uk
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Відкрити в Telegram

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Канал የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 14 309 підписників, посідаючи 6 167 місце в категорії Релігія і духовність та 2 365 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 14 309 підписників.

За останніми даними від 21 червня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 502, а за останні 24 години на 16, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 48.88%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 13.10% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 0 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 1 875 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 0.

📝 Опис та контентна політика

Опис каналу не надано.

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 22 червня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Релігія і духовність.

14 309
Підписники
+1624 години
+1117 днів
+50230 день
Архів дописів
14ኛው ዓለም አቀፍ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን በምሥራቅ ሸዋ ሀ/ስብከት በአዳማ ከተማ በድምቀት ተከበረ። የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ሰኔ 2/2017 ዓ.ም በዕለቱ የአዳማ ከተማ አጥቢያ ሰ/ት/ቤት አ
+4
14ኛው ዓለም አቀፍ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን በምሥራቅ ሸዋ ሀ/ስብከት በአዳማ  ከተማ በድምቀት ተከበረ። የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ሰኔ 2/2017 ዓ.ም በዕለቱ  የአዳማ ከተማ አጥቢያ ሰ/ት/ቤት አባላት፣ ሰባኪያን፣ የሀ/ስብከቱ ተወካይ የተገኙ ሲሆን፥ የሰት/ቤትን የሚዘክሩ እና የወደፊቱን አገልግሎት የሚያጠናክሩ : መርሐ ግብራት ተከናውነዋል። መረጃው የ/ስብከቱ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ነው። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

በዓለ ጰራቅሊጦስ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን በደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት በደሴ ከተማ ተከናወነ። ሰኔ 2 /2017ዓ.ም የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በደሴ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጉባ
+9
በዓለ ጰራቅሊጦስ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን በደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት በደሴ ከተማ ተከናወነ። ሰኔ 2 /2017ዓ.ም የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በደሴ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጉባኤ 14ኛውን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን ምክንያት በማድረግ "ዝማሬ-ጰራቅሊጦስ" የተሰኘ ከግንቦት 30- ከሰኔ 1 የቆየ የኹለት ቀን የዝማሬና የትምህርተ ወንጌል መርሐ ግብር ተከናወነ። በመርሐ ግብሩ ጉባኤው  ብጹዕ አቡነ መቃርዮስ የምዕራብ ካናዳ ሃገረስብከት ሊቀ-ጳጳስ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን የደ/ወሎ ሀገረ ስብከት የልዩ ልዩ መምሪያ ሓላፊዎች የወረዳ ቤተ ክህነት የሥራ ሓላፊዎች የሰ/ት/ቤት አባላት  በርካታ የከተማው ሕዝበ ክርስቲያን በተገኙበት ተከናውኗል። በመርሐ ግብሩ ላይ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ትውልድን በመቅረጽ እየሠሩት ያለውን ዘርፈ ብዙ ሥራ በመላው አድባራትና ገዳማት እየተተገበረ ስላለው ሥርዓተ ትምህርት ዙርያ ለምዕመናን ገለጻ የተደረገላቸው ተደርጎላቸዋል። አያይዞም በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ቃለ እግዚአብሔር እና ከደሴ ከተማ ሰንበት ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ መዘምራን ዕለቱን የተመለከቱ ዝማሬዎችን አቅርበዋል። ዕለቱ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን እንደመሆኑ ይህ መርሐ ግብር በየዓመቱ እንደሚከናወን የከተማው የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ገልጧል። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

ሊቀ ጳጳስ የምስካየ ኅዙናን መድኃኔዓለም ገዳም የበላይ ሓላፊ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ በ14ኛው ዓለም አቀፍ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ያስተላለፉት መልእክት በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ። አሜን እንኳን ለ14ኛው ዓለም አቀፍ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ እና የሰንበት ት/ቤቶች ቀን አደረሳችሁ "ተዘከሮ ለፈጣሪከ በመዋዕለ ውርዙትከ ዘእንበለ ይመጻእ መዋዕል እኩይ ወይመጽእ ዓመታተ በእለ ትብል ኢኮነኒ ቦቶን ፈቃድየ፦ የጭንቀት ቀን ሳይመጣ በጕብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስብ ደስ አያሰኙም የምትላቸውም ዓመታት ሳይደርሱ።” መክ 12፥1 ጠቢቡ ሰሎሞን ጭንቅ ቀን የመከራ ቀን ሳይመጣ የጉብዝና ወራት በተባለ የወጣትነት ዘመንን ለእግዚአብሔር መስጠት እንዲሚያስፈልግ ያስተምራል፡፡ ይህንንም መሠረት በማድረግ ቤተ ክርስቲያን የጉብዝናን ዘመን በቤተ ክርስቲያን በሰንበት ት/ቤት እንዲሆን ታስተምራለች። ሰንበት ትምህርት ቤት በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ከፍተኛ ሥፍራ ካላቸው ተቋማት አንዱ ነው። ዘመን ተሻጋሪዋ ቤተ ክርስቲያናችን ቀድማ የነገዋ ቤተ ክርስቲያን ተረካቢ ትውልድን ስብስባ፣ ታላላቅ ሥራዎችን የምትሠራበት፣ ትውልዱን በማስተዋል በእውቀት በሃይማኖት በሥነ ምግባር በልዩ ልዩ ጸጋ የምትቀርጽበት የተወደደ ሥፍራ ሰንበት ት/ቤት ነው፡፡ ከሰንበት ትምህርት ቤት ብዙ ሊቃውንት፣ ብዙ መሪዎች፣ ብዙ መምህራን፣ ብዙ አገልጋዮች፣ ብዙ ባለሙያዎች እና ጠንካራ አማኞች ተገኝተዋል። ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ልጆቿ ጽድቅን ይማሩ ዘንድ በሰንበት ት/ቤት አሰባስባ እግዚአብሔርን አውቀው እንዲያመልኩ፣ ሕጉን ጠብቀው፣ በሃይማኖት፣ በምግባርና በትሩፋት ጸንተው አምላካቸውን መስለው እንዲኖሩ፣ የእርሱ የሆነችውን መንግሥተ እግዚአብሔርን እንዲወርሱ በብሉይ ከአምላኳ የተቀበለችውን ሕግጋተ እግዚአብሔርን አስተምራ በሐዲስ ኪዳንም በ40ና በ80 ቀን እያጠመቀች ለምዕመናን እንደ እድሜያቸው ቃለ እግዚአብሔርን በስብከት፣ በዝማሬ፣ በቅዳሴ፣ በሰዓታት፣ በማሕሌት፣ በቅኔ፣ በትርጓሜው እያስተማረች ምዕመናንን በሃይማኖት አንፃ ለመንግሥተ ሰማያት እያዘጋጀች ዛሬ ላይ ደርሳለች። ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እና የዚህ ጉባኤ ታዳሚዎች ሰንበት ት/ቤት ሕጻናት ወጣቶች የቤተ ክርስቲያንን ዶግማ፣ ቅኖና፣ ሥርዓትና ትውፊት የሚማሩበት እና በእምነት፣ በምግባርና በሃይማኖት ጸንተው ይኖሩ ዘንድ መንፈሳዊ ሕይወታቸውን የሚያጠነክሩበት ታላቅ መንፈሳዊ ትምህርት ቤት ነው:: በመጽሐፍ ቅዱስ ሰንበት ት/ቤት ተብሎ የተፃፈ ቀጥተኛ የሆነ ስም ባይገኝም ዛሬ ላይ በሰንበት ት/ቤት የሚተገበረው መንፈሳዊ አገልግሎት ማለትም ልጆችን በቤተ እግዚአብሔር ማስተማር በብሉይ ኪዳን ዘመንም ይፈጸም እንደነበር መጽሐፍ ቅዱስ ያስረዳናል። የሰንበት ት/ቤት ፅንሰ ሀሳብም ከዚያ የመነጨ ነው። ኦሪት ዘዳግም 11÷18-21 በሐዲስ ኪዳንም መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመዋዕለ ሥጋዌ ልዩ ትኩረት ከሰጣቸው መካከል ሕፃናት (ወጣቶች) ወደ ቤተ ክርስቲያን ይመጡ ዘንድ ነበር። በዚህም ለሰንበት ትምህርት ቤት መነሻ የሆነ እና መሠረቱም መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሆኑን ያረጋግጥልናል። (ማቴ 18፥3፣ 21፥16፣ ማር 9፥37)። በዚህ መነሻነት ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮዎቿ _ ሳይበረዙ _ ለትውልድ እንዲተላለፉ በተለይ በሕጻናት እና በወጣቶች ላይ ትኩረት ተሰጥቶ ለመሥራት ተሞክሯል። ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እና የዚህ ጉባኤ ታዳሚዎች ይህ የቤተ ክርስቲያን ዋና ተልዕኮ ቅድሚያ የሚሰጠው ሐዋርያዊ ተግባር ሆኖ ሳለ እነዚህን የነገዋ ቤተ ክርስቲያን ተረካቢ የሰንበት ት/ቤት ልጆቻችንን በአግባቡ ባለመመልከታችን፣ እንደ አባት ለልጅ የሚደረገውን ባለማድረጋችን፣ የሚገባውን ሥፍራ ሰጥተን ባለመሥራታችን ምክንያት ከበረቱ የተበተኑ፣ ከቤቱ የራቁ፣ ከአገልግሎት የጠፉ፣ ጀመረው ያልጨረሱ፣ ወድቀው ያልተነሱ ያለአስታዋሽ የቀሩ ጥቂት የማይባሉ ናቸው። በተጨማሪም በዚህ ዘመን መሰማማት፣ መደማመጥ፣ መታዘዝ፣ መከባበር፣ ትህትና እና ፍቅር የጎደለው ቤተሰብን፣ ቤተ ክርስቲያንን፣ ሀገርን፣ የቤተ ክርስቲያን አባቶችን እና ሽማግሌዎችን የሚያከብር ትውልድ አጥተናል፡፡ በየዕለቱም ፍቅር ሳይሆን ጥላቻ፣ ርሕራሄ ሳይሆን ጭካኔ፣ መረዳዳት ሳይሆን መገፋፋት፣ ክብር ሳይሆን ማዋረድ፣ ምርቃት ሳይሆን እርግማን፣ ምስጋና ሳይሆን ስድብ እየበዛ ከመሄዱ አንጻር ትውልዱን እያጠፋ ይገኛል። ስለዚህ ሰንበት ት/ቤት ይህን እና ተመሳሳይ ጉዳዮችን ለመቅረፍ ለቤተ ክርስቲያን ጥቅሙና አስፈላጊነቱ የጎላ በመሆኑ ከየትኛውም ሥራችን አስቀድመን በዚህ ትውልድ ላይ በትኩረት አስፈላጊውን በጀት በመበጀት በገጠር በከተማ በሙሉ ኃይላችን ነፍሳችን ጭምር ሰጥተን መሥራት ይጠበቅብናል፡፡ እግዚአብሔር ቢፈቅድ እኛ ከእናንተ ከሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጋር ከወጣቱ ጋር ቤተ ክርስቲያንን ከፍ የሚያደርጉ ታላላቅ ሥራዎችን እቅድ አቅደን፣ ተገቢውን ጥናት አጥንተን፣ ተመካከረን፣ … ተወያይተን ሥራዎችን መሥራት ይገባናል፡፡ እንሥራለን እግዚአብሔርም ይረዳናል። ሰንበት ት/ቤቶች እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ የቤተ ክርስቲያን አባቶች፣ ሊቃውንት፣ አገልጋዮች፣ መምህራን እና ጽኑ አማኞች መገኛ እንደመሆኑ መጠን በየአጥቢያው ሰበካ ጉባኤው የአብነት መምህራን በመቅጠር ሰንበት ትምህርት ቤቱን በማጠናከር ትውልዱን በኦርቶዶክሳዊ የሃይማኖት ትምህርት በማነጽ፣ ዶግማን፣ ቀኖናን እና ትውፊትን በማስተማር በየሀገረ ስብከቱ በሁሉም አብያተ ክርስቲያናት ውስጥ ሰንበት ት/ቤቶች እንዲቋቋሙ፣ የተቋቋሙትም እንዲጠናከሩ ማድረግ ያስፈልጋል። በተጨማሪም የሰንበት ት/ቤቶች አገልግሎትን የበለጠ ለማጠናከር ሆኖ ዘርፈ ብዙ አገልግሎቶችን በመስጠት ወጣቱን ትውልዱ በዘመናዊነት ተፅዕኖ ውስጥ ወድቆ ከመንፈሳዊ ሕይወት እንዳይወጣ ልዩ ክትትል ማድረግ የሰንበት ት/ቤቶች ለተቋቋሙበት ዓላማና ተግባር እንዲንቀሳቀሱ ማገዝ መርዳት እንደሚያስፈልግ መዘንጋት የለብንም፡፡ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የዚሁ ጉባኤ ታዳሚዎች ቤተ ክርስቲያን በባሕርይዋ አንዲት፣ ሐዋርያዊት፣ ቅድስት እና ኩላዊት (ዓለም አቀፋዊት) እንደመሆኗ መጠን ትውልዱ ይህን በተግባር ማየት ይሻል። እውነት ነው ብዙ ያንቀላፋንበት፣ በእውነት በዓላማ ያልተንቀሳቀስንበት፣ ትኩረት ሰጥተን ያልሠራንበት፣ ተግተን ያላገለገልንበት፣ ጊዜ ብዙ ነፍሳት እና ብዙ ትውልድ አሳጥቶናል። ቀላልም የማይባል ዋጋም ጭምር አስከፍሎናል፡፡ ስለሆነም ከየትኛውም ጊዜ በላይ በቤተ ክርስቲያናችን፣ በቤተሰብ፣ በማኅበራዊ፣ በሀገራዊ፣ በአንድነታችን፣ በጠፋው ሰላማችን፣ በቀዘቀዘው ፍቅራችን፣ በደከመው እድገታችን፣ ትጋት በሌለው መንፈሳዊ አገልግሎታችን እና በሃይማኖታችን ጉዳዮች ላይ ይሄ የእግዚአብሔር የሥራ ጊዜ ነውና በፍቅር፣ በሰላም፣ በአንድነት፣ በመከባበር፣ በመተባበር፣ በትሕትና እና በመናበብ፣ እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ፣ እንደ አንድ ልብ መካሪ፣ በመሆን በተሰጠን ኃላፊነት ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን ክብር እና እድገት ልንሠራ ያስፈልጋል። የሰንበት ት/ቤቶችን አገልግሎት ያስፋልን፡፡ እግዚአብሔር በመንፈሳዊ በረከት ይባርካችሁ። ተባረኩ ብሩክ ሁኑ፡፡ እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ ግንቦት 3ዐ ቀን 2017 ዓ.ም አባ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ እና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ዱ አምላክ አሜን። "ሀበነ ንኅበር በዘዚአከ መንፈስ ቅዱስ-በአንተ ሕልውና ባለ መንፈስ ቄዱስ አንድ እንሆን ዘንድ አንድ መሆንን ስጠን" (ቅዳሴ ሐዋርያት ምዕ ፪ ክፍል ፪፥፴፬) ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጰሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ የምስራቅ ትግራይ ራያ ሀገረ ስብከትና የማሕበራት ማደራጃ መምሪያ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር አሀጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የመ/ፓ/ጠ/ቤ/ክ የመምሪያና የድርጅት ሓላፊዎች፤ እንዲሁም ሰንበት ትምህርት ቤቶቻችሁን ወክላችሁ ከየ ሀገረ ስብከቱ የመጣችሁ የሰንበት ት.ቤ.ቶች ክፍል ሓላፊዎችና የአንድነት አመራሮች በዚህ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ የተገኛችሁ ውሉደ ቤተ ክርስቲያን በሙሉ፤ "አቀድም አእኵቶቶ ለእግዚአብሔር በእንተ ኵልክሙ እስመ ተሰምዐት ሃይማኖትክሙ ውስተ ኵሉ ዓለም። -መሰብሰባችን፣ ጽንዐ ሃይማኖታችን በዓለም ሁሉ ተሰምቶዋልና  በዚህ ጉባኤ ላይ እንድንገኝ እንድናመሰግነውም የፈቀደልንን ልዑል እግዚአብሔርን ከሁሉ በማስቀደም እናመሰግናለን። እንኳን ለ፲፬ኛው ዓለም አቀፍ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤና በዓለ ጰራቅሊጦስ አደረሳችሁ!! እንኳንም ደህና መጣችሁ ለማለት እወዳለሁ።  በመቀጠልም፦ቅዱሳን ሐዋርያት "ሀበነ ንኅበር በዘዚአከ መንፈስ ቅዱስ በማለት የአንድነታቸው ማኀተም በሆነው መንፈስ ቅዱስ ኀብረታቸው እንዲጸና ለምነዋል የዚህም ታላቅ ጉባኤ ዓላማ ሕብረተ መንፈስ ቅዱስን አጽንቶ ትውልድን በቀናች ሃይማኖት ለማነጽ በመንፈስ ቅዱስ እርዳታ የተሰጠንን ኃላፊነት ለመወጣት ነው። እንደሚታወቀው ሕብረት ማለት የእርስ በርስ ግንኙነት ማለት ሲሆን ሕብረት ማድረግ ያስፈለገው አንድ ሰው ብቻውን ምንም ማድረግ ስለማይችል ነው።ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን አገልግሎቷ ሁሉን አሳታፊ ነው። ቅ.ዳዊት "ናሁ ሠናይ ወናሁ አዳም ሶበ ይሄልዉ አኃው ሕቡረ"= ወንድሞች በሕብረት ቢኖሩ መልካም ነው በማለት ሕብረት መልካምና የተወደደ መሆኑን ገልጦልናል ሕብረታችንን ደግሞ የሚያጸናው ፍቅር ነው ያለ ፍቅር ሕብረት ትርጉም የለውም በሕብረት ውስጥ የፍቅርን የበላይነት ቅዱስ ጳውሎስ ሲያስረዳን በልሳን ብናገር ትንቢትንም ሁሉ ባውቅ ሥጋዬንም ለእሳት አሳልፌ ብሰጥ ፍቅር ግን ከሌለኝ ከንቱ ነኝ በማለት ግልጹን ነግሮናል።1ኛቆሮ ፲፫፥፪ ቅዱሳን ሐዋርያትም መንፈስ ቅዱስ የወረደላቸው አብረው ስለተሰበሰቡ ብቻ አይደለም በአንድ ልብ በአንድ ሀሳብ በፍቅር ጸንተው ስለጠበቁት ነው።(ግሐ ፪፥፵፪) የተከበራችሁ የዚህ ታላቅ ጉባኤ ተሳታፊዎች እንዲሁም በመላው ዓለም ያላችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን፦ ይህን የሚያክል ታላቅ ሕብረት ፈጥረን በመካከላችን መለያየት ካለ ትርፉ ድካም ብቻ ነው እግዚአብሔርም በመካከላችን አይገኝም። መለያየት ዲያብሎስ ቤተ ክርስቲያንን ለማጥቃት ከሚጠቀምበት  መሣሪያ አንዱ ስለሆነ፤ሀበነ ንሕበር በዘዚአከ መንፈስ ቅዱስ እያልን በመማጸን ሕብረታችንን እናጽና። ቅዱስ አባታችን ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ክቡራን የዚህ ታላቅ ጉባኤ እድምተኞች ይህ በየ ዓመቱ በእለተ ጰራቅሊጦስ እየተከናወነ ያለው ጠቅላላ ጉባኤ ዘርፈ ብዙ መንፈሳዊ ፍሬ ያፈራ ጉባኤ ነው፤ ባሳለፍናቸው 3 ዓመታት እንኳን ለረዠም ዓመታት የተደከሙባቸው ሥርዓተ ትምህርት ትግበራ እና የመማሪያ መጻሕፍት ሕትመት ተግባራዊ ሆኖ ፍሬውን ለማየት በቅተናል፦ በሀገር ውስጥና በውጭው ዓለም የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ተጠናክሮ ዘመኑ በፈቀደልን ቴክኖሎጂ በመጠቀም ተናቦ ለመስራትም ተችሎዋል። ይህም የሆነው የቅዱስ ሲኖዶስ የቅርብ ክትትል ስላልተለየን የቅዱስ አባታችን ጸሎት እረድቶን የመንፈስ ቅዱስ እገዛ ተጨምሮበት ነው። በተጨማሪም፦ ያላቸውን ጥሪው ሸጠው በአንድነት ለመኖር ወስነው የመንፈስ ቅዱስ እርዳታ እንደጎበኛቸው  መቶ ሃያው ቤተሰብ በሀገር አቀፍ ደረጃና በውጭው ዓለም እያገለገሉ ያሉ ልጆቻችን ያላቸውን እውቀት፣ጉልበት፣ገንዘብና ጊዜአቸውን ያለ ምንም ስስት  በማዋጣት እያበረከቱ ያለው የአንድ ልብ አገልግሎትም ውጤት ነው። ለዚህም መንፈሱን ልኮ ዘወትር ከሕብረታችን ያልተለየው እግዚአብሔርን ሳመሰግን በታላቅ ደስታ ነው። ወደ ፊትም ከዚህ የበለጠ ሰፊ ሥራ የሚጠብቀን መሆኑን ለአፍታ እንኳን የምንዘነጋው አይደለም ጀመርን እንጂ አልጨረስንምና። ቅዱስ አባታችን ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ትውልዱ በጥያቄና በብዙ ፍላጎት የተሞላ ስለሆነ ዘመኑም ውስብስብና አስጨናቂ በመሆኑ በትውልዱ ላይ የተጫነው ዓለም አቀፍ ጫና ያለ እግዚአብሔር ቃል የሚታለፍ ስላልሆነ ከሥራችን ጎን ለጎን ብርቱ ጸሎትና ያላሰለሰ ክትትል ከምን ጊዜውም በላይ ያስፈልገናልና በጸሎታችሁ ይህን ጉባኤ እንድታስቡት እማጸናለሁ። በመጨረሻም የቤተ ክርስቲያኒቱን ጥሪ አክብራችሁ የትውልዱ ባለ አደራነታችሁን ተረድታችሁ በዚህ ታላቅ ጉባኤ ላይ ከሩቅም ከቅርብም የተገኛችሁ የቤተ ክርስቲያናችን ልጆች እናንተንም የወከላችሁንም ሀገረ ስብከት በታላቅ አክብሮት እናመሰግናለን። በምትቆዩባቸው ጊዜያት ሁሉ ዓለም እንደ ሚያገሳ አንበሳ ዙሪያውን በተለያዩ ርኩሰቶች አድብታ ለምትጠብቃቸው የዚህ ዘመን ትውልድ የሚጠቅም ፍሬአማ ውይይት እንድታደርጉ እያሳሰብኩ መልእክቴን አጠቃልላለሁ። ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!! የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

በ14ኛው ዓለም አቀፍ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ እና የሰንበት ት/ቤቶች ቀን የተላለፈ የብፁዕ አቡነ ቀለሜንጦስ የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ እና የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ
በ14ኛው ዓለም አቀፍ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ እና የሰንበት ት/ቤቶች ቀን የተላለፈ የብፁዕ አቡነ ቀለሜንጦስ የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ እና የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ መልእክት

(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ሰ/ት/ቤቶች ማ/መምሪያ ዓለም አቀፍ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ፲፬ኛው ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ የቃለ ጉባኤ ማጠቃለያ እና የጋራ የውሳኔ ሐሳብ የኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ፲፬ኛው ጠቅላላ ጉባኤ ግንቦት 30 እና ሰኔ 1/ 2017 ዓ.ም ከየአህጉረ ስብከቱ የተወከሉ የሀገር አቀፍ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ አባላት፣ የዐዲስ አበባ ሀ/ስብከት አጥቢያ ሰ/ት/ቤቶች አባላት እና ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት ተካሔዷል። በመሆኑም በጉባኤው ከቀረቡ ዓመታዊ ሪፖርቶች፣ ተዘጋጅተው ከቀረቡ ጥናታዊ ሰነዶች፣ ከየአህጉረ ስብከት ከቀረቡ አስተያየቶች እና ከጉባኤው ተሳታፊዎች ከተነሡ የውይይት ሐሳቦች ግብዓት በመነሣት ባለ 12 ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት ተጠናቋል፡፡ 1.በጠቅላላ ጉባኤው የቀረበውን የሰንበት ት/ቤቶች አንድነትና የአህጉረ ስብከት አንድነቶች የሥራ አፈጻጸም ሪፖርትና የተሰጡ የሥራ አቅጣጫዎችን ጠቅላላ ጉባኤው ተቀብሎ ያጸደቀ ሲሆን የሰንበት ት/ቤቶች የ5 ዓመት መሪ ዕቅድ አፈጻጸም በተጠናከረ መልኩ እንዲቀጥል ጉባኤው ወስኗል። 2.በቅዱስ ሲኖዶስ የጸደቀው መሪ ዕቅድን በተመለከተ በትኩረት የምንከታተለውና የብዙ ምሁራን ጊዜ፣ ዕውቀትና ጉልበት የፈሰሰበት ሥራ ወደ ተፈለገው ውጤት እንዳይመጣ የሚደረገው የማሰናከል ሥራ በእጅጉ ያሳዘነን ከመሆኑም ባሻገር እናት ቤተ ክርስቲያናችን ዘመኑን የዋጀ ስልታዊ አካሔድ እንዳትከተል አሉታዊ ተጽዕኖ እና ከፍተኛ ሥጋት አሳድሯል። የመሪ ዕቅድ ትግበራውን በተያዘበት አግባብ ማፋጠን፣ የሊቃውንቱ፣ የካህናት የምእመናን የሰ/ት/ቤት አባላትና ባለድርሻ አካላትን ሚና በሕግ ማውጣት ሥራ ላይ ከፍ እንዲል በአጽንዖት እንጠይቃለን። 3.በቤተ ክርስቲያን አስተዳደር በቃለ ዐዋዲ የተደነገገው የምእመናን፣ የካህናትና የሰንበት ት/ቤቶች ከመንበረ ፓትርያርክ እስከ አጥቢያ ሊኖራቸው የሚገባ የሰበካ ጉባኤ ሱታፌ በጽኑዕ እንዲተገበር እንዲሁም የሰ/ት/ቤት አባላት በጊዜ በጉልበትና በዕውቀት ከሚሰጡት የጎላ አስተዋጽዖ አንጻር ውክልናችን በቁጥር ከፍ እንዲል አበክረን እንጠይቃለን። 4.ልዩ ልዩ የአስተዳደርና የቀኖና ጥሰት እየተፈጸመ የቅድስት ቤተክርስቲያን አንድነቷ እንዲሸረሸር የሚደረጉ ድርጊቶችን በጽኑዕ እንቃወማለን። የቅዱስ ሲኖዶስ ልዕልና እንዲከበር፣ የቤተ ክርስቲያን አንድነት እንዲጸና፣ መለያየት እንዲወገድ ፣በዚህም የተፈጠሩ ልዩነቶች ተቀራርቦ በመነጋገርና የበደለ ክሶ፤ ያጠፋ በቀኖና ታርሞ እንዲስተካከሉ፣ በሀገር ሰላምና አንድነት ላይም ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የቀደመ ሚናዋን እንድትወጣ እንጠይቃለን። 5.በአብያተ ክርስቲያናት መካከል ያለው የሀብት ሥርጭት ፍትሐዊነት መጉደል ቤተ ክርስቲያን ከገጠር ወደ ከተማ እየተሰደደች መሆኗ በግልጽ የሚታይ በመሆኑ ለዚህ ችግር ትኩረት በመስጠት የአጥቢያ ዐቢይ ጉባኤን በማደራጀት ወደ ሥራ እንዲገባ እና በተደጋጋሚ እንደሚነሣው የፋይናንስ አስተዳደሩን የተማከለ የሚደረግበት ሥርዓት እንዲዘረጋ እንጠይቃለን። 6. አብዛኛው የቤተ ክርስቲያኗ ሀብት የሚመነጨው አጥቢያ ላይ በመሆኑ አስፈጻሚ አካላት ገንዘብ መልቀምና መጠበቅ ላይ በሀብት ምደባም ይሁን ለአስተዳደር ሥራ ብቻ ትኩረት በማድረጋቸው ሕፃናትን የማሠማራት፣ ወጣቶችንና ምእመናንን የመጠበቅ ሥራው በአብዛኛው ተዘንግቷል፣ ስለዚኽ ይኽ ጉዳይ በአስቸኳይ እንዲስተካከል እንጠይቃለን። 7.የሰንበት ትምህርት ቤቶች መዋቅር የበጀት ዕጥረት ከፍተኛ በመኾኑ፣ ሥርዓተ ትምህርቱን ማስፈጸም፣ የመጽሐፍ ስርጭቱንና ሌሎችንም ዘርፈ ብዙ የሰንበት ትምህርት ቤት ሥራዎች ከፍተኛ እንቅፋት በመፍጠሩ መፍትሔ እንዲሰጠው እንጠይቃለን። 8.ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት የጠነከረ የኢኮኖሚ አቅምና ማኅበራዊ መስተጋብር ፈጥረው ቤተ ክርስቲያናቸውን እንዲጠብቁና ለሀገርም ረብ ያለው ነገር ማበርከት እንዲችሉ የማድረግ ሚናዋን ዘንግታለች፣ ስለዚህም ጉዳዩ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶት በቂ ሀብት በመመደብና ተገቢ አመራር በመስጠት በአባላት ሁለንተናዊ ሕይወት ዙሪያ አስፈላጊ ለውጥ ማምጣት እንዲቻል ጥረት ይደረግ ዘንድ በአጽንዖት እንጠይቃለን። 9.የሰንበት ት/ቤቶችም ኾነ ሌሎች የቅድስት ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ የብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትን የቅርብ ክትትል የሚፈልግ ኾኖ እያለ ሀገረ ስብከቶቻቸውን በዓመት ለውስን ጊዜያት አንዳንዴም አንዴ ብቻ በሚጎበኙ ሊቃነ ጳጳሳት የተነሣ አገልግሎቶች እየታወኩ ይገኛሉ፤ ስለዚህ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳቱ ሀገረ ስብከቶቻቸውን በተገቢው መልኩ እንዲከታተሉ የሚመለከተው አካል ተገቢ ቁጥጥር እንዲያደርግ በአጽንዖት እንጠይቃለን። 10.የሰንበት ት/ቤቶች ጠቅላላ ጉባኤ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያሉ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነቶች ተወካዮች ተሰባስበው የሚመክሩበት፣ ስለ ቤተ ክርስቲያን የሚወያዩበት ቀጣይ ሥራዎች የሚተልሙበት ጉባኤ ነው። ይኽ ጉባኤ የሰንበት ትምህርት ቤት ተወካዮች ከቅዱስ ፓትርያርኩ፣ ከብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እና ከሌሎች የሥራ ሓላፊዎች ጋር የሚወያዩበትም ጭምር ነው። ይኹን እንጂ ይኽ ጉዳይ በትክክል ተፈጻሚ እየሆነ አይደለም። ስለዚኽ ይኽ ጉባኤ ከዚህ በኋላ የሚካሔዱ ጠቅላላ ጉባኤያት በቅዱስ ፓትርያርኩ ጸሎተ ቡራኬ ተከፍቶ፤ በቅዱስ ፓትርያርኩ ቃለ ምዕዳን የሚዘጋ፤ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትም ተገኝተው የሚመሯቸው እና የጠቅላይ ቤተ ክህነት የመምሪያ ሓላፊዎች እና የአህጉረ ስብከት ሥራ አስኪያጆች ተገኝተው የሰ/ት/ቤቶችን ጉዳይ በሓላፊነት የሚከታተሉባቸው እንዲኾኑ በአጽንዖት እንጠይቃለን። 11.. በዚኸ ጉባኤ ላይ በተለያዩ ምከንያቶች ያልተገኙ የአህጉረ ስብከት ተወካዮች እንዳሉ ቢታወቅም በተለይ ግን በትግራይ ከልል ከሚገኙ አህጉረ ስብከት ጋር በተፈጠረዉ እጅግ አሳዛኝ መለያየት የተነሣ የክልሉ አህጉረ ስብከት ተወካይ ወንድሞች እና እኅቶች ባለመገኘታቸዉ ጉባኤው ከፍተኛ ኀዘን ተሰምቶታል። ከዚህም በላይ ችግሩ ወደ ምእመናን እየሰፋ መሔዱ ጉባኤውን በእጅጉ አሳስቦታል፡፡ በ13ኛው ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ አበክረን፣ ከወንበራችን በመነሣት በልመናና በልጅነት መንፈስ መፍትሔ እንዲያገኝ ብንጠይቅም ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ ባለማየታችንና ይኸ መለያየት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየሰፋ ሔዶ በአንዲቷ ቤተ ክርስቲያን ላይ ከፍተኛ አደጋና የማይጠገን ስብራት እያደረሰ በመሆኑ ልዩነቶችን አስወግዶ በሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን አግባብ የክልል ትግራይ አህጉረ ስብከት ወደ መዋቅራቸው ጠቅላይ ቤተ ክህነት ይመለሱ ዘንድ፤ በእኛ በኩል የተቻለንን ኹሉ እንደምናደርግ ቃል በመግባት አሁንም ችግሩን ለመፍታትና እርቀ ሰላሙን ለማምጣት ከፍተኛዉን ድርሻ ሊወጡ የሚችሉት ብፁዕ ወቅዱስ አባታችን እንደኾኑ እናምናለን፡፡ ይኽንኑ ለመፈጸም ቅዱስነትዎ ቃል ይገቡልን ዘንድ የቤተ ክርስቲያን ልደት ተብሎ በሚታወቀው በዛሬው በዓለ ጰራቅሊጦስ ስም ልክ እንደ አምናው ኹሉ ከመቀመጫችን በመነሣት በታላቅ አከብሮት እና ትሕትና እንጠይቃለን። 12.እነዚህ የ14ኛው ሀገር ዐቀፍ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ የጋራ የውሳኔ ሐሳብ በቀጣይ የሲኖዶስ ስብሰባ አጀንዳዎች እንዲሆኑ አበክረን እንጠይቃለን። ሰኔ 1 ቀን 2017 ዓ.ም አዲስ አበባ ኢትዮጵያ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!

የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

የመንፈስንም ሰይፍ ያዙ እርሱም የእግዚአብሔር ቃል ነው'' ኤፌ 6÷17 14ኛው የሰንበት አቀፍ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ እና የሰንበት ት/ቤቶች ቀን የመክፈቻ መርሐ ግብር ተካሔደ።
+9
የመንፈስንም ሰይፍ ያዙ እርሱም የእግዚአብሔር ቃል ነው'' ኤፌ 6÷17 14ኛው የሰንበት አቀፍ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ እና የሰንበት ት/ቤቶች ቀን የመክፈቻ መርሐ ግብር ተካሔደ። (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት)፤ 29/09/2017 ዓ.ም 14ኛው ዓለም አቀፍ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ እና የሰንበት ት/ቤቶች ቀን የመክፈቻ መርሐ ግብር በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽርሐ ተዋሕዶ ፤ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ደቡብ ምዕራብ ሸዋ እና ሸገረ አኅጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፤ ብፁዕ አቡነ ማርቆስ የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልዕኮ ሊቀ ጳጳስ ፤ ብፁዕ አቡነ ጢሞቲዎስ ዳውሮና ኮንታ አኅጉረ ስብከት ጳጳስ ፤ ንቡረ እድ ኤልያስ አብርሃ በጠ/ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ም/ሥራ አስኪያጅ ፤ መ/ብ ቆሞስ አባ ተክለ ያሬድ ጎርጎርዎስ የቅዱስ ሲኖዶስ ም/ጸሐፊ ፤ የጠቅላይ ቤተ ክህነት የመምሪያ ሐላፊዎች ፣ ከየሀገረ ስብከቱ የተወከሉ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተወካይ ተሣታፊዎችና የሰ/ት/ቤት አባላት በተገኙበት የመክፈቻ መርሐ ገብር ተካሔዷል። በመርሐ ግብሩ ላይ "መንፈስ ቅዱስን እስክልክላቹ በዚሁ ቆዪ" በሚል መነሻ ቃል በብፁዕ አቡነ ማርቆስ ቃለ እግዚአብሔር ፤እንዲሁም '' የጭንቀት ቀን ሳይመጣ ፈጣሪህን አስብ" መክ 12፥1 በሚል መነሻ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ አባታዊ ቡራኬ እና መልዕክት አስተላልፈዋል። በመቀጠልም የማደራጃ መምሪያው ሊቀ ጳጳስ የብፁዕ አቡነ ቀለሜንጦስን የእንኳን ደና መጣቹ መልዕክት በመምሪያው ት/ምህርት ክፍል ሐላፊ በኩል ሲቀርብ የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የ2016/17 ዓ.ም የበጀት ዓመቱ የሥራ አፈጻጸምና የሒሣብ ሪፖርት በማደራጃ መምሪያ ሐላፊው መጋቤ ሐዲስ ጸጋ ወ/ትንሣኤ ቀርቧል።

ለ14ኛው የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ እና የሰንበት ት/ቤቶች ቀን የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ተጠናቀቁ። "የመንፈስንም ሰይፍ ያዙ እርሱም የእግዚአብሔር ቃል ነው" ኤፌ 6፡17 በሚል መሪ
+3
ለ14ኛው የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ እና የሰንበት ት/ቤቶች ቀን የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ተጠናቀቁ። "የመንፈስንም ሰይፍ ያዙ እርሱም የእግዚአብሔር ቃል ነው" ኤፌ 6፡17 በሚል መሪ ቃል ነገ እና ከነገ በስቲያ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ እንዲሁም በሁሉም ሀገረ ስብከት ይከበራል። የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok