ru
Feedback
ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem

ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem

Открыть в Telegram

የዘመናችንን ቀለም ያሳያሉ ያልናቸውን የዚህ ትውልድ የስነ ግጥም ውጤቶችን እንጋራ - እናጋራ። ለማካፈል የፈለጋችሁትን በGitem_Sitem ፣ gitemsitem@gmail.com የጸሃፊ ስም እና ርዕስ አክላችሁ ላኩልን። We are all about sharing this generation's poetry. Please email us your pieces gitemsitem@gmail.com

Больше
1 720
Подписчики
-224 часа
-47 дней
-930 день
Архив постов
Yes, that. Those days You know, Where your lungs feels like a solitary confinement with four people in it breathing over your shoulder You know, Where your eyes are sensitive to light, Any light Light coming from your phone, the window, fluorescent tubes, smiles and kind hearts You know, Where you can taste the rust against the weathering gears in your brain Where you hear others calling out your name but you have to blink hard a couple of times To make sure whether you’re falling asleep or if it’s really coming from across your table You know, Where you don’t want to get out of the taxi In fact, you didn’t want to get in, in the first place In fact, you wanted to stay in In your room your bed your mind your dream your skin You know, . . . Don’t you?

ክረምት እና ንባብ 📅 ሐምሌ 15 እስከ ነሐሴ 10 2013 📍 4ኪሎ ቱሪስት ሆቴል ጀርባ ኢክላስ ህንፃ 🙏 Siti አዘጋጁ ዋልያ ኢቨንት ሲሆን የዝግጅቱ መሪ ቃል "ንባብና ክረምት" ነው። የመጻህ
ክረምት እና ንባብ 📅 ሐምሌ 15 እስከ ነሐሴ 10 2013 📍 4ኪሎ ቱሪስት ሆቴል ጀርባ ኢክላስ ህንፃ 🙏 Siti አዘጋጁ ዋልያ ኢቨንት ሲሆን የዝግጅቱ መሪ ቃል "ንባብና ክረምት" ነው። የመጻህፍት አውደርእዩ ከሐምሌ 15 እስከ ነሐሴ 10 በሚቆይበት ጊዜ የተለያዩ መሪ ቃሉን የሚያጎሉ ዝግጅቶች በእያንዳንዱ ምሽቶች ሲካሄዱ ዋና ዋናዎቹም የሚከተሉት ናቸው _ቁጥራቸው ከአስር በላይ የሆኑ ነባርና አዳዲስ ደራስያን መጽሐፎቻቸውን ያስመርቃሉ። እንደ ደራሲ ሐይለመለኮት መዋእል ያሉ አንጋፋ ጀራስያን ልምዶቻቸውን ያካፍላሉ። ዛጎል የመጻሕፍት ባንክ ከአንባብያን የተለገሰውን መጻሕፍት ለተለያዩ ገጠርና ከተማ ለሚገኙ አስር መጻሕፍት ቤቶች ያስረክባል። ግጥሞች ለአባይ በሚል ርእስ ልዩ የስነጽሑፍ ምሽት ይደረጋል። በዚህ ዝግጅት ከነባር ገጣምያን መካከል የባለቅኔ ጸጋዬ ገብረመድሕንና ነሰይፉ መታፈርያ ፍሬው ግጥሞች አሁን ካሉት ደግሞ ዶክተር በድሉ ዋቅጅራና አንዱአለም አባተ (ያጸደ ልጅ) ይሳተፉበታል። ከቀናት መሃከል በአንዱ ወጣቱ ደራሲና የፍልስፍና ሰው መሐመድ ቡርሐን ዲስ @eventsethiopia

#መጨመሪያ
#መጨመሪያ

Follow me on Instagram! Username: gitemsitem https://www.instagram.com/gitemsitem?r=nametag
Follow me on Instagram! Username: gitemsitem https://www.instagram.com/gitemsitem?r=nametag

photo content

የሁለተኛው የአፍሪካ የግጥም ግጥሚያ ሁለተኛ ዙር ውድድር ቅዳሜ ሐምሌ 17 ቀን 2013 ዓ.ም ከ 9፡00 ጀምሮ በኦንላይን ይካሄዳል፡፡ በመጀመሪያው ዙር ከየምድቦቻቸው ያሸነፉ አራት ሀገራት … በአጠቃ
የሁለተኛው የአፍሪካ የግጥም ግጥሚያ ሁለተኛ ዙር ውድድር ቅዳሜ ሐምሌ 17 ቀን 2013 ዓ.ም ከ 9፡00 ጀምሮ በኦንላይን ይካሄዳል፡፡ በመጀመሪያው ዙር ከየምድቦቻቸው ያሸነፉ አራት ሀገራት … በአጠቃላይ 16 ሀገራት በዚህ ዙር ይፋለማሉ! እስታሁን 12 ሀገራትን ለይተን አውቀናል፡፡ ቀሪዎቹን አራት ሀገራት (ኢትዮጵያ ከምትወዳደርበት ምድብ) ዓርብ ላይ እናውቃለን፡፡ በ GUAC-ON ሬስቶራንት ደመቅ አድርገን እንጠብቃችኋለን! ብቅ ብቅ በሉና አበረን እንከታተል፡ The second round of the African Cup of Slam Poetry Competition will be held online on Saturday, July 24, 2013 starting at 3፡00 pm. Four countries from each group on the first round, 16 countries will battle in this second round! So far, we have 12 countries secured their spot on this round. The remaining four will be identified on Friday at the final group of the first rounds. Join us at GUAC-ON for a viewing party and closing celebration of the virtual rounds of the second edition of the African Cup of Slam Poetry! #CASP2021 #CASPEthiopia #SlamPoetry #Africa #Ethiopia

በሁለተኛው የአፍሪካ የግጥም ግጥሚያ ኢትዮጵያ የምትገኝበት የመጀመሪያው ዙር የመጨረሻ ምድብ ግጥሚያ ዓርብ ሐምሌ 16 ቀን 2013 ከምሽቱ 130 ጀምሮ መተላለፍ ይጀምራል፡፡ በሽፍታ ሬስቶራንት ሰብሰብ
በሁለተኛው የአፍሪካ የግጥም ግጥሚያ ኢትዮጵያ የምትገኝበት የመጀመሪያው ዙር የመጨረሻ ምድብ ግጥሚያ ዓርብ ሐምሌ 16 ቀን 2013 ከምሽቱ 130 ጀምሮ መተላለፍ ይጀምራል፡፡ በሽፍታ ሬስቶራንት ሰብሰብ ብለን ሻምፒዮናችን ሰይፈ ተማምን በመጀመሪያ የውድድር ተሳትፎው እንደግፈው! The final group of the first round matches of the second edition of the African Cup of slam poetry happens on Friday, July 23, 2013 at 1:30pm. Join us at Shifta Restaurant for a watch party, as our champion Seife Temam performs his first performance of the competition. #CASP2021 #CASPEthiopia #SlamPoetry #Africa #Ethiopia

የ ሁለተኛው የአፍሪካ የግጥም ግጥሚያ በሁለተኛ ቀን ምሽቱ በመጀመሪያ ምድብ የሚገኙ ሀገራት ተወካዮች ተፋልመውበት ተጠናቅቋል፡፡ በውጤቱም Diaw Fall - ከ ሞሪታኒያ 🇲🇷- በ 70.2 ነጥብ 1
+2
የ ሁለተኛው የአፍሪካ የግጥም ግጥሚያ በሁለተኛ ቀን ምሽቱ በመጀመሪያ ምድብ የሚገኙ ሀገራት ተወካዮች ተፋልመውበት ተጠናቅቋል፡፡ በውጤቱም Diaw Fall - ከ ሞሪታኒያ 🇲🇷- በ 70.2 ነጥብ 1ኛ ደረጃ DJ Huba - ከ አንጎላ🇦🇴 - በ 64.5 ነጥብ 2ኛ ደረጃ Bokon - ከ ቶጎ 🇹🇬 - በ 63 ነጥብ - 3ኛ ደረጃ Aladin - ከ ጋቦን 🇬🇦- በ61 ነጥብ (ከ80) 4ኛ ደረጃ ን በማግኘት ቅዳሜ ለሚደረገው ሁለተኛ ዙር ግጥሚያ ያለፉ የመጀመሪያዎቹ 4 ተወዳዳሪዎች መሆናቸውን አረጋግጠዋል፡፡ ---------------- ነገ ማክሰኞ ሐምሌ 13 በተመሳሳይ ሰዓት (ማታ 2፡00) በሚቀጥለው ውድድር የመጀመሪያው ዙር ሁለተኛ ምድብ ሀገራት ተወካዮች ይፋለማሉ፡፡ በዚህ ምድብ ናይጄሪያ ፣ ቻድ ፣ ሞሪሺየስ ፣ ኬንያ ፣ ሴኔጋል ፣ ካሜሩን ፣ ጋና እና ጊኒ ቢሳው ይገኛሉ፡፡ እነዚህ ሀገራት ያላቸውን ረጅም የግጥም ግጥሚያ ልምድ እና ባህል (poetry slam culture) ስናይ … ነገ ጠንከር ያለ ውድድር የሚታይበት ምሽት እንደሚሆን እንጠብቃለን! በፌስቡክ ቀጥታ በመግባት ውድድሩን እንድትከታተሉ እንጋብዛለን! #casp2021 #CaspEthiopia #slampoetry #Africa #Ethiopia Coupe d'Afrique de Slam poésie, CASP

የመክፈቻው ቀን ደስ በሚል ሁኔታ ተጠናቅቋል፡፡ የ33 የአፍሪካ ሀገራት ሻምፒዮኖች ይሳተፉበታል፡፡ ከነገ ጀምሮ የሚጀምረው ውድድር ቅደም ተከተል ምድብም ዕጣ ወጥቶ ነበር፡፡ ሻምፒዮናችን Seife Te
+3
የመክፈቻው ቀን ደስ በሚል ሁኔታ ተጠናቅቋል፡፡ የ33 የአፍሪካ ሀገራት ሻምፒዮኖች ይሳተፉበታል፡፡ ከነገ ጀምሮ የሚጀምረው ውድድር ቅደም ተከተል ምድብም ዕጣ ወጥቶ ነበር፡፡ ሻምፒዮናችን Seife Temam 9 ሀገራት ባሉበት የመጨረሻው ቀን ምድብ የደረሰው ሲሆን የመጀመሪያ ውድድሩን አርብ ዕለት ያደርጋል፡፡ ደቡብ ሱዳን ፣ ሞሮኮ ፣ ሞዛምቢክ ፣ ኬፕቬርድ ፣ ማዳጋስካር ፣ ማላዊ ፣ ኒጀር እና ቡሩንዲ በዚህ ምድብ ይገኛሉ፡፡ ቻድ ላይ በተደረገው የመጀመሪያው ውድድር ላይ አሸናፊ ሻምፒዮን የነበረው እና በሞት ያጣነው ሴኔጋላዊው አልፋሩቅ ም ታስቦ ነበር፡፡ ________ ውድድሩ ነገ ከምሽቱ 2፡00 ሰዓት ላይ ይጀምራል፡፡ በፌስቡክ ቀጥታ በመግባት እንድትከታተሉን እንጋብዛለን፡፡ በአካል መገኘት የምንችል ደግሞ ቀጥታ ስርጭታችንን ከሽፍታ ነውና የምናደርገው ብቅ ብላችሁ ደመቅ ደመቅ እናድርገው! Coupe d'Afrique de Slam poésie, CASP Gitem Sitem - ግጥም ሲጥም #casp2021 #CaspEthiopia #slampoetry #Africa #Ethiopia

ሁለተኛው የአፍሪካ የግጥም ግጥሚያ የመጀመሪያ ዙር ከሰኞ ሐምሌ 12 እስከ ቅዳሜ ሐምሌ 17 ድረስ በኦንላይን ይካሔዳል። ሀገራችንም በድንቅ ልጃችን "ሰይፈ ተማም" ትወከላለች! #CASP #CupOfAf
+1
ሁለተኛው የአፍሪካ የግጥም ግጥሚያ የመጀመሪያ ዙር ከሰኞ ሐምሌ 12 እስከ ቅዳሜ ሐምሌ 17 ድረስ በኦንላይን ይካሔዳል። ሀገራችንም በድንቅ ልጃችን "ሰይፈ ተማም" ትወከላለች! #CASP #CupOfAfricanSlamPoetry #CASP2021 #CASPEthiopia

አዝኛለሁ… በልፋቴ በድካሜ ባቆየሁት ሳቃችንን‐ ተንከርፍፎ ስላየሁት! አዝኛለሁ… ለተዝካሩ ለሙሾው ድንኳን ተክሎ እንዳይወጣ ዕድሜያችን‐የኩርፊያ እንኳን ትዝታ ቢያጣ። የደስታ የፈገግታ አሻራ ባናስቀር ደርሰን እንዴት በባዶ እንዲያው ዝም ብሎ ያለ እድሜው፣ እድሜ ያፍርሰን! አዝኛለሁ… ቀና ችን‐ቀን ሳለ ሳይዳምን ፀሐይ ባይወጣበት እንደሌላው እለት ወዝ ስለታጣበት። ፀሐይ ያጣ ተብሎ ቀን አይሰረዝም እድሜ ላይ ይጫናል ታሪክ እንዲያስረዝም። ሕይወታችን‐ድግሱ ውብ ነበር እንኳን ቁም ነገሩ ዋዛና ለበጣው አዝኛለሁ… ከተነሳንበት ተመልሰን ሄደን ፈልገን ስናጣው። ©️ያዴል ትዕዛዙ

Live Painting & Poetry Night Gojo Bar presents you a live painting and poetry night along with other entertainments. The show
Live Painting & Poetry Night Gojo Bar presents you a live painting and poetry night along with other entertainments. The show will be hosted by Gitem Sitem's co-host Seife Temam. Saturday, July 17 7PM - 8PM Hill Bottom Recreation Center Entrance fee is ETB 100. #July_17_21 https://t.me/Kunet_Sitem #Gojo_Bar #poetry #livepainting #gitemsitem #seifetemam #Hill_bottom

ቀድሼ ላግባሽ እምነ በሃ ቅድስት ቤተክርስቲያን ,.... ወስዕልት በእንቆጳዝዮን በሚለው ቃል ዜማ ስርአት መልሼ እባክሽን ላግባሽ ራሴው ቀድሼ: ተንስኡ እያልኩኝ በቅድስቱ ስፍራ በቀኖናው ድርስት ከእ
ቀድሼ ላግባሽ እምነ በሃ ቅድስት ቤተክርስቲያን ,.... ወስዕልት በእንቆጳዝዮን በሚለው ቃል ዜማ ስርአት መልሼ እባክሽን ላግባሽ ራሴው ቀድሼ: ተንስኡ እያልኩኝ በቅድስቱ ስፍራ በቀኖናው ድርስት ከእግዜሩ ጋር ላውራ በሚፈተትበት የቁርባኑ መና ከልቤ ላመስግን የግሌ ሁኚና የልቤ ህዋሶች በእንግዳ ስሜት በፍሰሐ ሰክረው በተመስጦ ስሌት በምስጋና ድምፀት የማወጣው ዜማ የጠለቀ እንዲሆን ከሰማይ ደመና ነጠላ አጣፍተሽ አክሊሉንም ደፍተሽ ህግሽን ጠብቀሽ ክብርን ተጎናፅፈሽ ካባውን ደርበን በእምነት ኪዳን ጥላ በፈገግታ ልይሽ የግሌ ሁኚና የኔታ የሰጡኝ የወንጌሉ በፍታ ጠንክሮ እንዲፀና ፍፁም ሳይረታ በግዕዝ ባራራይ ስርአት መልሼ 'እባክሽን ላግባሽ ራሴው ቀድሼ! የህይወቴን ምስጢር የኑሮዬን ድርሳን ልቤን ገልጩልሽ እያዜምኩኝ ምልጣን በክርስትናሽ ስም ፀሎትን አድርሼ የእለቱን ምስባክ ስንክሳር ከልሼ እባክሽን ላግባሽ ራሴው ቀድሼ! የተላለፍኩትን የኃጢአት ደዌ በንስሐ ስሽር በገሐድ ነነዌ የፈጣሪ ምሕረት ላንቺም እንዲመጣ በተክሊል ሱባዔ ከበደሌ ልንጣ አዎ የኔ መውደድ አንቺም ተለመኚ ገነትም ቀላል ናት ብቻ ከኔ ሁኚ! አንድም ለኔ ፅናት አንድም ላንቺ ጸጋ ቃልሽን ሸልሚኝ ልቤ ባንቺ ይርጋ። ውዴ ስብሐት ለአብ ብዬ ሠራዊት ዘልቄ በሐሴት ሰክሬ በደስታ ጠልቄ ተክህኖ ለብሼ ስርአት መልሼ እባክሽን ላግባሽ ራሴው ቀድሼ! ©️ዳዊት ጥዑማይ @jawithpoetdeva 2/9/2013 https://t.me/GitemSitem

የግጥም መጽሐፍ ምረቃ ርእስ፦ ርእስ የለውም ገጣሚ፦ ኤልያስ ሽታሁን በጥዑም ግጥሞቹ እና ግሩም ለዛ ባለው አቀራረቡ በርካታ መድረኮች ላይ የምታውቁትና የምትወዱት ኤልያስ ሽታኹን 'ርእስ የለውም' በሚ
የግጥም መጽሐፍ ምረቃ ርእስ፦ ርእስ የለውም ገጣሚ፦ ኤልያስ ሽታሁን በጥዑም ግጥሞቹ እና ግሩም ለዛ ባለው አቀራረቡ በርካታ መድረኮች ላይ የምታውቁትና የምትወዱት ኤልያስ ሽታኹን 'ርእስ የለውም' በሚል ርእስ የመጀመሪያ መጽሐፉን ለንባብ አብቅቷል። ቦታ፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቲያትር ቀን፦ ሐምሌ 5 ሰዓት፦ 11 ሰዓት አዘጋጅ፦ ሰምና ወርቅ #ኤልያስ_ሽታኹን #ርእስ_የለውም #ሰምናወርቅ https://t.me/GitemSitem

መኖር ሲገፉህ ተገፍተህ ሲያገኙ ሲረሡህ ስታገኝ ሲመጡ አንድ ያለህን ሠጥተህ።! ሀዘን ለቅሷቸውን ወደ አን እያጋቡ አንተን ሲያስለቅሡ ሀዘናቸው ወስዶህ ቀና ሳትል አንተ ሀሴት ነው ለነሡ። ላጣ ለተጎዳ
መኖር ሲገፉህ ተገፍተህ ሲያገኙ ሲረሡህ ስታገኝ ሲመጡ አንድ ያለህን ሠጥተህ።! ሀዘን ለቅሷቸውን ወደ አን እያጋቡ አንተን ሲያስለቅሡ ሀዘናቸው ወስዶህ ቀና ሳትል አንተ ሀሴት ነው ለነሡ። ላጣ ለተጎዳ ላገኘ ከበርቴ በዲናሩ ብዛት ለሚበላ ፍዳ ለሁሉም ሠው ሆነህ ያለህን ትልቁን ክቡር ጊዜ ሠጥተህ ምንም እንደማይሠጥ እንደ ንፉግ ታይተህ ማንም ካንተ ሳይሆን አንተ ለሠው ሆነህ ከማንም ሳጠብቅ ሁሌም እየሠጠህ መኖር በመኖር ታስተምረኛለህ። እንዲህ ቃል የሚሆን ነፍስ ያለው አንድ እውነት እንኳን ካጠገብህ ከየትስ ይገኛል ቢፈለግ ካለበት። ፈልጎ አለመድከም አግኝቶ አለመርካት ያው የልብን መኖር ያው የልብን መንካት።!!! መኖር ነው አንተነት መኖር ነው እኔነት።!!!! ©️ተስፋልደት በለጠ https://t.me/GitemSitem

photo content
+5

photo content
+9

አረተኛው የግጥም ሲጥም ነጻና ክፍት መድረክ ከብዙ በጥቂቱ ይህን 👇🏾ይመስል ነበር።

ዳሪክ ጥበባት ቀለም 🎨 እሁድ ሐምሌ 11/2013ዓ/ም ከቀኑ 9:00 ጀምሮ በበቀለ ሞላ ሆቴል አዳማ
ዳሪክ ጥበባት ቀለም 🎨 እሁድ ሐምሌ 11/2013ዓ/ም ከቀኑ 9:00 ጀምሮ በበቀለ ሞላ ሆቴል አዳማ