ru
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

Открыть в Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

Больше
2 931
Подписчики
-124 часа
+1487 дней
+38530 дней
Архив постов
የስምጥ ሸለቆው እንባ፡ የአጣዬ ሰቆቃ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ኤፍራታ ግድም ዛሬም ልብ የሚያደማ ንፋስ ይነፍሳል። ነገር ግን የሚሸተው የለመለመው መስክ ጠረን አይደለም፤ የቆሰለ ታሪክ፣ የነደደ ቤትና የባከነ እንባ ጠረን እንጂ። ​አይ አጣዬ...! ያቺ በሽዋ ስምጥ ሸለቆ እቅፍ ውስጥ የበቀለችው ምርጧ ከተማ። ምነው ስቃይሽ በዛ? ምነው ሰቆቃሽ የዘመን ጠባሳ ሆነ? ​ስንትና ስንት የአማራ ጀግኖች አጥንታቸውን የከሰከሱባት፣ ክብሬን ለባዕድ አልሰጥም ብለው ደማቸውን ያፈሰሱባት ያቺ ምድር፣ ዛሬ በገዛ ልጆቿ ክህደት ታጥባለች። ታሪክ የማይረሳቸው፣ ህሊናቸው በባዕድ አምልኮ የደነዘዘው የብአዴን ቅጥረኞች፣ በአረመኔያዊ አብይ አህመድ ትዕዛዝ የአጣዬን የመጨረሻ ቀይ መስመር አጠፉት። በዋቂ ፈቻ የቅዠት ባንዲራ ስር፣ በንጹሃን ደም የከተማዋን ታሪክ አደፈኑት። ክህደት በልማት ስም ​ይህ ነው ወርቅ ለአበዳሪ የሚባለው? ይህ ነው ባለውለታን ማረድ? ​አማራን ለማጥፋት፣ ከምድረ ገጽ ለማክሰም ብዙ ዶለቱ፣ ብዙ ፎከሩ። አልሳካ ሲላቸው ግን የክፋት ስልታቸውን ቀየሩ። ሰማዩም የእኛ ነው፣ መሬቱም የእኛ ነው እያሉ የትዕቢት መርዝ የሚረጩ የኦሮሞ ሊቅ ተባዮች፣ ዛሬ የከተማዋን ስም ቀይረው፣ በ“ኮሪደር ልማት የይስሙላ መጋረጃ ሸፍነው፣ አጣዬን በቁም እየገፈፏት ይገኛሉ። ልማት ሳይሆን የማንነት መደምሰስ! ልማት ሳይሆን የታሪክ ዘረፋ! ይህቺ ከተማ የቆመችው በድንጋይ ላይ አልነበረም ፤ ከአራቱም ማዕዘን በመጡ የአማራ ልጆች ፋኖዎች ነበር፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ስጋቸውን በገበሩ የአማራ ልጆች ደምና አጽም ላይ እንጂ! ​ዛሬ በአጣዬ ምድር የሚታየው ትዕይንት የሰውን ህሊና ያደማል፣ ልብን ይሰብራል ትናንት ከተማዋን በጥፍራቸው የቆፈሩ፣ ጥረው ግረው ያሳደጉ ስንት ባልንጀሮች ዛሬ በገዛ ምድራቸው ላይ ስደተኛ ሆነው ፊታቸውን አዙረው ያለቅሳሉ የልጆቻቸውን ደምና አጥንት የበላችው መሬት፣ ዛሬ በፖለቲካ ቁማርተኞች እጅ በሆዳም አማራ ለኦሮሞ ስትሸጥ የሚያዩ እናቶች እጃቸውን ወደ ሰማይ ዘርግተው ይጮኻሉ። ​የጀግኖች መቃብር ፈረሰ ለሀገራቸው የወደቁላት ጀግኖች አጽም ዛሬ በባዕዳን ኮቴ ሲረገጥ ማየት፣ የሰውን ልጅ ህሊና ከማንኛውም ነገር በላይ ያሳምማል። አጣዬ ዛሬም ታዝናለች። ሰማዩ በሀዘን ተክዟል፣ ምድሪቱም አልቅሳለች። ታሪክ በደማቅ ቀለም የጻፋትን ከተማ፣ ዛሬ በባዕዶ አለም ሰዎች ስትነጠቅና ስትሸጥ ማየት ህሊና ላለው ሰው ሁሉ የዘላለም የቁም ስቃይ ነው። ​ነገር ግን... መሬት የፈሰሰ ደም ዛሬ ባይናገር፣ ነገ ታሪክ ይፋረዳል! የአጣዬ እንባ መሬት ላይ አይቀርም! #Dawit #Amhara

ታሪክ የሌላቸው ሕዝቦች ታሪክ መሥራት አይችሉም፤ ምክንያቱም የታሪክ መሠረት የሌለው ስብስብ የትም ቢቆም የሚኖረው እውቅና የዱር አውሬ ወይም የወንበዴ ያህል ብቻ ነው። እኛ ግን ስማችን በዓለት ላይ የታተመ፣ ማንነታችን በጀግኖች አጥንት የተገነባ የድፍን ታሪክ ባለቤቶች ነን። ለዚህ ነው ዛሬም በፋኖነት የምናሳየው ጽናትና የምንከፍለው መስዋዕትነት የህልውናችንና የታሪካዊ ክብራችን ማረጋገጫ እንጂ፣ የታሪክ አልባዎች የዱር ጩኸት የማይሆነው። ውድ ቤተሰቦቻችን ከታች ያለውን የፊስቡክ ገፅ ይወዳጁት አዳዲስ መርጃዎች ያገኙበታል!! https://www.facebook.com/share/1BhZzwYo2D/

ወደ እዙ በገቡ አመራሮቺ የክፍለጦር ተሃድሶ! አፋብን ወለጋ/ቢዛሞ አንሻ ሰይድ ዕዝ ጌጤ ግርማ መብረቅ ክ/ጦር ለዘመናት የጅምላ ሰቆቃ እና የዘር ማፅዳት ቤተ ሙከራ ሁኖ የባጀው የወለጋ ቢዛሞ ራሱን ለመከላከል በተለያየ ግዜና ሁኔታ ተጋድሎዎቺን ሲያደርግ ቆይቷል። የአማራ ህዝብ የመግስትና የሀገር ባለቤትነትን መቀማቱን አማራ ክልል ከሚባለው ውጭ ላለው አማራ ማህበረሰብ ከፍተኛ የህልውና ስጋት እዳመጣበት በተጨበጭ የታየ ሀቅ ነው።በተለይ ወለጋ/ቢዛሞ ያለው ማህበረሰብ አማራ መሆንን ተከልክሎ ከመኖር ባሻገር ለዘመናት ከኖረበት አከባቢ ከአስተዳደራዊ በደል ጀምሮ ሰፊ የማንነት ጥቃት ተፈፅሞበታል። አማራ ነኝ እና አማራ አይደለህም በሚለው ተቃርኖ ውስጥ በስጋት ሲኖር የቆየው ማህበረሰብ በተለይ ከብልፅግና አገዛዝ መምጣት ቦኋላ መንግስታዊ እውቅና ባለው ይፋዊ የዘር ማፅዳት ዘመቻ ምክንያት በአስርሺዎቺ የሚቆጠሩት ተገድለዋል፣ከግማሺ ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ወደ ተለያዩ አከባቢዎች ተፈናቀለዋል።ይህ የዘር ማጥፋት አዋጂ መካከል የህልውና ጉዳይ በመሆኑ የቢዛሞ አማራ ተደራጂቶ ራስን የመከላከል እንቅስቃሴ ሲያደርግ መቆየቱ የታወቃል።ትግላቺን የአማራን ህልውና የመታደግ እና እንደ አማራ በምንኖርበት አከባቢ ፍትሃዊ በሆነ መልኩ የመተዳደር ወይም ራስን በራስ የማስተዳደር መብትን የመጎናፀፍ ነው። ይህ የአማራ ብሄርተኚነት ርዮታለም የትግል መስመር የአማራ ህዝብ ለዘመናት የተነፈገውን መብት የቦታ ልዩነት ሳይኖረው እዲከበር የማረጋገጥ ነው።ይህ መብት መከበር እኛ የምንኖርበት አከባቢ  ከሚኖረው ወድም የኦሮሞ ህዝብ እና ከሌላው ጋር ለሚኖረው ግንኙነት መሰረት ሲሆን የመብት መከበር ዘላቂ ሰላም የማረጋገጥም  ብቸኛው መፍተሄ እደሆነ እናምናለን።ይህንንም በማሰብ  የጠራ መዋቅራዊ መስመሮቺን በመዘርጋት የክፍለጦሩ የስራ አስፈፃሚ አባላትን እደሚከተለው ተቀምጠዋል፦ 1 አርበኛ ገነቱ አሰሜ  :ሰብሳቢ 2 አርበኛ አወቀ እምሩ :ም/ሰብሳቢ 3 አረበኛ በቃሉ ይታይህ :ወታደራዊ                       አዛዢ 4 አርበኛ በላይ ታምሩ: ም/ወታደራ                     ዊ አዛዢ 5 አርበኛ አስቻለው አድሱ: ህ/ግን               ኙነት መምሪያ 6 አርበኛ ታዘብ ሰደቅ: የፖለቲካ                           መምሪያ ሃላፊ 7 አርበኛ ዘለቀ አድሴ: ዘመቻ                     መምሪያ 8 አርበኛ አዷለም ወርቅነህ: አደረጃ                    ጀት መምሪያ 9 አርበኛ ትዛዙ ጌታቸው: ወታደራ                  ዊ አስተዳደር መምሪያ 10 አርበኛ አዷለም ማተቤ: የፋይና               ንስ መምሪያ 11 አርበኛ ደሳለኚ ሲሳይ: የሎጂስ                ቲክ መምራያ ሃላፊ 12 አርበኛ አበባው አያሌው:ፅ/ቤት                  ሃለፊ 13 አርበኛ ሰለሞን ዘውዴ:ጤና                      መምሪያ 14 አርበኛ መኮነን ሰጣለም:ወታደ                   ራዊ ስልጠና መምሪያ 15 አርበኛ አበባው አበረ:የኦርድናስ               መምሪያ ሃላፊ 16 አርበኛ በልስቲ ባሴ:የሰው                    ሀብት መምሪያ ሃላፊ 17 አርበኛ እሸቱ አጋዥ:ህግ እና              ስነምግባር መምሪያ 18 አርበኛ ተሾመ ደጉ:ማህበራዊ             ጉዳይ መምሪያ 19 አርበኛ አስማማው ደመቀ:              የሕዝብ አስተዳደር መምሪ 20 አርበኛ አገዘ ዳምጠው:ት/ትና              ስልጠና መምሪያ 21 አርበኛ ፍስሀ አታለል:ወታደራዊ           ጥናትና ስትራቴጂ መምሪያ 22 አርበኛ ሸጋው ደሴ:ሐብት አፈላ                ላጊ መምሪያ 23 አርበኝት ወይንሼት አትኩት:          የሴቶቺ ጉዳይ መምሪያ በማድረግ የስራ ስምሪትና ምደባ ሰጥቷል። ፨ለመላ ሰራዊታቺን፦የወለጋ/ቢዛሞ አንሻ ሰይድ እዝ ጌጤ ግርማ መብረቅ ክፍለጦር አባላትከዛሬ ጀምሮ አንድ ትግል አንድ አደረጃጀት መፈጠሩን እያበሰርን በአማራዊ ወድማማቺነት  እና የትግል ጓዳዊነት በመንፈስ የጀመርነውን የህልውናውን ትግል የፖለቲካ መስመሩን በማፅናትና የሚሰጡ ግዳጆቺን የአድነት አቅምን ተጠቅመን በበለጠ ፅናት እድንፈፅም ለማሳሰብ እንወዳለን።ከዚህ በተጨማሪ በእዛቺን ካሉት ሌሎቺ ክፍለጦሮቺ ጋር በሚኖሩ የጋራ ግዳጆቺ የሚጠይቀውን በቁርጠኚነት እድትፈፅሙ በድጋሜ እናሳስባለን። ግፍ የወለደን:ግፈኞቺን የምቀጣ የአንሻ ሰይድ ወድሞቺ ነን!!! አፋብን ወለጋ/ቢዛሞ አንሻ ሰይድ ዕዝ ህ/ግንኙነት መምሪያ ሰኔ24/2018ዓ.ም

ሲፈጠር ሕዝብን ለመጠበቅ የሚነሱ ማህበረሰባዊ ምላሾች እንደሆኑ ይተረጉማሉ። በተለይም የማንነት ጥያቄ፣ የፍትህ ፍለጋ እና የአካባቢ ደህንነት ስጋት በተጠናከረበት ሁኔታ ውስጥ እነዚህ እንቅስቃሴዎች በሕዝብ አንድ ክፍል ዘንድ የራስ መከላከያ እና የማንነት ጥበቃ ሚና እንደሚያገለግሉ ይታመናል። ነገር ግን በሌላ ትርጓሜ ደግሞ የእንዲህ ዓይነት አደረጃጀቶች መኖር የሕግ ሥርዓት እና የመንግሥት የደህንነት ተግባር ላይ ጥያቄ ሊያነሳ ይችላል። በወለጋ ፡ ያ የፍትሕ ያለህ ፣ በህግ አምላክ እያለ እንደ ጎርፍ የፈሰሰው የአማራዎች ደም ፤ ያ ተከስክሶ የተረው የአማራዎች አፅም ፤ ያ ቤተሰቡን ተሸክሞ የተፈናቀለው አማራ ፤ ያ አመቱን ሙሉ አርሶ አጭዶ አይኑ እያየ የእሕል ክምሩ የተቃጠለበት አማራ ዛሬ ላይ ራስን በመከላከል ተፈጥሯዊ ህግ ፍትሕ እያገኘ  ከየትኛው ፋኖ አደረጃጀት ጋር በመሆን በአንሻ ሰይድ ዕዝ እራሱን እያስከበረ ይገኛል ።  የአማራ መከራ በወለጋ፣ የሚቆመው በመልስ አልባው ደካማ አስጠቂ አገዛዝ ሳይሆን ፣ ነፃነትን እና ፍትህን በእጃቸው ለመፃፍ በወሰኑ ውድ ልጆች ነው፡፡ የተደራጁ እንቅስቃሴዎች የራስ መከላከያና የማንነት ጥበቃ የአዲሱ ትውልድ እይታችን ነው ። አርበኛ ግሩም ምሳሌ የአፋብን ምዕ/አማ/ቀጠና ምክትል የፖለቲካ መምሪያ ሃላፊ አዲስ ትውልድ ፤ አዲስ አስተሳሰብ ፤ አዲስ ተስፋ !

ቢዛሞ ዕዝ ፡ የእሪታ ዝምታ ማብቂያ ፤ የአሸናፊነታችን ማሣያ መነፀራችን ነው ! የአማራ መከራ በወለጋ፣ የሚቆመው በመልስ አልባው ደካማ አስጠቂ አገዛዝ ሳይሆን ፣ ነፃነትን እና ፍትህን በእጃቸው ለመፃፍ በወሰኑ ውድ ልጆች ነው፡፡ የተደራጁ እንቅስቃሴዎች የራስ መከላከያና የማንነት ጥበቃ የአዲሱ ትውልድ እይታችን ነው ። በኢትዮጵያ የቅርብ ዘመን ታሪክ ውስጥ ወለጋ በብዙዎች ዘንድ በለምለም መሬቱ፣ በተፈጥሮ ሀብቱና በሕዝቦቹ አብሮነት ይታወቅ ነበር። ዛሬ ግን ይህ መሬት በሌላ ስም ይጠራል፤ የማያቋርጥ ግድያ፣ የጅምላ መፈናቀል፣ የእገታ፣ የዘረፋና የፍርሃት ሸለቆ በሚል ይገለፃል። በአጠቃላይ ከብልፅግና አገዛዝ መፈጠር በኋላ ወለጋ፤ የዝምታ ሸለቆ፣ የሰው ሕይወት የረከሰበት መሬት ፤ በፍትህ እጦት የተሰቃዩ ድምፆች ይታዩበት ነበር ። ለብዙ ዓመታት በወለጋ የሚኖሩ አማራዎች ሕይወታቸውን በተከታታይ የደረሱ ጥቃቶች ውስጥ አሳልፈዋል። የቤተሰብ አባላትን አጥተዋል፣ ከቀያቸው ተፈናቅለዋል፣ ንብረታቸው ተቃጥሏል፣ እርሻቸውን ትተዋል፣ በየቀኑም በፍርሃት መኖር ለብዙዎች የተለመደ ሕይወት ሆኗል። ከተጎጂዎች የሚሰሙት ታሪኮች አንድ ሚያመለክቱት ነገር አለ፤ ጥቃቱ ከአንድ ክስተት ወደ ቀጣይ በመደጋገም የሕዝብን ደህንነት፣ ክብርና የመኖር መብት በጥልቅ መጉዳቱን በየጊዜው የዘሩትን ሳይሰበስቡ ፣ ያጨዱትን ሳይወቁ፣ ሜዳ የላኳቸውን እንስሳት ሳይመልሱ የእርድ መስዋዕት ሁነው ፣ የቻሉም ዝቆ የሚሰጥ እጃቸው ተኮድኩዶ ለምነው የሚደርስላቸው ያጡ እድል የቀናቸው ህይዎት አትራፊ ሁነው ተመልክተናል። በከንቱ ደማቸው የፈሰሰውን ቤት ይቁጠራቸው ። ከሁሉ የሚያሳዝነው ግን ጥቃቱ ብቻ አይደለም ። ከጥቃቱ በኋላ የተከተለው ዝምታ፣ ፍትሕ አለመገኘት፣ ተጠያቂነት አለመኖር እና በቂ ጥበቃ አለመሰጠት የብዙ ተጎጂዎችን ስቃይ እንዲቀጥል አድርጎታል። ተጎጂዎች ከሚጠይቁት ዋና ጥያቄ አንዱ፦ "የሚጠብቀን ማን ነው?" የሚለው ነበር ። በዚህ ዘመን የተከሰቱ ክስተቶች ስለ አንድ ማኅበረሰብ ብቻ አይናገሩም፤ ስለ የሰብአዊ  ክብር ዋጋ፣ ስለ የመንግሥት የጥበቃ ኃላፊነት፣ ስለ ፍትሕ መዘግየት እና ስለ ዝምታ ዋጋ ይናገራሉ ። አሁንም ድረስ ግን በሺዎች ለሚቆጠሩ የአማራ ቤተሰቦች "የጠፋ ቤት"፣ "የተበተነ ሕይወት" እና "ያልተሰማ ጩኸት" የሚያስታውስ ስም ሆኗል። በተከታታይ የተፈጸሙ ጥቃቶች፣ መፈናቀሎች፣ ንብረት ጥፋቶች፣ የኑሮ መፍረሶችና የሰብአዊ ቀውሶች በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎችን ከቀያቸው አፈናቀሉ፤ ከእርሻቸው አራቁ፤ ከቤታቸው አስወጡ፤ ከቤተሰባቸውም ለይቷቸዋል። ለብዙ ቤተሰቦች "ወደ ቤታችን መመለስ" የሚለው ህልም እስካሁን ድረስ ያልተፈጸመ ምኞት ሆኖ ቀርቷል። የወለጋው አማራ ተኮር የዘር ፍጅት ቀውስ የተጎጂዎችን ሕይወት ብቻ አልለወጠም፤ በኢትዮጵያ ውስጥ የሰብአዊ መብት፣ የዜግነት መብት፣ የደህንነት ዋስትና እና የፍትሕ ሥርዓት ላይ ያሉ ከባድ ጥያቄዎችን አንስቷል። ራሱ አገዛዙ ከሞታቸው በኃላ ባመነው ሪፖርት እንኳን በየጊዜው በአማራው ላይ  የሚደርሱ ጥቃቶች፣ የጸጥታ እጦት፣ የሕክምና እጦት፣ የምግብ እጦት እና ረጅም የመፈናቀል ሕይወት ለብዙ ዜጎች አዲስ መደበኛ ሕይወት ሆነዋል። ከሁሉም በላይ ግን ተጎጂዎቹን የሚያሳምማቸው ሌላ መሠረታዊ ሁለተኛ  ጥያቄ አለ ፦  የእኛን ድምፅ የሚሰማ ማን ነው ? የሚለው ነው ። አገዛዙ  የሁሉንም ዜጎች ደህንነት የመጠበቅ ሕገ-መንግሥታዊ ኃላፊነት አለበት። የክልል መንግሥታትም በተመሳሳይ መንገድ የነዋሪዎቻቸውን ሕይወትና ንብረት የመጠበቅ ግዴታ አለባቸው። ይሁን እንጂ ተጎጂዎች እና ተፈናቃዮች ከጥቃቱ በኋላ በቂ ጥበቃ፣ ፍትሕ፣ ሰብአዊ እርዳታ እና ዘላቂ መፍትሔ አላገኙም። ነገር ግን የወለጋ ታሪክ የስቃይ ታሪክ ብቻ አይደለም። የመቋቋም ታሪክ ነው። የመተባበር ታሪክ ነው። የእርስ በርስ መረዳዳት ታሪክ ነው። በተባበረ ክንድ ነፃ የመውጣት ታሪክም ነው ። ቤታቸውን ያጡ ሰዎች ለሌሎች መጠለያ ሆኑ፤ ሀብታቸውን ያጡ ቤተሰቦች የቀራቸውን እንጀራ ተካፈሉ፤ በፍርሃት የኖሩ ማህበረሰቦች እንደገና ራሳቸውን ለማደራጀትና ማህበራዊ ትስስራቸውን ለመገንባት ሞክረዋል። የሰብአዊ መብት አንድ መሠረታዊ እውነት አለው ፤ መብት የሚሰጥ ስጦታ አይደለም፤ በሕግ የተጠበቀ የሰው ልጅ ክብር እንጅ ። ዴሞክራሲም ከሥልጣን የሚቸር ስጦታ ሳይሆን በዜጎች የነፃነት ትግል ተሳትፎ፣ በሕግ የበላይነት፣ በፍትሕ እና በተጠያቂነት የሚገነባ ሥርዓት ነው ። በአማራው ላይ የተፈጸመው የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን፣ የተጎጂዎችን ድምፅ፣ የቀጠለውን ሰብአዊ ቀውስ እና ለዘላቂ ሰላም፣ ለፍትሕና ለሰብአዊ ክብር የሚያስፈልጉ እርምጃዎችን በማስረጃ አቅርበን አንድ ቀን ፍትህ አደባባይ እንጠይቃለን፡፡ ያ ግን አሁን በሞታቸን በሚደልቅ እና በሚቀልድ መንግስት እና ስርዓት አይደለም፡፡ ይልቁንስ ጀምረነዋል ስርዓቱን ቀብረን ስርዓት ገንብተን እርዝራዡን በዓለም አደባባይ ከፍትህ ፊት እንገትራቸዋለን እንጅ ። የተጎጂዎችን ድምፅ ለማሰማት፣ በወለጋ የተመዘገቡ የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን በማስረጃ ለማቅረብ፣ የቀጠለውን ሰብአዊ ቀውስ ለማሳየት እና ለፍትሕ፣ ለተጠያቂነት እና ለዘላቂ ሰላም የሚያስፈልጉ እርምጃዎች ለማመልከት አሁን የወለጋ ልጆች በአንድ ተሰባስበዋል።  የአማራ ህዝባዊ አቢዮት ከወለዳቸው አምስት ታላላቅ ዕዞች ውስጥ አንዱ በመከራ ክምር እና በደም እንባ ብዛት በቃን ብሎ በአፈሙዝ ላንቃ ነፃነቱን ለማስከበር የወጣ ቢዛሞ ዕዝ ወይም  አንሻ ሰይድ ዕዝ የሚባል መደበኛ ተዋጊ ጦር ተመስርቷል ። ከጄነራል እስከ ኮለኔል እየደመሠሠ በመታጠቅ ላይም ይገኛል ። ነፃነት የሚገኘውም በወርቅ ዘረፋ አዕሞራቸው የላሸቁ  የአብይ ስልጣን ዘበኛ ጀነራሎችን እና የቤተ መንግስቱ ፍርፋሪ ለቃቃሚ አጋፋሪ ፖለቲከኞቹን አሸኖፎ እንደሆነም በውል የሚረዳ ሐይል ነው ። ይሄ ዕዝ ለአገዛዙ ውልፍት ማለት የማይፈቅድ መገደል ሰልችቶት ፡ መከራ ያሣደገው እና ስደት ያስተማረው ጦር ሁኖ ተከስቷል ። ዛሬ የተጎጂዎችን ታሪክ ብቻ አይዘግብም፤ የተሰበሩ ቤቶችን፣ የጠፉ ሕይወቶችን፣ የተበተኑ ቤተሰቦችን፣ የፍትሕ ጥሪን እና አሁንም በፍርሃት ውስጥ የሚኖሩ ዜጎችን ማስታወሻ እያዩ ለነፃነት የሚቆሙ ጀግኖች ተፈጥረዋል ። አማራ በቀለኛ ሕዝብ አይደለም፤ የሚጠይቀው ፍትህን ነው ፡፡ ለአጥፊዎችን ፍትሕ የሚሰጠው ካጣ ግን ' ደም መላሽ' የሚል ስም ለልጁ እያወጣ ነው የኖረው ፡፡ አሁን አንሻ ሰይድ ዕዝ  የሚታገል እውነት እንዲታወቅ፣ ተጠያቂነት እንዲረጋገጥ ፣ ተጎጂዎች ፍትሕ እንዲያገኙ፣ ስርአቱ እንዲወገድ  እና ሁሉም ዜጎች ያለ ፍርሃት የመኖር መብታቸው እንዲከበር ነው ። "ሰላም የሚገነባው በዝምታ ሳይሆን በእውነት፣ ፍትሕ እና የሰው ክብር መከበር ላይ ነው።" አሁን ግን "የሚጠብቀን ማን ነው?" የሚል መልስ የገዛ ልጆቻቸው እና በኢትዮጵያዊነቱ የሚቆመው ሰው ሁሉ ነው፡፡ ሞት ያንገሸገሻቸው  ደም ገባሪነት የመረረራቸው የወለጋ ልጆች አሁን ሞትን ራሱን ለማንበረከክ ተነስተዋል፡፡ በአንድ ቁመው ቅያቸውን ፍትህ እና ርትዕ ያልገዛውን ፣ ነፃነት ገፋፊ ሃይል ጀኔራል ማርከው ፣ ቁሞ አስ/ገዳያቸውን ወይም ገዳያቸውን እየቀደሙት ነው፡፡    የተደራጁ እንቅስቃሴዎች በደጋፊዎቻቸው ዘንድ ብዙ ጊዜ የራስ መከላከያ፣ የማህበረሰብ ደህንነት ጥበቃ እና የማንነት ክብር ለመጠበቅ የተቋቋመ መሣሪያ እንደሆነ ይታወቃሉ። በዚህ አመለካከት መሠረት፣ ደጋፊዎች እነዚህን እንቅስቃሴዎች የመንግሥታዊ የደህንነት አቅም ክፍተት

​👉 ቤተሰባችንን የፊስቡክ ገጻችን ይወዳጁን!! https://www.facebook.com/share/1P6KxYkqKP/

የጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ ጊዜያዊ መንግስት የመጀመሪያ ዙር ለቀበሌ አመራሮች ስልጠና ተሰጠ ============================= ..........ሰኔ 24/2018 ዓ.ም የ201ኛ ኮር 74ኛ
+8
የጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ ጊዜያዊ መንግስት የመጀመሪያ ዙር ለቀበሌ አመራሮች ስልጠና ተሰጠ ============================= ..........ሰኔ 24/2018 ዓ.ም የ201ኛ ኮር 74ኛ ክፍለ ጦር በተመረጡ ወቅታዊ ድርጅታዊ ጉዳዮች ማለም፦ ➺ ፋኖነት እና የትግሉ አሁናዊ ቁመና ➺ ፖለቲካ መር የትጥቅ ትግል ➺የለውጥ ጊዜ የመሪነት ጥበብ ➺የማህበራዊ ፍትህ አሰጣጥ ዙሪያ በወረዳችን ውስጥ ያጋጠሙ ተግዳሮቶችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ በወረዳው ውስጥ በሚገኙ ቀጠናዎች ማለትም በቀጠና አንድ ከሰኔ 5 _7በቀጠና 3 ከሰኔ 19_ 21 ለቀበሌ አመራሮች እና መቺ ሃይሎች ስልጠና ተሰጥቷል ከዚህ በተጨማሪም በቀጠናዎቹ መቺ ሃይል በማዋቀር ቀጠናውን በንቃት በመጠበቅና የተለያዩ ግዳጆችን በመፈፀም ላይ ይገኛሉ። ስልጠናውንና ግዳጆችን የወረዳው ጊዜያዊ መንግስት ፋኖ መምህር አብርሃም የሽዋስ እና ሌሎች የወረዳ አመራሮቹ ተሳተትፈውበታል። አዲስ ትውልድ ፣አዲስ አስተሳሰብ ፣አዲስተስፋ የአፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 74ኛ ክ/ጦር ህዝብ ግንኙነት መረጃውን አጋርቶናል ።

የአማራ ፋኖ የህልውና ተጋድሎ ከቁጭት ወደ ዝግጅት፣ ከዝግጅት ወደ አኩሪ ገድል ፈፃሚነት! በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ምድር እየተካሄደ ያለው የፋኖ ትግል፣ ተራ የአመፅ ክስተት ሳይሆን፣ በአለም ታሪክ ከታዩ ታላላቅ የህዝብ የነፃነት ተጋድሎዎች የሚመደብ፣ የመንግስትን የሃይል የበላይነት በአጭር ጊዜ ውስጥ የናደ ክስተት ነው። ይህ ትግል የፈረንሳይን የነፃነት ታጋዮች ፅናትና የአድዋን የጀግንነት ድል ስነ-ልቦና አጣምሮ የያዘ ድንቅ የ21ኛው ክፍለ ዘመን ክስተት ነው። የአብይ አህመድ የብልፅግና ስርዓት ወንበር ጠባቂ ሰራዊት ዛሬ ላይ የሞራልና የወታደራዊ ክስረት ላይ ይገኛል። የፋኖ ድል በቁጥር ብቻ የሚገለፅ ሳይሆን፣ በስልታዊ ጥቃት የጠላትን ሰንሰለት የበጣጠሰ ነው። ለዚህ ማሳያ የሚሆኑት በቅርቡ የተመዘገቡት አስደናቂ ድሎች ናቸው፦ 1. የአፋብን ወለጋ (ቢዛሞ) አንሻ ሰይድ ዕዝ በወሰደው የተቀናጀና መብረቃዊ ጥቃት ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖች ጄነራሎችንና ኮሎኔሎችን ጨምሮ መደምሰስና ከአውደ ውጊያው የተረፉት ደግሞ ተማርከዋል። ይህ የሚያሳየው የአገዛዙ ሰራዊት የመዋጋት አቅሙና አመራሩ ሙሉ በሙሉ መክሸፉን ትልቅ ማሳያ ነው። 2. አፋበን|ቴዎድሮስ ዕዝ በደጋ ዳሞት ግንባር ከፍተኛ የጦር መኮንኖች ኮሎኔሎችንና ሻለቆችን ጨምሮ ብዛት ያለው እግረኛ ሰራዊት የተገደሉበት አውደ ውጊያ፣ ፋኖ ከደፈጣ ውጊያ አልፎ ወደ ስልታዊ የማጥቃት ጦርነት መሸጋገሩን ያረጋገጠ ነው። እነዚህ ድሎች የሚያሳዩት፣ ፋኖ ስርዓቱን እስከ መጨረሻው ከመንበረ ስልጣኑ ነቅሎ የሚጥል አቅም መገንባቱን ነው። ለዚህ ሁሉ ድል መሰረቱ የአማራ ፋኖ መሪ ድንቅ ፖለቲካዊ አስተውሎት ነው። የአማራ ፋኖ መሪው አርበኛ ዘመነ ካሴ ገና ስርዓቱ የጥፋት መንገዱን ሲጀምር፣ የአማራን ህዝብ የህልውና ስጋት ቀድሞ የተረዳ የፖለቲካ ነብይ ነው። ሁሉም ሰው ሊረዳው የሚገባው ሃቅ፣ አርበኛ ዘመነ ካሴ ገና ስርዓቱ በዴሞክራሲ ስም የአማራን ህዝብ ለዘር ማጥፋት እያዘጋጀ መሆኑን ቀድሞ የተረዳ አሰላሳይና አርቆ አሳቢ መሪ ነው። የመሪው ድንቅ ብቃት የሚገለፀው፦ የስጋት ትንበያ፦ የአማራን ህዝብ የህልውና ስጋት የፖለቲካ ጥያቄ ብቻ ሳይሆን፣ የመኖርና ያለመኖር ጉዳይ መሆኑን ለህዝቡ በማስረገጥ ብቁ የፖለቲካ ንቃት መፍጠሩ። ፖለቲካዊ ዲፕሎማሲ፦ ትግሉን ለፍትህና በህልውና ተጋድሎ ላይ የተመሰረተ በማድረግ፣ በአለም አቀፍ ደረጃ የሚነሱ የሀሰት ትረካዎችን የመመከት ችሎታው። እንዲሁም ህዝባዊ የሃይል ቅንጅት የመፍጠር ችሎታው ናቸው። በቪዲዮ ምስሉ ላይ የሚታዩት እነዚህ የፋኖ ሰልጣኝ ወጣቶች በአዲሱ የአማራ ትውልድ ንቃተ-ህሊና የተቀረፁ ናቸው። ይህ ትውልድ ይደራጃል፣ ይሰለጥናል፣ ይማርካል፣ ይታጠቃል የሚለውን በተግባር እያሳየ ይገኛል። ይደራጃል ሲባል በሰበካ ሳይሆን በራሱ ፍላጎት ለህልውናው አንድ ሆኗል። ይሰለጥናል ስንል የትግሉን ሳይንስ፣ የጠላትን ደካማ ጎን እና የራሱን ጥንካሬ በሚገባ እየቀሰመ ነው። በሌላ መልኩ ይማርካል የጠላትን መሳሪያ ለጠላት ማጥፊያነት እየተጠቀመበት ነው። በመጨረሻም ይታጠቃል የአባቶቹን ወኔ እና ዘመናዊ መሳርያዎችን አጣምሮ የታጠቀ ኃይል ነው። እነዚህ ሰልጣኞች የአማራን ህዝብ ክብር የሚጠብቁ የብረት መጋረጃዎች ናቸው። ከጠላት የሚማርከው መሣሪያ ፋኖን የአፍሪካ ቀንድ እጅግ ግዙፍና የማይበገር ጦር እያደረገው ነው። ይህ ትውልድ ከታሪክ ተረካቢነት ወደ ታሪክ ሰሪነት ተሸጋግሯል። ይህ የፋኖ ትግል የማይቀለበስ የታሪክ ግስጋሴ ላይ ነው። የጄነራሎች፣ ኮሎኔሎች እንዲሁም ሻለቃ ማዕረግ ያላቸው መኮነኖች መውደቅና የብልፅግና ሰራዊት መማረክ የአንድ ሰሞን ወሬ ሳይሆን፣ የአንድ ጨቋኝ ስርዓት የመጨረሻው ምዕራፍ መጀመሪያ ነው። ፋኖ ዛሬ የአማራን ብቻ ሳይሆን፣ የፍትህ ፈላጊውን የሰው ልጅ ሁሉ ድምፅ እየታደገ ነው። እነዚህ ሰልጣኞች የታሪክ ተመልካች አይደሉም፤ የታሪክ ዳኞች ናቸው። ቁጭታቸው ለዝግጅት፣ ዝግጅታቸው ለድል፣ ድላቸው ለዘላቂ የአማራ ህልውና መጠበቅ ነው!

የዓፄ ዘርያዕቆብ ፩ኛ ኮር ነጎድጓድ ክፍለ ጦር ከአገልግሎት ሰጪ ተቋም ሰራተኞች ጋር ውይይት አካሔደ!            ሰኔ 24/2018 ዓ.ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ ዘርዓ ያዕቆብ ፩ኛ ኮር ነጎድጓድ ክፍለ ጦር፣ በተጉለትና ቡልጋ አውራጃ ከሚገኙ የአገልግሎት ሰጪ ተቋም ሰራተኞች ጋር በወቅታዊ የትግል ሁኔታና በአገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ ውይይት አድርጓል። በውይይቱም የክፍለጦሩ ሰብሳቢ ፋኖ አንባቸው ጌጤ ክ/ጦሩ ህዝባዊነቱን ለማረጋገጥ እና ቀጣይ አሰራራችን  ለማዘመን ህዝባችንን እና የህዝብ አገልግሎት ሰጪ ተቋማትን ማወያዬትና ሀሳብ መቀበል አስፈላጊ በመሆኑ የናንተ ሀሳብ ለተቋማችን ግብአት ነው  ያለ ሲሆን አክሎም አገዛዙ በሁሉም ነገር የወደቀ በመሆኑ እና የአማራን ህዝብ በሚችለው ያክል ተበቅሎ ቀጣይ የሞት ቀኑን የሚጠባበቅ እንጅ ህዝባዊ ቅቡልነት ማጣቱን እና በፋኖ ውጊያ መሸነፉን በብዙ መንገድ አረጋግጧል ብሏል።   የተቋማት ሰራተኞች በአስተያዬታቸው      በትምህርት፣ በጤና እና በግብርና ሙያ ዘርፍ ትግሉን እንደሚደግፉ እና ተግተው ህዝባቸውን እንደሚያገለግሉ አረጋግጠው፣ ለ2019 ዓ.ም  ለትግሉ አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ እና ከዘርፉ በሚጠበቁ ተግባራት ሁሉ ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል። የክፍለ ጦሩ ሕዝብ አስተዳደር ኃላፊ በበኩላቸው፤ ተቋማችን ከጊዜ ወደ ጊዜ አሰራሮቹን እያዘመነ እና የህዝብን ደህንነት በመጠበቅ ጉዞውን እያፈጠነ መሆኑን ጠቅሶ፤ መላው ህዝባችን እና የህዝብ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ለቀጣዩ ሥር ነቀል ለውጥ ራሱን ዝግጁ እንዲያደርግ ያለ ሲሆን የህዝብ አገልግሎት ሰጭ ተቋማትም ነጎድጓድ ክፍለጦር እያደረገ ያለው የማወያዬትና የችግር ፈቺነት ሚናን አመስግነው ውይይቱ ተጠናቋል። "ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! "ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

የዓፄ ዘርያዕቆብ ፩ኛ ኮር ነጎድጓድ ክፍለ ጦር ከአገልግሎት ሰጪ ተቋም ሰራተኞች ጋር ውይይት አካሔደ! ሰኔ 24/2018 ዓ.ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ ዘርዓ ያዕቆብ ፩ኛ ኮር ነጎድጓድ ክፍለ ጦር፣ በተጉለትና ቡልጋ አውራጃ ከሚገኙ የአገልግሎት ሰጪ ተቋም ሰራተኞች ጋር በወቅታዊ የትግል ሁኔታና በአገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ ውይይት አድርጓል። በውይይቱም የክፍለጦሩ ሰብሳቢ ፋኖ አንባቸው ጌጤ ክ/ጦሩ ህዝባዊነቱን ለማረጋገጥ እና ቀጣይ አሰራራችን ለማዘመን ህዝባችንን እና የህዝብ አገልግሎት ሰጪ ተቋማትን ማወያዬትና ሀሳብ መቀበል አስፈላጊ በመሆኑ የናንተ ሀሳብ ለተቋማችን ግብአት ነው ያለ ሲሆን አክሎም አገዛዙ በሁሉም ነገር የወደቀ በመሆኑ እና የአማራን ህዝብ በሚችለው ያክል ተበቅሎ ቀጣይ የሞት ቀኑን የሚጠባበቅ እንጅ ህዝባዊ ቅቡልነት ማጣቱን እና በፋኖ ውጊያ መሸነፉን በብዙ መንገድ አረጋግጧል ብሏል። የተቋማት ሰራተኞች በአስተያዬታቸው በትምህርት፣ በጤና እና በግብርና ሙያ ዘርፍ ትግሉን እንደሚደግፉ እና ተግተው ህዝባቸውን እንደሚያገለግሉ አረጋግጠው፣ ለ2019 ዓ.ም ለትግሉ አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ እና ከዘርፉ በሚጠበቁ ተግባራት ሁሉ ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል። የክፍለ ጦሩ ሕዝብ አስተዳደር ኃላፊ በበኩላቸው፤ ተቋማችን ከጊዜ ወደ ጊዜ አሰራሮቹን እያዘመነ እና የህዝብን ደህንነት በመጠበቅ ጉዞውን እያፈጠነ መሆኑን ጠቅሶ፤ መላው ህዝባችን እና የህዝብ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ለቀጣዩ ሥር ነቀል ለውጥ ራሱን ዝግጁ እንዲያደርግ ያለ ሲሆን የህዝብ አገልግሎት ሰጭ ተቋማትም ነጎድጓድ ክፍለጦር እያደረገ ያለው የማወያዬትና የችግር ፈቺነት ሚናን አመስግነው ውይይቱ ተጠናቋል። "ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! "ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

ትናንት የነበረው ጽናት ዛሬም አልደገዘም። በደም ስራችን ውስጥ የሚመላለሰው የአማራነት ስነ-ልቦና፣ በአዲስ ዘመን ብዕርና ቴክኖሎጂ ተኳሽሎ እነሆ ብቅ ብሏል። እኛ አንድነታችንን የውበት ያህል የምንለብሰዉ፣ ማንነታችንን እንደ አክሊል የምንደፋው ትውልዶች ነን። ​ይህ የጋራ ቤታችን፣ ይህ የሐሳብ ማዕከላችን... የፊስቡክ ገጻችን በአዲስ መልክ ተስተካክሎ ይጠብቃችኋል። ኑ፣ ውበታችንን አብረን እንሳለው፣ አንድነታችንን እናጠናክረው። ​👉 ቤተሰባችንን ለመቀላቀል እዚህ ጋ ይወዳጁን፦ የፊስቡክ ገጻችን

የአዲስ አበባ ልጅ ፖሊስ መሆን አለበት የምንለው በምክንያት ነው! ​ቢያንስ የአዲስ አበባ ልጅ የከተማዋን ስነ-ልቦና ያውቃል፤ ከማህበረሰቡ ጋር በሰለጠነ መንገድ መግባባት እና በአግባቡ ህግን ማስከበር ይችላል። ህግ ማስከበር ማለት የህዝብን ባህል፣ ቋንቋና አኗኗር መረዳት ማለት ነው። ​ ዛሬ በከተማችን የምናየው ግን ፍጹም ተቃራኒውን ነው፦ ​ለገዢው እንጂ ለህግ ያልቆሙ፦ በህዝብ ላይ ግፍ የሚፈፅሙ፣ ስለ ህዝቡ ስቃይና እንግልት ቅንጣት ታክል ግድ የሌላቸው አካላት ስልጣን ላይ ያሉትን ለማስደሰት እንጂ ለህግና ለፍትህ የቆሙ አይደሉም። ​ ከአዲስ አበባ ማህበረሰብ ጋር መግባባትና አብሮ መስራት የማይችሉ አካላት በከተማዋ ሰላም ላይ ትልቅ እክል ፈጥረዋል።​በንጹሃን ዜጎች ላይ የሚደረገው መዋከብና ኢ-ሰብአዊ አያያዝ በአስቸኳይ ሊቆም ይገባል! ​ህግ ሊከበር የሚገባው ህዝብን በማክበር እንጂ በሃይልና በማስፈራራት አይደለም! ህዝብን ያላከበረ አሰራር ፍትህን ሊያመጣ አይችልም። የከተማዋን ሰላምና ደህንነት ለመጠበቅ የራሷን ማህበረሰብ የሚያውቁና የሚያከብሩ የህግ አስከባሪዎች ያስፈልጉናል። ​#አዲስአበባ #ፍትህ #ሰብአዊመብት #የአዲስአበባልጅ #ህግናፍትህ

የድል ዜና!! የአ.ፋ.ብ.ን 305ኛ ጎቤ መልኬ ኮር በቀን 24/10/2018 ዓ/ም በማዕከላዊ አርማጭሆ ወረዳ ከራማ ቀበሌ በአገዛዙ ሀይል ላይ ከፍተኛ ም*ት*ን በማሳ*ረፍ በርካታ ቁጥር ያለዉን የጠላ
+1
የድል ዜና!! የአ.ፋ.ብ.ን 305ኛ ጎቤ መልኬ ኮር በቀን 24/10/2018 ዓ/ም በማዕከላዊ አርማጭሆ ወረዳ ከራማ ቀበሌ በአገዛዙ ሀይል ላይ ከፍተኛ ም*ት*ን በማሳ*ረፍ በርካታ ቁጥር ያለዉን የጠላት ሀይል እስከወዲያኛዉ በመሸኘት አንፀባራቂ ድልን ተጎናፅፏል። በታላቁ አርበኛ ዋዋ ጎቤ ስም የተሰየመዉ ግዙፉ ኮር ልክ እንደ ስሙ ትልልቅ ጀብዶችን በመፈፀም በድል ጎዳና ወደፊት እየገሰገሰ ይገኛል። ትልቅ ታሪክም እያስመዘገበ ይገኛል።