uk
Feedback
ㅤ♰ ማሕተቤ ✟

ㅤ♰ ማሕተቤ ✟

Відкрити в Telegram

“ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሂድ ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ።” — መዝሙር 122፥1 💬 ለማንኛውም ጥያቄና አስተያየት @Ortho_29 🙏 ♡ እንኳን ደኅና መጡ። ♡

Показати більше
Країна не вказанаКатегорія не вказана
291
Підписники
-124 години
+67 днів
+630 день
Архів дописів
“ለእኔ ግን ወደ እግዚአብሔር መቅረብ ይሻለኛል፤ መታመኛዬም እግዚአብሔር ነው በጽዮን ልጅ በሮች ምስጋናህን ሁሉ እናገር ዘንድ።”
  — መዝሙር 73፥28

​"አንድን ትልቅ እንጨት ብቻውን ካስቀመጥከው ነፍሳቶች በቀላሉ ይበሉታል፤ ከሌሎች እንጨቶች ጋር አንድ ላይ ካሰርከው ግን ሊሰብሩት አይችሉም። በክርስቲያኖች መካከል ያለው አንድነትም እንዲሁ ነው። ዲያብሎስ እኛን ለብቻችን ነጥሎ ሊያጠቃን ይፈልጋል፤ እኛ ግን በፍቅርና በአንድነት ከጸናን የገሃነም ደጆች እንኳ አይችሉን ."
+ ቅዱስ እንጦንስ +

“ብዙ ማር መብላት መልካም አይደለም፤ እንዲሁም የራስን ክብር መፈላለግ አያስከብርም።”
  — ምሳሌ 25፥27

photo content

ፍቅር ማለት የምትወደውን ሰው ስለ እውነት መታገሥ ማለት ነው። ፍቅር የበደልን አቧራ ያራግፋል እንጂ ቂምን አያበቅልም። እግዚአብሔርን መውደድህን የምታረጋግጠው በአጠገብህ ያለውንና የሚበድልህን ወንድምህን በፍቅር መሸከም ስትችል ብቻ ነው።" ​+ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ +

እደዚ አይነት እና የተለያዩ ነገሮችን የምታገኙበት በጣም አሪፍ ቻናል ነው ስለሀይማኖት ስለ አለም እውነታዎች እና የተለያዩ ሀሳቦች የሚሰነዘሩበት ቻናል ነው እደምትወዱር አልጠራጠርም ከስር link አስቀምጬላቹሀለው አንዴ በመንካት Join ብለው ይቀላቀሉ እደዚ አይነት አስተማሪ ናቸው ብዬ ያሰብኩትን የማመጣላቹ ይሆናል ሰላም እደሩልኝ 🥰 https://t.me/mezgebe_ewnet

የኖርዝ ካሮላይና መካነ አራዊት ለዝንጀሮዎች እና ለጦጣዎች የሠሩላቸው ቤት ልክ ከላይ በምስሉ ላይ እንደሚታዩት የላሊበላን ቤተክርቲያንን ኪነ ህንጻ በሚመስል መልኩ አድርገው ነው። የላሊበላ አብያተ ክ
+3
የኖርዝ ካሮላይና መካነ አራዊት ለዝንጀሮዎች እና ለጦጣዎች የሠሩላቸው ቤት ልክ ከላይ በምስሉ ላይ እንደሚታዩት  የላሊበላን ቤተክርቲያንን ኪነ ህንጻ በሚመስል መልኩ አድርገው ነው።  የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናት በኢትዮጵያም ሆነ በዓለም ወደር የማይገኝላቸው ቅርስ መሆናቸው እየታወቀ፣  የዝንጀሮዎቹን ቤት በዚህ መልኩ አስመስለው መሥራታቸው  ለቤተክርስቲያንም ሆነ ለኢትዮጵያ ያላቸውን ንቀት ማሳየታቸው ነው

ያከብርዋ ለሰንበት መላዕክት በሰማያት ጻድቃን በውስተ ገነት /2/ ወኩሉ ፍጥረት አሳት ወአናብርት እለ ውስተ ደይን ያእረፉ ባቲ እስመ ባቲ አእረፈ እምኩሉ ግብሩ 💗

“ለእግዚአብሔር የምስጋናን መሥዋዕት ሠዋ፥ ለልዑልም ስእለትህን ስጥ፤”
  — መዝሙር 50፥14

ኃጢአት ላለማድረግ በግልጽም በስውርም ስትጋደል ያየህም ያላየህም ሰው አይቶ ሰምቶ ሲፈርድብህ፣ ”አልቀረብህም” ሲልህ… ግልጽና ስውር ትግልህን አይቶ ለመተው መሞከርህን ተመልክቶ ስለትግልህ ዋጋ ኃጢአ
ኃጢአት ላለማድረግ በግልጽም በስውርም ስትጋደል ያየህም ያላየህም ሰው አይቶ ሰምቶ ሲፈርድብህ፣ ”አልቀረብህም” ሲልህ… ግልጽና ስውር ትግልህን አይቶ ለመተው መሞከርህን ተመልክቶ ስለትግልህ ዋጋ ኃጢአቱን የሚያስተውህ እግዚአብሔር ነው! ዲ/ን ዘለዓለም ታዬ

​“በደስታም ለእግዚአብሔር ተገዙ፥ በሐሤትም ወደ ፊቱ ግቡ።”
  — መዝሙር 100፥2

‛‛የራስህን ድካም ማወቅ፣ መላእክትን ከማየት የበለጠ ታላቅ ጸጋ ነው።’’
                         ቅዱስ ይስሐቅ ሶርያዊ ~ ㅤ    ❍ㅤ     ⎙ㅤ   ⌲             ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢᵃᵛᵉ    ˢʰᵃʳᵉ

"በሃይማኖት ጥንቃቄ እንጂ ምናለበት አይሠራም፤ ጥንቃቄ ፍጻሜው ሕይወት፣ ምናለበት መድረሻው ሞት ነው!"
(ቅ. ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ)

_"ጌታ ሆይ፣ ዛሬ መስቀልህን አስባለሁ። የእኔንም መስቀል የመሸከም ኃይል ስጠኝ። አሜን። #መልካም_እለተ አርብ"_

ሕይወታችሁ ምንድር ነው? ጥቂት ጊዜ ታይቶ ኋላ እንደሚጠፋ እንፍዋለት ናችሁና። በዚህ ፈንታ። ጌታ ቢፈቅድ ብንኖርም ይህን ወይም ያን እናደርጋለን ማለት ይገባችኋል። አሁን ግን በትዕቢታችሁ ትመካላችሁ፤ እንደዚህ ያለ ትምክህት ሁሉ ክፉ ነው። እንግዲህ በጎ ለማድረግ አውቆ ለማይሠራው ኃጢአት ነው።
 😇የያቆብ መልክት 4 ፥14-17

​“የጭንቀት ቀን ሳይመጣ በጕብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስብ፤ ''
   መክብብ 12፥1

ከተኛሁበት የኃጢአት አልጋ ተነሥ ልትለኝ ወደ እኔ መቼ ትመጣለህ?
“ማዕዜ ትመጽእ ኀቤየ”

😇 " ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደሚመስላቸው ጌታ ስለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም፥ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንዲደርሱ እንጂ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ስለ እናንተ ይታገሣል።"🧡
😇(2ኛ የጴጥሮስ መልእክት 3:9)

ንስሐ🙌 🛜 ንሰሐ ሰው ሕይወቱን ወደተሻለ ደረጃ ለመለወጥ የሚያስችለው መንፈሳዊ ጥንካሬ ወይም ኃይል ነው:: 💙ንስሐ በልቡናችን ውስጥ ከፍተኛ የሆነ ፍቅረ እግዚአብሔር እንዲወለድ ያደርጋል:: 🔻ምክንያቱም በንስሐ ሕይወት የምንኖረው ከሆነ እግዚአብሔር ስለ እኛ ብሎ የተሸከመልንን ሸክምና ይቅር ያለንን እጅግ የከፋ ኃጢአት እንድናስብ ስለሚያደርግና ለእግዚአብሔርም ያለን ፍቅር እያደገ ስለሚሄድ ነው::

“ጽድቅንና ምሕረትን የሚከተል ሕይወትንና ጽድቅን ክብርንም ያገኛል።”
  — ምሳሌ 21፥21