uk
Feedback
Haala Ilaalcha Ortodoksii(ኦርቶዶክሳዊ ማዕቀፈ እሳቤ)

Haala Ilaalcha Ortodoksii(ኦርቶዶክሳዊ ማዕቀፈ እሳቤ)

Відкрити в Telegram

Waa'ee Mana Kiristaanaa Fi Biyya Keenyaa Haala Ilaalcha Ortodoksiin Hubachuu የቤተክርስቲያናችንና ሀገራዊ ሁኔታዎችን በኦርቶዶክሳዊ ማዕቀፈ እሳቤ መረዳት

Показати більше
Країна не вказанаКатегорія не вказана
273
Підписники
Немає даних24 години
-37 днів
-1330 день
Архів дописів
  የብልጣብልጦች ቢዝነስ በቤተ ክርስቲያን 1) ጵጵስና  ፦በወር  ከ50ሺ እስከ 70ሺ ብር ደምወዝ ያስገኛል።በዚህ ላይ ከቦታ ቦታ በተንቀሳቀሱ ቁጥር  አበል ይከፈላል።ከሙዳየ ምጽዋት አለ።የሀብታም ማዕድ በመባረክ የሚገኝ ብር አለ። አሜሪካና አውሮፓ ሲኬድ  የሚቀፈል የዶላር አለ። ታቦት በመነገድ የሚመጣ ብር አለ።ለኪስ ተብሎ በዓመት እስከ 300ሺ ብር ይሰጣል። 2) የከተሜ ምንኩስና፦የመነኩሴ መናሪያ ገዳም ነው ከተማ ለከተማ የሚዞሩት ምንኩስናን ለጽድቅ ሳይሆን ለእንጀራ መብያነት ይጠቀሙበታል።ሰብስቦ ወደ ገዳም መሸኘት ያስፈልጋል። 3)  አስተዳዳሪነት፦አንድ ሰው እንደምንም ብሎ ወደ አስተዳደርነት ከመጣ  ከአንድና ከሁለት ዓመት በኋላ ዘመናዊ መኪና ይገዛል ቪላም ይገነባል ዘመዶቹን በሙሉ በ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ይሰበስባል።ዋሸሁ እንዴ? 4) በአንድ አጥቢያ ብዙ ታቦታትን መደራረብ ፦  በአንድ አጥቢያ ብዙ ታቦታትን በማብዛት በነዚህ ታቦታት ወራዊና ዓመታዊ በዓላት ሚነግሱበት ዕለት ይኽን አመካኝቶ የሕዝቡን ኪስ ማጠብ ከዚያን ለግል ዓላማ ማዋል። 5) የሕንጻ ግንባታ፦ የተሠራ ቤተ ክርስቲያን እያለ ሌላ ቤተ ክርስቲያን  መጀመር ከዚያን ቶሎ ተሠርቶ እንዳያጠናቀቅ ማዘግየት።ሕንጻው ቶሎ የሚጠናቀቅ ከሆነ  የሕዝቡን ኪስ ለማጠብ አይመቻቸውም። ስለዚህ ያላቸው አማራጭ ሕንጻው ቶሎ እንዳይልቅ ማጓተት ነው።በደብራችሁ ይኽ የለም? 6) ጉባኤያትን ማብዛት፦ የጉባኤ ትልቁ ዓላማ ወንጌልን ማስተማር ቢሆንም ቅሉ ትንሽ ቆሎ ይዘው ወደ አሻሮ ጠጋ እንዲሉ አበው በወንጌሉ አመካኝቶ"  ካባ ለባሽ ፕሮፌሽናል ለማኞችን" ተከራይቶ በማምጣት ሕዝቡን በሆሆህታ ሞቅ ሞቅ እያደረጉት እያካዋከቡት  የቅዱሳንን ስም እየጠሩ እስቲ በእገሌ አማላጅነት የምታምኑ እጃችሁን ከፍ አድርጉት ከፍ ከፍ ይህ እጃችሁ እንዲባርክ አጨብጭቡበት 😂ከዚያን ወደ ኪሳችሁና ቦርሳችሁ ክተቱት😂 በሉ በኪሳችሁና በቦርሳችሁ ያለውን አውጥታችሁ ስጡ።ስጡ! ዛሬ ቤታችሁ ሁሉ ሙሉ ሆኖ ይቆያችኋል።እንዲህና እንዲያ እያሉ ኑሮ ከብዶት መሄጃ ያጣውን ምስኪኑን ሕዝብ ያጥቡታል። 7) ሰባኪነት፦ ይኽም ወፍራም ብሮችን ያስገኛል።አንድ ሰባኪ ከአዲስ አበባ ተነስቶ ጎንደር ወይም ሐዋሳ ለመሄድ ከ100ሺ እስከ 200ሺ ልጠይቅ ይችላል።ይኽ ካስተሟላለት አይንቀሳቀሳት። 8)  ዘማሪነት፦ ይልቁኑ የእመቤታችን ስም ጥሩ የእንጀራ መብያ ሆኗል።ተራራውን ወጣሁ፣ቁልቁለቱን ወረድሁ፣ወንዙን ተሻግርሁ፣ጫካውን አለፍሁ፣ጓደዬን ሞላ ወዘተ...የሚሉ ለዘፈን የቀረቡ መዝሙሮችን ዩቲዩብ ላይ ትለቃለህ 200ሺ ተመልካች ታገኛለህ ።የተዋጣለት የመዝሙር ነጋዴ ትሆናለህ። 9) አጥማቂነት፦አጥማቂነት ክህነት ያላቸው ሰዎች ሁሉ የሚከውኑት አገልግሎት እንጂ ለጥቂቶች ብቻ የሚሰጥ ጸጋ አይደለም።ብዙዎች ግን የማጥመቅ ጸጋ ተሰጥቶናል እያሉ  ምስኪኑን ሕዝብ ይነዱታል ኪሱንም ያጥቡታል።እነዚህ ሰዎች   ሕዝቡን በመዝረፍ በኢኮኖሚ የበለጸጉ ናቸው  በአሜሪካ ሳይቀር ሰፊ መሬቶችን ገዝተው የግል ቤተ ክርስቲያን እስከጳጳሳትን ሳይቀር 10)የከተሜ  ንስሐ አባት መሆን፦ ከንስሐ ሌጆቻቸው ገንዘብ መሰብሰብ ከዚያን ከጥቂት ዓመታት በኋላ ባለቤት ባለ መኪና መሆን።  ንስሐን በብር መግዛት ይሉሃል ይኽ ነው።እውነተኛ ካህናት እናንተን አይመለከትም። 11)  ደብተራነት(መርጌትነት)፦ ደብተራነት የእውቀት ማደርያ መሆን ነው።ግብዞች ግን በዚህ ስም ተጠቅመው መስተፋቅር እንሠራለን፣ ገንዘብ እንድታገኙ እናደርጋለን ወዘተ... እያሉ  ሚሊየኖችን ያታልላሉ ።አሁን አሁንማ ተራ ሰዎች ሳይቀሩ በቴሌግራም  መርጌታ እገሌ እያሉ  በማጭበርበር ላይ ይገኛሉ። 12)የሚዲያ ልመና፦ በቲክቶክና በዩቲዩብ ፕላትፎርሞች ቤተ ክርስቲያን እንረዳለን፣ቤተ ክርስቲያን እናሠራለን በማለት የሕዝቡን ኪስ ማጠብ 13) የቲክቶክ ሰባኪ፦በዓረብ ሀገራት ያሉ ምስኪን እህቶቻችንን ለማለብ።እውነተኛ መምህሮችንና ወንድሞችን አያካትትም። 14)ባዛር፦በበረከት ስም የሕዝቡን ኪስ ማጠብ 15) ጉዞ ማዘጋጀት 16) ማኅበራትን መፈልፈል 17) ጸበል፦ጸበልን ለፈዋሽነት መጠቀሙ ቀርቶ የሕዝብ መሰብሰቢያና የገንዘብ ማግኛ ሆኗል። https://t.me/Eyo21e

አለመጠርጠር ጅልነት ነው ጀርመኖች 6 ሚሊየን አይሁዳውያንን ለመጨፍጨፍ ያመቻቸው ዘንድ አስቀድመው ደኅንነታችሁን ልናስጠብቅላችሁ ነው ፣ ዳግም ልናሰፍራችሁ ነው በማለት አታለው ከሕዝቡ ለይተው ካስወጧ
+1
አለመጠርጠር ጅልነት ነው ጀርመኖች 6 ሚሊየን አይሁዳውያንን ለመጨፍጨፍ ያመቻቸው ዘንድ አስቀድመው  ደኅንነታችሁን ልናስጠብቅላችሁ ነው ፣ ዳግም ልናሰፍራችሁ ነው በማለት አታለው ከሕዝቡ ለይተው ካስወጧቸው በኋላ በተዘጉ ከተሞች ውስጥ ሰበሰቧቸው። ይኽን ካደረጉ በኋላ ነው ሠራዊት አሰማርተው የፈጇቸው ። የሽርካ ኦርቶዶክሳውያን እጣፈንታ እንዲህ እንዳይሆን ያሰጋል።አለመጠርጠር ጅልነት ነው።ከወረዳው ተሰደው በቆጂ ከተማ የተጠለሉት  እነዚህ ኦርቶዶክሳውያን ዳግም ወደ ወረዳቸው መመለሳቸው ይበል የሚያሰኝ ነው  ነገር ግን  በአንድ አከባቢ ላይ ብቻ ማስፈሩ አደጋ አለው።ዳግም መጥተው እንደማይጨፈጭፏቸው በምን እርገጠኞች እንሁን? ሥርዐቱ ኦርቶዶክስን የጥቃት ዒላማ አድርጎ በሚንቀሳቀስበት በዚህ ዘመን አለመጠርጠር  ጅልነት ነው።መፍትሔ የሚሆነው የኦርቶዶክሱን  ኅልውና ማስጠብቅና በራሱ ርስት ላይ እንዲኖር ማድረግ ነው።የሽርካ ኦርቶዶክሳውያን ሆይ ጥንቃቄ አይለያችሁ ።

የብሔርተኝነት የመጨረሻው የድንቁርና "የብቃት ደረጃ" ላይ ስትደርስ እግዚአብሔርን መምሰል ትተውና ጎሣህን፣ባህልህን፣ቋንቋህን፣ጎጥህን፣የፖለቲካ ፓርቲህን የሚመስል እግዚአብሔር መፈልግ ትጀምራለህ።እኛስ በዚህ መንገድ ላይ አይደለንም ወይ?

ፖለቲካና ሃይማኖት በሥጋና በደም፣ በአጥንትና በጅማት ተያይዙ በእስትንፋስ የሚመላለስ ክርስቲያን በዚህ ምድር ላይ ሲኖር ለቁመተ ሥጋው የሚከተሉት ወሳኝ 4 ሀብታት ያስፈልጉታል ብዬ አስባለሁ፦ 1) #የተፈጠሮ #ሀብትን ።፦ ይህን ሀብት ከማንም ከሌላ ወገን ቁጥጥር ውጭ እግዚአብሔር እንደሰጠው በሚያስፈለገው ልክ የመጠቀም ሙሉ ዋስትና (ውሃ፣ አፈር (ማዕድናት)፣ ዕጽዋት፣ የፀሐይ ብርሃን፣ አየር፣ እሣት/ኃይል)፤ 2) በማኅበረሰብ ማኅቀፍ ውስጥ  አዎንታዊነት ያለው ማኅበራዊ  የቤተሰብ ግኑኝነት፣ የታወቀ ሥርዓት፣ የአኗኗር ደንብ፣ እና  መዋቀር፤ 3) ሥርዓተ መስተገፈጋብር:- የማኅበረሰቦች ትሥሥር፣ የተፈጥሮ ሀብት ፍትሐዊ አጠቃቀም ሥርዓት፣ የመብቶች ጥበቃ፣ ልማት፣ ክፍፍል፣ ዋስትና የሚያረጋግጥ መንግሥታዊ ሥርዓትና መዋቅር፤ 4) ሥጋውን በተፈጥሮ እና ማኅበራዊ ሀብታት፣ ነፍሱን  በተስፋ፣ በእምነት፣ በፍቅር ገርቶ ለራሱና ለሌላው የሰው ልጅ ሁሉ እንቅፋትና አጥፊ እንዳይሆን የሚመራ  መንፈሳዊ ትምህርት፣ የሚቀደሰበት የሚሥጢራት አገልግሎትና እረኝነት፣ 4ቱ ለሰው በዚህ ዓለም በምድር የመኖር መሠረቶች  እንዲገኙ  እና እንዲጠበቁ ሥራዓተ መንግሥትና ሥራዓተ ማኅበረሰብ፣ ሥርዓተ ቤተሰብ እና ሥርዓተ አምልኮ በዘለቄታዊነትና በአስተማማኝ መሠረት ላይ  የአንድን ቤተሰባዊ፣ ማኅበረሰባዊና አገራዊ   አስተዳደር ያስፈልጋል።  አስተዳደር ፖለቲካዊ ነው። አንድ አዋጭ  የፖለቲካ ሥርዓት ደግሞ  ሥርዓቱ የሚመራበት ነጽሮተ ዓለምና የሚጠበቅበት ሕግ ያስፈልገዋል። ---- ሥርዓቱን፣ ሕጉንና ተግባራዊነቱን የሚቆጣጠር ሥርዓታዊ የመዋቅራት መስተጋብር ጥበቃ የሚደረገው በፖለቲካ ነጽሮት በሚበጅ ሕግና መዋቅር  ነው።  ፖለቲካው ጤናማ እንዲሆን ፈሪሃ እግዚአብሔር ያላቸው፣ የሰው ልጅን ክብር የሚያውቁ፣ የሞራል ልዕልና እንዳላቸው በሕይወታቸው ያስመሰከሩ፣ ለባእዳንና ለግል ፍተወታቸው ባርያ ያልሆኑ፣ ለፍትሕና ለእውነት መስክረው በነፍሳቸው እንኳ ዋጋ ለመክፈል የተዘጋጁ ሰዎች  መሆን አለባቸው።  እንዲህ አይነት ሰዎች በርግጠኝነት የሚግኙት ከኦርቶዶክሳውያን ከርስቲያኖች መካከል ነው።  በ2000 የኢትዮጵያ የተምዘግቦ ታሪክ (የነገሥታትን ግለሰባዊ ስሕተቶችና እብደቶች ሳንጭምር) በአስተምህሮና በተግባር ከኦርቶዶክሳውያን በቻና ብቻ ነው። ---- ሌሎች ምን አደረጉ? መልሱ 👉 አህመድ ግራኝ፣ 👉 የገዳ የሉባዎች የምሰፋፋት ዘመን ፍጅት፣ 👉 የዮዲት የሺ ዘመናት ሥልጣኔ ውድመት፣ 👉  የጣሊያን ዘር የማጥፋት ሙከራ፣ 👉በፖርቱጋል እና ሮማ ሚሽነሮች ያበዱ መሳፍንቶች፣ 👉 የማርክሲስት አብዮተኞች፣ 👉 የሕወሃትና የኦነግ አገር ይማፈርሰና ዘር ያማጥፋት ፕሮጄክት እና በብልጽግና የቀጠለው ውድመት --- ---ምስክሮች ናቸው!!! ኣትዮጵያዊነት ያነጸው ነባር እስልምናም ከኦርቶዶክሳዊ ክርስታያን የተቀሬረበ ሰብእና ያፈራ በመሆኑ ሁለቱ ተባብረው አገራቸውን ማዳን አለባቸው። ስሐዚህ ኦርቶዶክሳውያን ፖለቲካውን ለመቀደስ ቀኢትዮጵያዊነት ከታነጸው ባህል፣ እምነት ወጥተው ለባእዳን መገልገያ ከሆኑት በክርስትናና እስልምና ስም መለያየትና መጠፋፋትን ከሚያራምዱ  ቡድኖች እጅ ፖለቲካውን ነጻ ማውጣት አለባቸው። መ/ር ፋንታሁን ዋቄ

ጥያቄ ለታች ሰፈር ሰዎች ኦርቶዶክስ "ኦሮሞን አጥምቃ አማራ ካደረገች " አማራውንስ አጥምቃ ምን ታደርጋለች ?ሌሎች ማኅበረሰቦችንስ አጥምቃ ምን ታደርጋለች?

በ"አዲሲቷ ኢትዮጵያ"ርዕዮተ ዓለም ኦርቶዶክስ ጠልነት እንደ ባህል እንደ አንድ ማኅበራዊ ሕይወት ይቆጠራል

miidhaa fi cunqursaan Mana Kiristaana Ortoodoksii Tawaahidoo Itoophiyaafi ijoollee ishee irra gahaa jiru  gabaabinaan:- 1. Mana Kiristaanaa irratti seenaa fi oduu sobaa uumuu . 2. Sadarkaa mootummaa fi hoggansa kamiyyuu keessaa fageessuu fi alatti dhiibuu. 3. Maanifeestoo fi Imaammata hordoftoota Ortoodoksii irratti xiyyeeffate qopheessuu. 4. "Itoophiyaa Haaraa" uumuun pirojektiwwan jibbiinsa Ortoodoksii irratti hundaa'an dhimma hojii godhachuu. 5. Hordoftootoonni Ortoodoksii  ፦jumlaan ajjeefamuu, baqachuu, duguuginsa sanyii, fi fincilummaa mootummaa akka waan salphaatti baran gochuu, akkasumas Ortoodoksii miidhuun akka aadaatti akka fudhatamu gochuu. 6. Gocha lakkoofsa shan (5) irratti tarreeffaman erga barsiisanii booda hordoftoota Ortoodoksii irratti tarkaanfii miidhaa qaamaa kallattiin fudhachuu. 7. Manni Kiristiyaanichaa akka dhaabbataatti akka laaftu gochuu:    👉Sinoodosii irraa kaasee hanga namoota dhuunfaatti bakka bu'aa dhabsiisuu.    👉Jeequmsa uumuu.    👉Caasaalee ishee hundiinuu basaastotaan akka qabaman gochuu.    👉Hayyama malee baajata ishee saamuun fudhachuu.    👉Waldaalee jajjaboo  ta'an laamshessuu fi dadhabsiisuu.    ✍Sinoodosichi ijoollee isaa akka baraarree gochuu. 8. Keessaas ta'e alaa namni sagalee isaa dhageessisu fi "maaliif" jedhee gaafatu akka hin jirre erga taasisanii booda, Dhoorkas Tokko Malee Ortoodoksoota balleessuu. 9. Hordoftoota Ortoodoksii irratti miidhaa gama hundaan geessisuu; warri du'a irraa oolan dhiphachaa akka jiraatan, boqonnaa sammuu akka dhaban, bahanii galuu fi galanii Bahuun akka itti ulfaatu gochuu. 10. Naannoolee hawaasni Ortoodoksii baay'inaan keessa jiraatan xiyyeeffannoo miidhaa godhachuu; waraana dheeraa xumura hin qabne kan biyyoonni alaa (kan akka Emirates) keessatti hirmaatan gaggeessuun Ortoodoksoota Ajjeesuu, xiqqeessuu fi dadhabsiisuu. 11. Paastaroota  fi namoota sobdootaan maqaashee xureessuu, duudhaalee ishee gadi xiqqeessuu, fi raajii badinsaa akka irratti dubbatan gochuu. 12. Wahaabiyyoota (Musliimota Shororkeessitoota) ijaaruun Ortoodoksii irratti olola propagaandā, miidiyaa hawaasaa fi miidhaa qaamaa akka geessisan gochuu. 13. Sinoodosii Duuka bu'oota irraa adda bahee, siyaasa jibbiinsa Ortoodoksii irratti hundaa'een Sinoodosii  gandaa uumuun ajjeechaa raawwachuu fi tokkummaa Ortoodoksii diiguu. 14. Ijoollee ishee dammaqoo ta'an kanneen manneen barnoota gubaa'ee, waldaalee, manneen barnoota sanbataa, daldala, Siyaasaa, fi dhaabbata barnootaa keessatti argaman ari'achuu, dhiphisuu, hidhuu fi ajjeesuun Ortodoksoonni sagalee akka dhaban gochuu. 15. Manni Kiristaanaa dhiphina kanneen keessa utuu jirtuu yeroo itti deebitee of jabeessituu fi boqonnaa akka hin arganne  gochuu Furmaanni Maali?   👉 Haalota jiran sirriitti hubachuu: Waan kaleessa nurra gahe, waan amma nurra gahaa jiru, fi waan boru  nurra gahuuf karoorfame gadi fageenyaan beekuu. 👉 Tokkummaa uumuu: Waee dhaabbata Mana Kiristiaana Ortoodoksii tokkittii ilaalchisee hidhata keessoo jabaa fi hin cinne uumuu. 👉 qaamaa Bilisa Baasaa Eeggachuu Dhiisuu Hundi keenya qaama furmaataa kallattii ta'uu. 👉 Gufuu fi lallaba  sammuu Namaa hadoochan adda baasan hin dhaga'u jedhanii diduun dhaabbachuu.   👉 Kadhachaa hojjechuu, hojjechaa kadhachuu: (Hojii fi Amantii qindoominaan gaggeessuu). https://t.me/rete14

በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንና ልጆችዋ ላይ እየደረሱ ያሉ ሥርዐታዊ፣መዋቅራዊና ርዕዮተ ዓለማዊ በደሎች ከብዙ በጥቂቱ 1) በ ቤተ ክርስቲያንቱ ላይ የውሸት ትርክት መፈብረክ 2) ከየትኛውም የሥልጣን  ከመሪነት እርከን ማግለል 3) ኦርቶዶክሳውያንን ታርጌት ያደረገ ማኒፌስቶና ፖሊሲ መቅረጽ 4)ኦርቶዶክስ ጠልነት የ"አዲሲቷ ኢትዮጵያ "የፕሮጄክት አካል ይደረጋል 5) ኦርቶዶክሳውያን፦ነውርን፣በጅምላ መገደልንና መሰደድን  ፣የዘር ፍጂትን ማለማመድ፣ሥርዐታዊ ውንቡድናን እንዲለማመዱ ማድረግ ፣ኦርቶዶክሳውያንን ማጥቃት እንደ ባሕል እንዲቆጠር ማድረግ 6)ቁጥር አምስት (5) ላይ የተዘረዘሩ በደሎችን ካለማመዱ በኋላ ኦርቶዶክሳውያን ላይ ተግባራዊ ጥቃት ማድረግ 7) ቤተ ክርስቲያን በተቋም ደረጃ እንድትዳከም ማድረግ 👉ከሲኖዶስ ጀምሮ እስከ አንድ ግለሰብ  ተወካይ ማሳጣት 👉ሁከት መፍጠር 👉መዋቅሮቿ ሁሉ በሰላዮች እንዲያዙ ማድረግ 👉ሳያስፈቅዱ በጀቷን መቀማት 👉 ጠንካራ ማኅበራትን ማዳከም ሽባ ማድረግ 👉ሲኖዶሲ ልጆቹን እንዳይታደግ 8) ከውስጥም ከውጭም ጯሂ ለምን ብሎ የሚጠይቅ እንዳይኖር ካደረጉ በኋላ ያለ ከልካይ ኦርቶዶክሳዊነትን ማጥፋት 9) ኦርቶዶክሳውያን ላይ ሁለገብ ጥቃት ማድረስ፣ከሞት የተረፉት እንዲሳቀቁ የእዕምሮ እረፍት እንዳይኖራቸው፣ገብተው መውጣት ፣ወጥተው መግባት እንዳይችሉ ማድረግ 10) ኦርቶዶክሳዊው ማኅበረሰብ የሚበዛባቸው አከባባዊዎችን የጥቃት ዒላማ ማድረግ፣ዉክልና ያለው እንደ Emirates ያሉ ሀገራት የተሳተፉበት ተራዛሚ  የማይቋጭ ጦርነት ማካሄድ ኦርቶዶክሳውያንን መጨድጨፍ፣ማሳነስና ማዳከም 11)በወጠጤ ፓስተሮችና ዉሸታም ሰዎች ስሟን እንዲያጠለሿት፣እሴቷን እንዲያናኑ፣የጥፋት ትንቢት እንዲተነብዩባት ማድረግ 12)  ወሀቢስቶች(አክራሪ ሙስሊሞች) በማደራጀት ኦርቶዶክሳውያን ላይ የፕሮፓጋንዳ፣ የማኅበራዊ ሚዲያ፣አካላዊ ጥቃት እንዲያደርሱባት ማድረግ 13) ከሐዋርያት ሲኖዶስ የተለየ በኦርቶዶክስ ጠል ፖለቲካ የሚመራ የሰፈር ሲኖዶስ በመፈበርክ እልቂት መፈጸም ፣ኦርቶዶክሳዊ ኅብረትን መበተን 14) ቀድመው የነቁ በጉባኤ ቤት፣በማኅበራት፣በሰንበት ትምህርት ቤት፣በንግድ፣በፖለቲካ፣በትምህርት ተቋማት ወዘተ...ውስጥ ያሉ  ልጆችዋን በማሳደድ ፣በማሳቀቅ፣በማሰርና በመግደል ኦርቶዶክሳውያን ድምፅ የሚሆናቸው እንዲያጡ ማድረግ 15)ቤተክርስቲያን በዚህ ሁሉ ስቃይ ውስጥ ሆና  የማገገሚያ ጊዜ እረፍት እንዳተገኝ  ያለማቋረጥ መነዝነዝ መፍትሔው ምንድን ነው? 👉ሁኔታዎችን በትክክል መረዳት፦ትናንት የሆነብንን፣አሁን እየሆነብን ያለውን ፣ነገ ይሆንብን ዘንድ የታቀደውን 👉 ስለ አንዲት ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ትስስር መፍጠር 👉ነጻ አውጪ አለመጠበቅ ሁላችንም የመፍትሔው አካል መሆን 👉አደናቂፊ እና አደንዛዥ የሴራ ሰበካዎችን ለይቶ እምቢ አልሰማም ማለት 👉እየጸለዩ መሥራት እየሠሩ መጸለይ https://t.me/rete14

          ◈ርቱዓዊ ልምምድ፦ ◈ርቱዓዊነት በሕይወት በር እየተመላለሱ የተስፋ ፍጻሜን ለማግኘት በጸናች በቀናች ሐዋርያዊት ጉባኤ ውስጥ የተዋሕዶት ልምምድ ማድረግ ነው። ◈ወይም በዚህች ርትዕት ሐዋርያዊት ጉባኤ ውስጥ እስከ ፍጻሜ ድረስ የእውነት በሩን ሳይለቁ  በግብርም በነገርም የጸና የቀና ክርስቲያን የመሆን ልምምድ ነው። ◈ወይም በሐዋርያዊት ጉባኤ ውስጥ ሁኖ ርቱዓዊነትን በማወቅ እና በመረዳት ላይ ተመሥርቶ የመሆን ልምምድን እያስቀደሙ እስከ ህቅታ ድረስ የመዳን መንገድን ለመጨረስ ሳያቋርጡ ወደ ምድረ ርሥት መጓዝ ነው። ◈ቅዱስ ፍጹም ሐዋርያዊ ተስፋን መውረስ የሚቻለው በዚህ ሕያው መንገድ ነውና።"አመንኩ በዘነበብኩ-የተናገርሁትን አመንሁ።"መዝ.፻፲፭፥፩እን. የአፍ ሌላ የልብ ሌላ ሳይሉ ያመኑትን በሕይወት ልምምድ እየኖሩ ማሳየት የሚቻለው በርቱዓዊነት ልምምድ ውስጥ ነው። ◈የርቱዕነት መነሻው ከእግዚአብሔር ለቅዱሳን የተሰጠው፦ርቱዕ ክሡት ፍጹም የሆነው አስተሳስብ ነው። ◈በዚህ መንገድ፦ረቂቁን ከግዙፉ፣ቋሚውን ከሀላፊው፣እውነቱን ከሀሰቱ፣ጽኑዑን ከወጪ ወራጁ በመለየት የሀሳባትን ቅደም ተከተል በመረዳት ጥርት ያለ ርቱዕ ሐዋርያዊ ህሊናን መፈለግ ነው። ◈ሀሳበ እግዚአብሔር፣ሀሳበ መላእክት፣ሀሳበ ሰብእ፣ሀሳበ ደማውያን፣ሀሳበ ዕፅዋት፣ሀሳበ ፍጥረታት አለ፤ ◈ከዚህ ሁሉ ሀሳብ መካከል ለድኅነተ ነፍስ ለርቱዓዊነት የሚበጀንን መለየት እና ሁሉንም በየመልኩ ተረድቶ በርቱዓዊነት መሠረት ላይ ጸንቶ በጠራ ህሊና መገለጽ ያስፈልጋል። ◈ደግሞም ከአቅማችን ድካም የተነሣ ወደ ጽሩይ ህሊና ገብቶ ልቡናን አስፍቶ አእምሮን አቅንቶ መለማመድ እና ከፍ ያለውን ጣዕመ ምሥጢር ማየት ቢያቅተን ወደ ባለቤቱ እንለምናለን፦ "ወንስአል አንቃዲወነ ላዕለ ወሶቤሃ ይሠርቅ ለነ ብርሃን እምነ መጻሕፍተ መለኮት ወእምኔሆሙ ንበርህ በአስማተ ቅድስት ሥላሴ ዘውእቱ እምነትነ- ወደላይ አቅንተን እንለምን ያንጊዜ የመለኮተን ነገር ከማናገሩ መጻሕፍት ዕውቀት የገልጽለናል ከእነርሱም የሦስቱን ስም በመጥራት አዋቆች እንሆናለን ይሄውም ማመናችን ነው።"ሃይ.አበ.፲፥፪እን.

እብድ ፖስተሮችን አሰማርቶ ቤተ ክርስቲያንቱን የመነዝነዝ መንግሥታዊ ሴራ

እነዚህን ሰዎች አባት ብለን የምንቀልብበት አንዳች ምክንያት የለም
+3
እነዚህን ሰዎች አባት ብለን የምንቀልብበት አንዳች ምክንያት የለም

ወንድማዊ መልእክት ለኦሮሚኛ ተናጋሪ ኦርቶዶክሳውያን፦ 1) በአራቱም አቅጣጫ ያለው ኦርቶዶክስ የጥቃት ዒላማ ቢሆንም  ቀድሞ ዘሩ ከምረ ገጽ የሚጠፋው በኦሮሚያ ክልል ያለው ኦርቶዶክስ ነው። እየሆነ ያለውን እናስተውል። 2) በማይረባ አጀንዳ ላይ መንጫጫት እናቁም። 3) አንዳንዶቻችሁ ያለ ጸጋችሁ የንጽጽር ትምህርት እያላችሁ 24  ሰዓት ሚዲያ ላይ ተጥዳችሁ ትውላላችሁ ። እንዲህ ዓይነት አገልግሎቶችን እንደ እፎይ ላሉ ብርቱ ወንድሞች እንተውላቸውና ኦርቶዶክሳውያንን የማንቃት ሥራ ላይ እንረባረብ።ቅድሚያ ለ ኅልውናችን። 4) በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ፎቶአችንን ከምንፖስትና  በኮሜንት ጋጋታ ነፍሳችንን ከምናጎላቁል የኦርቶዶክሳውያንን ሰቆቃ የቤተ ክርስቲያንን ስደት የሚያሳዩ ጽሑፎችን ሕዝባችን በሚገባው ቋንቋ አዘጋጅተን ብንፖስት ።መጻፍ ካልቻልን ደግሞ በአማርኛ የተፉትን ወደ ኦሮሚኛ በመተርጎም ብናገራው። 5) ከጥቂቶች በቀር አብዛኛው ወጣት አሁንም ከቋንቋ፣ከሔርተኝነት በሽታ አልተላቀቅም ።ከዚህ ድንቁርና ወጥተን ኦርቶዶክሳዊ ኅብረታችንን አጠናክረን የተጋረጠብን መከራ እንጋፈጥ። 6) የሚያጸድቀን ኦሮሞነታችን ሳይሆን ኦርቶዶክሳዊነታችን ነው።በኦሮሞነታችን እንኩራ ነገር ግን ከኦርቶዶክሳዊነት በታች መሆኑን እንወቅ እንረዳ። 7) "ኦሮሞ፦ ተበደለ፣ እንዲህ ሆነ ፣እንዲያ ሆነ "እያሉ አቧራ ሲያስነሱ የነበሩ  ነገር ግን ኦሮሞ በኦርቶዶክሳዊነቱ በማዕተቡ ምክንያት በጅምላ ሲታረድና ሲሰደድ አንዳች ቃል የማይተነፍሱ ውሸታሞችን መከተል እናቁም። 8) በኦሮሞ ስም የተመሠረቱት  ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች   ኦርቶዶክስ ጠል መሆናችንን አውቀን ራሳችንን የምናድንበትን መፍትሔ ማፈላለግ ግድ ይለናል። https://t.me/rete14

Odeeffannoo 1 Kiristaanonni Ortodoksii Baha Arsii keessa jiraatan kanneen du’arraa oolan, caasaa mootummaatiin  dinagdeen akka dadhaban erga taasifamanii booda, "ta'e jedhamee karoorfamee yeroo yerootti buusiidhaan(baasiidhaan) akka dhiphannu taasifamaa jirra" jechuun komii isaanii dhageessisaa jiru. Dhiibbaan akkasii Kiristiaanota Ortodoksii kanneen irratti Raawwatamaa  jiru keessaa, aanaan Shirkaa ishee tokkodha. Filannoo gara fuulduraatti godhama jedhamee yaadamuuf affeerraaf(Diggisiif), qotee bulaan tokko tokkoon qarshii 5000 akka buusu kan murtaa'e yoo tahu, "humna kaffaluu hin qabnu" kanneen jedhan milishootaan reebamaa gara magaalaa guddoo aanichaa Kan Taate, Gobeesaatti Fudhatamuun hidhamaa jiru. Odeeffannoo 2 Naannooleen Kiristaanonni Ortodoksii baay'inaan keessa jiraatan kanneen akka: aanaa Honqoloo Waabee keessatti Worqee fi Maciituu, aanaa Shirkaa keessatti immoo Miitanaa Sakkee, Anolee, fi Gandi Sollee Ciisaa erga harka gareewwan Shororkeessitootaa keessa bu'anii waggaa lamaa ol lakkoofsisaniiru. Raayyaan Ittisa Biyyaa ta'e jedhamee karoorfamee gara naannoo sanaa akka hin deemne taasifameera. Naannooleen kunniin iddoo Ortodoksiin Oromoo Shawaa baay'inaan argaman yoo ta'an, haala akkamii keessa akka jiranii fi rakkoo isaanirra gahaa jiru beekuun hin danda'amu. Odeeffannoo 3 Qotee bulaan Ortodoksii Oromoo Tuulamaa Finfinnee fi Sheger Siitii keessa jiraatan lafti isaanii irraa fudhatamee hordoftoota amantii biroof hiramutti jira. Lafti Finfinnee keessa jiru dargaggoota amantii Pirootestaantii fi Waaqeffannaa hordofanii fi dhiha Shawaarraa dhufaniif kennamaa kan jiru yoo tahu, lafti Sheger Siitii keessa jiru immoo dureeyyii amantii Islaamaa ta'anii Arsii, Jimma, fi Baaleerraa dhufaniif gurguramaa jira. https://t.me/rete14

ሦስት መረጃዎች 1)ከሞት የተረፉት በመንግሥታዊ መዋቅር በኢኮኖሚ እንዲደቁ የተደረጉ በምሥራቅ አርሲ የሚኖሩ ኦርቶዶክሳውያን ሆን ተብሎ ታቅዶበት በየጊዜው በመዋጮ እንድንሰቃይ እየተደረግን ነው ሲሉ ቅ
ሦስት መረጃዎች 1)ከሞት የተረፉት በመንግሥታዊ መዋቅር  በኢኮኖሚ እንዲደቁ የተደረጉ በምሥራቅ አርሲ የሚኖሩ ኦርቶዶክሳውያን ሆን ተብሎ ታቅዶበት በየጊዜው በመዋጮ እንድንሰቃይ እየተደረግን ነው ሲሉ ቅሬታቸውን እያሰሙ ነው።እንዲህ ዓይነት ጫና በኦርቶዶክሳውያን ላይ ከሚደርሱባቸው ወረዳዎች ሽርካ አንዷ ናት።ቀጣይ ይደረጋል ተብሎ ለሚታሰበው ምርጫ ለድግስ የሚሆን እያንዳንዱ ገበሬ 5000ብር እንዲያዋጣ የተወሰነ ሲሆን የመክፈል አቅም የለንም የሚሉ ገበሬዎች በሚሊሾች እየተደበደቡ ወደ ወረዳው ዋና ከተማ ጎቤሣ እስር ቤት እየተወሰዱ ነው። 2)ኦርቶዶክሳውያን በ ብዛት የሚኖሩባቸው በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ ወርቄ እና መጪቱ  ፣በሽርካ  ወረዳ ሚታና ሰኬ ፣አኖሌ፣ ሶሌ ጪሳ የሚባሉ አከባቢዎች   በ አክራሪ ቡድኖች እጅ ላይ ከወደቁ  ከሁለት ዓመት በላይ አስቆጥረዋል።ሆን ተብሎ ታቅዶ መከላከያ ወደዚያ ስፍራ እንዳይሄድ ተደርጓል። እነዚህ አከባቢዎች የሸዋ ኦሮሞው ኦርቶዶክስ በ ብዛት የሚገኝባቸው ሲሆኑ በምን ዓይነት ሁኔታ ላይ እንዳሉ የሚደርስባቸውን መከራ ማወቅ አይቻልም።    3) በአዲስ አበባና  በሸገር  ሲቲ የሚኖሩ   የቱለማ  ኦሮሞ ኦርቶዶክሳውያን ገበሬዎች መሬታቸው ተወስዶባቸው ለ ሌሎች ቤተ እምነቶች እየታደለ ነው።በአዲስ አበባ ያለውን መሬት ከምዕራብ ሸዋ  ለመጡ ለፕሮቴስታንትና ለዋቄና እምነት ተከታይ ወጣቶች እየተሰጠ ነው ፣በሸገር ሲቲ ያለው ደግሞ ከአርሲ፣ ከጅማና ከባሌ ለመጡት ለእስልምና ባለሀብቶች እየተሸጠ ነው ። https://t.me/Eyo21e

ይኽን የሊቁን መልእክት ኦርቶዶክስ ለሆነ ሁሉ እንዲደርስ እናድርግ https://t.me/rete14