uk
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Відкрити в Telegram

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Канал የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 14 434 підписників, посідаючи 6 048 місце в категорії Релігія і духовність та 2 328 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 14 434 підписників.

За останніми даними від 27 червня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 543, а за останні 24 години на 21, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 36.43%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає N/A% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 5 252 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 0 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 33.

📝 Опис та контентна політика

Опис каналу не надано.

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 28 червня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Релігія і духовність.

14 434
Підписники
+2124 години
+1247 днів
+54330 день
Архів дописів
"የኢትዮጵያ ድንኳኖች ሲጨነቁ አየሁ፤ የምድያም አገር መጋረጃዎች ተንቀጠቀጡ።" ዕምባ 3፡7 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! ✍️Youtube �
"የኢትዮጵያ ድንኳኖች ሲጨነቁ አየሁ፤ የምድያም አገር መጋረጃዎች ተንቀጠቀጡ።" ዕምባ 3፡7 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! ✍️Youtube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu

የቀያፋ ንግግር ሊቀ ካህናት ነውና ከልቡ አምኖበት በመንፈስ ቅዱስ በታደሰ አእምሮው አይደለም የእርሱ ሹመት በዚያን ዓመት ነውና የበለዓምን አህያ የሆሳዕናን ድንጋዮች በተዓምራት እንዳናገረ እግዚአብሔር በተአምራት አናገረው እንጂ። አንድም በአእምሮ ጠባይዕ አውቆ አይደለም በሹመቱ አድሮ ያለ ሀብት አናገረው እንጂ ይህም ማለት እግዚአብሔር በሳዖል አድሮ ሠላሳ ስምንት ዘመን የመንግሥት ሥራ እንደ ሠራ በኃጥዕ ቄስ አድሮ ሥጋውን ደሙን እንዲለውጥ በቀያፋ አድሮ ተናገረ። የቀያፋ ንግግር ኢየሱስ ክርስቶስ ለህዝብ ሁሉ ቤዛ ሆኖ ይሞት ዘንድ መምጣቱን ነገር ግን ቤዛነቱ ለሕዝብ ብቻ አለመሆኑ በኃጢአት በጣዖት የተበተኑ አህዛብንም አንድ ያደርጋቸው ዘንድ መሆኑን የሚያስረዳ ነው። እዚህ ጋር ሕዝብና አህዛብ አንድ የሆኑማ በሃይማኖት አይደለምን? ቢሉት ሞቱ ያለ ሃይማኖቱ ሃይማኖት ያለ ሞቱ አይሆንምና እንዲህ አለ እንጂ አንድ የሆኑት በሃይማኖት ነው። ይቆየን ሚኪያስ ግዛቸው ጥቅምት 2016 (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Tiktok👇 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion

"ከራስ ያልሆነን በራስ አንደበት መናገር" መነሻ ጥቅስ፦ "ይህንንም የተናገረ ከራሱ አይደለም" ዮሐ 11፥51 አንደበት መልዕክት ማስተላለፊያ መሳርያ ነው። ከአንደበት የሚወጣ ንግግር ጥንስሱ ልብ ነው። በልባችን ያሰብነው ሐሳብ አካል ነስቶ የሚገለጠው በአንደበት ነው። ልብ ደግሞ ክፉም ያስብ ደግ ምድራዊም ያስብ ሰማያዊ የልብ ሐሳብ በአንደበት ቢሉ በተግባር የተገለጠ ነው። እንዲህ ስንል ግን የልብ ሐሳብ ሁሉ የተገለጠ ነው አያሰኝም በልብ ተሰውሮ የሚኖር ግዘፍ ያልነሳ የተሰወረ እግዚአብሔርና የሰወረው አካል ብቻ የሚያውቁት ጊዜና ሰዓቱን የሚጠብቅ አንዳች ሐሳብ (ፈቃድ) መኖሩን ልብ ልንል ይገባል። ሰው የሚናገረው ሁሉ ከራሱ ነወይ? የሚለው ጥያቄ ብዙዎችን የሚያከራክር ነው። ከራስ ቁጥጥር ውጪ በራስ አንደበት ቃላትን ሊያወጣ ሊናገር ይችላልና። ይህም በተለያየ አጋጣሚ ሊፈጸም የሚችል ነው። አንባቢ ሆይ፦ የምንናገረውን ሁሉ እናውቅ ይሆንን? የምንናገረውስ በራሳችን ፈቃድና ሀሳብ ነውን? ከራሳችን ያልሆነ፣ ይህን ከየት አመጣሁት ብለን የተገረምንበት እንዲሁ ይህን ለምንና እንዴት ተናገርሁ ብለን የተቆጨንበት ንግግር የለምን? በአንድም በሌላም መንገድ በተለያዩ አጋጣሚዎች ለራሳችን እስኪገርመን ድረስ ከራስ ያልሆነን ንግግር በራሳችን አንደበት ስንናገር እንደመጣን ይህ እንዴት ይሆናል? በዚ ጽሑፍ ከማስረጃ ጋር በጥቂቱ እንመለከታለን። ⓵ በዲያብሎስ ግፊት (አንደበታችንንና መላ አካላችንን ሲቆጣጠር፦ ይኸ ከእኛ ፈቃድ ውጪ የሚከወን ለሰው እንጂ ለራሳችን በማይታወቀን መልኩ ሊፈፀም ይችላል ። ከቀድሞ ማንነታችንን ከመታወቂያ ጠባያችን ባፈነገጠ መልኩ ሌላ ማንነትን የሚያላብስ በሰዎች እንድንጠላ የሚያደርገን ይሆናል። ዲያቢሎስ በእባብ ሰውነት ቢዋሐድና መላ ነውነቷን ቢቆጣጠር በአዳም ፊት ቀድሞ ታሳየው ከነበረው በፊቱም ትናገረው ከነበረው ንግግር በተለየ እፀ በለስን ስለመከልከላቸው "ከእርስዋ በበላችሁ ቀን ዓይኖቻችሁ እንዲከፈቱ እንደ እግዚአብሔርም መልካምንና ክፉን የምታውቁ እንድትሆኑ እግዚአብሔር ስለሚያውቅ ነው እንጂ። በማለት አዲስ ቃልን ወይም ሐሳብን አቀረበች" ዘፍ 3 ፥5 ይኽ ንግግር መልካም የሚመስል በውስጡ ግን መርዝ ያለበት ንግግር ነበር። ምንም እንኳ መጽሐፍ " እባብም እግዚአብሔር አምላክ ከፈጠረው ከምድር አውሬ ሁሉ ይልቅ ተንኰለኛ ነበረ" ዘፍ 3 : 1 ቢልም እባብ ይህንን ግን ትናገር የነበረች ከራስዋ አልነበረም። ዛሬም በዲያብሎስ አሽክላ የተያዙ መላ ሰውነታቸውን የተቆጣጠራቸው ምን እንደሚያደርጉና እንዳደረጉ የማያውቁ ከአንደበታቸውም ምን እንደወጣና እንደሚወጣ የማያስታውሱ፣ እውነትነት የሌለው ከራሳቸው (ከቀልባቸው ማለትም ከአእምሮአቸው) ያልሆኑ አሉ። እንዲህ አይነቱን (ከዲያብሎስ የሆነ) ጥቅም የለሽ ንግግር ጆሮ ሰጥተው ሊሰሙት ፍሬ አገኝበታለሁ በማለት ወደ ልብ ሊያስገቡት የማይገባ ነው። ሌላው በመጽሐፍ ቅዱስም እንደሰፈረልን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ጴጥሮስን ብፁዕ ብሎ የማሰርና የመፍታት ሥልጣንን ከሰጠው በኋላ ወደ ኢየሩሳሌም ሊሄድና መከራን ሊቀበል ሊሞትም ከሙታንም እንደሚነሳ በተናገረ ግዜ ቅዱስ ጴጥሮስ እሞታለሁ ማለቱን ሰምቶ አይሁንብህ ብሎ ገሰጸው። ክርስቶስ ግን "ዘወር ብሎ ጴጥሮስን፦ ወደ ኋላዬ ሂድ፥ አንተ ሰይጣን፤ የሰውን እንጂ የእግዚአብሔርን አታስብምና ዕንቅፋት ሆነህብኛል አለው።" ማቴ16 : 23 ይህ የቅዱስ ጴጥሮስ ንግግር መልካም ቢመስልም ከእርሱ አንጻር የተናገረ ነብያትንና ትንቢታቸውን ሐሰተኛ ለማድረግ የሚሻ ምዕመናን እንዲድኑ የማይፈልግ ዲያቢሎስ ነውና በእርሱ አንጻር ዲያቢሎስን ሂድ ከዚህ አለ። ከብፅአት ወደ ተግሳፅ በአንድ ግዜ ተመልሶ ሂድ ማለቱ እንደ ግዜ ግብሩ የሚፈርድ አምላክ ስለሆነ ነው። ቅዱስ ጴጥሮስ እንደ ጊዜ ፍርዱ ብፁዕ አለው ከዚያም እንደ ግዜ ግብሩ ሰይጣን አለው። ⓶ በስሜታዊነት ራስን ባለመግዛት ጦስ ሰው በአንድም በሌላም መንገድ ከራሱ ያልሆነ ( ለማን ለምን ምን የሚሉትን ጉዳዮች አስቦበት ጥቅምና ጉዳቱን መዝኖ፣ የንግግሩን ፍሬ ሐሳብ ለይቶ ከአንደበቱ ያላወጣው) በቅጽበታዊ ሀዘን ወይ ንዴት አልያም ደስታ ባለ ስሜታዊነት ውስጥ ሆኖ የሚናገረው ያ ንግግር ለብዙዎች ስብራትና ቀቢፀ ተስፋ ምክንያት ሊሆን ይችላል። እንዲህ አይነቱ ንግግር ለሰው ብቻ ሳይሆን ከስሜታዊነት ርቀው በሰከነ ልቦና ሆነው ወደ ኋላ ባጤኑት ጊዜ ራስንም ለታላቅ ፀፀት የሚዳርግ ነው። ከራስ (ከልብ መክረው አስበው) የተናገሩት አይደለምና። እንደ ክርስቲያን ራሳችንን ከእንዲህ ዓይነት ስሜታዊነት ልናርቅ በአንደበታችንም እንዳገኘን ከመናገር ልንገታ ይገባል። ምክንያቱም የአምልኮ መገለጫ አይደለምና። መጽሐፍ " አንደበቱን ሳይገታ ልቡን እያሳተ እግዚአብሔርን የሚያመልክ የሚመስለው ማንም ቢኖር የእርሱ አምልኮ ከንቱ ነው።" ያዕ 1 : 26 እንዲል። ነገረ ክርስቶስን በማስተማሩ ቅዱስ ጳውሎስና ትምህርቱ ላይ "ጳውሎስ ሆይ አብደሃል እኮ ብዙ ትምህርትህ ወደ እብደት ያዞርሃል" በማለት ለተናገረ ፊስጦስ ለተባለው ሰው ቅዱስ ጳውሎስ በፍፁም ትህትና አገልግሎቱና ትምህርቱ ከስሜታዊነት የራቀ እውነት ላይ የተመሠረተ እንደሆነ ምላሽን ሲሰጥ " ክቡር ፊስጦስ ሆይ፥ የእውነትንና የአእምሮን ነገር እናገራለሁ እንጂ እብደትስ የለብኝም።" ሐዋ26 : 25 ብሎታል። ⓷ በተአምራት መጽሐፍ "እግዚአብሔር በአንድ መንገድ በሌላም ይናገራል፤ ሰው ግን አያስተውልም" ኢዮብ 33 : 14 እንዲል እግዚአብሔር ለሰው ልጆች መልዕክትን ማስተላለፍ ሲሻ የተለያዩ መንገዶችን ይጠቀማል። ከነዚህም መካከል ገቢረ ተአምራት ዋነኞቹ ናቸው። በለዓምን ለማስተማር የአህያይቱን አፍ ከፍቶ ከራሷ ያልሆነን ቃል እንድትናገር በማድረግ መልዕክትን እንድትናገር ያደረገ እግዚአብሔር ነው። ዘኁልቅ 22፥28 አህያይቱ ከራሷ ያልሆነ መልዕክቱ ብቻ አይደለም በሰው ልሳን መናገሯም ጭምር መሆኑን ልብ እንበል። በሐዲስ ኪዳንም ቢሆን በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ በክፉ ቅንዓት የታወሩ አይሁድ በሆሳዕና ሕፃናት ስለክብሩ ሲዘምሩለት ሰምተው ስለ አምላክነቱም ዘንባባን ሲያነጥፉለት ተመልክተው ሕፃናቱን ዝም እንዲያሰኙ በተናገሩ ግዜ " እነዚህ ዝም ቢሉ ድንጋዮች ያመሰግኑኛል" ያለው ቃል ተፈጽሞ አንደበት የሌላቸው ግዑዛኑ አዕባን ማመስገናቸው ገቢረ ተአምራቱን የሚያሳይ ነው። ሉቃ 19፥40 የአዕባን መናገር የራስ የማያሰኘው መልዕክቱ ብቻ ሳይሆን ከተፈጥሮ ባሕርይ ውጭ መሆኑ ነው። ከሰውም ወገን ቢሆን ሰዎችን ሊያናግር መልዕክትንም ሊያስተላልፍ እንደሚቻለው በተግባር ያየነው ጉዳይ ነው። በአልዐዛር ከሞት መነሳት ያጉረመረሙት የካህናት አለቆችና ፈሪሳውያን እንዲሁ ብንተወው ሁሉ በእርሱ ያምናሉ፤ የሮሜም ሰዎች መጥተው አገራችንን ወገናችንንም ይወስዳሉ የሚል ፓለቲካዊ ምክንያት አቅርበው ዮሐ 11 : 48 ምን እናድርግ? ብለው ሸንጎ ሰበሰቡ። ከእነርሱም መሀከል ሹመቱ በዚያን ወራት የሆነ ቀያፋ የተባለ ሰው " ሕዝቡም ሁሉ ከሚጠፋ አንድ ሰው ስለ ሕዝቡ ይሞት ዘንድ እንዲሻለን አታስቡም" በማለት ምክርን አቀረበላቸው። ነገር ግን " ይህንም የተናገረ ከራሱ አይደለም፥ ነገር ግን በዚያች ዓመት ሊቀ ካህናት ነበረና ኢየሱስ ስለ ሕዝቡ ሊሞት እንዳለው ትንቢት ተናገረ፤" ዮሐ11 : 51

"ይህ ስፍራ የእግዚአብሔር ቤት ነው እንጂ ሌላ አይደለም፤ ይህም የሰማይ ደጅ ነው።" ዘፍ 28፡17 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! ✍️Yout
"ይህ ስፍራ የእግዚአብሔር ቤት ነው እንጂ ሌላ አይደለም፤ ይህም የሰማይ ደጅ ነው።" ዘፍ 28፡17 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! ✍️Youtube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu

ክርስትና ከዘውግ ባሻገር የሆነ ማንነት የሰው ልጅ ሁሉ ከአዳም የተገኘ የእግዚአብሔር አምላክ የእጅ ሥራ ነውና ከላይ በቀለም በቅርፅ ወዘተ ልዩነት ቢኖረው እንኳ የሚመሳሰልበት ከውስጥ የሆነ ሥነ-ሕይ
ክርስትና ከዘውግ ባሻገር የሆነ ማንነት የሰው ልጅ ሁሉ ከአዳም የተገኘ የእግዚአብሔር አምላክ የእጅ ሥራ ነውና ከላይ በቀለም በቅርፅ ወዘተ ልዩነት ቢኖረው እንኳ የሚመሳሰልበት ከውስጥ የሆነ ሥነ-ሕይወታዊ አንድነት አለው፡፡ ይህም ተመሳሳይ ተፈጥሮአዊ እና ሥነ ልቡናዊ (Bio-Psychic Union) ውቁር እንዲኖረው አድርጓል፡፡ በማኅበራዊ ፍጡርነቱ በፈጠረው በማኅበራዊ መስተጋብሩ ምክንያት ደግሞ በሒደት ራሱን ካንድ የባህል መሠረት ካለው ማንነት ጋር ያዛምዳል፡፡ ይህ ልዩነት ደግሞ የተለያየ አስተሳሰብ/ እና የአረዳድ አድማስ እንዲኖረው ያደርገዋል፡፡ ክርስትና ለነፍሳችን መድኅን የሆነው የእውነትና የሕይወት መንገድ ጌታችን መድኃኒታችን ክርስቶስ ኢየሱስ ብቻ መሆኑን ያስተምራል፡፡ ክርስቲያንም ይህን እውነት ብቻ ይከተላል፡፡ ከአምልኮ መልስ ባለው ማኅበራዊ መስተጋብር ግን ብዝኃነትን ያከብራል፡፡ ማንበብ ይቀጥሉ... 👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://eotc-gssu.org/a/ክርስትና-ከዘውግ-ባሻገር-የሆነ-ማንነት/ ክርስትና ከዘውግ ባሻገር የሆነ ማንነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Tiktok👇 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion

እንኳን ለመድኃኔዓለም ዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ። መድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ራሱን አሳልፎ በመስጠት ለዓለም መድኃኒት የሆነው መጋቢት 27 በዕለተ ዓርብ መኾኑ የታወቀ ነው፡፡ (ይህም ዕለት የስቅለት በዓል ነው፡፡ መጋቢት 27 ጥንተ ስቅለት ነው፡፡ መጋቢት 29 ደግሞ ጌታ የተነሣበት በመሆኑ ጥንተ ትንሣኤ ነው፡፡) በዚህም የተነሣ ምንም እንኳን ዓመታዊው ዋናው በዓል መጋቢት 27 ቢሆንም ወር በገባ በ27 መድኃኔዓለምን እንዘክራለን፡፡ ጥቅምት 27 ዓመታዊ በዓል ሆኖ የሚከበርበት ምክንያት ሁለት እንደ ኾነ ትውፊታችን ይመሰክራል። የመጀመሪያው ምክንያት መጋቢት 27 ዐቢይ ጾም ከሚውልባቸው ቀናት አንዱ በመሆኑና በዐቢይ ጾም ደግሞ ዐበይት በዓላትን በድምቀት ለማክበር ወቅቱ የማይፈቅድ ስለሆነ ከአባ መብዓ ጽዮን መታሰቢያ በዓል ጋር በጥቅምት 27 እንዲከበር አባቶች ቀኖና በመሥራታቸው ነው፡፡ ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ የመድኃኔዓለምና የኪዳነምህረት ወዳጅ አባ መብዓ ጽዮን የሚታሰቡበት ዕለት ጥቅምት 27 በመኾኑ ነው። ጨለማን ያሳደደው ብርሃን፥ ዓለምን ሁሉ ያበራው ፋና ፥የማይናወጥ መሠረት ፥የማይፈርስ ግንብ ፤የማይሰበር መርከብ ፥የማይሰረቅ ማህደር፤ ያማረ ቀንበር፥ የቀለለ ሸክም፥ ለአባቱ ኃይሉ ጥበቡም የሚሆን እርሱ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። እንዳለ ቅዳሴ ወልደ ነጎድጓድ ጌታችን መድኃኔዓለም ለኛ ሲል በፈጸመው፥ የማዳን ሥራ ክፉዎች አይሁዶች ፥ከምሽቱ ሦስት ስዓት በጌቴሴማኔ፥ ውስጥ ሁሉን የያዘውን ያዙት ፤ሁሉን የሚገዛውን አሰሩት የሕያው አምላክ ልጅን አሰሩት ፤በቁጣ ጎተቱት በፍቅር ተከተላቸው፤ በሚሸልቱት ፊት እንደማይናገር እንደ የዋኅ በግ ከኋላቸው እየተከተለ ወሰዱት። ቅዳሴ ዮሐንስ አፈወርቅ ቁ፦፵፮ እንዳለ ሌሊቱን ሙሉ ከቀያፋ ወደ ሃና፥ ከሃና ወደ ቀያፋ ስያመላልሱት ፤አስረውት ሲደበድቡት አድረዋል፥ ሊቃነ መላእክት በመፍራትና በመንቀጥቀጥ በፊቱ የሚቆሙለትን በአደባባይ አቆሙት ፤ ኃጢኣትን ይቅር የሚለውን ኃጥእ አሉት ፥በመኳንንት የሚፈርደውን እርሱን ፈረዱበት ። ቅ/ዮ/አፈ ቁ፦ ፵፯ እንዲል እርሱ ዝም ሲላቸው አይኑን ሸፍነው በጥፊ መቱት፤ ርኲስ ምራቃቸውን ተፉበት፤ ራሱንም በዘንግ መቱት እርሱ ግን ሁሉንም ታገሰ፤ በጠዋቱ ሞት እንድፈረድበት፤ ከገዢው ዘንድ አቀረቡት በሦስት ስዓት አካሉ እስኪያልቅ ድረስ ስድስት ሺህ ስድስት መቶ ስድሳ ስድስት ጊዜ ገረፉት፤ ሊጦስጥራ አደባባይ ላይ እርጥብ መስቀል አሸክመው ወደ ቀራንዮ ወሰዱት፤ በቀትር ስድስት ስዓት ላይ በአምስት ረዣዥም ችንካሮች ቸንክረው ሰቀሉት፤ በዚያች ሰዓት ሰባት ታላላቅ ተዓምራት በምድርም በሰማይም ታዩ፤ በባሕርይ ሥልጣኑ ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት ቅድስት ነፍሱን ከሥጋው ለየ፤ በዚያች ሰዓት ወደ ሲዖል ወርዶ የታሰሩትን ነፍሳት ፈታቸው አሥራ አንድ ሰዓት ደጋጎች ዮሴፍና ኒቆድሞስ ከመስቀል አውርደው በአዲስ መቃብር ቀበሩት፤ በዚያች ቀን ድንግል ማርያም ልቧ በታላቅ ሐዘን ተሰበረ፥ ወዳጁ ቅዱስ ዮሐንስም፥ ፍጹም ለቅሶን አለቀሰ፥ ቅዱሳን አንስት በዋይታ ዋሉት። ማቴ ፳፯፥፩ ማር ፲፭ ፥፩ ሉቃ ፳፫፥፩ ዮሐ ፲፱፥፩ ለኛ ለኃጢኣን ሲል ይህን ሁሉ መከራ የተቀበለ አምላካችን ስለ አሥራ ሦስቱ ሕማማት፥ አምስቱ ቅንዋተ፥ ስለ ቅዱስ መስቀሉ፥ ስለ ድንግል እናቱ ለቅሶ፥ ስለ ወዳጁ ቅዱስ ዮሐንስ ብሎ ይማረን አሜን። ምንጭ ፦ ስንክሳር መጋቢት 27 ቅዳሴ ዮሐንስ አፈወርቅ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! መልካም ዕለተ ሰንበት! ✍️Youtube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu

ሰራዊተ መላእክቲሁ ለመድኃኔዓለም እንኳን ለመድኃኔዓለም ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion/video/7298398944680250
ሰራዊተ መላእክቲሁ ለመድኃኔዓለም እንኳን ለመድኃኔዓለም ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion/video/7298398944680250666?is_from_webapp=1&sender_device=pc&web_id=7288000334784579078

ከረፋዱ 4፡00 ጀምሮ ይከታተሉ! https://youtu.be/rQFooFLKPHA

"እግዚአብሔር ቸር እንደሆነ ቅመሱ እዩም፤ በእርሱ የሚታመን ሰው ምስጉን ነው።" መዝ 33፡8 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! መልካም ዕለተ ሰ
"እግዚአብሔር ቸር እንደሆነ ቅመሱ እዩም፤ በእርሱ የሚታመን ሰው ምስጉን ነው።" መዝ 33፡8 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! መልካም ዕለተ ሰንበት! ✍️Youtube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu

"በፈተና የሚጸና ሰው የተባረከ ነው፤ ከተፈተነ በኋላ ለሚወዱት ተስፋ ስለ እርሱ የሰጣቸውን የሕይወትን አክሊል ይቀበላልና።" ያዕ 1፡12 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራ
"በፈተና የሚጸና ሰው የተባረከ ነው፤ ከተፈተነ በኋላ ለሚወዱት ተስፋ ስለ እርሱ የሰጣቸውን የሕይወትን አክሊል ይቀበላልና።" ያዕ 1፡12 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! ✍️Youtube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu

"ምስክሮችህ ድንቆች ናቸው፤ ስለዚህ ነፍሴ ፈለገቻቸው!" መዝ 118፡119 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! ✍️Youtube 👇 https://w
"ምስክሮችህ ድንቆች ናቸው፤ ስለዚህ ነፍሴ ፈለገቻቸው!" መዝ 118፡119 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! ✍️Youtube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu