ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem
Відкрити в Telegram
የዘመናችንን ቀለም ያሳያሉ ያልናቸውን የዚህ ትውልድ የስነ ግጥም ውጤቶችን እንጋራ - እናጋራ። ለማካፈል የፈለጋችሁትን በGitem_Sitem ፣ gitemsitem@gmail.com የጸሃፊ ስም እና ርዕስ አክላችሁ ላኩልን። We are all about sharing this generation's poetry. Please email us your pieces gitemsitem@gmail.com
Показати більше1 719
Підписники
-224 години
-77 днів
-1830 день
Архів дописів
የሁለተኛው የአፍሪካ የግጥም ግጥሚያ ሁለተኛ ዙር ውድድር ቅዳሜ ሐምሌ 17 ቀን 2013 ዓ.ም ከ 9፡00 ጀምሮ በኦንላይን ይካሄዳል፡፡
በመጀመሪያው ዙር ከየምድቦቻቸው ያሸነፉ አራት ሀገራት … በአጠቃላይ 16 ሀገራት በዚህ ዙር ይፋለማሉ!
እስታሁን 12 ሀገራትን ለይተን አውቀናል፡፡ ቀሪዎቹን አራት ሀገራት (ኢትዮጵያ ከምትወዳደርበት ምድብ) ዓርብ ላይ እናውቃለን፡፡
በ GUAC-ON ሬስቶራንት ደመቅ አድርገን እንጠብቃችኋለን! ብቅ ብቅ በሉና አበረን እንከታተል፡
The second round of the African Cup of Slam Poetry Competition will be held online on Saturday, July 24, 2013 starting at 3፡00 pm.
Four countries from each group on the first round, 16 countries will battle in this second round!
So far, we have 12 countries secured their spot on this round. The remaining four will be identified on Friday at the final group of the first rounds.
Join us at GUAC-ON for a viewing party and closing celebration of the virtual rounds of the second edition of the African Cup of Slam Poetry!
#CASP2021 #CASPEthiopia #SlamPoetry #Africa #Ethiopia
በሁለተኛው የአፍሪካ የግጥም ግጥሚያ ኢትዮጵያ የምትገኝበት የመጀመሪያው ዙር የመጨረሻ ምድብ ግጥሚያ ዓርብ ሐምሌ 16 ቀን 2013 ከምሽቱ 130 ጀምሮ መተላለፍ ይጀምራል፡፡
በሽፍታ ሬስቶራንት ሰብሰብ ብለን ሻምፒዮናችን ሰይፈ ተማምን በመጀመሪያ የውድድር ተሳትፎው እንደግፈው!
The final group of the first round matches of the second edition of the African Cup of slam poetry happens on Friday, July 23, 2013 at 1:30pm.
Join us at Shifta Restaurant for a watch party, as our champion Seife Temam performs his first performance of the competition.
#CASP2021 #CASPEthiopia #SlamPoetry #Africa #Ethiopia
የ ሁለተኛው የአፍሪካ የግጥም ግጥሚያ በሁለተኛ ቀን ምሽቱ በመጀመሪያ ምድብ የሚገኙ ሀገራት ተወካዮች ተፋልመውበት ተጠናቅቋል፡፡
በውጤቱም
Diaw Fall - ከ ሞሪታኒያ 🇲🇷- በ 70.2 ነጥብ 1ኛ ደረጃ
DJ Huba - ከ አንጎላ🇦🇴 - በ 64.5 ነጥብ 2ኛ ደረጃ
Bokon - ከ ቶጎ 🇹🇬 - በ 63 ነጥብ - 3ኛ ደረጃ
Aladin - ከ ጋቦን 🇬🇦- በ61 ነጥብ (ከ80) 4ኛ ደረጃ ን
በማግኘት ቅዳሜ ለሚደረገው ሁለተኛ ዙር ግጥሚያ ያለፉ የመጀመሪያዎቹ 4 ተወዳዳሪዎች መሆናቸውን አረጋግጠዋል፡፡
----------------
ነገ ማክሰኞ ሐምሌ 13 በተመሳሳይ ሰዓት (ማታ 2፡00) በሚቀጥለው ውድድር የመጀመሪያው ዙር ሁለተኛ ምድብ ሀገራት ተወካዮች ይፋለማሉ፡፡
በዚህ ምድብ ናይጄሪያ ፣ ቻድ ፣ ሞሪሺየስ ፣ ኬንያ ፣ ሴኔጋል ፣ ካሜሩን ፣ ጋና እና ጊኒ ቢሳው ይገኛሉ፡፡ እነዚህ ሀገራት ያላቸውን ረጅም የግጥም ግጥሚያ ልምድ እና ባህል (poetry slam culture) ስናይ … ነገ ጠንከር ያለ ውድድር የሚታይበት ምሽት እንደሚሆን እንጠብቃለን!
በፌስቡክ ቀጥታ በመግባት ውድድሩን እንድትከታተሉ እንጋብዛለን!
#casp2021 #CaspEthiopia #slampoetry #Africa #Ethiopia Coupe d'Afrique de Slam poésie, CASP
የመክፈቻው ቀን ደስ በሚል ሁኔታ ተጠናቅቋል፡፡
የ33 የአፍሪካ ሀገራት ሻምፒዮኖች ይሳተፉበታል፡፡
ከነገ ጀምሮ የሚጀምረው ውድድር ቅደም ተከተል ምድብም ዕጣ ወጥቶ ነበር፡፡
ሻምፒዮናችን Seife Temam 9 ሀገራት ባሉበት የመጨረሻው ቀን ምድብ የደረሰው ሲሆን የመጀመሪያ ውድድሩን አርብ ዕለት ያደርጋል፡፡
ደቡብ ሱዳን ፣ ሞሮኮ ፣ ሞዛምቢክ ፣ ኬፕቬርድ ፣ ማዳጋስካር ፣ ማላዊ ፣ ኒጀር እና ቡሩንዲ በዚህ ምድብ ይገኛሉ፡፡
ቻድ ላይ በተደረገው የመጀመሪያው ውድድር ላይ አሸናፊ ሻምፒዮን የነበረው እና በሞት ያጣነው ሴኔጋላዊው አልፋሩቅ ም ታስቦ ነበር፡፡
________
ውድድሩ ነገ ከምሽቱ 2፡00 ሰዓት ላይ ይጀምራል፡፡ በፌስቡክ ቀጥታ በመግባት እንድትከታተሉን እንጋብዛለን፡፡
በአካል መገኘት የምንችል ደግሞ ቀጥታ ስርጭታችንን ከሽፍታ ነውና የምናደርገው ብቅ ብላችሁ ደመቅ ደመቅ እናድርገው!
Coupe d'Afrique de Slam poésie, CASP Gitem Sitem - ግጥም ሲጥም #casp2021 #CaspEthiopia #slampoetry #Africa #Ethiopia
ሁለተኛው የአፍሪካ የግጥም ግጥሚያ የመጀመሪያ ዙር ከሰኞ ሐምሌ 12 እስከ ቅዳሜ ሐምሌ 17 ድረስ በኦንላይን ይካሔዳል።
ሀገራችንም በድንቅ ልጃችን "ሰይፈ ተማም" ትወከላለች!
#CASP #CupOfAfricanSlamPoetry #CASP2021 #CASPEthiopia
አዝኛለሁ…
በልፋቴ በድካሜ ባቆየሁት
ሳቃችንን‐ ተንከርፍፎ ስላየሁት!
አዝኛለሁ…
ለተዝካሩ ለሙሾው ድንኳን ተክሎ እንዳይወጣ
ዕድሜያችን‐የኩርፊያ እንኳን ትዝታ ቢያጣ።
የደስታ የፈገግታ አሻራ ባናስቀር ደርሰን
እንዴት
በባዶ እንዲያው ዝም ብሎ ያለ እድሜው፣ እድሜ ያፍርሰን!
አዝኛለሁ…
ቀና ችን‐ቀን ሳለ ሳይዳምን ፀሐይ ባይወጣበት
እንደሌላው እለት ወዝ ስለታጣበት።
ፀሐይ ያጣ ተብሎ ቀን አይሰረዝም
እድሜ ላይ ይጫናል ታሪክ እንዲያስረዝም።
ሕይወታችን‐ድግሱ ውብ ነበር
እንኳን ቁም ነገሩ ዋዛና ለበጣው
አዝኛለሁ…
ከተነሳንበት ተመልሰን ሄደን ፈልገን ስናጣው።
©️ያዴል ትዕዛዙ
Live Painting & Poetry Night
Gojo Bar presents you a live painting and poetry night along with other entertainments. The show will be hosted by Gitem Sitem's co-host Seife Temam.
Saturday, July 17
7PM - 8PM
Hill Bottom Recreation Center
Entrance fee is ETB 100.
#July_17_21 https://t.me/Kunet_Sitem
#Gojo_Bar #poetry #livepainting #gitemsitem #seifetemam #Hill_bottom
ቀድሼ ላግባሽ
እምነ በሃ ቅድስት ቤተክርስቲያን
,.... ወስዕልት በእንቆጳዝዮን
በሚለው ቃል ዜማ ስርአት መልሼ
እባክሽን ላግባሽ ራሴው ቀድሼ:
ተንስኡ እያልኩኝ በቅድስቱ ስፍራ
በቀኖናው ድርስት ከእግዜሩ ጋር ላውራ
በሚፈተትበት የቁርባኑ መና
ከልቤ ላመስግን የግሌ ሁኚና
የልቤ ህዋሶች በእንግዳ ስሜት
በፍሰሐ ሰክረው በተመስጦ ስሌት
በምስጋና ድምፀት የማወጣው ዜማ
የጠለቀ እንዲሆን ከሰማይ ደመና
ነጠላ አጣፍተሽ አክሊሉንም ደፍተሽ
ህግሽን ጠብቀሽ ክብርን ተጎናፅፈሽ
ካባውን ደርበን በእምነት ኪዳን ጥላ
በፈገግታ ልይሽ የግሌ ሁኚና
የኔታ የሰጡኝ የወንጌሉ በፍታ
ጠንክሮ እንዲፀና ፍፁም ሳይረታ
በግዕዝ ባራራይ ስርአት መልሼ
'እባክሽን ላግባሽ ራሴው ቀድሼ!
የህይወቴን ምስጢር የኑሮዬን ድርሳን
ልቤን ገልጩልሽ እያዜምኩኝ ምልጣን
በክርስትናሽ ስም ፀሎትን አድርሼ
የእለቱን ምስባክ ስንክሳር ከልሼ
እባክሽን ላግባሽ ራሴው ቀድሼ!
የተላለፍኩትን የኃጢአት ደዌ
በንስሐ ስሽር በገሐድ ነነዌ
የፈጣሪ ምሕረት ላንቺም እንዲመጣ
በተክሊል ሱባዔ ከበደሌ ልንጣ
አዎ የኔ መውደድ አንቺም ተለመኚ
ገነትም ቀላል ናት ብቻ ከኔ ሁኚ!
አንድም ለኔ ፅናት አንድም ላንቺ ጸጋ
ቃልሽን ሸልሚኝ ልቤ ባንቺ ይርጋ።
ውዴ
ስብሐት ለአብ ብዬ ሠራዊት ዘልቄ
በሐሴት ሰክሬ በደስታ ጠልቄ
ተክህኖ ለብሼ ስርአት መልሼ
እባክሽን ላግባሽ ራሴው ቀድሼ!
©️ዳዊት ጥዑማይ
@jawithpoetdeva
2/9/2013
https://t.me/GitemSitem
የግጥም መጽሐፍ ምረቃ
ርእስ፦ ርእስ የለውም
ገጣሚ፦ ኤልያስ ሽታሁን
በጥዑም ግጥሞቹ እና ግሩም ለዛ ባለው አቀራረቡ በርካታ መድረኮች ላይ የምታውቁትና የምትወዱት ኤልያስ ሽታኹን 'ርእስ የለውም' በሚል ርእስ የመጀመሪያ መጽሐፉን ለንባብ አብቅቷል።
ቦታ፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቲያትር
ቀን፦ ሐምሌ 5
ሰዓት፦ 11 ሰዓት
አዘጋጅ፦ ሰምና ወርቅ
#ኤልያስ_ሽታኹን #ርእስ_የለውም #ሰምናወርቅ
https://t.me/GitemSitem
መኖር
ሲገፉህ ተገፍተህ
ሲያገኙ ሲረሡህ
ስታገኝ ሲመጡ አንድ ያለህን ሠጥተህ።!
ሀዘን ለቅሷቸውን ወደ አን እያጋቡ አንተን ሲያስለቅሡ
ሀዘናቸው ወስዶህ ቀና ሳትል አንተ ሀሴት ነው ለነሡ።
ላጣ ለተጎዳ
ላገኘ ከበርቴ በዲናሩ ብዛት ለሚበላ ፍዳ
ለሁሉም ሠው ሆነህ
ያለህን ትልቁን ክቡር ጊዜ ሠጥተህ
ምንም እንደማይሠጥ እንደ ንፉግ ታይተህ
ማንም ካንተ ሳይሆን አንተ ለሠው ሆነህ
ከማንም ሳጠብቅ ሁሌም እየሠጠህ
መኖር በመኖር ታስተምረኛለህ።
እንዲህ ቃል የሚሆን ነፍስ ያለው አንድ እውነት
እንኳን ካጠገብህ ከየትስ ይገኛል ቢፈለግ ካለበት።
ፈልጎ አለመድከም አግኝቶ አለመርካት
ያው የልብን መኖር ያው የልብን መንካት።!!!
መኖር ነው አንተነት
መኖር ነው እኔነት።!!!!
©️ተስፋልደት በለጠ
https://t.me/GitemSitem
ዛሬ ለግርምት (ሰርፕራይዝ) የሽፍታው Gitem Sitem - ግጥም ሲጥም ላይ የሚገኙ በዚህ ዓመት መጽሐፍ ያሳተሙ 3 ገጣሚያን /አጣሚያን/።
የሶስቱንም ስም በትክክል ለመለሱ የመጀመሪያ 4 ሰዎች እያንዳንዳቸው የገጣሚያኑን መጽሐፍት የሚሸለሙ ይሆናል።
በነገራችሁ ላይ የመግብያ ባናስከፍልም መጽሐፍ እንድትገዙ ልንጨቀጭቃችሁ እንችላለን።
PS: We love you
Come join Poetic Saturdays at GUAC-ON in Hayahulet this coming Saturday, July 10 2021!
https://www.facebook.com/guaconaddis
Entrance: 100 ETB (includes free Arada)
Please note that this event is 21 and over only.
As usual, we will start registration at 2: 00 pm.
Only perform YOUR ORIGINAL work. The audience is there to listen to your truth!
Each performer gets 5 minutes total. You can perform as many times but respect the time limit.
All languages welcome.
All performance art forms welcome!
We are excited our audiences and honored our performing family is growing. So come by and witness the amazing talents brewing in our city.
Tell a friend!
Marumbo is a spoken word artist and poet, whose poetry is deeply rooted in the understanding of Culture, Life, Love and God. He draws deeply from life’s experiences and his observations to create well-meaning and relatable poetry that not only entertains but also educates and raises awareness for the struggles and issues of daily life. These attributes were showcased in an array of contexts in his debut EP Broken Keys and later in a poem titled Poetry in Africa more recently in an EP named ‘Conversations of a broken and mended heart’
He has featured at Lake of Stars, Likoma Festival, Tumaini Festival and Ufulu festival to name a few.
Good luck Malawi!
https://www.facebook.com/1719463041680780/posts/2630974210529654/
#marumbo_sichinga #Malawi #AfricanCupofSlamPoetry #CASP #PoeticSaturdays #poetry #poetryslam #poetrylovers #artinaddis
#AddisAbeba #JulyNovember2021
The African Cup of Slam Poetry is a source of motivation when we know that in Africa art does not feed its man, through this continental competition we encourage and support young talented artists in the art of public speaking to consider professional careers.
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
