችን  ወላጆች ለእስልምና እምነት ተከታዬች እንኳን ለ1444ኛዉ ኢድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ ። በኢድ አልፈጥር በዓል ምክንያት  ነገ ዓርብ ሚያዚያ 13 /2015ዓ.ም ትምህርት ቤት ዝግ ሆኖ ይውላል፡፡ ቅዳሜ ሚያዚያ 14/2015 ዓ.ም በበዓሉ ምክንያት የማጠናከሪያ ት/ት የማይኖር መሆኑን እየገለፅን። ሰኞ ሚያዚያ 16 ቀን 2015 ዓ.ም መደበኛው ትምህርት ይቀጥላል፡፡  ግሎው ት/ቤት

ለመላው የክርስትና ዕምነት ተከታዮች እንኳን ለብርሀነ ትንሳኤው በሰላም አደረሳችሁ!! አደረሰን! መልካም ዓመት በዓል! ግሎው ት/ ቤት