የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU 的分析概览
频道 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 14 430 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 6 084,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 336 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 14 430 名订阅者。
根据 27 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 543,过去 24 小时变化为 21,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 36.43%。内容发布后 24 小时内通常能获得 N/A% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 252 次浏览,首日通常累积 0 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 33。
📝 描述与内容策略
尚未提供频道描述。
凭借高频更新(最新数据采集于 28 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
14 430
订阅者
+2124 小时
+1247 天
+54330 天
帖子存档
"የኢትዮጵያ ድንኳኖች ሲጨነቁ አየሁ፤ የምድያም አገር መጋረጃዎች ተንቀጠቀጡ።" ዕምባ 3፡7
የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ።
ሰናይ ሌሊት!
✍️Youtube 👇
https://www.youtube.com/@eotc-gssu
የቀያፋ ንግግር ሊቀ ካህናት ነውና ከልቡ አምኖበት በመንፈስ ቅዱስ በታደሰ አእምሮው አይደለም የእርሱ ሹመት በዚያን ዓመት ነውና የበለዓምን አህያ የሆሳዕናን ድንጋዮች በተዓምራት እንዳናገረ እግዚአብሔር በተአምራት አናገረው እንጂ። አንድም በአእምሮ ጠባይዕ አውቆ አይደለም በሹመቱ አድሮ ያለ ሀብት አናገረው እንጂ ይህም ማለት እግዚአብሔር በሳዖል አድሮ ሠላሳ ስምንት ዘመን የመንግሥት ሥራ እንደ ሠራ በኃጥዕ ቄስ አድሮ ሥጋውን ደሙን እንዲለውጥ በቀያፋ አድሮ ተናገረ።
የቀያፋ ንግግር ኢየሱስ ክርስቶስ ለህዝብ ሁሉ ቤዛ ሆኖ ይሞት ዘንድ መምጣቱን ነገር ግን ቤዛነቱ ለሕዝብ ብቻ አለመሆኑ በኃጢአት በጣዖት የተበተኑ አህዛብንም አንድ ያደርጋቸው ዘንድ መሆኑን የሚያስረዳ ነው። እዚህ ጋር ሕዝብና አህዛብ አንድ የሆኑማ በሃይማኖት አይደለምን? ቢሉት ሞቱ ያለ ሃይማኖቱ ሃይማኖት ያለ ሞቱ አይሆንምና እንዲህ አለ እንጂ አንድ የሆኑት በሃይማኖት ነው።
ይቆየን
ሚኪያስ ግዛቸው
ጥቅምት 2016
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
✍️YouTube 👇
https://www.youtube.com/@eotc-gssu
✍️ FaceBook 👇
https://www.facebook.com/EOTC.GSSU
✍️Telegram 👇
https://t.me/EOTCNSSU
✍️Website👇
https://eotc-gssu.org/a/
✍️Tiktok👇
https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion
"ከራስ ያልሆነን በራስ አንደበት መናገር"
መነሻ ጥቅስ፦ "ይህንንም የተናገረ ከራሱ አይደለም" ዮሐ 11፥51
አንደበት መልዕክት ማስተላለፊያ መሳርያ ነው። ከአንደበት የሚወጣ ንግግር ጥንስሱ ልብ ነው። በልባችን ያሰብነው ሐሳብ አካል ነስቶ የሚገለጠው በአንደበት ነው። ልብ ደግሞ ክፉም ያስብ ደግ ምድራዊም ያስብ ሰማያዊ የልብ ሐሳብ በአንደበት ቢሉ በተግባር የተገለጠ ነው። እንዲህ ስንል ግን የልብ ሐሳብ ሁሉ የተገለጠ ነው አያሰኝም በልብ ተሰውሮ የሚኖር ግዘፍ ያልነሳ የተሰወረ እግዚአብሔርና የሰወረው አካል ብቻ የሚያውቁት ጊዜና ሰዓቱን የሚጠብቅ አንዳች ሐሳብ (ፈቃድ) መኖሩን ልብ ልንል ይገባል።
ሰው የሚናገረው ሁሉ ከራሱ ነወይ? የሚለው ጥያቄ ብዙዎችን የሚያከራክር ነው። ከራስ ቁጥጥር ውጪ በራስ አንደበት ቃላትን ሊያወጣ ሊናገር ይችላልና። ይህም በተለያየ አጋጣሚ ሊፈጸም የሚችል ነው።
አንባቢ ሆይ፦ የምንናገረውን ሁሉ እናውቅ ይሆንን? የምንናገረውስ በራሳችን ፈቃድና ሀሳብ ነውን? ከራሳችን ያልሆነ፣ ይህን ከየት አመጣሁት ብለን የተገረምንበት እንዲሁ ይህን ለምንና እንዴት ተናገርሁ ብለን የተቆጨንበት ንግግር የለምን?
በአንድም በሌላም መንገድ በተለያዩ አጋጣሚዎች ለራሳችን እስኪገርመን ድረስ ከራስ ያልሆነን ንግግር በራሳችን አንደበት ስንናገር እንደመጣን ይህ እንዴት ይሆናል? በዚ ጽሑፍ ከማስረጃ ጋር በጥቂቱ እንመለከታለን።
⓵ በዲያብሎስ ግፊት (አንደበታችንንና መላ አካላችንን ሲቆጣጠር፦
ይኸ ከእኛ ፈቃድ ውጪ የሚከወን ለሰው እንጂ ለራሳችን በማይታወቀን መልኩ ሊፈፀም ይችላል ። ከቀድሞ ማንነታችንን ከመታወቂያ ጠባያችን ባፈነገጠ መልኩ ሌላ ማንነትን የሚያላብስ በሰዎች እንድንጠላ የሚያደርገን ይሆናል። ዲያቢሎስ በእባብ ሰውነት ቢዋሐድና መላ ነውነቷን ቢቆጣጠር በአዳም ፊት ቀድሞ ታሳየው ከነበረው በፊቱም ትናገረው ከነበረው ንግግር በተለየ እፀ በለስን ስለመከልከላቸው "ከእርስዋ በበላችሁ ቀን ዓይኖቻችሁ እንዲከፈቱ እንደ እግዚአብሔርም መልካምንና ክፉን የምታውቁ እንድትሆኑ እግዚአብሔር ስለሚያውቅ ነው እንጂ። በማለት አዲስ ቃልን ወይም ሐሳብን አቀረበች" ዘፍ 3 ፥5 ይኽ ንግግር መልካም የሚመስል በውስጡ ግን መርዝ ያለበት ንግግር ነበር። ምንም እንኳ መጽሐፍ " እባብም እግዚአብሔር አምላክ ከፈጠረው ከምድር አውሬ ሁሉ ይልቅ ተንኰለኛ ነበረ" ዘፍ 3 : 1 ቢልም እባብ ይህንን ግን ትናገር የነበረች ከራስዋ አልነበረም።
ዛሬም በዲያብሎስ አሽክላ የተያዙ መላ ሰውነታቸውን የተቆጣጠራቸው ምን እንደሚያደርጉና እንዳደረጉ የማያውቁ ከአንደበታቸውም ምን እንደወጣና እንደሚወጣ የማያስታውሱ፣ እውነትነት የሌለው ከራሳቸው (ከቀልባቸው ማለትም ከአእምሮአቸው) ያልሆኑ አሉ።
እንዲህ አይነቱን (ከዲያብሎስ የሆነ) ጥቅም የለሽ ንግግር ጆሮ ሰጥተው ሊሰሙት ፍሬ አገኝበታለሁ በማለት ወደ ልብ ሊያስገቡት የማይገባ ነው።
ሌላው በመጽሐፍ ቅዱስም እንደሰፈረልን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ጴጥሮስን ብፁዕ ብሎ የማሰርና የመፍታት ሥልጣንን ከሰጠው በኋላ ወደ ኢየሩሳሌም ሊሄድና መከራን ሊቀበል ሊሞትም ከሙታንም እንደሚነሳ በተናገረ ግዜ ቅዱስ ጴጥሮስ እሞታለሁ ማለቱን ሰምቶ አይሁንብህ ብሎ ገሰጸው። ክርስቶስ ግን "ዘወር ብሎ ጴጥሮስን፦ ወደ ኋላዬ ሂድ፥ አንተ ሰይጣን፤ የሰውን እንጂ የእግዚአብሔርን አታስብምና ዕንቅፋት ሆነህብኛል አለው።" ማቴ16 : 23
ይህ የቅዱስ ጴጥሮስ ንግግር መልካም ቢመስልም ከእርሱ አንጻር የተናገረ ነብያትንና ትንቢታቸውን ሐሰተኛ ለማድረግ የሚሻ ምዕመናን እንዲድኑ የማይፈልግ ዲያቢሎስ ነውና በእርሱ አንጻር ዲያቢሎስን ሂድ ከዚህ አለ። ከብፅአት ወደ ተግሳፅ በአንድ ግዜ ተመልሶ ሂድ ማለቱ እንደ ግዜ ግብሩ የሚፈርድ አምላክ ስለሆነ ነው። ቅዱስ ጴጥሮስ እንደ ጊዜ ፍርዱ ብፁዕ አለው ከዚያም እንደ ግዜ ግብሩ ሰይጣን አለው።
⓶ በስሜታዊነት
ራስን ባለመግዛት ጦስ ሰው በአንድም በሌላም መንገድ ከራሱ ያልሆነ ( ለማን ለምን ምን የሚሉትን ጉዳዮች አስቦበት ጥቅምና ጉዳቱን መዝኖ፣ የንግግሩን ፍሬ ሐሳብ ለይቶ ከአንደበቱ ያላወጣው) በቅጽበታዊ ሀዘን ወይ ንዴት አልያም ደስታ ባለ ስሜታዊነት ውስጥ ሆኖ የሚናገረው ያ ንግግር ለብዙዎች ስብራትና ቀቢፀ ተስፋ ምክንያት ሊሆን ይችላል። እንዲህ አይነቱ ንግግር ለሰው ብቻ ሳይሆን ከስሜታዊነት ርቀው በሰከነ ልቦና ሆነው ወደ ኋላ ባጤኑት ጊዜ ራስንም ለታላቅ ፀፀት የሚዳርግ ነው። ከራስ (ከልብ መክረው አስበው) የተናገሩት አይደለምና።
እንደ ክርስቲያን ራሳችንን ከእንዲህ ዓይነት ስሜታዊነት ልናርቅ በአንደበታችንም እንዳገኘን ከመናገር ልንገታ ይገባል። ምክንያቱም የአምልኮ መገለጫ አይደለምና። መጽሐፍ " አንደበቱን ሳይገታ ልቡን እያሳተ እግዚአብሔርን የሚያመልክ የሚመስለው ማንም ቢኖር የእርሱ አምልኮ ከንቱ ነው።" ያዕ 1 : 26 እንዲል።
ነገረ ክርስቶስን በማስተማሩ ቅዱስ ጳውሎስና ትምህርቱ ላይ "ጳውሎስ ሆይ አብደሃል እኮ ብዙ ትምህርትህ ወደ እብደት ያዞርሃል" በማለት ለተናገረ ፊስጦስ ለተባለው ሰው ቅዱስ ጳውሎስ በፍፁም ትህትና አገልግሎቱና ትምህርቱ ከስሜታዊነት የራቀ እውነት ላይ የተመሠረተ እንደሆነ ምላሽን ሲሰጥ " ክቡር ፊስጦስ ሆይ፥ የእውነትንና የአእምሮን ነገር እናገራለሁ እንጂ እብደትስ የለብኝም።" ሐዋ26 : 25 ብሎታል።
⓷ በተአምራት
መጽሐፍ "እግዚአብሔር በአንድ መንገድ በሌላም ይናገራል፤ ሰው ግን አያስተውልም" ኢዮብ 33 : 14 እንዲል እግዚአብሔር ለሰው ልጆች መልዕክትን ማስተላለፍ ሲሻ የተለያዩ መንገዶችን ይጠቀማል። ከነዚህም መካከል ገቢረ ተአምራት ዋነኞቹ ናቸው። በለዓምን ለማስተማር የአህያይቱን አፍ ከፍቶ ከራሷ ያልሆነን ቃል እንድትናገር በማድረግ መልዕክትን እንድትናገር ያደረገ እግዚአብሔር ነው። ዘኁልቅ 22፥28 አህያይቱ ከራሷ ያልሆነ መልዕክቱ ብቻ አይደለም በሰው ልሳን መናገሯም ጭምር መሆኑን ልብ እንበል።
በሐዲስ ኪዳንም ቢሆን በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ በክፉ ቅንዓት የታወሩ አይሁድ በሆሳዕና ሕፃናት ስለክብሩ ሲዘምሩለት ሰምተው ስለ አምላክነቱም ዘንባባን ሲያነጥፉለት ተመልክተው ሕፃናቱን ዝም እንዲያሰኙ በተናገሩ ግዜ " እነዚህ ዝም ቢሉ ድንጋዮች ያመሰግኑኛል" ያለው ቃል ተፈጽሞ አንደበት የሌላቸው ግዑዛኑ አዕባን ማመስገናቸው ገቢረ ተአምራቱን የሚያሳይ ነው። ሉቃ 19፥40 የአዕባን መናገር የራስ የማያሰኘው መልዕክቱ ብቻ ሳይሆን ከተፈጥሮ ባሕርይ ውጭ መሆኑ ነው።
ከሰውም ወገን ቢሆን ሰዎችን ሊያናግር መልዕክትንም ሊያስተላልፍ እንደሚቻለው በተግባር ያየነው ጉዳይ ነው። በአልዐዛር ከሞት መነሳት ያጉረመረሙት የካህናት አለቆችና ፈሪሳውያን እንዲሁ ብንተወው ሁሉ በእርሱ ያምናሉ፤ የሮሜም ሰዎች መጥተው አገራችንን ወገናችንንም ይወስዳሉ የሚል ፓለቲካዊ ምክንያት አቅርበው ዮሐ 11 : 48 ምን እናድርግ? ብለው ሸንጎ ሰበሰቡ። ከእነርሱም መሀከል ሹመቱ በዚያን ወራት የሆነ ቀያፋ የተባለ ሰው " ሕዝቡም ሁሉ ከሚጠፋ አንድ ሰው ስለ ሕዝቡ ይሞት ዘንድ እንዲሻለን አታስቡም" በማለት ምክርን አቀረበላቸው። ነገር ግን " ይህንም የተናገረ ከራሱ አይደለም፥ ነገር ግን በዚያች ዓመት ሊቀ ካህናት ነበረና ኢየሱስ ስለ ሕዝቡ ሊሞት እንዳለው ትንቢት ተናገረ፤" ዮሐ11 : 51
"ይህ ስፍራ የእግዚአብሔር ቤት ነው እንጂ ሌላ አይደለም፤ ይህም የሰማይ ደጅ ነው።" ዘፍ 28፡17
የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ።
ሰናይ ሌሊት!
✍️Youtube 👇
https://www.youtube.com/@eotc-gssu
ክርስትና ከዘውግ ባሻገር የሆነ ማንነት
የሰው ልጅ ሁሉ ከአዳም የተገኘ የእግዚአብሔር አምላክ የእጅ ሥራ ነውና ከላይ በቀለም በቅርፅ ወዘተ ልዩነት ቢኖረው እንኳ የሚመሳሰልበት ከውስጥ የሆነ ሥነ-ሕይወታዊ አንድነት አለው፡፡ ይህም ተመሳሳይ ተፈጥሮአዊ እና ሥነ ልቡናዊ (Bio-Psychic Union) ውቁር እንዲኖረው አድርጓል፡፡ በማኅበራዊ ፍጡርነቱ በፈጠረው በማኅበራዊ መስተጋብሩ ምክንያት ደግሞ በሒደት ራሱን ካንድ የባህል መሠረት ካለው ማንነት ጋር ያዛምዳል፡፡ ይህ ልዩነት ደግሞ የተለያየ አስተሳሰብ/ እና የአረዳድ አድማስ እንዲኖረው ያደርገዋል፡፡ ክርስትና ለነፍሳችን መድኅን የሆነው የእውነትና የሕይወት መንገድ ጌታችን መድኃኒታችን ክርስቶስ ኢየሱስ ብቻ መሆኑን ያስተምራል፡፡ ክርስቲያንም ይህን እውነት ብቻ ይከተላል፡፡ ከአምልኮ መልስ ባለው ማኅበራዊ መስተጋብር ግን ብዝኃነትን ያከብራል፡፡
ማንበብ ይቀጥሉ...
👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://eotc-gssu.org/a/ክርስትና-ከዘውግ-ባሻገር-የሆነ-ማንነት/
ክርስትና ከዘውግ ባሻገር የሆነ ማንነት
የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
✍️YouTube 👇
https://www.youtube.com/@eotc-gssu
✍️ FaceBook 👇
https://www.facebook.com/EOTC.GSSU
✍️Telegram 👇
https://t.me/EOTCNSSU
✍️Website👇
https://eotc-gssu.org/a/
✍️Tiktok👇
https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion
እንኳን ለመድኃኔዓለም ዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ።
መድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ራሱን አሳልፎ በመስጠት ለዓለም መድኃኒት የሆነው መጋቢት 27 በዕለተ ዓርብ መኾኑ የታወቀ ነው፡፡ (ይህም ዕለት የስቅለት በዓል ነው፡፡ መጋቢት 27 ጥንተ ስቅለት ነው፡፡ መጋቢት 29 ደግሞ ጌታ የተነሣበት በመሆኑ ጥንተ ትንሣኤ ነው፡፡) በዚህም የተነሣ ምንም እንኳን ዓመታዊው ዋናው በዓል መጋቢት 27 ቢሆንም ወር በገባ በ27 መድኃኔዓለምን እንዘክራለን፡፡
ጥቅምት 27 ዓመታዊ በዓል ሆኖ የሚከበርበት ምክንያት ሁለት እንደ ኾነ ትውፊታችን ይመሰክራል። የመጀመሪያው ምክንያት መጋቢት 27 ዐቢይ ጾም ከሚውልባቸው ቀናት አንዱ በመሆኑና በዐቢይ ጾም ደግሞ ዐበይት በዓላትን በድምቀት ለማክበር ወቅቱ የማይፈቅድ ስለሆነ ከአባ መብዓ ጽዮን መታሰቢያ በዓል ጋር በጥቅምት 27 እንዲከበር አባቶች ቀኖና በመሥራታቸው ነው፡፡
ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ የመድኃኔዓለምና የኪዳነምህረት ወዳጅ አባ መብዓ ጽዮን የሚታሰቡበት ዕለት ጥቅምት 27 በመኾኑ ነው። ጨለማን ያሳደደው ብርሃን፥ ዓለምን ሁሉ ያበራው ፋና ፥የማይናወጥ መሠረት ፥የማይፈርስ ግንብ ፤የማይሰበር መርከብ ፥የማይሰረቅ ማህደር፤ ያማረ ቀንበር፥ የቀለለ ሸክም፥ ለአባቱ ኃይሉ ጥበቡም የሚሆን እርሱ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። እንዳለ ቅዳሴ ወልደ ነጎድጓድ ጌታችን መድኃኔዓለም ለኛ ሲል በፈጸመው፥ የማዳን ሥራ ክፉዎች አይሁዶች ፥ከምሽቱ ሦስት ስዓት በጌቴሴማኔ፥ ውስጥ ሁሉን የያዘውን ያዙት ፤ሁሉን የሚገዛውን አሰሩት የሕያው አምላክ ልጅን አሰሩት ፤በቁጣ ጎተቱት በፍቅር ተከተላቸው፤ በሚሸልቱት ፊት እንደማይናገር እንደ የዋኅ በግ ከኋላቸው እየተከተለ ወሰዱት። ቅዳሴ ዮሐንስ አፈወርቅ ቁ፦፵፮ እንዳለ ሌሊቱን ሙሉ ከቀያፋ ወደ ሃና፥ ከሃና ወደ ቀያፋ ስያመላልሱት ፤አስረውት ሲደበድቡት አድረዋል፥ ሊቃነ መላእክት በመፍራትና በመንቀጥቀጥ በፊቱ የሚቆሙለትን በአደባባይ አቆሙት ፤ ኃጢኣትን ይቅር የሚለውን ኃጥእ አሉት ፥በመኳንንት የሚፈርደውን እርሱን ፈረዱበት ። ቅ/ዮ/አፈ ቁ፦ ፵፯ እንዲል እርሱ ዝም ሲላቸው አይኑን ሸፍነው በጥፊ መቱት፤ ርኲስ ምራቃቸውን ተፉበት፤ ራሱንም በዘንግ መቱት እርሱ ግን ሁሉንም ታገሰ፤ በጠዋቱ ሞት እንድፈረድበት፤ ከገዢው ዘንድ አቀረቡት በሦስት ስዓት አካሉ እስኪያልቅ ድረስ ስድስት ሺህ ስድስት መቶ ስድሳ ስድስት ጊዜ ገረፉት፤ ሊጦስጥራ አደባባይ ላይ እርጥብ መስቀል አሸክመው ወደ ቀራንዮ ወሰዱት፤ በቀትር ስድስት ስዓት ላይ በአምስት ረዣዥም ችንካሮች ቸንክረው ሰቀሉት፤ በዚያች ሰዓት ሰባት ታላላቅ ተዓምራት በምድርም በሰማይም ታዩ፤ በባሕርይ ሥልጣኑ ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት ቅድስት ነፍሱን ከሥጋው ለየ፤ በዚያች ሰዓት ወደ ሲዖል ወርዶ የታሰሩትን ነፍሳት ፈታቸው አሥራ አንድ ሰዓት ደጋጎች ዮሴፍና ኒቆድሞስ ከመስቀል አውርደው በአዲስ መቃብር ቀበሩት፤ በዚያች ቀን ድንግል ማርያም ልቧ በታላቅ ሐዘን ተሰበረ፥ ወዳጁ ቅዱስ ዮሐንስም፥ ፍጹም ለቅሶን አለቀሰ፥ ቅዱሳን አንስት በዋይታ ዋሉት።
ማቴ ፳፯፥፩ ማር ፲፭ ፥፩ ሉቃ ፳፫፥፩ ዮሐ ፲፱፥፩ ለኛ ለኃጢኣን ሲል ይህን ሁሉ መከራ የተቀበለ አምላካችን ስለ አሥራ ሦስቱ ሕማማት፥ አምስቱ ቅንዋተ፥ ስለ ቅዱስ መስቀሉ፥ ስለ ድንግል እናቱ ለቅሶ፥ ስለ ወዳጁ ቅዱስ ዮሐንስ ብሎ ይማረን አሜን።
ምንጭ ፦ ስንክሳር መጋቢት 27
ቅዳሴ ዮሐንስ አፈወርቅ
የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ።
ሰናይ ሌሊት! መልካም ዕለተ ሰንበት!
✍️Youtube 👇
https://www.youtube.com/@eotc-gssu
ሰራዊተ መላእክቲሁ ለመድኃኔዓለም
እንኳን ለመድኃኔዓለም ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion/video/7298398944680250666?is_from_webapp=1&sender_device=pc&web_id=7288000334784579078
"እግዚአብሔር ቸር እንደሆነ ቅመሱ እዩም፤ በእርሱ የሚታመን ሰው ምስጉን ነው።" መዝ 33፡8
የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ።
ሰናይ ሌሊት! መልካም ዕለተ ሰንበት!
✍️Youtube 👇
https://www.youtube.com/@eotc-gssu
"በፈተና የሚጸና ሰው የተባረከ ነው፤ ከተፈተነ በኋላ ለሚወዱት ተስፋ ስለ እርሱ የሰጣቸውን የሕይወትን አክሊል ይቀበላልና።" ያዕ 1፡12
የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ።
ሰናይ ሌሊት!
✍️Youtube 👇
https://www.youtube.com/@eotc-gssu
"ምስክሮችህ ድንቆች ናቸው፤ ስለዚህ ነፍሴ ፈለገቻቸው!" መዝ 118፡119
የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ።
ሰናይ ሌሊት!
✍️Youtube 👇
https://www.youtube.com/@eotc-gssu
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
