የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
Відкрити в Telegram
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
Показати більше2 752
Підписники
-124 години
+227 днів
+5330 день
Архів дописів
+9
ነሐሴ 13 በታላቅ ድምቀት የሚከበረው የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን በደብረ ታቦር ብርሃነ መለኮቱን የገለጠበትን በዓል ምክንያት በማድረግ የሰንበት ት/ቤታችን ማእከላውያን ክፍል አባላት በተለያዩ አካባቢዎች በመዘዋወር የበዓሉን ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን፤ በመጨረሻም በደብራችን በርካታ ምዕመናን በተገኙበት፤ ስለ በዓሉ ቃለ እግዚአብሔር ከተሰጠ በኋላ በችቦ ማብራት እና በዝማሬ የበዓሉ ፍጻሜ ሆኗል። የማእከላውያን ክፍል አባላት በየዓመቱ ለምናካሂደው ጉዞ ከፍለው መጓዝ ለማይችሉ አባሎቻችን፤ ከቡሄ ዝማሬ የሚያገኙትን ገቢ ሙሉ በሙሉ ለጉዞ ኮሚቴ በማስረከብ ለጉዞው ድጋፍ የሚያደርጉ ሲሆን፣ ለዚህ በጎ አገልግሎታቸው አምላከ ሚካኤል ዋጋቸውን ይክፈልልን ለማለት እንወዳለን።
እግዚአብሔር ማኅበራችንን ይባርክ!
+1
📢 ደረሰ ደረሰ...
ውድ አባላቶቻችን ፤ ለጉዞው የቀረን ጊዜ በጣም አጭር በመሆኑ ሁላችሁም የጉዞ ትኬት በሰ/ትቤቱ ጽ/ቤት፣ ልማት ሱቅ እንዲሁም የዲጂታል አማራጮችን በመጠቀም እንድትቆርጡ ስንል በአክብሮት እናሳስባለን። በተጠቀሱት ስልክ ቁጥሮች በመደወልም መመዝገብ ይችላሉ።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተከፈቱ የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ናቸው። ቤተሰብ በመሆንና ለሌሎች በማጋራት አብረውን ያገልግሉ።
የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን
https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
+1
📢 የአንድነት ጉዞ
ውድ አባላቶቻችን ፤ ለጉዞው የቀረን ጊዜ በጣም አጭር በመሆኑ ሁላችሁም የጉዞ ቲኬት በእነዚህ አማራጮች እንድትከፍሉ ስንል በአክብሮት እናሳስባለን።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተከፈቱ የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ናቸው። ቤተሰብ በመሆንና ለሌሎች በማጋራት አብረውን ያገልግሉ።
የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን
https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
📢 የአንድነት ጉዞ
ውድ አባላቶቻችን ፤ ለጉዞው የቀረን ጊዜ በጣም አጭር በመሆኑ ሁላችሁም የጉዞ ቲኬት ከዛሬ ነሐሴ 11/2018 ዓ.ም ጀምሮ እንድትቆርጡ ስንል በአክብሮት እናሳስባለን። በተጠቀሱት ስልክ ቁጥሮች በመደወል መመዝገብ ይችላሉ።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተከፈቱ የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ናቸው። ቤተሰብ በመሆንና ለሌሎች በማጋራት አብረውን ያገልግሉ።
የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን
https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
#የነሐሴ_ሰባት_ስንክሳር
አንድ አምላክ በሆነ #በአብ_በወልድ_በመንፈስ_ቅዱስ ስም ነሐሴ ሰባት በዚች ቀን #እግዚአብሔር የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤልን ወደ ከበረና ከፍ ከፍ ወዳለ ጻድቅ ኢያቄም ላከው፥ አምላክን የወለደች የእመቤታችን የድንግል ማርያምን #ፅንሰቷንና ልደቷን በእርሷም ለዓለሙ ሁሉ ድኀነትና ተድላ ደስታ እንደሚሆን ነገረው።
ይህ ጻድቅ ሰው #ኢያቄምና የከበረች ሚስቱ #ሐና ልጅ ሳይወልዱ ሸመገሉ፤ የከበረች ሐና መካን ሁናለችና ስለዚህም እጅግ ያዝኑ ነበር፤ የእስራኤል ልጆች ልጅ ያልወለደውን #ከእግዚአብሔር በረከትን ያጣ ነው እያሉ ያቃልሉት ነበርና።
እነርሱም ልጅን ይሰጣቸው ዘንድ ወደ #እግዚአብሔር ፡ ዘወተር ፈጽሞ ይለምኑ ነበር። ከዚህም በኋላ ወንድ ልጅን ወይም ሴት ልጅን ቢወልዱ #ለእግዚአብሔር ቤት፡አገልጋይ ሊያደርጉ ስለትን ተሳሉ፡፡
የክበረ #ኢያቄምም በተራራ ላይ ሳለ ሲጸልይና ሲማልድ እነሆ በላዩ እንቅልፍ እንቅልፍ ብሎት አሸለበ፤ ያን ጊዜ ከእግዚአብሔር የተላከ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ተገለጸለት እንዲህም አለው ሚስትህ #ሐና ትፀንሳለች ዓለሙ ሁሉ ደስ የሚሰኝባትን የብዙዎችም ዐይነ ልቡናቸው በእርሷ የሚበራላቸውን በእርሷም ድኅነት የሚሆንባትን ሴት ልጅን ትወልድልሃለች።
በነቃ ጊዜም ወደ ቤቱ ሒዶ ለሚስቱ ለቅድስት ሐና ነገራት፤ ራእይዋን እውነት እንደሆነች አመኑዋት ከዚህም በኋላ #ነሐሴ_ሰባት_በዚች_ቀን_የከበረች_ሐና_ፀነሰች፤ ለዓለም ሁሉ መመኪያ የሆነች በሁለት ወገን ድንግል የሆነች የአምላክ እናት እመቤታችንን ማርያምን ወለደቻት።
"የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ዘርን ባያስቀርልን ኖሮ፥ እንደ ሰዶም በሆንነ እንደ ገሞራም በመሰልነ ነበር።"ኢሳ 1፥9
#ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ኢያቄምና ሐና ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ይኑር ለዘላለሙ አሜን።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተከፈቱ የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ናቸው። ቤተሰብ በመሆንና ለሌሎች በማጋራት አብረውን ያገልግሉ።
የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን
https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
አባቶቻችን " ያለ ጸሎት ከሚደረግ አገልግሎት ይልቅ ያለ አገልግሎት የሚደረግ ጸሎት ይሻላል። " ይላሉ ጸሎት ለሁሉም ነገሮች መሰረት ነው።
ጸሎት የእግዚአብሔርን ቸርነት የምንለምንበት ነው። ጸሎት የቅዱሳንን ረድኤት የምናገኝበት ነው። በዚህ በእመቤታችን ጾም ስለ ሕይወታችን፣ ስለ ቤተክርስቲያናችን፣ ስለ ሀገራችን፣ ስለ አገልግሎታችን እንድንጸልይ ተጠርተናል። የምንችል በሰንበት ት/ቤታችን ተገኝተን፤ በርቀት ምክንያት የማይመቸን ባለንበት ስፍራ በጸሎት እንድንበረታ እግዚአብሔር ይርዳን።
መልካም ሱባዔ!
ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት
የሰንበት ት/ቤታችን በጎ አድራጎት ክፍል እያከናወናቸው ከሚገኙ አገልግሎቶች መካከል በጥቂቱ በዚህ ቪዲዮ ለመግለጽ ተሞክሯል። ለዚህ አገልግሎት መሳካት የአባላትና የበጎ አድራጊ ምዕመናን ድርሻ ከፍተኛ ነው። ለሁሉም በጎ አድራጊዎች አምላከ ነዳያን እግዚአብሔር ይስጥልን ማለት እንፈልጋለን። አገልግሎቱ ቀጣይነት ያለው በመሆኑ ድጋፋችሁ እንዳይለየን እንላለን።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተከፈቱ የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ናቸው። ቤተሰብ በመሆንና ለሌሎች በማጋራት አብረውን ያገልግሉ።
የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን
https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
+9
የአገልግሎት ዜና
ባሳለፍነው ቅዳሜና እሑድ በሰንበት ት/ቤታችን ከሕጻናት ክፍል እስከ ባለትዳር ክፍል የተለያዩ አገልግሎቶች የተከናወኑ ሲሆን፤ በዚህም ለአንድ ዓመት በሕጻናት ክፍል የአባልነት ኮርስ ሲከታተተሉ የነበሩ ሕጻናት ወላጆቻቸው በተገኙበት ተመርቀዋል፤ በተጨማሪም የባለትዳር ወርሐዊ ጉባኤ፣ የተልእኮ ት/ት 5ኛ ዙር ተማሪዎች እንዲሁም በተልእኮ ትምህርት ለተመረቁ ተማሪዎች የሚዘጋጀው የዝክረ ቅዱስ ሚናስ የአንድነት ጉባኤ ተከናውኖ ሳምንቱ አልፏል።
እግዚአብሔር ማኅበራችንን ይባርክ!
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተከፈቱ የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ናቸው። ቤተሰብ በመሆንና ለሌሎች በማጋራት አብረውን ያገልግሉ።
የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን
https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
+7
📢የ2018 ዓ.ም የሀገረ ስብከት አቀፍ ምዘና በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተሰጠ
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ያዘጋጀው የ2018 ዓ.ም የ4ኛ፣ የ8ኛ እና የ10ኛ ክፍል እርከን ማጠናቀቂያ ምዘና ዛሬ ሐምሌ 26 ቀን 2018 ዓ.ም በስኬት ተካሂዷል።
በዚሁ መሠረት የደብራችን ጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት እና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት በ4ኛ እና በ8ኛ ክፍል 86 ተማሪዎች ያስፈተነ ሲሆን፣ ተማሪዎቻችን በመርካቶ ደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ቤተክርስቲያን አንቀጸ ብርሃን ሰ/ት/ቤት በተመደበው የፈተና ጣቢያ ከሌሎች አህት ሰንበት ትምህርት ቤቶች ጋር በመሆን በድምሩ 341 ተማሪዎች በተገኙበት ፈተናቸውን በሰላም አጠናቀዋል።
በሀገረ ስብከት ደረጃ በ191 ጣቢያዎች ከ20,000 በላይ ተማሪዎች የተፈተኑ ሲሆን፣ በእኛ ክፍለ ከተማ (ልደታ፣ ቂርቆስ እና አዲስ ከተማ) 1,513 ተማሪዎች መፈተናቸውን የሀገረ ስብከቱ መረጃ ያሳያል።
ለተፈተኑት ተማሪዎቻችን በሙሉ መልካም ውጤትን እንመኛለን!
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
"በእግዚአብሔር ቤት በመቅደሱ ውስጥ እንገናኝ" ነህምያ 6፥10
"በተስፋ ደስ ይበላችሁ፤ በመከራ ታገሡ፤ በጸሎት ጽኑ፤" ሮሜ 12፥12
የጾመ ፍልሰታ ለማርያምን ምክንያት በማድረግ በየእለቱ የውዳሴ ማርያም እና የምህላ ጸሎት ለማድረግ አባላት ለጸሎት እንድንሰበሰብ መንፈሳዊ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተከፈቱ የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ናቸው። ቤተሰብ በመሆንና ለሌሎች በማጋራት አብረውን ያገልግሉ።
"እነዚህ ሁሉ ከሴቶችና ከኢየሱስ እናት ከማርያም ከወንድሞቹም ጋር በአንድ ልብ ሆነው ለጸሎት ይተጉ ነበር።" ሐዋ 1፥14
የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን
https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የሐዘን መግለጫ
የሰንበት ት/ቤታችን አባል የሆነችው ቆንጂት ወልደ ሰንበት አባቷ አርፈው ክፍለ ሀገር ቀብራ ስለመጣች የምትችሉ አባላት ቤቷ በመሄድ እንድታጽናኗት ለማሳወቅ እንወዳለን።
ስልክ ቁጥሯ = +251946665159
አድራሻ= ከጎላ በላይኛው በር ወደ ዘርዓይ ድረስ ትምህርት ቤት መሄጃ ፖሊስ ጣቢያ አጠገብ።
+1
የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ልጆች ከእያለንበት ስፍራ በናፍቆት የምንሰበሰብበት ዓመታዊ ጉዞዋችን እየደረሰ ነው። ከወዲሁ የጊዜ ቀጠሮዎትን እንዲያስተካክሉ እንጠይቃለን።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተከፈቱ የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ናቸው። ቤተሰብ በመሆንና ለሌሎች በማጋራት አብረውን ያገልግሉ።
የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን
https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
