uk
Feedback
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ)

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ)

Відкрити в Telegram

ኢዜማ ኢትዮጵያ የሁሉም ዜጎች መብት የተከበረባት፣ ማኅበራዊ ፍትህ የሰፈነባት ሰላማዊ እና የበለፀገች ሀገር እንድትሆን የሚሠራ ሀገር አቀፍ ፓርቲ ነው።

Показати більше
2 997
Підписники
-224 години
-87 днів
-3330 день
Архів дописів
ጦርነትን ሳይጀመር ማስቆም የሁሉም ኢትዮጵያውያን የጋራ የቤት ሥራ ሊሆን ይገባል!!
ሀገራችን በታሪኳ እስከአሁን ድረስ በተለያዩ የኃይል አማራጮች ችግሮችን ለመፍታት እንዲሁም የመንግሥት ሥልጣንን ለመቀየር ስትባዝን አለች፤ ሆኖም የረጅም ዓመት ሀገረ መንግሥት ታሪኳን በማይመጥን መልኩ እስከአሁን ኋላቀር ከሚባሉት ሀገራት ግንባር ቀደም ከመሆን የዘለለ አንዳች ነገር አላገኘችም። ላለፉት ከ 30 ዓመታት በላይ በሀገሪቱ ውስጥ ላሉ ችግሮች፣ ግጭቶች፣ ጥቃቶች እንዲሁም ሌሎች በርካታ ችግሮች በዋነኛነት ምክንያቱ ደግሞ ሕወሓት ሥልጣነ መንበሩን በኃይል ካረጋገጠ በኋላ ያሠፈነው የብሔር ፖለቲካ ነው። ይኽ የፖለቲካ ሥርዓት ከፍተኛ ችግር ያስከተለ ቢሆንም በሕወሓት ተንኳሽነት የተጀመረው እና ከሁለት ዓመታት በላይ የፈጀው የሰሜኑ ጦርነት ያስከተለውን የሰው ህይወትና የንብረት ውድመት በከፍተኛነቱ የሚስተካከለው የለም። ከዚህ ጥፋት መልስ በፕሪቶሪያ ስምምነት ከጦርነት መውጣት የተቻለ ቢሆንም ይህ በዘላቂነት እንዳይቀጥል በተለይ ሕጋዊ ማንነቱን ባጣው ሕወሓት በኩል እንደሥምምነቱ እንዳይፈፀም የታዩ ዳተኝነቶች እና እንደ አጠቃላይ የፖለቲካ ሥሪቱ ላይ ውጤት ሊያመጣ የሚችለውን ሀገራዊ ምክክር፣ የ2018 ዓ.ም ምርጫ በትግራይ ክልል እንዳይከናውን በማድረግ፣ በክልሉ የሚገኙ ተፈናቃዮች ወደ ቀዬአቸው እንዳይመለሱ በታጋችነት በመያዝ በአጠቃላይ በክልሉ ያለው ችግር እንዳይፈታ በማድረግ ይኸው ችግር መልሶ ይፈጠር ይሆን የሚል ስጋትን እንደያዘ አለ። ለትግራይ ማኅበረሰብ እቆረቆራለሁ የሚለው ይህ ቡድን ከእሰጠዓገባ ውጪ መኖር የማይችል በሚመስል መልኩ የተለያዩ ችግሮችን ለመፍጠር እየሞከረ የከረመ ሲሆን ግንቦት 02/2018 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ እና በክልሉ አፀደቀ በተባለው አዋጅ ግልጽ የጦርነት አዋጅን ለፍፏል። በተለይም በአዋጁ ያካተተው አስገዳጅ የወታደር ምልመላ፤ የተለዩ ድምፆች በትግራይ እንዳይሰሙ ያስቀመጠው ልጓም፤ ሁሉም ነገር ወደ ጦር ግንባር የሚመስለው የፕሮፖጋንዳ ልፈፋ ይኽንን ተፈጥሯዊ ጠበኛ ባሕርዩን እና ፍላጎቱ አሁንም የትግራይን እና አጠቃላይ የኢትዮጵያን ህዝብ በስንት ልፋት ወዳስቆመው ጦርነት እና እልቂት መክተት መሆኑን ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ ነው። በመሰረቱ አዋጁን ማውጣቱ እና በተለይም ከወታደር ምልመላ እና ጦርነቱን ካለመደገፍ ጋር በተገናኘ የተካተቱት ቅጣቶች ማኅበረሰቡ በጦርነቱ ለመሣተፍ ፍላጎት እንደሌለው እና በዚህም ቡድኑ ስጋት ያደረበት መሆኑን በግልፅ የሚያሣይ ነው፤ ይህ ተስፋ የቆረጠ እድሜያቸው የገፋ የሥልጣን ጥመኞች ስብስብ አሁንም በግጭት ውስጥ አፍላ ወጣቶችን የመማገድ ዓላማ አድርጎ ከዚህ ቀደም ልጆቻቸውን ያጡትን እናቶች፤ በስለት ከጦርነቱ የተረፈ የቀረ ልጅ ያላቸውን ጧሪ ቀባሪያቸውን ሊነጥቃቸው አሰፍስፎ መምጣቱ ለትግራይ ህዝብም ሆነ ለሰው ልጆች ሁሉ እንጥፍጣፊ ርህራሄ እንደሌለው ያሳያል። ይህንን ኃይል በቃህ ማለት እና በትግራይ ያሉ ወገኖቻችንን ከማያባራ መከራ መታደግ የሁላችንም ኢትዮጵያውያን የጋራ የቤት ሥራ ሊሆን ይገባል፤ ጦርነትን ሳይጀመር በፊት ማስቆም ይገባናል። ኢዜማ የትኛውም ፖለቲካዊ ችግር በውይይት መፈታት አለበት ብሎ በጽኑ የሚያምን ሲሆን ይህንን ለማድረግ ፈቃደኛ ያልሆነን እንደ ሕወሓት ዓይነት ደም የማይጠረቃ አካል እና እሱን የሚዘውሩ ጥቂት ግለሰቦች በቃችሁ ብሎ ለማስቆም እና የትግራይ ህዝብን ካላስፈላጊ መከራ ለመታደግ በህዝብ ላይ ምንም አይነት መስዋዕትነት በማያስከትል መልኩ በሕገወጥ ቡድኑ ላይ ብቻ ያነጣጠረ አስፈላጊ ሕጋዊ እርምጃ በመንግሥት እና ከመንግሥት ጋር በጋራ በሚቆሙ ማንኛውም ለትግራይ ማኅበረሰብ በሚቆረቆር አካል ሊወሰድ እንደሚገባ ያምናል፤ ማኅበረሰቡም አሁን ለጦርነት ዕያሣየ ያለውን እምቢተኝነት በተጠናከረ መልኩ እንዲገፋበት ጥሪ እናቀርባለን። በመጨረሻም በዚህ ሒደት ውስጥ ፓርቲያችን ማኅበረሰቡ እያለፈበት ያለውን ጭንቀት እየኖረበት ያለውን አሰቃቂ ሁኔታ ለመቅረፍ ባለው አቅም ሁሉ በቀጥታ ለማገዝ ከማንኛውም ሀገራዊ ኃይል ጋር በጋራ ለመሥራትና የበኩሉን ለማበርከት ዝግጁ መሆኑን ያረጋግጣል። የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) ግንቦት 04/ 2018 ዓ.ም.

ኢዜማ እስካሁን በ5 የምርጫ ክልሎች ላይ ውጤትን የቀየሩ ችግሮች ተፈፅመዋል ብሎ ስለሚያምን በነዚህ ቦታዎች ላይ ውጤቱ ተሰርዞ በድጋሚ ምርጫ እንዲደረግ ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫ አቤቱታ ያስገባ ሲ
ኢዜማ እስካሁን በ5 የምርጫ ክልሎች ላይ ውጤትን የቀየሩ ችግሮች ተፈፅመዋል ብሎ ስለሚያምን በነዚህ ቦታዎች ላይ ውጤቱ ተሰርዞ በድጋሚ ምርጫ እንዲደረግ ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫ አቤቱታ ያስገባ ሲሆን የቦርዱን ውሳኔ የሚጠባበቅ ይሆናል። አቤቱታ ያስገባንባቸው ምርጫ ክልሎች፤ 1. ባኮ ጋዘር ቁጥር 1 ምርጫ ክልል 2. ላስካ መደበኛ ምርጫ ክልል 3. ቢጣ ጌሻ ምርጫ ክልል 4. ፈለገ ሰላም ምርጫ ክልል 5. ማረቃ ጌና ምርጫ ክልል በሌሎች ምርጫ ክልሎችም በተመሳሳይ አቤቱታዎችን እየመረመርን ሲሆን ሲጠናቀቁ ለቦርዱ የምናቀርብ ይሆናል። #ኢዜማ #ኢትዮጵያ #ምርጫ_2018

የምርጫው ሂደት ስኬታማ እንዳይሆን ካደረጉት ዋነኛ መዋቅራዊ ተግዳሮቶች መካከል በመንግሥት አካላት የተፈጸሙ ሕጋዊ ጥሰቶች በቀዳሚነት ይጠቀሳሉ። መንግሥት ለሕዝብ የጋራ አገልግሎት የሚውሉ ንብረቶችን ለገዢው ፓርቲ የፖለቲካ ጥቅም እንዲውሉ አሳልፎ ሰጥቷል። በምርጫው ዕለትም "የሰላም ሠራዊት" ተብለው የተደራጁ አካላትን፣ የወረዳ ሥራ አስፈጻሚዎችንና የመንግሥት ሠራተኞችን በሕግ ባልተሰጣቸው የምርጫ ተግባራት ውስጥ በማሳተፍ ግልጽ ጣልቃገብነት ፈጽሟል። በተለይም ደግሞ ከከተማ ርቀው በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ላይ የመንግሥት የጸጥታ አካላትና የገዢው ፓርቲ አመራሮች የተፎካካሪ ፓርቲ ታዛቢዎችን ሲያስፈራሩ፣ ሲያዋክቡና በጉልበት ከጣቢያዎች ሲያስወጡ ተስተውለዋል። ይህ ዓይነቱ አሠራር የመንግሥትን ገለልተኝነትና የሕግ የበላይነትን የገፈፈ እና ጭልጭል የሚለውን የዲሞክራሲ ጅማሮ ጨርሶ የሚያጠፋ አደገኛ ተግባር ነው። በሌላ በኩል፣ የዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙኅን አቀራረብም ሌላኛው የሂደቱ ፈተና ነበር። የእነዚህ አካላት መመዘኛና መስፈርት በዋነኛነት በገዛ ራሳቸው ፖለቲካዊና ስትራቴጂካዊ ተጠቃሚነት ላይ ብቻ የታጠረ ነው። በዚህም ምክንያት የሀገሪቱን የምርጫ ሂደት እነርሱ ለዘመናት ካለፉበት የዲሞክራሲ ጎዳና አንጻር ከመመልከት ይልቅ፣ የምርጫ ሂደቱ ሙሉ በሙሉ ቅቡልነት እንዳይኖረው ለማድረግ ሲሰሩ ተስተውሏል። ይህም በምርጫ የሚመሠረት መንግሥት እንዳይኖረን በማድረግ በጎረቤት ሀገራት ጭምር እንደታዘብነው መንግሥት አልባ ሀገር የማድረግ የብሔራዊ ጥቅማችን ተቃራኒ ተግባር ሆኖ አግኝተነዋል። ማጠቃለያ ኢዜማ መንግሥታዊ ሥልጣን ሊያዝ የሚችለው በሰላማዊ መንገድ እና በምርጫ ሥርዓት ብቻ መሆኑን ያለማወላወል ያምናል። በምርጫው ሒደት ውስጥ ሰፊ መዋቅራዊ ተግዳሮቶች እና የገዢው ፓርቲ ካድሬዎች ስልታዊ የጥርነፋ ስልቶች በግልጽ የታዩ ቢሆንም፣ ፓርቲያችን በሰላማዊና በሰለጠነ የሐሳብ ክርክር የሕዝብን ልብ የማሸነፍ መርሆውን አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን በድጋሚ ማረጋገጥ ይፈልጋል። በዚህ የምርጫ ተሳትፏችን ውስጥ ውስብስብ ችግሮችን በጽናት ተጋፍጠን ማለፋችን እንደተጠበቀ ሆኖ፣ ፓርቲያችን ካለፉት የምርጫ ተሞክሮዎቹ በእጅጉ የተሻሉ ስኬቶችን ማስመዝገቡን በበጎ ጎኑ ገምግሟል። የሀገራችንን የዲሞክራሲ ባህልን ከዳዴ ጉዞው አውጥቶ በጠንካራ መሠረት ላይ ለመገንባት፣ ኢዜማ በሰላማዊ የፖለቲካ ትግል ውስጥ ያለውን የማይናወጥ ቁርጠኝነት እያደሰ፣ ለዘላቂ ሀገር ግንባታ ከሕዝባችን ጋር በጽናት እንደሚቆም በድጋሚ ያረጋግጣል። የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ.ም. አዲስ አበባ

7ተኛው ሀገራዊ ምርጫን አስመልክቶ ከኢዜማ የተሰጠ መግለጫ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የተካሄደው ሀገር አቀፍ ምርጫን በተመለከተ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋዊ ውጤቶችን ካሳወቀ በኋላ እንደፓርቲ ዝርዝር ሪፖርት ወደፊት ማቅረቡ እንደተጠበቀ ሆኖ ምርጫውን በተመለከተ አጭር ግምገማ አድርጓል። ፓርቲያችን ምርጫው በተካሄደባቸው አካባቢዎች ከሞላ ጎደል በሰላም መጠናቀቁን እንደ አንድ በጎ ክስተት ይገነዘበዋል። ፓርቲያችን በዚህ ሀገር አቀፍ ምርጫ ለመወዳደር ሲወስን የምርጫው ሂደት አልጋ በአልጋ ይሆናል ከሚል ተላላነት በመነሳት አይደለም። ለዚህም ዋነኛው ምክንያት የዴሞክራሲ ባህላችን ገና በዳዴ ላይ ያለ በመሆኑ እና ይህንን ባህል ለማጎልመስ የሚወስደው ጊዜ ቀላል አለመሆኑን ከመረዳት የመነጨ ነው። ኢዜማ ምርጫውን ሂደት እና ውጤት ሊጎዱ የሚችሉ ሁኔታዎች የመኖር እድላቸው እጅግ ከፍተኛ መሆኑን አምኖ፤ ነገር ግን የዴሞክራሲ ግንባታ በአስተሳሰብ፣ በመተማመን እና በተደጋጋሚ በማድረግ ጥረት የሚሳካ መሆኑን በመገንዘብ ነው በሂደቱ ውስጥ በሙሉ ልብ መሳተፉን የቀጠለው። 👉 የምርጫው ጠንካራ ጎኖች ምንም እንኳ በምርጫው ሂደት ገዢው ፓርቲ ዜጎችን በማስገደድ የምርጫ ካርድ እንዲወስዱ ማድረጉ አግባብነት የሌለውና የሚኮነን ቢሆንም፣ በሂደቱ ከፍተኛ ቁጥር ያለው መራጭ ሕዝብ መመዝገቡ አንዱ መነቃቃትን ያሳየ ጠንካራ ጎን ነው። ከዚህም በተጨማሪ፣ የአሰራሩ አዲስነት እና የቴክኖሎጂ አፈጻጸም ክፍተቶች በስፋት ቢታዩም፣ መራጮችና እጩዎች ለመጀመሪያ ጊዜ በኦንላይን (በኢንተርኔት) አማካኝነት መመዝገብ መጀመራቸው ለዲሞክራሲ ስርዓቱ መዘመን ትልቅ እመርታ ነው። በሌላ በኩል፣ ለሁሉም ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሰፊ የሚዲያ እድል፣ የጋራ የክርክር መድረክና የአየር ሰዓት በአግባቡ መመቻቸቱ የሂደቱ ሌላኛው ስኬት ነው። ፓርቲያችን እነዚህን የታዩ በጎ ጅምሮች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የራሱን አስተዋጻኦ መወጣቱን ይቀጥላል። 👉 በምርጫው ሂደት ላይ የታዩ መዋቅራዊ ፈተናዎችና ተግዳሮቶች የገዢው ፓርቲ መዋቅራዊ ተፅዕኖዎች ቀዳሚው ፈተና በገዢው ፓርቲ (ብልጽግና) የተፈጸሙ የተዛቡ አሠራሮች ናቸው። ፓርቲው እንደ ማኅበራዊ ጥበቃ፣ የትምህርት ቤት ምገባና መሠረታዊ አገልግሎቶችን ማቅረብን የመሰሉ የመንግሥት የልማት ፕሮግራሞችን ለምርጫ ቅስቀሳ ፖለቲካዊ መጠቀሚያ አድርጓቸዋል። ዜጎች ለገዢው ፓርቲ ድምጽ ካልሰጡ እነዚህ አግልግሎቶችን እንደሚያጡ ስጋት ውስጥ በመክተት፣ ድምፅን በቁሳዊ ፍላጎት የመግዛት ስልት ተከትሏል። ይህንንም "ትስስር፣ የብልጽግና ቤተሰብ" በሚባል የዳቦ ስም በመጠረነፍ የምርጫ ውሳኔያቸው ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ አሳድሮባቸዋል። የመንግሥት መገናኛ ብዙኅንን የገዢው ፓርቲ የግል ንብረት አድርጎ የመጠቀም ሁኔታም ዐይን ባወጣ መልኩ በምርጫው ወቅትም ቀጥሏል። በመራጮች ምዝገባ ወቅት የአካባቢው የመንግሥት አስተዳደር ሠራተኞችና የፓርቲው ካድሬዎች መራጮች ከምርጫ ጣቢያ ካርድ ይዘው ሲወጡ እና መረጃዎችን ቤት ለቤት በመሰብሰብ፣ ምርጫው በምስጢር የሚካሄድ በማይመስልበት ሁኔታ የሥነ-ልቦና ጫና ፈጥረዋል። ይህ ተፅዕኖ በምርጫ ቀኑም ቀጥሎ፣ ካድሬዎች በሕግ ተለይቶ ባልተሰጣቸው ኃላፊነት ሰልፍ እናስተናብራለን በሚል ሰበብ በምርጫ ጣቢያዎች ውስጥ በአካል በመገኘት መራጮች ላይ በተለያዩ መንገዶች ተጽእኖ አሳድሯል። ወደ ምርጫ ጣቢያ በሚወስዱ መንገዶች ላይ በመቆም "ስንዴን ምረጡ" የሚሉ ይፋዊ ቅስቀሳዎችን በማድረግ የመራጩን ማኅበረሰብ ነጻነት የሚገፍፍ ተግባራትን ሲፈጽሙ ተስተውለዋል። በተለይም ከከተሞች ውጪ የመንግሥትን የሕዝብ ሀብትና ንብረት ለፓርቲው የምርጫ ቅስቀሳ ሥራዎች በሠፊው አውሏል። ገዢው ፓርቲ ምርጫውን የሚያውኩ እነዚህን የመሰሉ መዋቅራዊ ጥሰቶች ለማስተካከል ቁርጠኛ ካልሆነ፣ በማኅበረሰቡ ዘንድ "በሰላማዊ ትግልና በምርጫ ሥልጣን መያዝ አይቻልም" ወደሚል ተስፋ መቁረጥ እንዳይገፋው ያሰጋናል። ይህ ደግሞ ከሰላማዊ ትግል ያፈነግጡ አማራጮችን በማበረታታት ሀገራችንን ወደ ሌላ ሊቀለበስ የማይችል አጠቃላይ ቀውስ ውስጥ የሚጥላት መሆኑን ለአፍታም ሊዘነጋ አይገባም። 👉 በተፎካካሪ ፓርቲዎች የታዩ ጉድለቶች አንዳንድ ተፎካካሪ ፓርቲዎች የምርጫ ሂደቱን በሙሉ ልብ ተቀብለው የዲሞክራሲ ምህዳሩን ለማሻሻል ከመጣር ይልቅ፣ ከጅምሩ ለምርጫው ቅቡልነት ማጣት ምክንያት የሚሆኑ “ሁለት ልብ” አቋሞችን ከማንጸባረቃቸውም በላይ ከሰላማዊ ትግል ውጪ የሆኑ አቋራጭ መንገዶችን የመጠቀም ፍላጎት ተስተውሏል። በምርጫ ክርክሮች ወቅትም ተጨባጭ አማራጭ የመፍትሔ ሐሳቦችን ከማቅረብ ይልቅ ሁላችንም የምናውቃቸውን ሀገራዊ ችግሮች በማጉላት የሕዝብን ስሜት በመቀስቀስ መጠቀሚያ ለማድረግ ከመሯሯጥ በተጨማሪ እጩዎች በተወዳደሩባቸው የምርጫ ክልሎች እንኳ ሂደቱን የሚከታተል የተሟላ የታዛቢ መዋቅር ማሠማራት አለመቻላቸው ሌላው ጉድለታቸው ነው። 👉 የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ክፍተቶች የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ አሁንም ቢሆን በበቂ የሰው ኃይልና በቴክኖሎጂ የዳበረ ጠንካራ ተቋም መሆን አለመቻሉ አሳዛኙ እውነታችን ነው። ከሁሉም በላይ አሳሳቢው ጉዳይ፣ በምርጫው ዕለት ሂደቱን እንዲያስተናብሩ የተመደቡ የቦርዱ አስፈጻሚዎች ሕጋዊ ኃላፊነታቸውን በሌሎች የመንግሥት አስተዳደር አካላትና ግለሰቦች ሲነጠቁ፣ ድርጊቱን ከማስቆም ይልቅ ዝምታን መምረጣቸው ነው። ተቋሙ ካለፉት ምርጫዎች በቂ ትምህርት በመውሰድ የተሻሉ፣ ገለልተኛና ለሕሊናቸው ታማኝ የሆኑ አስፈጻሚዎችን በጥንቃቄ መመልመል፣ ማሰማራት እና መቆጣጠር ሲገባው፤ በተመሳሳይ መልኩ በ"ይድረስ ይድረስ" ለማጋፈር መሞከሩ በምርጫው ገለልተኝነት ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ አሳድሯል። በዚህም ምክንያት ቁጥራቸው ቀላል የማይባል የቦርዱ አስፈጻሚዎች፣ በተግባር የገዢው ፓርቲ ታማኝ ጉዳይ አስፈጻሚዎች ሆነው ተገኝተዋል። 👉 የሲቪክ ማኅበራትና የማኅበረሰቡ ሚና ሲቪክ ማኅበራት ባለፉት ዓመታት የዜጎችን መብትና ግዴታዎች የማስተማር ተቋማዊ ግዴታቸውን ከመወጣት አኳያ የረባ ተሳትፎ እንዳልነበራቸው የአደባባይ ምሥጢር ነው። በምርጫው ዕለትም ተሳትፏቸው "አሉ ለመባል" እና ተምሳሌታዊ ከመሆን ባለፈ፣ የምርጫውን ነጻነትና ፍትሐዊነት በቅጡ አልተወጡም። በሌላ በኩል፣ ማኅበረሰባችን በምርጫ ሥርዓት "ለውጥ አመጣለሁ" የሚል የፖለቲካ እምነትና መተማመንን ገና በበቂ ሁኔታ ባለማዳበሩ ምክንያት፣ ምንም እንኳን ከቀደሙት ጊዚያት የተሻለ ቢሆንም በሂደቱ ላይ የሚጠበቀውን ያህል በንቃት ተሳትፏል ብለን አናምንም። በምርጫው ለመሳተፍ የምርጫ ካርድ የወሰደው የማኅበረሰብ ክፍል እንኳ ሳይቀር በገዢው ፓርቲ መዋቅራዊ ጫናዎችና ስጋቶች ውስጥ በቀላሉ የመውደቅ ዝንባሌ አሳይቷል። በምርጫው ዕለት የታዩ የመስተንግዶ መጓተቶች ባስከተሉት መሰላቸት ምክንያት በርካታ ዜጎች ድምፅ ከመስጠት ተቆጥበዋል። ማኅበረሰቡ አግባብ ባለው መልኩ ኃላፊነት ወስዶና ነቅቶ ከተንቀሳቀሰ፣ በዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ሂደት ላይ ፈጣንና ሥር ነቀል ለውጥ ማምጣት የሚችለው ቀዳሚው ኃይል ማኅበረሰቡ ነው። ይህንን ኃላፊነት አለመወጣት ግን በሂደቱ ላይ የሚመጣውን ከፍተኛ ጉዳት ቀድሞ የሚያስተናግደው ራሱ ማኅበረሰቡ መሆኑን አውቆ፣ በቀጣይ ዜጎች ፖለቲካዊ መብቶቻቸውንና ተሳትፏቸውን በንቃት እንዲወጡ አጥብቆ መሥራት ይጠበቅብናል፤ ማኅበረሰቡም ኃላፊነቱን ሊወስድ ይገባል። 👉 የመንግሥት ዳተኝነት እና የዓለም አቀፉ ሚዲያ ጣልቃገብነት

በምሥራቅ አርሲ ማንነትን (ሃይማኖትን) መሠረት ባደረገ ጥቃት በርካታ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታይ የሆኑ ዜጎች እስከአሁን ማንነቱ ባልታወቀ አካል እንደተገደሉ እና ቤተክርስቲያን መቃጠሉ፣ ከጥ
በምሥራቅ አርሲ ማንነትን (ሃይማኖትን) መሠረት ባደረገ ጥቃት በርካታ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታይ የሆኑ ዜጎች እስከአሁን ማንነቱ ባልታወቀ አካል እንደተገደሉ እና ቤተክርስቲያን መቃጠሉ፣ ከጥቃቱ የሸሹ ዜጎችም ከቀያቸው መሰደዳቸው ከመገናኛ ብዙሃንና ከሀገረስብከቱ የሚወጡ መረጃዎች ያሳያሉ። ኢዜማ ሁሌም እንሚያስገነዝበው ለዚህ ዐይነቱ ማንነትን መሠረት ያደረገ ጥቃት ምንጬ ፖለቲካችን በማንነት ላይ የተመሠረተ በመሆኑ ነው ብሎ ያምናል። በተጠቀሰው ስፍራ በተደጋጋሚ የሚደርሰው መሰል ጥቃትን የመከላከል ኃላፊነት የአካባቢው የመንግሥት አስተዳዳር እና የጸጥታ ተቋማት መሆኑ የታወቀ ነው። በዚህ ረገድ የአካባቢው አስተዳደርና የኦሮሚያ ክልል መንግሥት በተደጋጋሚ ተፈትኖ እንደወደቀ ማየት ይቻላል። ስለሆነም አስፈላጊውን ማጣራት ተደርጎ ኃላፊነት የሚወስዱ አካላትን በመለየት አስተማሪና ሕጋዊ የእርምት እርምጃ መንግሥት እንዲወስድ እናሳስባለን። በዚህ ኢሰብአዊ ጥቃት ለተገደሉት ዜጎች የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እየገለጽን ለሟች ቤተሰቦችና ዘመዶች እንዲሁም ለመላው ኢትዮጵያውያን መጽናናትን እንመኛለን። በማንነት ላይ የተመሠረተው ፕለቲካችን ጨርሶ አንድ በአንድ ሳያጠፋን መፍትሔ ማበጀት የሁሉም ባለድርሻ አካላት የቤት ሥራ መሆኑንም ኢዜማ ማስገንዘብ ይወዳል። #ኢዜማ #ኢትዮጵያ

ከኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) የተሠጠ መግለጫ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) ግንቦት 07/2018 ዓ.ም. "ዴሞክራሲያዊ መብቶች በብሔር ማንነት እና በመንግሥት አሉታዊ ተፅዕኖ ውስጥ መውደቃቸው ምርጫውን ችግር ውስጥ ይከታል" ሲል ባወጣው መግለጫ፤ የሐረሪ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ለሐረሪ ክልል ም/ቤት የሚወዳደሩ እጩዎች የሐረሪ ብሔረሰብ ተወላጅ መሆን ለመመረጥ እንደ አስገዳጅ መስፈርት መቀመጥ በኢፌዴሪ ሕገመንግስት የተደነገገውን ዜጎች ያለምንም ዘር፣ ሐይማኖት እና ሌሎች ማንነት ልዩነቶች ሊጎናፀፉት የሚገባን የመምረጥ እና መመረጥ መብትን የሚጥስ መሆኑን ገልፆ መቃወሙ ይታወሳል። በተጨማሪም በዚሁ ክልል ለሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የሚወዳደሩ እጩዎች ለሐረሪ ም/ቤት እንደሚወዳደሩ ዕጩዎች የሐረሪ ብሔረሰብ ተወላጅነትን እንደ አስገዳጅ መስፈርት ባያስቀምጥም በክልሉ ኢዜማን ወክሎ ለሕ/ተ/ም/ቤት እንዲወዳደር ያቀረብነው እጯችን በሐረሪ ጠ/ፍ/ቤት የወንጀል እና ፍትህ ብሔር ችሎት መዝገብ ቁ 08916 ከሕግ አግባብ ውጪ የሐደሬ ብሔር ተወላጅ አይደሉም በሚል ፓርቲያችን ባልተሣተፈበት እና ባላወቀው ክርክር እጩው እንዳይወዳደሩ ወስኗል። የውሳኔው ይዘት ምንም እንኳን ስለ ሐረሪ ክልል ም/ቤት ተወዳዳሪዎች የተሰጠ ቢሆንም ለሕ/ተ/ም/ቤት ያቀረብነው አባላችን ስም ተካቶ የተሠጠው ውሳኔ ሕጋዊ ባለመሆኑ ምርጫ ቦርድ ለፍ/ቤቱ ማብራሪያ ቢጠይቅም እንዲሁም ፓርቲያችን በሌለበት የተሠጠው ውሳኔ ተገቢ አለመሆኑንና የክርክሩ አካል እንድንሆን ያቀረብነውን ጥያቄ ከፍትሕ ይልቅ ፖለቲካዊ ውሳኔ ተጭኖት ሳይቀበል ቀርቷል። በመሆኑም ምርጫ ቦርድ የፓርቲያችንን እጩ ተወዳዳሪ ሕጋዊ ባልሆነ/ባልተሠጠ ውሳኔ ላይ በመመሥረት ከእጩነት ማገዱ ተገቢ አለመሆኑን በመጥቀስ እንዲታረም ለፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት አቤቱታችንን ያቀረብን ሲሆን ክርክሩ ውሳኔ እስከሚያገኝ ድረስ የምርጫ ቦርድ እጯችንን ለመሠረዝ የሠጠው ውሳኔ እንዲታገድ የፍ/ቤቱን ውሳኔ የጠየቅን ቢሆንም ፍ/ቤቱ ግን ተከሳሽ የሆነውን ምርጫ ቦርድን ሳያስቀርብ በእራሡ የተከሳሽን የመከራከርያ ነጥቦች በማንሳት ውሳኔ አሳልፏል። የተላለፈው ውሳኔ አግባብነት ያለው እና ፍትሐዊ ነው ብለን የማናምን መሆኑን እየገለጽን ኢዜማ የዚህ ዓይነት ኢፍትሐዊ አሠራሮች ከሀገራችን እስከሚጠፉ ድረስ እስከመጨረሻው ድረስ እንደሚሞግት ለመግለጽ ይወዳል። #ኢዜማ #ኢትዮጵያ

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1447ኛው ዒድ አል አድሐ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ! የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ)
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1447ኛው ዒድ አል አድሐ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ! የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ)

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) የቅስቀሳ መዝጊያ መርሐግብርን በሚመለከት የተሰጠ ማብራሪያ በቅድሚያ ለእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው ዒድ አል አድሐ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ። በዓሉ የሰላም የፍቅር እና የመተሣሠብ እንዲሆንላችሁ እየተመኘን የቅስቀሳ መዝጊያ መርኃግብራችን ላይ የሚከተለውን ማብራሪያ ለመሥጠት እንወዳለን። ፓርቲያችን ኢዜማ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ2018 ምርጫ ቅስቀሳ መጀመሩን ካወጀበት ቀን ጀምሮ በተለያዩ መንገዶች ለማኅበረሰቡ ያዘጋጃቸውን አማራጭ የፖሊሲ ሀሳቦች አቅርቦ ለመመረጥ ሲቀሰቅስ መቆየቱ ይታወቃል። ምርጫ ቦርድ ባስቀመጠው የቅስቀሳ የጊዜ ሰሌዳ መሠረት ፓርቲያችን ያዘጋጀውን የመዝጊያ መርኃግብር አስመልክቶ ሚዲያዎች እንዲዘግቡ ጥሪ ያቀረበበትን ደብዳቤ በማያያዝ መርኃግብሩ በበዓሉ ቀን መደረጉ ግርታ የፈጠረባቸው ወገኖች በቀናነት ማብራሪያ እንድንሰጥበት ጠይቀውናል። የምርጫ ቅስቀሳ ማጠቃለያችንን በዚህ ዕለት ማድረግ የተመረጠበት ምክንያቶች የሚከተሉት ናቸው 1. ከበዓሉ ማግስት አንስቶ ማንኛውም ከቅስቀሳ ጋር የተያያዙ ተግባራት የማይፈጸምበት የጽሞና ጊዜ በመሆኑ፤ 2. በሥራ ቀናት አባላቱን (ሁሉንም የእምነት ተከታዮች) የማሣተፍ እድሉ ዝቅተኛ በመሆኑ፤ 3. መርሐግብሩን አመሻሽ ላይ ማድረግ ያስፈለገው የእስልምና እምነት ተከታይ አባላት እና ደጋፊዎቻችን በበዓሉ የሚደረጉት የሶላት ስግደት እና ከቤተሰቦቻቸው ጋር የሚያሳልፉትን የበዓል ጊዜ ታሣቢ በማድረግ ምሽት ላይ መርሐግብራችንን እንዲካፈሉ በማሰብ፤ 4. የመርኃግብሩ ይዘት ሰላማዊ ሰልፍ ሳይሆን የፓርቲው ቅስቀሳውን ማገባደዱን የሚገልጽበት መሆኑን ለማሣወቅ እንወዳለን። አስተያየታችሁን በቀናነት የገለፃችሁልን ወገኖቻችንን ሁሉ ከልብ እያመሰገንን በድጋሚ መልካም በዓል እንዲሆንላችሁ እንመኛለን። #ኢዜማ #ኢትዮጵያ #ምርጫ_2018

የኢዜማ የሐረሪ ክልል ሕዝብ ተወካዮች እና የክልል ም/ቤት ዕጩዎች ኢዜማን ይምረጡ!! #ኢዜማ #ኢትዮጵያ #ምርጫ_2018
የኢዜማ የሐረሪ ክልል ሕዝብ ተወካዮች እና የክልል ም/ቤት ዕጩዎች ኢዜማን ይምረጡ!! #ኢዜማ #ኢትዮጵያ #ምርጫ_2018

መፈፀም የማንችለውን ቃል አንገባም፤ ለገባነው ቃል ተጠያቂ የሚሆን መንግሥት እንገነባለን!! #ኢዜማ #ኢትዮጵያ #ምርጫ_2018
መፈፀም የማንችለውን ቃል አንገባም፤ ለገባነው ቃል ተጠያቂ የሚሆን መንግሥት እንገነባለን!! #ኢዜማ #ኢትዮጵያ #ምርጫ_2018

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) በወቅታዊ የምርጫ ጉዳዮች ላይ የተሰጠ መግለጫ "ዴሞክራሲያዊ መብቶች በብሔር ማንነት እና በመንግሥት አሉታዊ ተጽዕኖ ውስጥ መውደቃቸው ምርጫውን ችግር ውስጥ ይከታል !" የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) በሃገሪቱ ውስጥ የሰላማዊ ፖለቲካ ፉክክርን መርጦ ሲንቀሳቀስ ሃገራችን የምትተዳደርባቸውን ሕጎች አክብሮ፣ ዴሞክራሲ በሒደት የሚሳካ ልምምድ መሆኑን በመረዳት እያንዳንዱን ጉዳይ ለፖለቲካ ትርፍ ከማዋል ይልቅ ለወደፊት የዘመነ ፖለቲካ መሠረት የሚሆን መተማመንን ለመፍጠር ለሚመለከታቸው አካላት ጉዳዩን እያሳወቀ እና እልባት እንዲያገኙ መጣርን መርጦ የሚንቀሳቀስ እና በፖለቲካ ውስጥ የፖለቲካ ፓርቲ ሚና ምን እንደሆነ የለየ እና እነዚያ ሚናዎች ላይ ትኩረት ሰጥቶ የሚንቀሳቀስ ዘመኑን የዋጀ ፓርቲ ነው። ፓርቲያችን አሁን በምንገኝበት የምርጫ ወቅትም ከወትሮው በተለየ ልዩነቶቹን አጉልቶ የሚያሳይባቸውን ከ50 በላይ ፖሊሲዎች አሰናድቶ እነዚህን መሠረት ያደረጉ አጀንዳ ተኮር ክርክሮችን ሁሌ እንደሚለው በዕውቀት እና ስክነት ላይ ተመሥርቶ ማድረጉም የዐደባባይ ሚስጥር ነው፤ ሆኖም አንድ እጅ ብቻውን እንደማያጨበጭብ ሁሉ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን ለማስፈን የምናደርገው ምርጫ የሁሉንም አካላት የድርሻ ሚና በሕግ አግባብ እና በቅጡ መወጣትን ይጠይቃል። በመሆኑም በምርጫው ላይ እያደረግን ባለው ተሳትፎ ከአቅማችን በላይ የሆኑትን ጉዳዮች ለማኅበረሰቡ ማሳወቅ አስፈላጊ በመሆኑ ከዚህ በታች የምርጫ ሒደቱ ላይ አሉታዊ ተጽእኖዎች ያልናቸውን ጉዳዮች እንደሚከተለው እናቀርባለን፤ 1. በብሔር ማንነት ምክንያት የተነጠቀ ዜጋዊ እና ዴማክራሲያዊ መብት በሐረሪ ክልል የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መገለጫ መርሆዎች አንዱ በፖለቲካ ውስጥ በንቃት መሳተፍ (political participation) ሲሆን በዚህ ውስጥ ከሚወድቁት መካከል የመምረጥ እና የመመረጥ መብት አንዱ ነው። ይህ መርሆ በኢፌዴሪ ሕገመንግሥት ምዕራፍ 3 አንቀጽ 38 (1) ላይ “ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ዜጋ በቀለም፣ በዘር፣ በብሔር፣ በብሔረሰብ፣ በፆታ፣ በቋንቋ፣ በሃይማኖት፣ በፖለቲካ ወይም በሌላ አመለካከት ወይም አቋም ላይ የተመሰረተ ልዩነት ሳይደረግበት . . . በማናቸውም የመንግስት ደረጃ በየጊዜው በሚካሄድ ምርጫ የመምረጥም ሆነ የመመረጥ መብት” እንዳለው በግልፅ የሕግ ድጋፍ ተሰጥቶታል። ምንም እንኳን የኢፌዴሪ ሕገመንግስት ይህንን በግልጽ ቢደነግግም የሐረሪ ክልል ሕገመንግሥት ከዚህ ፍጹም በተቃራኒ ለሐረሪ ብሄራዊ ጉባኤ የሚወዳደሩ አባላት በምርጫው ለመወዳደር የሐረሪ ብሔረሰብ አባልነትን መስፈርት አድርጎ በማስቀመጥ ለሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ዕጩነት ያቀረብነው ተወካያችንን እና የሌሎች ተፎካካሪ ፓርቲ እጩዎችን በሐረሪ ክልላዊ መንግሥት ጠ/ፍ/ቤት የወንጀል እና ፍትህ ብሔር ችሎት መ/ቁ 08916 ውሳኔ መሠረት ከምርጫው ውጪ እንዲደረጉ ተወስኗል፤ ምርጫ ቦርድም በዚህ ዕጩ ፋንታ የመብቱ ባለቤት ከሚያደርገው ኢትዮጵያዊ ዜግነቱ ይልቅ ከግለሰቡ ብዙ ማንነት አንዱ የሆነውን የዘውጌ ማንነቱን የሚያሟላ እጩ እንድንተካ በፍ/ቤቱ ውሳኔ መሠረት ትዕዛዝ ሰጥቶናል። ይህ ውሳኔ በአጠቃላይ የሃገራችን የብሔር ፖለቲካ ሥርዓት ያመጣብን ውጤት እንደሆነና ዜጎች በተለያዩ አከባቢዎች ሲንቀሳቀሱ አንደኛ እና ሁለተኛ ዜጋ ተደርገው እንደሚታዩ በግልጽ ማስረጃ ሆኖ ሊቀርብ የሚችል ነው፤ ይህ አይነት ድንጋጌዎች በተለያዩ ክልሎች የሕገመንግሥት ድንጋጌዎች ውስጥ እንደሚገኝም ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ እየገለጽን የነበረ ሲሆን የፖለቲካ ሥሪታችን ከብሔር መላቀቅ እንዳለበት በተደጋጋሚ የምንወተውተውም ለዚህ መሆኑ ሊታወቅ ይገባል። በዓለምአቀፍ ደረጃ ኢትዮጵያዊነትን ከሚገልጡት አንዱ በሆነው ጀጎል ግንብ የተከበበችው ሃረር የደም እና አጥንት ግንብ ገንብቶ እየሰራ ግብር ከፍሎ በሚኖርበት፣ ከማህበረሰቡ ጋር የተለያዩ ቁርኝቶች ያለውን ኢትዮጲያዊ ዜጋን የሚኖርበትን አከባቢ ለማስተዳደር ሲሆን ከእኛ ወገን አይደለህም የሚል መገፋትን የመሰለ ትልቅ ቁስል እንደሌለ ሊታወቅ ይገባል፤ ገዢው ፓርቲም እከተለዋለሁ፤ አስቀጥለዋለሁ የሚለው በስም አሳምሮ ሲጠራው ሕብረ-ብሔራዊ ፌዴራሊዝም የሚለው ይህንን አይነት ደምና አጥንት ቆጥሮ የሚተገብር ሥርዓት መሆኑን አሁንም ሊታወቅ ማኅበረሰቡም ሊያውቀው ይገባል። ኢዜማ ይህ የፖለቲካ ሥሪት ወደ ዜግነት ፖለቲካ እንዲሁም የፌደራል ሥርዓታችን በዋነኛነት ቋንቋን መሠረት ካደረገ መሥፈርት ባለፈ የሃገርን አንድነት እና የኢኮኖሚ እድገት መፍጠር በሚችሉ መስፈርቶች እስኪለወጥ እየሞገትነው የምንቆየው ዋነኛ ጉዳያችን መሆኑን በድጋሜ ለማሳወቅ እንወዳለን ይህንን የፍ/ቤት ውሳኔም በኢፌደሪ ሕገመንግሥት አንቀጽ 9 መሠረት ውሳኔውን ለማስቀልበስ እስከመጨረሻው ሒደት እንደምንጓዝበት ለማሳወቅ እንወዳለን። 2. የጸጥታ አካላት ወገንተኝነት እና የአባላት ለእስር መዳረግ የጸጥታ አካላት ከፖለቲካ ወገንተኝነት ወጥተው ሕግን ብቻ የማስከበር ግዴታ ቢኖርባቸውም በተግባር ግን ለገዢው ፓርቲ ዐይን ያወጣ ወገንተኝነታቸውን በዐደባባይ ከማሳየት አልፈው አባላቶቻችንን ማሠር እና ማንገላታታቸው ለዴሞክራሲያዊ ሀገር ግንባታ የምናደርገውን እንቅስቃሴ አንድ እርምጃ ወደፊት ሁለት እርምጃ ወደኋላ እንዲመለስ በማድረግ አሰልቺ እና አታካች እያደረገው ይገኛል። ለዚሁ አስረጅ የሚሆነው በደቡብ ኢትዮጵያ፣ በጋሞ፣ በኮሬ፣ በዳውሮ እና በአርባምንጭ ዞኖች ዕጩዎቻችንን እና አስተባባሪዎቻችንን ያለ ምንም የሕግ መሠረት በማሰርና በማንገላታት ላይ ይገኛሉ፡፡ በአሁን ወቅት እጩ ሆነው የቀረቡ አባሎቻችን በምርጫ ቦርድ ግፊት ከእስር ቢለቀቁም ከመለቀቃቸው በፊት የተፈፀሙ ሕግን የጣሱ ተግባራት ግን በጣም አሳፋሪ መሆናቸውን እየገለፅን ከሕግ አግባብ ውጪ በእስር ላይ የሚገኙ አባላቶቻችን በአስቸኳይ ከእስር እንዲፈቱ እንጠይቃለን። በተጨማሪም በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች እና ክልሎች አባሎቻችን እና እጩ ተወዳዳሪዎቻችንን ከደሞዝና ጥቅማጥቅም የማገድ (ለምሳሌ በከፋ ዞን፤ በጋርዱላ ዞን )፤ ከህግ አግባብ ውጪ ለብልፅግና መዋጮ በሚል ከደሞዛቸው መቁረጥ (ለምሳሌ በሲዳማ ክልል ካሉ መምህራን አባሎቻችን ላይ) በተለያዩ የሀገሪቱ ክልሎች ላይ በመራጮች፤ በአባሎቻችን እና በደጋፊዎቻችን ላይ የሚፈፀሙ ዛቻና ማስፈራራቶች የምርጫውን ተዓማኒነት እና ዴሞክራሲያዊነት እየፈተኑ ያሉ ተግባሮች በመሆናቸው ተገቢው ትኩረት ተሰጥቷቸው ሊፈቱ ይገባል። መንግስት በየሚዲያው በሚያደርገው ዲስኩር የሚገልፀውን ምርጫውን ዴሞክራሲያዊ ማድረግ በተግባር እንዲያረጋግጥ እና በየደረጃው የሚገኙ ካድሬዎቹን ሀይ እንዲል እናሳስባለን። የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ምንም እንኳን የቦርዱ አመራሮች ለምናቀርባቸው ጥያቄዎች ምላሽ በመስጠት ከህግ ውጪ የታሰሩ ዕጩዎች እንዲለቀቁ ማድረጋቸው የሚደነቅ ቢሆንም፣ የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ከመፃፍ ባለፈ በመንግስት በኩል የማያዳግም እና ቆንጣጭ እርምጃዎች እንዲወሰዱ በማድረግ በህገወጥ ተግባር የሚሳተፉ የመንግስት ሹመኞች ተጠያቂነትን እንዲያረጋግጥ እንጠይቃለን። የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ ግንቦት 07/2018 ዓ.ም. #ኢዜማ #ኢትዮጵያ #ምርጫ_2018

የመርኃግብር ማስታወሻ!! የበይነ መረብ ውይይት 2018 ሀገራዊ ምርጫ እና የኢዜማ እንቅስቃሴ #ኢዜማ #ኢትዮጵያ #ምርጫ_2018
የመርኃግብር ማስታወሻ!! የበይነ መረብ ውይይት 2018 ሀገራዊ ምርጫ እና የኢዜማ እንቅስቃሴ #ኢዜማ #ኢትዮጵያ #ምርጫ_2018

ከአፍታ ቆይታ በኋላ‼ በሕገመንግሥት እና ፌደራሊዝም ላይ የተደረገውን የምርጫ ክርክር ይከታተሉ!! ኢዜማ በፓርቲው የድርጅት ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ብሥራት ጌታቸው እና የቀድሞው ም/መሪ ዮሐንስ መኮንን
ከአፍታ ቆይታ በኋላ‼ በሕገመንግሥት እና ፌደራሊዝም ላይ የተደረገውን የምርጫ ክርክር ይከታተሉ!! ኢዜማ በፓርቲው የድርጅት ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ብሥራት ጌታቸው እና የቀድሞው ም/መሪ ዮሐንስ መኮንን ተወክሎ ሙግቱን አቅርቧል። #ኢዜማ #ኢትዮጵያ #ምርጫ_2018

ኢዜማ ወጣቱ ለዕውቀት ያለውን ጉጉት በመጠቀም የተሻለውን አማራጭ አሳይቶ ይሁንታን ማግኘት እንጂ በስሜት ገፍቶ ሕይወቱን እንዲገብር ፍላጎት የለውም፤ አዲስ የፖለቲካ ባሕል ለመገንባት ኢዜማን ይምረጡ!
ኢዜማ ወጣቱ ለዕውቀት ያለውን ጉጉት በመጠቀም የተሻለውን አማራጭ አሳይቶ ይሁንታን ማግኘት እንጂ በስሜት ገፍቶ ሕይወቱን እንዲገብር ፍላጎት የለውም፤ አዲስ የፖለቲካ ባሕል ለመገንባት ኢዜማን ይምረጡ!! #ኢዜማ #ኢትዮጵያ #ምርጫ_2018

እንደመብት የሚሠጡ መንግሥታዊ አገልግሎቶችን ሕዝብን ማስፈራሪያ እና የምርጫ መጠቀሚያ ከማድረግ ይልቅ ተጠያቂነት ያለበት መንግሥት እንመሠርታለን!! ኢዜማን ይምረጡ!! ሚዛንን ይምረጡ!! #ኢዜማ #ኢት
እንደመብት የሚሠጡ መንግሥታዊ አገልግሎቶችን ሕዝብን ማስፈራሪያ እና የምርጫ መጠቀሚያ ከማድረግ ይልቅ ተጠያቂነት ያለበት መንግሥት እንመሠርታለን!! ኢዜማን ይምረጡ!! ሚዛንን ይምረጡ!! #ኢዜማ #ኢትዮጵያ #ምርጫ_2018

የመንግሥት ተቋማት ዜጎች በስጋት የሚሔዱባቸው ሳይሆን ለኑሯቸው አመቺነት የሚያስፈልጋቸውን አገልግሎት አግኝተው የሚመለሱበት ተቋማት እናደርጋቸዋለን!! ኢዜማን ይምረጡ!! ሚዛንን ይምረጡ!! #ኢዜማ #
የመንግሥት ተቋማት ዜጎች በስጋት የሚሔዱባቸው ሳይሆን ለኑሯቸው አመቺነት የሚያስፈልጋቸውን አገልግሎት አግኝተው የሚመለሱበት ተቋማት እናደርጋቸዋለን!! ኢዜማን ይምረጡ!! ሚዛንን ይምረጡ!! #ኢዜማ #ኢትዮጵያ #ምርጫ_2018