Diinii kee Anaakara (Md Ali)
Відкрити в Telegram
دروس وفتاوي ومحاضرات باللغة العفرية ★Diini barittooy, fatwaa kee Daqwa Qafar afat Tû mabul=> @Anaakar or @acmadxalol
Показати більше1 617
Підписники
-124 години
+67 днів
+2030 день
Архів дописів
★ Abtam xiqah abe wayte taama, sarrah arre sinni nadaama kol takkeeh,
★ Abtam faxah abtu teffere taamak sarrah tayse cogda gorrissa!!
✍Md Ali
Repost from NESIHA TV | ነሲሓ ቲቪ
ምርጥ ሕዝቦች በሸይኽ ኢልያስ አህመድ || NesihaTv
ነሲሓ ቲቪ...
ኢስላማዊ እውቀት ለሁሉም!!
@nesihatv
Repost from "ኡማ ቲቪ " Tv
"ቶጵያ" መፅሐፍ ተመረቀ
....
የኢትዮጵያን እውነተኛ እና ያልተነገሩ ታሪኮችን የያዘው በደራሲ ነጃሺ ከድር የተፃፈው "ቶጵያ"መፅሐፍ በዛሬው ዕለት በኦሮሚያ ባህል አዳራሽ በድምቀት ተመርቋል።
በምረቃ ስነስርዓቱ ላይ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች ታላላቅ ፀሀፊያን የማህበረሰብ አንቂወችን ጨምሮ በርካታ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
⭕️ Gad kee Qhuraàn Inki numih alilit matangoorowa.
Sitta sada namma caagidiy, wiilih sittah yani kinniimih taagah⭕️
👇
✍ قال الإمام ابن القيم
- رحمه الله تعالى - :
📝 القرآن والغناء لا يجتمعان في القلب أبدًا ؛ لما بينهما من التضادّ ؛ فإن القرآن ينهىٰ عن اتباع الهوىٰ ، ويأمر بالعِفَّة ، ومُجانبة شهوات النفوس ، وأسباب الغيّ ،
📝 والغناء يأمر بضد ذلك كلِّه ، ويُحسِّنه ، ويُهيِّج النفوس إلىٰ شهوات الغيِّ ، فيُثير كامِنَها ، ويُزعجُ قاطنها ، ويُحرِّكها إلىٰ كل قبيح ،
📝 وهو جاسوس القلوب ، وسارق المروءة ، وسُوس العقل ، يتغلغل في مكامن القلوب ، وسرائر الأفئدة ، فبينما ترى الرجل وعليه سمة الوقار ، وبهاء العقل ، وبهَجة الإيمان ، ووقار الإسلام ، وحلاوة القرآن ،
📝 فإذا استمع الغناء ومال إليه ، نقص عقلُه ، وقَلّ حياؤه ، وذهبت مروءته ، وفارقه بهَاؤه ، وتخلىّٰ عنه وقاره ، وفرح به شيطانه ، وشكا إلىٰ الله تعالىٰ إيمانُه ، وثَقُل عليه قرآنه .
📜〖 اغاثة اللهفان - ابن القيم 〗.
خطبة الجمعة
الجامع: الإحسان
الخطيب: دكتور محمد حسين ويعسى
التاريخ: ١٤٤٤/٥/١هجري
Repost from 𝐀𝐟𝐚𝐫 𝐊𝐚𝐬𝐬𝐢𝐬 𝐌𝐞𝐝𝐢𝐚
#Wakti_dagoh_immay_Maraaqina
Shekh Yacaya Qabdalla samarak ruftaanah derrel geytima masjiidil kulli bar magh-rib kee qishak fanal qhur'aan yafsiir qimbiseh geytima.
Wakti dagom naaxigeh immay wokkel kaadu wakti kaxxam daggoowah salfa luk raaqa qilmi. Toysa maraaqina.
Nikac amaxxe kalah yan barralih(faxentolih) gaba gabat hayya heenih tasaawir ugutaanaah, digraanam maxiqta!
✍Md Ali
https://t.me/httpsDiiniKeeAnaakara
وَيْلٌ لِلَّذِي يُحَدِّثُ بِالْحَدِيثِ لِيُضْحِكَ بِهِ الْقَوْمَ فَيَكْذِبُ وَيْلٌ لَهُ وَيْلٌ لَهُ
(ሰዎችን ለማሳቅ ብሎ እየዋሸ ወሬን የሚያወራ ሰው ወዮለት! ወዮለት! ወዮለት!) አልባኒ “ሐሰን” ብለውታል፡፡
8. የኳስ ፍቅርህን ለከት አርግለት፡፡ ለኳስ ብለህ የምትጠላ፣ ለኳስ ብለህ የምትወድ፣ በኳስ ምክንያት ሐራም ላይ የምትወድቅ፣ በኳስ ምክንያት እምነታዊ ግዴታዎችን የማትፈፅም ከሆንክ አትጠራጠር ኳሱን ጣኦት አድርገህ ይዘኸዋል ማለት ነው፡፡ መልእክተኛው ﷺ “የዲናር ባሪያ ጠፋ! የዲርሃም ባሪያ ጠፋ! … ሲሰጡት ይወዳል! ካልሰጡት ይጠላል” ይላሉ፡፡ ዛሬ ኳስ ከገንዘብ ባልተናነሰ ምናልባትም በባሰ ሁኔታ ጣኦት ሆኖ በገሃድ እየታየ ነው፡፡ ይሄ ስሜትን አምላክ ማድረግ ካልሆነ ምን ሊሆን ነው! በሚከተለው አንቀፅ ከተገለፁት እንዳትሆን ጠንቀቅ በል!
أَفَرَأَيْتَ مَنِ اتَّخَذَ إِلَهَهُ هَوَاهُ وَأَضَلَّهُ اللَّهُ عَلَى عِلْمٍ وَخَتَمَ عَلَى سَمْعِهِ وَقَلْبِهِ وَجَعَلَ عَلَى بَصَرِهِ غِشَاوَةً فَمَنْ يَهْدِيهِ مِنْ بَعْدِ اللَّهِ أَفَلَا تَذَكَّرُونَ
{ዝንባሌውን አምላኩ አድርጎ የያዘውን፣ አላህም ከእውቀት ጋር ያጠመመውን፣ በጆሮውና በልቡ ላይም ያተመበትን፣ በዐይኑም ላይ ሺፋን ያደረገበትን ሰው አየህን! ታዲያ ከአላህ በኋላ የሚያቀናው ማነው አትገሰፁምን?} [ጃሢያህ፡ 23]
9. በኳስ ምክንያት የራስህንም ሀላፊነት ያለብህን አካላትም ሐቅ እንዳትሸራርፍ፡፡ ሰርክ ኳስ እያሳደድክ በዚያ ሳቢያ ሀላፊነትህን ባግባቡ እየተወጣህ ካልሆነ አደጋ ላይ ነው ያለኸው፡፡ ነብዩ ﷺ “ሁላችሁም እረኛ ናችሁ (ሀላፊነት አለባችሁ)፡፡ እያንዳንዳችሁም ስለእረኝነታችሁ (የተሸከማችሁት ሀላፊነት) ተጠያቂ ናችሁ" ይላሉ፡፡ መከታተሉ በጤናም ይሁን በትኛውም መልኩ እራስህንም የሚጎዳ መሆን የለበትም፡፡ አይደለም በቀልድና በዛዛታ ቀርቶ በዒባዳም እራስን መጎዳት አይፈቀድም፡፡ እስኪ ይህን ታሪክ አንዴ እንመልከት፡፡ ነብዩ ﷺ መዲና ሲገቡ ሰልማኑል ፋሪሲን እና አቡ ደርዳእን ረዲየላሁ ዐንሁማ ወንድማማች አድርገው አቆራኟቸው፡፡ ሰልማን አቡደርዳእን ሊጎበኝ ቤቱ ሲመጣ ሚስቱ ኡሙ ደርዳእ ረዲላሁ ዐንሃ ራሷን ጥላ አያት፡፡ “ምን ሆነሻል?” አላት፡፡ “አይ ወንድምህ አቡደርዳእ ለዱንያ ደንታ የለውም” ስትል እንዲያ የሆነችበትን ምክንያት ነገረችው፡፡ ከዚያ አቡ ደርዳእ መጣ፡፡ ለሰልማን ምግብ አዘጋጀለትና “ብላ እኔ ፆመኛ ነኝ” አለው፡፡ ሰልማን ግን “አንተ ካልበላህ የምበላ አይደለሁም” አለው፡፡ ከዚያም (ፆሙን አፍርሶ) በላ…፡፡ ሌሊቱ ሲመጣ አቡ ደርዳእ ለሰላት ተነሳ፡፡ “ተኛ” አለው ሰልማን፡፡ ቆይቶም ተነሳ፡፡ “ተኛ” አለው አሁንም፡፡ የሌሊቱ መጨረሻ ሲደርስ ሰልማን እራሱ “ተነስ” አለውና አብረው ሰገዱ፡፡ ከዚያም ሰልማን እንዲህ አለው “ለጌታህ ባንተ ላይ ሐቅ አለ፡፡ ለራስህም ባንተ ላይ ሐቅ አለ፡፡ ለቤተሰብህም ባንተ ላይ ሐቅ አለ፡፡ እያንዳንዱን ባለሐቅ ሐቁን ስጥ!!” አቡ ደርዳእ ከነብዩ ﷺ ዘንድ ሄደና የሆነውን ነገራቸው፡፡ እሳቸውም “ሰልማን እውነት ተናገረ” አሉ፡፡ [ቡኻሪ የዘገቡት ነው] እንግዲህ አስተውል ሶሐባው በኳስ ሳይሆን በዒባዳ እንኳን እራሱን መጠበቅ እንዳለበት ተነግሮታል፡፡ አንተስ?
10. በኳስ ምክንያት አጉል ወገንተኝነትና ዘረኝነት ውስጥ አትግባ!! ዘረኝነት የመሀይማን መገለጫ ነው!! ነብዩ ﷺ (ተዋት! እሷ ጥንብ ነችና!) ይላሉ፡፡
11. በኳስ ምክንያት አጉል ቁጣ ውስጥ አትግባ፡- ነብዩ ﷺ “ምከረኝ” ያላቸውን ሰው (አትቆጣ!) ብለውታል፡፡ ደጋግሞ ሲጠይቃቸው ደጋግመው (አትቆጣ!) ብለውታል፡፡ “እከሌ ቡድን ተሸነፈ” ብሎ አጉል ብስጭት ውስጥ የሚገባን “ቂል” የሚለው ቃል በበቂ ሁኔታ ይገልፀው ይሆን?!! እኔ እንጃ!
12. አንዱን ቡድን ለመደገፍ በሚል ተልካሻ ሰበብ አታጨብጭብ! አትዝፈን! አትጨፍር፡፡ ዘፈን የተፈቀደው ውስን የሆኑ ክስተቶችን ምክንያት በማድረግ ለሴቶች ብቻ ነው፡፡ ነብዩ ﷺ እንዲህ ይላሉ፡ (ሁለት ድምፆች የተረገሙ ናቸው!! የፀጋ ጊዜ መዝሙርና የፈተና ጊዜ ዋይታ!) “ወንድ ከዘፈነ ሴት ሆነ” ይላሉ ሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይሚያ እና ሸይኹል አልባኒ አላህ ይማራቸውና፡፡
13. ኧረ ከአቅል ሁን! ለመሆኑ ኳስ ሲከታተሉ ገደብ የለሽ ስሜት ውስጥ ስለገቡ ብቻ የሚሞቱ ሰዎች እንዳሉ ታውቅ ይሆን? ካላወቅክ በዚህ ላይ የተደረጉ ጥናቶችን አፈላልግ፡፡ “እከሌ ቡድን ተሸነፈ” ብለው እራሳቸውን የሚያጠፉ እንደሚያጋጥሙስ ይሰወርህ ይሆን? ብቻ ከኳስ ጋር በተያያዘ በየትኛውም ምክንያት ህይወትህን ብታጣ ነገ አላህ ፊት መልስህ ምን እንደሚሆን ከወዲሁ አስብበት!! ጂሃድ ላይ አስደናቂ ጀብዱ ሲፈፅም ውሎ በደረሰበት ቁስለት ስቃዩን መቋቋም አቅቶት እራሱን የገደለውን ሰው ነብዩ ﷺ “የእሳት ነው!” ማለታቸውን አትዘንጋ፡፡ አንተ ከሱ የተሻለ አሳማኝ ምክንያት ካለህ ቀጥልበት!! አስተውል! ሞት አማክሮ አይመጣም፡፡
14. በኳስ ምክንያት አንዱን በመደገፍ ሌላውን በመንቀፍ፣ ሌሎችን ለማናደድ፣ ወይም እንዲሁ በአጉል ብስጭት ፀያፍ ቃላትን አታውጣ! ዘወትር “ሐያእ” አይለይህ፡፡ ነብዩ ﷺ ምን እንደሚሉ አስተውል!
الْبَذَاءُ مِنَ الْجَفَاءِ, وَالْجَفَاءُ فِي النَّارِ, وَالْحَيَاءُ مِنَ الْإِيمَانِ, وَالْإِيمَانُ فِي الجنة
(ፀያፍ ቃላት መጠቀም ዋልጌነት ነው! ዋልጌነት ደግሞ ወደ እሳት ነው!! “ሐያእ” ከኢማን ነው፡፡ ኢማን ደግሞ ወደ ጀነት ነው!) [አሶሒሐህ፡ 495]
15. ኳስ ለማየት ብለህ አስካሪ መጠጥ ከሚሸጥበት ወይም ከሚጠጣበት ባርና ካፍቴሪያ ውስጥ ወይም ሌሎች ወንጀሎች ከሚፈፀሙባቸው አካባቢዎች ድርሽ እንዳትል፡፡ አላህን ፍራ! እምነትህንም እራስህን አክብር፡፡
ኢን ሻአላህ ከቻልኩ በዚህ ጉዳይ የኡለማዎችን ብይን አሰባስቤ ለመመለስ እሞክራለሁ፡፡
~----~~ ----
(ኢብኑ ሙነወር፣ ሃምሌ 03/2006)
የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor
ጥቂት ምክር ለኳስ ጨዋታ ተመልካቾች
~
1. ኳስ እየተመለከትክ ወይም በኳስ ምክንያት እንቅልፍህን አጥተህ ሰላት እንዳታሳልፍ!! ልብህ በህይወት ካለ ደወል እየተደወለ ነው፡፡ ስማ!!
فَخَلَفَ مِنْ بَعْدِهِمْ خَلْفٌ أَضَاعُوا الصَّلَاةَ وَاتَّبَعُوا الشَّهَوَاتِ فَسَوْفَ يَلْقَوْنَ غَيًّا
{ከእነርሱም (ከነቢያቱ) በኋላ ሰላትን ያጓደሉ፣ ከንቱ ፍላጎቶችንም የተከተሉ፣ መጥፎ ምትኮች ተተኩ! የጀሀነምንም ሸለቆ በእርግጥም ያገኛሉ!} [መርየም፡ 59]
አስተውል! አይደለም ስንት አላስፈላጊ ኮተት አጭቆ በያዘው እግር ኳስ ምክንያት ይቅርና አንድ ሰው በተራዊሕ ሰላት ምክንያት ማምሸቱ የፈጅር ሰላትን በወቅቱ እንዳይሰግድ የሚያደርገው ከሆነ ተራዊሕ ሰላት መስገዱም አይፈቀድለትም፡፡ በኳስ ምክንያት እያመሹ የፈጅር ሰላትን ማሳለፉስ ይቻል ይሆን? ብይኑን ለራስህ ትቼዋለሁ፡፡ እስኪ ህሊናህን አዳምጠው፡፡
2. ለኳስ ብለህ የወላጆችን ሐቅ አትጣስ! ቁርኣኑ “ ‘ኡፍ’ አትበሏቸው” ይላል። ዛሬ ግን በጋጠ-ወጥ ልጃቸው ሰዐት እላፊ በራቸው ይደበደባል፣ ጎል ገባ ብሎ ይጮህባቸዋል፡፡ የሚደግፈው ቡድን “ተሸነፈ” ብሎ እየተበሳጨ ይገባባቸዋል፡፡ ካሁን ካሁን ምን አግኝቶት ይሆን እያሉ በስጋት ይጨርሳቸዋል። ጌታችን አላህ እንዲህ ይላል፡-
وَقَضَى رَبُّكَ أَلَّا تَعْبُدُوا إِلَّا إِيَّاهُ وَبِالْوَالِدَيْنِ إِحْسَانًا إِمَّا يَبْلُغَنَّ عِنْدَكَ الْكِبَرَ أَحَدُهُمَا أَوْ كِلَاهُمَا فَلَا تَقُلْ لَهُمَا أُفٍّ وَلَا تَنْهَرْهُمَا وَقُلْ لَهُمَا قَوْلًا كَرِيمًا (23) وَاخْفِضْ لَهُمَا جَنَاحَ الذُّلِّ مِنَ الرَّحْمَةِ وَقُلْ رَبِّ ارْحَمْهُمَا كَمَا رَبَّيَانِي صَغِيرًا (24)
{ጌታህም (እንዲህ ሲል) አዘዘ፡- “እርሱን እንጂ ሌላን አትገዙ፡፡ በወላጆቻችሁም መልካምን ስሩ፡፡ በአንተ ዘንድ ሆነው አንዳቸው ወይም ሁለታቸው እርጅናን ቢደርሱ “ኦፍ” አትበላቸው፡፡ አትገላምጣቸውም፡፡ ለእነርሱም መልካምን ቃል ተናገራቸው፡፡} [ኢስራእ፡ 23-24) ለመሆኑ ቁርኣን ሲነበብ ልባችን ይደነግጣል?
3. መሰረታዊ የእምነትህን ድንጋጌዎች ሳትለይ ነጋ ጠባ ኳስ ላይ የምታፈጥ ከሆነ አትጠራጠር ኪሳራ ላይ ነው ያለኸው! እርግጥ ነው ሸሪዐችን ሐላል በሆኑ ነገር ራስን ዘና ማድረግን አይከለክልም፡፡ ነገር ግን ሐላል በሆነ ነገር ከዋጂብ መዘናጋትን አይፈቅድም፡፡ የእምነቱ ምሰሶ የሆነውን ተውሒድና ከአደጋው ሁሉ የከፋውን የሺርክ አደጋ በቅጡ ሳይለይ፣ ሰለ ሶላት፣ ሰለፆም፣… ስለሌሎችም መሰረታዊ የዲኑ ክፍሎች እዚህ ግባ የሚባል እውቀት የሌለው ሰው በኳስ ላይ ጊዜውን እንዲያጠፋ የሚፈቅድለት እምነቱ ይቅርና የትኛው ህሊና ነው?! ይሄ ችላ ካላሉት በቀር ብዙም ማሰብ አይጠይቅም፡፡ “ነገ ከመመርመራችሁ በፊት ዛሬ እራሳችሁን መርምሩ” ይላል ዑመር ብኑልኸጣብ፡፡ ከአላህ ፊት ስላጠፋሃው ጊዜ፣ ገንዘብና ወጣትነትህ እንደምትጠየቅ አትርሳ፡፡ ነብዩ ﷺ እንዲህ ይላሉ፡-
لاَ تَزُولُ قَدَمَا عَبْدٍ يوم القيامة حَتَّى يُسْأَلَ عَنْ خمس، عَنْ عُمْرِهِ فِيمَا أَفْنَاهُ؟ وعن شبابه فيما أبلاه؟ وَمَالِهِ مِنْ أَيْنَ اكْتَسَبَهُ؟ وَفِيمَا أَنْفَقَهُ؟ وماذا عمل فيما علم؟
(የቂያማ እለት ከአምስት ነገሮች ሳይጠየቅ የአንድ ባሪያ እግሮች አይንቀሳቀሱም! እድሜውን በምን እንዳጠፋው፤ ወጣትነቱን በምን እንደጨረሰው፣ ገንዘቡን ከየት እንዳገኘው፤ እና በምን ላይ እንዳዋለው፤ በእውቀቱ ምን እንደሰራበት።) [አሶሒሐህ፡ 946)
4. ኳስ ለመመልከት ብለህ ከባዕድ ሴቶች ጋር ተቀላቅለህ አትቀመጥ። መቀላቀሉ ሌላው ቀርቶ ሰይጣናዊ ጉትጎታ ከሚቀንስበትም ቦታም አልተፈቀደም፡፡ ለሴቶች ከመስጂድ ይልቅ ቤታቸው እንዲሰግዱ መመረጡን ለመስገድ ከወጡም ሽቶ ሳይቀቡ፣ ሳይዋዋቡ መሆኑን አስተውል፡፡ ነብዩ ﷺ “ከወንዶች የሶላት ሶፎች በላጩ የመጀመሪያው ነው፣ የከፋው ደግሞ የመጨረሻው (ለሴቶቹ የሚቀርበው) ነው፡፡ ከሴቶቹ የሶላት ሶፎች ደግሞ በላጩ የመጨረሻው (ከወንዶች የራቀው) ነው፡፡ የከፋው ደግሞ የመጀመሪያው (ለወንዶቹ የቀረበው) ነው” ማለታቸውን አስተውል፡፡ ሌላው ቀርቶ ነብዩ ﷺ ወንዶችና ሴቶች ከመስጂድ ውጭ ከሶላት ሲመለሱ ቢቀላቀሉ ሴቶቹን “ወደ ኋላ ሁኑ” ብለው ዳር ይዘው እንዲሄዱ ነው የነገሯቸው፡፡
በተጨማሪም ከባእድ ሴቶችም ላይ አታፍጥጥ! አላህ እንዲህ ይላል:-
قُلْ لِلْمُؤْمِنِينَ يَغُضُّوا مِنْ أَبْصَارِهِمْ وَيَحْفَظُوا فُرُوجَهُمْ ذَلِكَ أَزْكَى لَهُمْ إِنَّ اللَّهَ خَبِيرٌ بِمَا يَصْنَعُونَ
{ለአማኞችም ንገራቸው፡- ዐይኖቻችሁን (ያልተገባ ነገር ከማየት) ይስበሩ፣ ብልቶቻቸውንም ይጠብቁ፣ ይህ ለነሱ የተሻለ ነው፡፡ አላህ በሚሰሩት ሁሉ ውስጥ አዋቂ ነው፡፡} [ኑር፡ 30] ውድድሩ የሴቶች እግር ኳስ ከሆነ ግን አትጠራጠር በሐራም እየተጨማለቅክ ነው! ሀፍረተ-ገላቸውን ያልሸፈኑ ሰዎችን እየተከታተልክ ከሆነም ስሜትህ ልቦናህን ሸፍኖት ካልሆነ በስተቀር ሐቁ አይሰወርህም፡፡ ባይሆን እኔ የወንድምነት ሃላፊነቴን አድርሻለሁ! “አላህን ፍራ!” ብያለሁ፡፡
5. ላንቃህ እስኪበጠስ አትጩህ! ድምፅህን ዝቅ አድርግ፡፡ ወከባ ቀንስ፡፡ ጎረቤት አትረብሽ! ሀያሉ ጌታ አላህ ምን እንደሚል ረጋ ብለህ አስተውል!
وَاقْصِدْ فِي مَشْيِكَ وَاغْضُضْ مِنْ صَوْتِكَ إِنَّ أَنْكَرَ الْأَصْوَاتِ لَصَوْتُ الْحَمِيرِ
{በአካሄድህም መካከለኛ ሁን፡፡ ከድምፅህም ዝቅ አድርግ፡፡ ከድምፆች ሁሉ አስቀያሚው የአህዮች ድምፅ ነውና!} [ሉቅማን፡ 19]
የቤት ስራ ሰጥቼሃለሁ፡፡ በጮህክ ቁጥር የአህዮችን አስቀያሚ ድምፅ አስታውስ፡፡ ጯሂዎችን አላህ በምን እንደመሰላቸውም በህሊናህ ያዝ፡፡
6. ተረጋጋ! የምትደግፈው ቡድን ስላሸነፈ አትንቀባረር፡፡ አትጎረር፡፡ ስርኣት አልባ አትሁን! ሀያ ምናምን ወጠምሾች ከሆነ ሜዳ ውስጥ አንዲት ቅሪላ ተከትለው ከመሯሯጣቸው ውጭ ይህን ያክል ጮቤ የሚያስረግጥ ምንም ነገር የለም፡፡
وَلَا تُصَعِّرْ خَدَّكَ لِلنَّاسِ وَلَا تَمْشِ فِي الْأَرْضِ مَرَحًا إِنَّ اللَّهَ لَا يُحِبُّ كُلَّ مُخْتَالٍ فَخُورٍ
{ጉንጭህንም (በኩራት) ከሰዎች አታዙር፡፡ በምድርም ላይ ተንበጥርረህ አትሂድ፡፡ አላህ ተንበጣራሪን ጉረኛን ሁሉ አይወድምና!} [ሉቅማን፡ 18]
7. ከቡድንና ከጨዋታ ጋር በተያያዘ ለቀልድና ለተረብ እያልክ አትዋሽ! ውሸት አስቀያሚ ነቀርሳ ነው! ሰሚ ጆሮ ካለህ ነብዩ ﷺ እንዲህ ይላሉ፡-
«ኳስ የዘመናችን ጣዖት
~
ዛሬ ላይ ኳስ ከተራ መዝናኛነት አልፏል።
* በአላህ መንገድ ላይ የማይወጣው በቢሊዮን ዶላር የሚቆጠር ወጭ ይወጣበታል። ሚሊዮኖች እየተራቡ፣ በክህ -ደት ሰባኪዎች እየተጠለፉ ከግለሰቦች እስከ መንግስታት ለዚህ ቆሻሻ ነገር ግን የማይገመት ወጭ ያወጣሉ።
* ዘረኝነት ይንፀባረቅበታል።
* በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ አስካሪ መጠጥ ይተዋወቅበታል።
* የጭፈራና የዘፈን ድግስ ይቀርብበታል።
* እጅግ በርካቶች ለሱ ሲሉ ግዴታ የሆነባቸውን ሶላት ያሳልፋሉ።
* እጅግ በርካቶች ለሱ ሲሉ ጎረቤት ይበጠብጣሉ፣ የወላጅ ሐቅ ይጥሳሉ፣ እርስ በርስ ይጋጫሉ፣ ለሱ ሲሉ ይወዳሉ፣ ይጠላሉ።
* የመገናኛ አውታሮች፣ ማህበራዊ ሚዲያዎች፣ ጋዜጦችና መፅሔቶች፣ ግለሰቦች፣ በቤትም በውጭም፣ በየጎዳናው፣ በየ ካፌው፣ ቆመው ተቀምጠው፣ ... ለዲንም ይሁን ለዱንያ በሚጠቅም ጉዳይ ላይ ከሚጮሁት እጅግ በላቀ ስለዚህ ርካሽ ነገር ሆኗል ውትወታቸው። እንዲያውም ቀላል የማይባሉ ጥራዝ ነጠቆች ስለ ኳስ መተንተንን የንቃት ማሳያ አድርገውታል። ስለ ኳስ አለማወቅን ፋራነት አድርገውታል። ከዚህ በላይ ምን ዝቅጠት አለ?!
* በዚህ ቆሻሻ ነገር የተነሳ እጅግ በርካታ ወጣቶቻችን ከሃዲዎችን፣ የሉጥ ህዝቦችን ተግባር የሚፈፅሙ፣ ለሱ ጥብቅና የሚቆሙ ርካሽ ፍጡሮችን እንዲያደንቁ ሆነዋል። ደካማ ሰበብ እየደረደሩ ራሳቸውን አደንዝዘዋል።
* ከዚህ ሁሉ በኋላ አንዳንዶች ጂሃድ ሊያስመስሉት ሲዳዳቸው ይታያሉ። ኳስ በዚህ በመከራ በተከበበ ህዝብ ላይ የተከፈተ ወደን የተቀበልነው ጦርነት ነው።
ይሄ ሁሉ እውነታ በገሃድ ፈጦ የሚታይ ከመሆኑ ጋር ቢያንስ ሸሩን በመቀነስ ላይ እንኳ ዱዓቶች እየሰሩ አይደለም። የዱዓት ትልቁ በሽታ ሰፊው ህዝብ የወደቀባቸውን ጉዳዮች ለመጋፈጥ ወኔ ማጣት ነው። መሬት ላይ ባለው ተጨባጭ (ዋቒዕ) መሸነፍ። አትጠራጠር ወንድሜ! ኳስ ከዘመናችን ብዙ ዓይነት ጣዖቶች ውስጥ አንዱ ጣዖት ሆኗል። አደራ! ሌላው ቢቀር ቢያንስ ለዚህ የቦዘኔዎች ስራ ብለን ሶላት ከወቅቱ የምናሳልፍ እንዳንሆን እንጠንቀቅ። ለዚህ የጂላጂሎች ስራ ብሎ መስጂዶቻችንን ማራቆት የሚያሳፍር ጉዳይ ነው። ስለዚህ ነፍሲያችንን እንርገጥ። ተቅዋን እናስቀድም።
ማሳሰቢያ፦
- ያወራሁት ስለ ኳስ እንጂ ስለ ቀጠር አይደለም።»
©: Ibnu Munewor
ማህበራዊ ሚዲያን ለዲንም ለዱንያም መጠቀም
~
ማህበራዊ ሚዲያን ሃይማኖታችንን ለመማማር መጠቀም ትልቅ ስኬት ነው። ነገር ግን እዚህ ላይ መቆም አይገባም። ሁሉም እንደተገራለትና እንደ ተሰጥኦው ወገኑን በመርዳት ላይ ቢተጋ መልካም ነው። የህክምና እውቀት ያለው ጠቃሚ ትምህርቶችን ያሰራጭ። የስራ ፈጠራና ጠቃሚ የቢዝነስ ሃሳቦች ያሏችሁ ችላ ሳትሉ የምክር አገልግሎት በመስጠት ወገናችሁን እርዱበት። ኤሌክትሮኒክስ ወይም ሌላ ቴክኖሎጂ ተኮር እውቀቱ ያላችሁ መረጃ በመስጠት ማገዝ ትችላላችሁ። በሌሎችም ዘርፎች እንዲሁ። በተናጠል የሚከብድ ከሆነ ተመሳሳይ ሙያ ያላቸው ተቀናጅተው ቢሰሩት ብዙ ህዝብ መጥቀም፣ ብዙ አጅር ማፈስ ይቻላል።
ከዚህም አልፎ ማህበራዊ ሚዲያን ለነፃ ግልጋሎት ብቻ ሳይሆን ቢዝነስን ለማቀላጠፍ መጠቀምም ይገባል። የራስንም ይሁን የሌሎች ወንድም እህቶችን ምርትና ሌሎች አቅርቦቶችን፣ ሙያና አገልግሎቶችን ማስተዋወቅ፣ ግብይት ማከናወን፣ ዛሬ እየታየ እንዳለው ድለላ መስራት፣ ተቋማትንና የሚሰጡትን አገልግሎት ማስተዋወቅ፣ ... አስፈላጊ እንቅስቃሴ ነው። ስለዚህ የገባችሁበትም፣ ዝንባሌው ኖሯችሁ እያሰባችሁ ያላችሁም በታማኝነትና በሃላፊነት ለመጥቀምም ለመጠቀምም ነይታችሁ ስሩ።
ባይሆን አላህን ፍሩ! ውሸትን ተጠንቀቁ። የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
”يا مَعشرَ التُّجّارِ ! إياكُم والكذبَ“
እናንተ ነጋዴዎች ሆይ! ውሸትን ተጠንቀቁ!" [ሶሒሑ ተርጊብ: 1793]
ብዙ ነጋዴዎች በተለይ በዚህ ዘመን አመፅ የነገሰባቸው፣ ዱንያ አላህን ከመፍራት የጋረዳቸው ሆነዋል። ወደ ዲን የቀረቡ የሚባሉት እንኳ ከሌሎች የተሻሉ መሆን እያቃታቸው ነው። ያስተውሉ! ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡-
إن التجار يبعثون يوم القيامة فجارا، إلا من اتقى الله وبر وصدق
“ነጋዴዎች በትንሳኤ ቀን አመፀኞች ሆነው ነው የሚቀሰቀሱት። አላህን የፈራ፣ መልካምን የሰራ እና እውነትን ያወራ ሲቀር።" [አሶሒሓህ፡ 994]
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
በጫማ መስገድና ተያያዥ ነጥቦች
~
[ሀ] በጫማ መስገድ ይቻላል?
አንዳንድ ሰዎች በጫማ መስገድ የማይፈቀድ ይመስላቸዋል። ለዚህ ያደረሳቸው ጉዳዩ በዑለማእ ሲፈፀም ወይም ሲነገር ስላላጋጠማቸው ይሆናል። ነገር ግን በጫማ ከመስገድ የሚከለክል አንድም ማስረጃ የለም። ይልቁንም በተቃራኒው በጫማ መስገድ የማያሻማ ሸሪዐዊ መሰረት ያለው ሱና ነው። ይህንን ከሚያረጋግጡ ማስረጃዎች ውስጥ ከፊሉን ብናይ፡-
1. አቡ መስለማ ሰዒድ ብኑ የዚድ አልአዝዲ ረሒመሁላህ እንዲህ ብለዋል፡-
سَأَلْتُ أَنَسَ بْنَ مَالِكٍ: أَكَانَ النَّبِيُّ ﷺ يُصَلِّي فِي نَعْلَيْهِ؟ قَالَ: «نَعَمْ»
“አነስ ኢብኑ ማሊክን ‘ነብዩ ﷺ በጫማዎቻቸው ይሰግዱ ነበርን?’ ብዬ ጠየቅኩት። ‘አዎ’ አለኝ።” [ቡኻሪና ሙስሊም]
2. ዐብዱላህ ብኑ አቢ ሐቢባ ረዲየላሁ ዐንሁ እንዲህ ብለዋል፡-
جاءنا رسول الله ﷺ في مسجدنا ب(قباء فجئت وأنا غلام (حدث) حتى جلست عن يمينه (وجلس أبو بكر عن يساره) ثم دعا بشراب فشرب منه ثم أعطانيه وأنا عن يمينه فشربت منه ثم قام يصلي فرأيته يصلي في نعليه
“የአላህ መልእክተኛ ﷺ ቁባእ ወዳለው መስጂዳችን መጡ - እኔ ለጋ ልጅ ነኝ በጊዜው መጣሁና በቀኛቸው በኩል ተቀመጥኩ። አቡበክር በግራቸው ተቀመጡ። ከዚያም የሚጠጣ ነገር ጠየቁና ከሱ ጠጡ። ከዚያም በቀኛቸው ላለሁት ለኔ ሰጡኝና ከሱ ጠጣሁ። ከዚያም ሊሰግዱ ተነሱ። በጫማዎቻቸው ሲሰግዱ አየኋቸው።” [አሶሒሐህ፡ 2941]
3. ከዐምር ብኑ ሹዐይብ ከአባታቸው፣ ከአያታቸው ተይዞ እንዲህ ብለዋል፡-
رأيت رسول الله ﷺ يصلي حافيا ومنتعلا.
“የአላህ መልእክተኛን ﷺ በባዶ እግራቸውም ተጫምተውም ሲሰግዱ አይቻቸዋለሁ።” [ሶሒሕ አቢ ዳውድ፡ 660]
4. አቡ ሰዒድ አልኹድሪ ረዲየላሁ ዐንሁ እንዲህ ብለዋል፡-
“አንድ ቀን የአላህ መልእክተኛ ﷺ አሰገዱን። በከፊል ሶላታቸው ላይ ሳሉ ጫማዎቻቸውን አወለቁና በግራቸው በኩል አስቀመጧቸው። ሰዎች ይህንን ሲያዩ ጫማዎቻቸውን አወለቁ። ሶላታቸውን ሲያጠናቅቁ ‘ምን ሆናችሁ ነው ጫማዎቻችሁን ያወለቃችሁት?’ አሉ። እነሱም ‘ጫማዎችህን ስታወልቅ ስናይህ ጫማዎቻችንን አወለቅን’ አሉ። በዚህን ጊዜ እሳቸው ﷺ እንዲህ አሉ፡-
"إن جبريل أتاني، فأخبرني أن فيها قذراً؛ فألقيتهما، فإذا جاء أحدكم إلى المسجد؛ فلينظر في نعليه: فإن رأى فيهما قذراً؛ فليمسحهما، ولْيصلِّ فيهما"
‘ጂብሪል ከኔ ዘንድ መጥቶ በነሱ (በጫማዎቼ) ላይ ቆሻሻ እንዳለባቸው ሲነገረኝ አወለቅኳቸው። አንዳችሁ መስጂድ ሲመጣ ጫማዎቹን ይመልከት። ቆሻሻ ካየባቸው ይጥረጋቸውና ይስገድባቸው።’” [ሲፈቱ ሶላት፡ 80]
5. ከሸዳድ ብኑ አውስ ረዲየላሁ ዐንሁ ተይዞ ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡-
«خالفوا اليهود فإنهم لا يصلون في نعالهم ولا خفافهم»
“አይሁዶችን ተፃረሩ። እነሱ በጫማዎቻቸውና በኹፎቻቸው አይሰግዱምና።” [ሶሒሑል ጃሚዕ፡ 3210]
ማሳሰቢያ፡-
ባሳለፍናቸው አምስት ሐዲሦች በጫማ መስገድ እንደሚቻል አይተናል። ስላሳጠርኩት እንጂ ማስረጃዎቹ ከዚህም በላይ ናቸው። ትንሽ ሰፋ ያለ ነገር የፈለገ የሸይኽ ሙቅቢልን ረሒመሁላህ “ሸርዒየቱ ሶላቲ ፊኒዓል” ኪታብ ይመልከት። ነገር ግን:-
1ኛ፡- የሚሰገድበት ጫማ ንፁሕ መሆን አለበት።
2ኛ፡- በጫማ የሚሰገደው ለመታወቅ ወይም ተለይቶ ለመታየት አይነት ኒያ እንዳይሆን
3ኛ፡- ዛሬ ሰዎች ለሱናው ባይተዋር ሆነዋል። ስለሆነም በጫማ በመስገድ የሚነሳ ፈተና ካለ መታቀብ ያስፈልጋል። ጉዳትን ማስወገድ የሚወደድን/ የሚፈቀድን ነገር ከመፀም ይቀድማልና። በዚህን ጊዜ ወደ ተግባር ከመግባት በፊት ማስተማር ይቀድማል ማለት ነው።
4ኛ፡- በሶላትም ውስጥ ይሁን ከሶላት ውጭ ከአውሬዎች ቆዳ የተዘጋጀ ጫማ መልበስ አይቻልም።
[ለ] በጫማ መስገድ የተፈቀደ ወይስ የተወደደ?
በጫማ መስገድ እንደሚቻል ካለፉት ማስረጃዎች አይተናል። ግን ከነጫማ መስገድ የሚፈቀድ ብቻ ነው ወይ የሚወደድም ጭምር ነው? ሸይኽ ኢብኑ ዑሠይሚን ረሒመሁላህ በዚህ ጉዳይ ላይ ከጥንት ጀምሮ ውዝግብ እንደተከሰተ ከጠቀሱ በኋላ “የሚያደላው ይሄ ከሸሪዐዊ ድንጋጌዎች መሆኑ ነው፤ ስለሆነም የተወደደ ነው” ብለዋል። ለዚህም “አይሁዶችን ተፃረሩ። እነሱ በጫማዎቻቸውና በኹፎቻቸው አይሰግዱምና” የሚለውን ሐዲሥና ሌላም ማስረጃ ጠቅሰዋለል። [መጅሙዑ ፈታዋ ኢብን ዑሠይሚን]
[ሐ] በዘመናችን ባሉ መስጂዶች ውስጥ በጫማ መስገድ
በአሁ ሰዓት መስጂዶች ውድ ውድ ምንጣፎች ተነጥፎባቸዋል። ሰው ሁሉ ከነጫማው ቢገባ ምንጣፎቹ በቆሻሻ ይሞላሉ። ይሄ ደግሞ ሰጋጆችን ያስቸግራል። በዚህም የተነሳ ምንጣፍ በተነጠፉ መስጂዶች ውስጥ ከነጫማ መግባት አይገባም። ነገር ግን ከዚህ ሁኔታ ውጭ ከሆኑ (በቤታቸው ወይም ምንጣፍ በሌለባቸው ቦታዎች) ፍላጎታቸው ከሆነ ከነጫማቸው መስገድ ይችላሉ።
[መ] ሶላት ሊሰግድ ሲል ጫማውን ማውለቅ ከፈለገ የት ያድርግ?
በቀኙ በኩል ማስቀመጥ የለበትም። ስለዚህ በግራው በኩል ማድረግ ይችላል። በግራው በኩል ሌላ ሰጋጅ ከኖረ በግራ በኩል ማድረግ የለበትም። ምክንያቱም ለሱ በቀኝ በኩል ይሆንበታልና። በዚህን ጊዜ በእግሮቹ መሀል ያድርግ። ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡- “አንዳችሁ መስገድ ካሰበ ጫማዎቹን በቀኙ በኩል አያድርግ። በግራውም አያድርግ፣ በሌላ ሰው ቀኝ በኩል ይሆናልና - በግራው በኩል ማንም ከሌለ ነው እንጂ። (በግራ ሰው ከኖረ ግን) በእግሮቹ መሀል ያድርጋቸው።” [ሶሒሑል ጃሚዕ፡ 645]
=
(ኢብኑ ሙነወር፣ ሚያዚያ 17/2010)
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ገና ሰው ከፈጅር ሶላት እየተመለሰ 3 ትንንሽ ልጆቹን ከፊት ይዞ፣ ቦርሳዎቻቸውን ተሸክሞ እየተዋከበ ሲሄድ አየሁት። ባቅራቢያ የመንግስት ትምህርት ቤት ስለሌለ ራቅ ወዳለ ሰፈር መሄድ አለባቸው። ለዚያ ነው በማለዳ መውጣቱ። የትራንስፖርት መክፈል ስለማይችል ነው በሌሊት የሚያዋክባቸው። እያሰብኩት ቤቴ ገባሁ። ብዙ ነገር መጣብኝ። ለማስተማር ያለውን ቁርጠኝነት አሰብኩ። በዚህ ዘመን አለመማር እድሜ ልክ የሚዘልቅ ትልቅ ጠንቅ ነው። በዚህ በኩል ራሱን እያንገላታ፣ አካሉ አልቆ ለልጆቹ ትልቅ ውለታ እየዋለ ነው። ልጆች ይህንን ውለታ ይረዱ ይሆን? ለዲናቸውስ ይሄን ያህል ቦታ ይሰጥ ይሆን? አላህ ያግዘው። ለታክሲ የተቸገረው ሰው ቤት ውስጥ ኑሮው እንዴት ይሆን? ሳስበው ጨነቀኝ። ከሱም የባሰ ብዙ አለ። ግን በያካባቢያችን መቸገሩን የማይናገር ችግር ክፉኛ የሚያንገላታው ስንት ሰው አለ?! የጎረቤት ሐቅ እንዳያስጠይቀን እናስብ ይሆን? ለማንኛውም ነብዩ ﷺ እንዲህ ይላሉ፦
ليس المؤمنُ الذي يشبعُ وجارُه جائِعٌ إلى جنبهِ
"አማኝ ማለት ጎረቤቱ ከጎኑ እየተራበ የሚጠግብ ሰው አይደለም።" [ሶሒሑል ጃሚዕ፡ 5382]
ሸይኹል አልባኒይ ረሒመሁላህ በዚህ ሐዲሥ ስር እንዲህ ይላሉ፦
"ሃብታም ጎረቤት ጎረቤቶቹን እየተራቡ መተው ሐራም እንደሆነ በሐዲሡ ውስጥ ግልፅ መረጃ አለ። እናም ረሃብን የሚያስወግዱበት ያህል ሊሰጣቸው ግዴታ አለበት። ታርዘው ከሆነም እንዲሁ ሊያለብሳቸው ይገባል። ሌሎችም እነዚህን የመሳሰሉ መሰረታዊ ጉዳዮች ላይ እንዲሁ።" [አሶሒሐ፡ 1/230]
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
خطبة الجمعة
بتاريخ ١٤٤٤/٤/٢هجري
لفضيلة الشيخ دكتور إدريس إسماعيل محمد
في جامع نعمة المنان بمدينة لوغيا في إقليم العفر
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ዘፈኖችን የስልክ መጥሪያ ማድረግ በየትኛውም ቦታ አይፈቀድም። መስጂድ ውስጥ ሲከሰት ደግሞ ይበልጥ የከፋ ሐራም ይሆናል። ምክንያቱም:-
* የመስጂድን ክብር መዳፈር ነው።
* ለሶላት የማይመጥን ነውረኛ ተግባር ነው። ሰው እንዴት ከጌታው ፊት ቆሞ ይሄ ይሆናል?!
* ሰጋጆችን መረበሽ አለበት።
* መላእክትን አዛ ማድረግ አለበት። መላእክት ሰዎች በሚፈተኑበት ነገር ይፈተናሉና።
ስለዚህ የስልካችንን መጥሪያ የማይረብሽ፣ ዘፈን ያልሆነ ጠቋሚ ድምፅ ልንመርጥ ይገባል።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ኒካሕና ቃዲ
~
እንደሚታወቀው በኢስላም የትኛዋም ሴት ያለ ወሊይ ፈፅሞ ልታገባ አይፈቅድላትም። ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል:–
أَيُّمَا امْرَأَةٍ نُكِحَتْ بِغَيْرِ إِذْنِ وَلِيِّهَا فَنِكَاحُهَا بَاطِلٌ، فَنِكَاحُهَا بَاطِلٌ، فَنِكَاحُهَا بَاطِلٌ
"ያለ ወሊዩዋ ይሁንታ የተገባች የትኛዋም ሴት ጋብቻዋ ውድቅ ነው! ጋብቻዋ ውድቅ ነው! ጋብቻዋ ውድቅ ነው!" [አቡ ዳውድና ቲርሚዚ ዘግበውታል።]
ወሊይ ከሌለስ? በዚህን ጊዜ ኒካሑ በቃዲ ይታሰራል። ስለዚህ ኒካሕ ለማሰር ቃዲ የሚያስፈልገው ወሊይ ለሌላት ሴት ነው ማለት ነው። ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
َ (فالسلطان ولي من لا ولي له)
"አስተዳዳሪ ወሊይ ለሌለው ወሊይ ነው።" [አልባኒይ ሶሒሕ ብለውታል]
በተጨማሪም ወሊዮች ያለ ተጨባጭ ምክንያት ለመዳር ፈቃደኛ ሳይሆኑ ከቀሩም ኒካሑ በቃዲ ይታሰራል። ከዚህ ውጭ አባት ወይም ሌላ ወሊይ ወይም ወኪል ካለ ኒካሑን የሚያስሩት እነሱ እንጂ ቃዲዎች አይደሉም። ወሊይ ወይም ወኪሉ "ሰጥቻለሁ" ካለ፣ አግቢው ወይም ተወካዩ "ተቀብያለሁ" ካለ ኒካሕ ታስሯል። ኹጥባውን (ሸርጥ ካለመሆኑም ጋር) ወሊይ ወይም ሌላ ቦታው ላይ የተገኘ ሰው ሊያደርገው ይችላል።
ኒካሕ ለማሰር የተለየ ውስብስብ መስፈርት የለም። የዐረብኛ ቃላት መጠቀምም አይጠበቅም። ሌሎች መስፈርቶች እስከተሟሉ ድረስ በየትኛውም ቋንቋ ቢሆን መስጠትና መቀበል ከተገኘ ኒካሕ ታስሯል። ስለዚህ በሃገራችን በሰፊው እንደሚደረገው ወሊይ እያለ ቃዲ መጥራት አይጠበቅም። ቃዲዎች ወሊይ ባለበት ሁኔታ ኒካሕ ለማሰር አትቀደሙ። ያለ ስልጣናችሁ ጣልቃ አትግቡ።
ወሊይ የሆናችሁ ሰዎች ደግሞ ቃዲዎችን ለሰርግ ከጠራችሁ እንደማንኛውም እድምተኛ ተስተናግደው ይመለሱ እንጂ እዚያው ተቀምጣችሁ ለነሱ ውክልና አትስጡ። "ልጄን እከሊትን ድሬሃለሁ" ማለት ያቅታችኋል? ምንም የተለየ የተቀመጠ ቃል የለምኮ። እሱም "ተቀብያለሁ" ካለ፣ ቦታው ላይ ሁለት ታማኝ ምስክሮች ከኖሩ ኒካሑ ታስሯል አለቀ። ባገር እያለህ፣ ዐቅልህ ጤነኛ ሆኖ ሳለ እንዴት ከፊትህ ለሚፈፀም ጉዳይ ውክልና ትሰጣለህ? ምንም የሚያስፈራ ነገር የለምና እራስህ ፈፅመው። ሁሉም ነገር በቃዲ በኩል እንዲያልፍ መደረጉ አንዳንድ መረን የለቀቁ ባለስልጣናት በማያገባቸው የእምነታችን ጉዳይ ጣልቃ እንዲገቡ በር እየከፈተ ነው።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
