1 479
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
Немає даних30 днів
Архів дописів
Repost from Amhara Education Bureau
አሁን ያለውን የትምህርት ስርዓት መቀየር ካልቻልን በቀጣዩ አለም ተወዳዳሪ ሀገርና ትውልድ መፍጠር አንችልም¬- ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ
ትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ቤቶችን መሰረተ ልማት ማሻሻል ላይ ያተኮር ህዝባዊ ንቅናቄ ለማካሄድ ያለመ የማስጀመሪያ ሀገር አቀፍ መድረክ ዛሬ አካሂዷል፡፡
..................................................//.............................
ሰኔ 25/2015 ዓ.ም (የትምህርት ሚኒስቴር) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በሁሉም ዜጎችና ተቋማት ተሳትፎ የትምህርት ቤቶችን መሰረተ ልማት ለማሻሻል“ትምህርት ለትውልድ” በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀውን ሀገር አቀፍ ህዝባዊ ንቅናቄን አስጀምረዋል፡፡
ዛሬ የተገናኘነው ትናንት ያሰተማረን ማህብረሰብ እዳ ስላለብን ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒሰትሩ በየትኛውም የኢትዮጵያ ጫፍ የተማራችሁ ሁሉ የተማራችሁባቸው ትምህርት ቤቶች ዛሬ የናንተን ድጋፍ ይሻሉ ብልዋል፡፡
12ኛ ክፍል ሲደርሱ ተማሪዎችን ሰብስቦ መፈተን ብቻ ሳይሆን ከታች መሰረቱ ላይ መስራት ይጠበቃል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ አሁን ያለውን የትምህርት ቤት ሁኔታ ለመቀየር በገንዘብ፣ በጉልበት እንዲሁም በዕውቀት ተባብረን የላቀች ኢትዮጵያን ለመገንባት፤ ቀድመን የላቁ ትምህርት ቤቶችን አብረን እንገንባ!ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በበኩላቸው በተለያየ ጊዜ ትምህርትን ተደራሽ ለማድረግ የተሄደው ርቀት ጥራትን ከማረጋገጥ አንጻር የራሱ አሉታዊ ተጽዕኖ ነበረው ብለዋል፡፡
ለተማሪዎች ትምህርት መቀበል ዋናው ነገር የትምህርት መሰረተ ልማት ቢሆንም አሁን ካሉት ትምህርት ቤቶች ውስጥ 86 ከመቶ የሚሆኑት ከደረጃ በታች ናቸው ብለዋል፡፡
በመሆኑም እነዚህን ትምህርት ቤቶች በመንግስት አቅም ብቻ መገንባት የማይቻል በመሆኑ ሁሉንም ገንዘቡ፣ እውቀቱ እና ጉልበቱ ያላቸውን ማሳተፍ በማስፈለጉ ይህ ንቅናቄ ማስጀመሪያ መድረክ ተዘጋጅቷል ብለዋል፡፡
ትምህርት ቤቶች ላይ ያለውን ችግር ለነገ ልንተወው የሚገባ ባለመሆኑ ፊት ለፊት ልንጋፈጠው ይገባል ያሉት የትምህርት ሚኒስትሩ ይህ የትውልድና የሀገር ጥሪ መሆኑን አውቃችሁ ልትደግፉ ይገባል በማለት ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ኢትዮጵያውን ከተባበርን የማናስተካክለው ነገር የለም በዚህም በሚመጡት አምስት ዓመታት የኢትዮጵያን ትምህርት ቤቶች ችግር ሙሉ በሙሉ እንፈታለንም ብለዋል፡፡
በትምህርት ቤቶቹ ከሚስተዋሉ የመሰረተ ልማት ችግሮች መካከልም የመማሪያ ክፍል ፣ የንጹህ መጠጥ ውኃ አገልግሎት፣ የመጸዳጃ ቤት፣ ኤሌክትሪክ እንዲሁም የትምህርት ግብዓት እጥረት በዋናነት ይጠቀሳሉም ተብሏል፡፡
ይህ የትምህርት ቤቶችን መሰረተ ልማት ማሻሻል ህዝባዊ ንቅናቄ በቀጣይም በየደረጃው በሁሉም ክልሎች በተዋረድ እንደሚካሄድ በመደረኩ ተገልጿል፡፡
በመድረኩም የሁሉም ክልል ርዕሰ መስተዳድሮች፣ ሚኒስትሮች፣ ታዋቂ ግለሰቦችና ባለሀብቶች፣አጋር ድርጅቶች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡
Repost from Bright Minds Academy☀️
ለማስታወስ...
ሀገር አቀፍ ፈተናዎች እየተቃረበ ነው። ታዲያ በዚህ ወቅት ተማሪዎችን እጅግ የሚያስጨንቁ ጉዳዮች እንዴት አድርገን ለፈተናው እናጥና? ያጠናነውንስ ላለመርሳት ምን ማድረግ አለብን የሚሉት ጥያቄዎች ናቸው።
ከዋናው ጥናት በኋላ ፈተናው ሲቀርብ የክለሳ ዝግጅት ማድረግ የተለመደ ነው። ነገር ግን ከየት ነው የሚጀመረው? ቢቢሲ የትምህርት ባለሙያዎችን፣ የዩኒቨርሲቲ መምህራንን፣ የሥነ ምግብ ተመራማሪዎች፣ ውጤታማ ተማሪዎችን እንዲሁም የሥነ አእምሮ ባለሙያዎችን አነጋግሮ ይጠቅማሉ ያላቸውን 12 ነጥቦች አዘጋጅቶላችኋል።
በእነዚህ ምክሮች መሠረት የማስታወስ ችሎታችሁንና የትኩረት አቅማችሁን ታዳብራላችሁ።
1. ቁርስና ጠቃሚ ምግቦች ( እዚች ላይ sciencun ለመናገር ያህል ነዉ እንጂ በዚህ ሰዓት ለማሟላት ከበድ ሊል ስለሚችል በቻላችሁት መጠን የምታገኙትን ምግብ ሁሉ በደንብ ተመገቡ የምትለዋን point ያዙልኝ 😊)
ሰውነታችን በአግባቡ ሥራውን እንዲሰራ ኃይል ያስፈልገዋል፤ አንጎላችን ደግሞ ትኩረት እንዲኖረውና የማስተዋል አቅማችን እንዲጨምር በቂ የሆነና ያልተቆራረጠ የኃይል አቅርቦት ይፈልጋል።
ጥናቶች እንደሚያሳዩት ቁርሳቸውን ተመግበው ወደፈተና የሚገቡ ተማሪዎች የተሻለ ውጤት ያስመዘግባሉ። የተመጣጠነ ምግብ ተመግበው ለፈተና የሚቀርቡት ደግሞ የበለጠ የማስታወስና የማስተዋል አቅም ይኖራቸዋል።
ስለዚህ ሁሌም ቢሆን ፈተና ያለባቸው ተማሪዎች እንደ የገብስ ገንፎ፣ ዳቦ፣ ሩዝና ድንች ያሉ በካርቦሃይድሬት የበለጸጉ ምግቦችን በቁርስ ሰዓት ተመግበው ቢወጡ ይመከራል።
እርጎ፣ እንቁላል፣ አሳ፣ ጎመን፣ ቲማቲምና አቮካዶ ዓይነት ምግቦችም እጅጉን ጠቃሚ ናቸው።
2. በጠዋት ወደ ጥናት መግባት
ሁሌም ቢሆን ነገሮችን አስቀድሞ መጀመርን የመሰለ ነገር የለም። ለፈተናም ቢሆን ጥናት በጠዋት ተነስቶ መጀመር በፈተና ወቅት የተረጋጋ መንፈስ እንዲኖረን ይረዳል።
ጠዋት ላይ ጭንቅላታችን እረፍት አድርጎ በአዲስ መንፈስ ሁሉንም ነገር ስለሚጀምር፤ በዚህ ሰዓት ማጥናት ውጤታማ ያደርጋል። በተለይ ደግሞ የክለሳ ጥናቶችን ለከሰዓት ማሸጋገር ተገቢ አይደለም።
ጠዋት ጥናት የምንጀምርበትና የምናበቃበት ሰዓት ከፈተናው በፊት ባሉት ሁለት ወይም ሦስት ሳምንታት ውስጥ ተመሳሳይ ለማድረግ መሞከርም ውጤታማ ያደርጋል።
3. ምን ላይ ትኩረት ማድረግ እንዳለባችሁ ወስኑ
በመጀመሪያ ፈተናው የጽሁፍ ነው ወይስ የተግባር? ወይስ ቃለመጠይቅ ነው የሚለውን መለየት ወሳኝ ነው።
ሁሉም ዓይነት ፈተናዎች የራሳቸው የሆነ የተለያየ አይነት አቀራረብ አላቸው። በምሳሌ አስደግፎ ማብራሪያ መስጠት የሚጠይቅ ዓይነት ፈተና ከሆነ ከዚህ በፊት የተሠሩ ፈተናዎችን እያመሳከሩ ጥቂት ቦታዎች ላይ በትኩረት መዘጋጀት።
ምናልባት ፈተናው ምርጫ አልያም አጭር መልስ የሚፈልግ ዓይነት ከሆነ ቀለል ያለና አጠቃላይ መረጃዎችን ለመያዝ መሞከር።
4. እቅድ ማዘጋጀት
ምናልባት ነገሮችን ቦታ ቦታ ለማስያዝና እቅድ ለማውጣት የምናጠፋው ጊዜ የባከነ መስሎ ሊሰማን ይችላል። ነገር ግን እውነታው በተቃራኒው ነው። ምክንያቱም ምን ማጥናት እንዳለባችሁና መቼ ማጥናት እንዳለባችሁ እቅዳችሁ ይነግራችኋል።
ከዚህ በተጨማሪም ምን ያክል እንደተጓዛችሁ ለመመዝገብና ለመከታተል ይረዳል።
የትኞቹን ማስታወሻ ደብተሮች መቼ መመልከት እንዳለባችሁ፣ የትኞቹን መጻህፍት ለተጨማሪ ማብራሪያ እንደምትጠቀሙ እንዲሁም የፈተና ጥያቄዎችን መቼ መለማመድ እንዳለባችሁ በእቅድ ውስጥ ማስገባት ውጤታማ ያደርጋል።
እዚህ ጋር መርሳት የሌለብን ለእረፍትና አካላዊ እንቅስቃሴም ቦታ መስጠት እንዳለብን ነው።
5. ከፋፍሎ ማጥናት
የክለሳ ጥናትን ከፋፍሎ ማካሄድን የመሰለ ነገር የለም። አንድ የትምህርት ዓይነት ላይ 10 ሰዓት ሙሉ ከማሳለፍ በየቀኑ አንድ ሰዓት በማጥናት በ10 ቀን መጨረስ ይበልጥ ውጤታማ ያደርጋል።
ያጠናነውን ነገር ለማስታወስና በቀላሉ ለመሸምደድ ጭንቅላታችን ጊዜ ይፈልጋል። ከፋፍሎ ማጥናት ደግሞ ለዚህ ፍቱን መድሃኒት ነው። ከፋፍሎ ማጥናት እጅግ ውጤታማው መንገድ እንደሆነም በመላው ዓለም የተሰሩ የተለያዩ ጥናቶች ያለመክታሉ።
6. ራሳችሁን ቶሎ ቶሎ ፈትኑ
የሥነ አዕምሮ ጥናት ባለሙያዎች እንደሚሉት የማስታወስ ችሎታን ለማዳበርና በራስ መተማመናችንን ለመጨመር ራስን መፈተን ውጤታማ ያደርጋል።
ከዚህ በተጨማሪ እየተዘጋጀንበት ያለነውን ጉዳይ በደንብ እንድናውቀው ከማድረጉ በተጨማሪ የረሳናቸው አልያም የዘለልናቸው ርዕሶችን ለመለየት ይረዳናል።
7. መምህር መሆን
ከባዱን የክለሳና ራሳችሁን የመፈተን ሥራውን ካከናወናችሁ በኋላ ጓደኞቻችሁን ሰብሰብ አድርጋችሁ በጭንቅላታችሁ የሚመጣውን ነገር በሙሉ ንገሯቸው። ራሳችሁን በመምህር ቦታ አድርጋችሁ እውቀታችሁን ለማካፈል ሞክሩ።
ምን ያህል እንደምታስታውሱ ለማወቅ ከመርዳቱ በተጨማሪ ጓደኞቻችሁንም ትጠቅሟቸዋላችሁ።
8. ከተንቀሳቃሽ ስልካችሁ ራቅ በሉ
ስልኮች በጣም ብዙ ጥቅም አላቸው። ነገር ግን በጥናት ወቅት ከጥቅማቸው ይልቅ ጉዳታቸው ነው የሚያመዝነው። በተለይ ደግሞ ማህበራዊ ሚዲያዎችን የምትጠቀሙ ከሆነ።
ብዙ ጥናቶች እንዳረጋገጡት ብዙ ጊዜያቸውን ስልካቸው ላይ የሚያሳልፉ ተማሪዎች የትምህርት ውጤታቸው ሁሌም ቢሆን ዝቅ ያለ ነው።
ብትችሉ ስልካችሁን አጠገባችሁ እንኳን አታድርጉት።
9. ሙዚቃ መቀነስና በጸጥታ ማንበብ
በጸጥታ ውስጥ ሆነው ጥናታቸውን የሚያከናወኑ ተማሪዎች ሙዚቃ እየሰሙ ከሚያጠኑት ጋር ሲወዳደሩ በእጅጉ የተሻለ የማስታወስና የትኩረት አቅም እንዳለቸው ማረጋገጥ ተችሏል።
10. ቋሚ እረፍትና አካላዊ እንቅስቃሴ
ውጤታማ የክለሳ ጥናት ማለት እረፍት አልባ ጥናት ማለት አይደለም። በጥናታችን መሀል መሀል ላይ ጥሩ አየር ለማግኘትና ሰውነታችንን ለማፍታታት ወጣ ብሎ እንቅስቃሴ ማድረግ የማስታወስ ችሎታችንን በደንብ ከፍ ያደርገዋል።
ከዚህ በተጨማሪ ሰውነታችን እና ጭንቅላታችን በእጅጉ የተሳሰሩ በመሆናቸው እንቅስቃሴ ስናደርግ የደም ዝውውራችን ይስተካከላል፤ ይህ ደግሞ በቂ ኦክስጅን ወደ ጭንቅላታችን እንዲሄድ ይረዳል።
አካላዊ እንቅስቃሴ ማድረግ ተዘርዝሮ የማያልቅ ጥቅሞች ያሉት ሲሆን ጭንቀትን መከላከልና በራስ መተማመንን መጨመር ከነዚህ መካከል ይጠቀሳሉ።
11. እንቅልፍ
ከፈተና በፊት ያለችውን ምሽት ጥሩ እንቅልፍ አግኝቶ ማሳለፍ ተገቢ እንደሆነ ብዙዎች ይስማማሉ። ነገር ግን ጥሩ እንቅልፍ ፈተናው ሲቃረብ ብቻ ሳይሆን ከሳምንታት በፊት ገና ዋናው ጥናት ሲደረግና ክለሳ በሚደረግበት ወቅትም እጅግ ወሳኝ ነው።
በጠዋት ተነስቶ ውጤታማ የክለሳ ጥናት ካደረጉ በኋላ በጊዜ ተኝቶ ጥሩ እንቅልፍ ማግኘት ሰውነታችንና ጭንቅላታችን በደንብ ተግባብተው እንዲሰሩ ይረዳቸዋል። ሌሊቱን በሙሉ ለማጥናት ሙከራ አታድርጉ ይላሉ የዘርፉ ባለሙያዎች። ምክንያቱም ራሳችን ላይ ጫና እያሳደርን ስለሆነ።
12. መረጋጋትና በጎ በጎውን ማሰብ
እስካሁን የተዘረዘሩትን ነገሮች ሁሉ ተግባራዊ ካደረጋችሁ ምንም የሚያሳስባችሁ ነገር ሊኖር አይገባም። ዘና ብላችሁ ወደ ፈተና መግባት ብቻ ነው የሚቀራችሁ። ምናልባት ጥሩ ያልሆነ አጋጣሚ ቢገጥማችሁ እንኳን እሱን ረስታችሁ ለቀጣዩ በጥሩ መንፈስ ለመዘጋጀት ሞክሩ።
በመጨረሻም በእያንዳንዱ ጥሩ የፈተና ጊዜ ለራሳችሁ ሽልማት መስጠት አትርሱ።
@Ethio_Students_only
@Ethio_Students_only
@Elshio_Academy
የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል የክፍልና ሞዴል ፈተና ውጤት ትንተና ቅጽ የላክን ሲሆን በቅጹ መሰረት በጥንቃቄ ተሞልቶ በተቀመጠው ጊዜ ገደብ እንዲላክልን እንጠይቃለን::
መረጃው ተጠቃሎ ለመምሪያ የሚላከው በጉድኝት ማዕከሉ በኩል ሲሆን በተናጥል የሚመጣ መረጃ የማንቀበል መሆኑን እንገልጻለን::
የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል የክፍልና ሞዴል ፈተና ውጤት ትንተና ቅጽ የላክን ሲሆን በቅጹ መሰረት በጥንቃቄ ተሞልቶ በተቀመጠው ጊዜ ገደብ እንዲላክልን እንጠይቃለን::
መረጃው ተጠቃሎ ለመምሪያ የሚላከው በጉድኝት ማዕከሉ በኩል ሲሆን በተናጥል የሚመጣ መረጃ የማንቀበል መሆኑን እንገልጻለን::
የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል የክፍልና ሞዴል ፈተና ውጤት ትንተና ቅጽ የላክን ሲሆን በቅጹ መሰረት በጥንቃቄ ተሞልቶ በተቀመጠው ጊዜ ገደብ እንዲላክልን እንጠይቃለን::
መረጃው ተጠቃሎ ለመምሪያ የሚላከው በጉድኝት ማዕከሉ በኩል ሲሆን በተናጥል የሚመጣ መረጃ የማንቀበል መሆኑን እንገልጻለን::
💚💛❤️
ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ እንኳን አደረሳችሁ እያልን የሞዴል ፈተናል ከ28_30/10/2015ዓ.ም ጀምሰሮ ይሰጣል። ስለሆነም:-
ሁሉም ተማሪ ዩኒፎርም መልበስ አለበት::
መታወቂያ እንዳይለያችሁ።💚💛❤️
ት/ቤቱ
Repost from Ethiopian Education//የኢትዮጵያ ትምህርት
በትምህርት ቤቶች ማሻሻያ ንቅናቄ ከ50 ሺህ በላይ ት/ ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል ይሰራል - ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር)
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 22፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል የት/ቤቶች መሰረተ ልማት የማሻሻል ሕዝባዊ ንቅናቄ የፊታችን እሑድ በይፋ እንደሚጀመር ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
የትምህርት ሚኒስቴር በመላው ሀገሪቱ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል የሚደረገውን የንቅናቄ መርሐ-ግብር አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዚሁ ወቅት÷ የትምህርት ስርዓቱን ለማሻሻል በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።
በንቅናቄው ከ50 ሺህ በላይ ትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል መታቀዱ ነው ሚኒስትሩ የተናገሩት፡፡
ሀገር አቀፍ ንቅናቄው የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ የሚሰሩ ስራዎችን የሚያግዝ መሆኑንም አስረድተዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ ያሉ ትምህርተ ቤቶች ከደረጃ በታች መሆናቸውን የገለጹት ሚኒስትሩ÷ በሚቀጥሉት አምሰት ዓመታት የትምህርት ቤቶቹን ደረጃ የማሻሻል እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡
https://t.me/mnistryofeducation
https://t.me/mnistryofeducation
22/10/2015ዓ ም
በዛሬው እለት አድሚሽን ካርድ የወሰዳችሁ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በካርዱ ላይ ያሉ መረጃዎች ስህተት ያለባቸው ከሆነ በአሰቸኳይ እስከ 23/10/2015ዓ.ም ድረስ ር/መምህር ቢሮ ሪ ፖርት እንድታደርጉ እያሳሰብን ከተገለፀው ቀን ውጪ ት/ቤቱ ኃላፌነት የማይወስድ መሆኑን እንገልፃለን።
Repost from Tana haik secondary school
ቀን15/10/2015ዓ.ም
ማስታወቂያ
ለ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናል ለምትወስዱ ተማሪወች በሙሉ
አድሚሽን ካርድ ስለመጣ ሁሉም ተማሪዎች በ22/10/2015ዓ.ምከጧቱ3:00 ሰዓት ት/ቤቱ መሰብሰቢያ አዳራሽ ድረስ በመገኘት እንድትወስዱ እናሳስባለን::
ት/ቤቱ
ማሳሰቢያ
የሌላ ሰው ካርድ መውሰድ አይቻልም::
ሠላም የትም/መምሪያ ሃላፊዎች!
የሚከተለው መልዕክት ከሃገር አቀፍ ፈተናዎች አገልግሎት የተላለፈ መልዕክት ነው። ስለሆነም በተቀመጠው አግባብ ስለመፈፀሙ ጥብቅ ክትትል እንድታደርጉ እያሳሰብን መልዕክቱም:-
ሁሉም ዞኖች የ2015 ዓ.ም ተፈታኞች አዲሚሽን ካርድ በተያዘው ጊዜ በመውሰዳቸው እናመሰግናለን፡፡ ከአዲሚሽን ካርድ ጋር በተያያዘ የሚቀርቡ ቅሬታዎች በተለይም የፎቶ(no photo)፣ የጾታ(sex)፣ የእይታ(blind)፣ የትምህርት(stream) መስክ ችግሮች አስከ ሰኔ 25/2015 ዓ.ም ድረስ ብቻ እንዲቀርብልን እያሳሰብን ከተጠቀሰው የጊዜ ገደብ ውጪ የሚቀርቡ ቅሬታዎችን የማናስተናግድ መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን፡፡ በተለይም የእይታ፣የጾታ፣የትምህርት መስክና ችግር ያለባቸው ተፈታኞች ተጣርቶ የማይደርሰን ከሆና በፈተና አሰጣጡ ላይ ችግር የሚገጥማቸው በመሆኑ ከወዲሁ እንዲሰርሰን ለማሰሳብ እንወዳለን፡፡
ለሁሉም የትምህርት/ ሱፐርቫይዘሮች ተቋማት
ሀ. የ2015 ዓ.ም የጂኢኩፕ በጀት ያወራረዱ የትምህርት ተቋማት መረጃ ተለይቶ በዝርዝር እስከ 20/10/2015 ዓ.ም እንዲላክልን
ለ. የትምህርት ቤቶች የመሰረተ ልማት መረጃ በትምህርት ቤት ደረጃ ተሞልቶ በተላከዉ መሰርት መረጃዉ በፊደራል ደረጃ በተዘጋጀዉ ዳታ ቤዝ የሁሉም የመንግስት የትምህርት ተቋማት እንዲገባ ተገድጓል፡፡ በቀጣይ የትምህርት ቤቶችን ችግር ሊፈታ የሚችል የሃብት አሰባሳቢ ኮሚቴ በየደረጃዉ በማቋቋም የሚከናወኑ ተግባራት ማስፈጸሚያ ሰነድ የአብክመ ትም/ቢሮ ልኳል፡፡
ስለሆነም በትምህርት ቤት ደረጃ የኮሚቴው ስያሜ የትምህርት ቤት መሰረተ ልማት መሻሻል ኮሚቴ ተብሎ የሚቋቋም ሲሆን የአባላት ስብጥሩም
1. የወላጅ፣ ተማሪ፣ መምህር ህብረት ሰብሳቢ
2. የትምህርት ቤቱ ር/መምህር ም/ሰብሳቢ
3. የትምህርት ቤት መሻሻል ኮሚቴ ሰብሳቢ አባል እና ፀሐፊ
4. የትምህርት ቤቱ ም/ር/መምህር አባል
5. የመሰረታዊ የመምህራን ማህበር ሊቀመንበር አባል
6. የተማሪዎች ተወካይ አባል
7. የበጎ ፈቃድ ክበብ የሚወከል አባል
8. እንደአስፈላጊነቱ ሌሎች አባላትን በመጨመር እንዲደራጅ እና ተግባርና ኃላፊነቱን አብክመ ትም/ቢሮ ያዘጋጀዉን ሰነድ መሰረት በማድረግ እንዲገለጽ እንዲሁም የአባላቱ ፎቶግራፍ እንዲዘጋጀልን
መ. የትምህርት ቤት የግለ ግምገማ መረጃ በተላከዉ ቅጽ መሰረት ተሞልቶ እንዲላክልን በጥብቅ እናሳስባለን፡፡
