ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
Открыть в Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
Больше2 918
Подписчики
-1524 часа
+287 дней
+37030 дней
Архив постов
የ106ኛ ኮር 22ኛ ክፍለጦር ሰኔ 20/2018 ዓ/ም በመቄት ወረዳ ከመድፍና ፔምፒ ጋር ጉሮሮ ለጉሮሮ በመተናነቅ ታላቅ ጀብድን ተፈፅሟል!
ከፍላቂት ተነስቶ ወደ ጋሸና ሲግተለተል በነበረ የጠላት ሰራዊት ላይ 22ኛ ክፍለጦር መብረቃዊ ጥቃት ተፈፅሟል። ከወደ ፋኖዎቹ ከባድ የከበባ ጥቃት የተፈፀመበት ከበባውን ለመስበር የድሽቃ፣ የፔምፒና የመድፍ ቅቡላን ለተከታታይ ሁለት ሰዓት ሲተኩስ የዋለ ሲሆን፤ በመቄት አናብስቶች የስርዓቱ ስልጣን ጠባቂ የአገዛዙ ሰራዊቶች ግን ወደ ሲዖል ከመሸኘታቸው የታደጋቸው ምንም አይነት ስርዓታዊ ሀይል አልነበረም።
መቄት ቁርአበሳ ከተባለ ቦታ ላይ የብልፅግናው አገዛዝ ተከፋይ ሰራዊት በአናብስቶቹ የ22ኛ ክፍለጦር ነፍጠኞች ነፍሱ ለሲዖል ስጋው ለጅብ ሲደረግ፤ በዚህ አውደ ውጊያ በጠላት ላይ የተወሰደ አካላዊ እና ቁሳዊ ኪሳራዎች፦
✔️42 የተደመሰሰ የጠላት ሰራዊት
✔️ 37 ቁስለኛ የተደረገ
✔️ 531 የክላሽ ተተኳሽ
✔️ 301 የብሬን ተተኳሽ እና
✔️ ከ17 በላይ ቦንብና
✔️ ዘጠኝ የወገብ ትጥቅ
ከዚህ በተጨማሪ ለወቅቱ ማዕረጋቸው ያልታወቁ ሁለት(2) ከፍተኛ የአገዛዙ የጦር መኮነኖች መደምሰሳቸውን ከስርፋው ማረጋገጥ ተችሏል።
መዳረሻውን ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ሕዝብ የሕልውና ተጋድሎ ይቀጥላል ሲል መረጃውን የ106ኛ ኮር ሚዲያና ኮሚኒኬሽን መምሪያ ሃላፊ አርበኛ እሸቱ አባተ መረጃውን አድርሷል።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
ሰኔ 20/2018 ዓ/ም
በሽዋ ጠቅላይ ግዛት የተራሮች ሁሉ ንጉስ አቡዬ ሜዳ ወይም አስቴ ጎማ ተራራ ነው።
ሰኔ 20/2018 ዓ.ም
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መንዝና ይፋት አወራጃ ወሰን ላይ የሚገኘው በአካባቢው ማኅበረሰብ አጠራር አስቴ ጎማ ይባላል። በጥንት ዘመን በተራራው አናት ላይ አስቴ እና ጎማ የሚባሉ ወንድማማቾች ይኖሩበት እንደነበር ይነገራል። በጂኦግራፊያዊ አጠራሩ ግን «አቡዬ ሜዳ» በሚል ስም ነው የሚታወቀው።
ይህ ተራራ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ከሚገኙት ሁሉ በከፍታው ቀዳሚ ነው። በዘለቀ በጋሻው በተጻፈው "የግሼ ሕዝቦች ሕያው ባህልና ታሪክ" በተሰኘው መጽሐፍ ላይ ከባሕር ወለል በላይ 4 ሺሕ ሜትር ከፍታ እንዳለው ተጠቅሷል።
ከመሐል ሜዳና ከአንፆኪያ ገምዛ ወደ ግሼ ራቤል ወረዳ የሚያደርሱት የጠጠር መንገዶች በዚሁ ተራራ ምሥራቃዊ አቅጣጫ ግርጌ ላይ ይገናኛሉ። መነሻችን ከመሐል ሜዳ ከሆነ በ85 ኪሎ ሜትር፣ ከአንፆኪያ ገምዛ ወረዳ ከሆነ ደግሞ በ25 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ስንደርስ ተራራውን እናገኘዋለን።
በዋናው መንገድ ያለንን ጉዞ ገታ አድርገን ወደ ተራራው አናት እንውጣ። በተራራው ምሥራቃዊ ክፍል የመኪና መንገዱን ትተን ወደ አናቱ ስንወጣ የጦስኙ ጠረን ያውዳል። በአካባቢው ማኅበረሰብ ንቦች ማር የሚሠሩበት፣ እረኞችም የሚመጡት የቋቁቴ አበባ ማራኪነት ከነፋሻማውና ከንጹሑ አየር ጋር ተዳምሮ የዳገቱን ድካም ያስረሳል።
ከጉም ጋር እየታገሉ ዓይን ማየት እስከሚችል ድረስ የሚታየው መልክዓ ምድር ልዩ የሆነ ግርማ ሞገስ አለው።
በተራራው አናት ላይ ሆነን ስንመለከት ታች ያሉ የመኖሪያ መንደሮች የጠጠር ያህል ያንሳሉ። አልፎ አልፎ በአነስተኛ ተራሮች ላይ ያለው የባሕር ዛፍ ደን ደግሞ የልጆች ቆንጮ ይመስላል።
ቀልብን የመግዛት ተፈጥሯዊ ኃይል ያለው ይህ የአቡዬ ሜዳ መልክዓ ምድር፤ ቀን ቀን ለስለስ ብሎ፣ ምሽት ሲመጣ ደግሞ በከፍተኛ ግፊት የሚነፍሰው ነፋስ የተራራውን ከፍተኛነት ማሳያ ምስክር ነው።
የተራራው ዙሪያ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ተጠብቆ መቆየቱ በጦስኝና በኮሶ ዛፎች መሸፈን መጀመሩን የአስቴ ጎማ ተራራ ክፍለ ጦር ፋኖ ለደን ጥበቃ የሰጠውን ትኩረት ያሳያል። በተለይ ደግሞ ጦስኙን የአካባቢው ማኅበረሰብ እያጨደ በመሸጥ እንደ አንድ የገቢ ምንጭ አድርጎ እየተጠቀመበት መሆኑ፣ አካባቢው ጥቅም ሊሰጥ በሚችል መንገድ እየተጠበቀ ስለመሆኑ ማሳያ እንደሆነ ያመላክታል።
ይህን የሸዋ ጠቅላይ ግዛት ከፍተኛ ቦታ መሰረት በማድረግ የስም ሰያሜ የያዘው የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ መሐመድ ቢሆነኝ ኮር ግዙፉ አስቴ ጎማ ተራራ ክፍለ ጦር በመቶ አለቃ ኤርሚያስ ግጨውና ሌሎች አመራሮች በጥበብ እየተመራ ባለፉት ሶስት አመታት የአማራ ህዝብ ትግል በመደበኛና በደፈጣ ወጊያ የጠላትን ሃይል መጊብያና መውጫ ከማሳጣት በላይ ብዛት ያለው የጠላት ሃይል በመደምሰሰ የጠላትን አስክሬን ሳይቅር በክብር ያስቀበር ጀግና ጦር ነው።ክፍለ ጦሩ በምሃንዲሶቹ የጠላትን ሃይል አካለ ጎደሎ ከማድረጉም በላይ ቀጠናውን የማይደፈር በማድረግ ጀግንነታቸውን አስመስክረውበታል ከአስራ ሰባት በላይ የአብይን ኮማንዶ ሲማርኩ ከመቶ ሃምሳ በላይ ከነሙሉ ትጥቃቸው በመክዳት ፋኖን ተቀላቅለዋል።
አስቴ ጎማ ተራራ ክፍለ ጦሩ በሰው ሃይልና በትጥቅ የተደራጀና በርካታ ድሎችን የተቀዳጀች ለጠላት የቁም ቅዠት የሆነ የጀግኞች ስብስብ ናቸው።
እንደ አባቶቻቸው ሆነው ሰማዕትነትን የተቀበሉባት ከጠላት ጋር አንገት ለአንገት ተናንቀው የጠላትን ቦኔትና ሬንኮት በእጃቸው የሚቀሙ የጠላትን የድሽቃ አፈሙዝ የሚጨብጡ በከበባ ውስጥ ሲገቡ እና በጠላት ጥይት ሲቆስሉ የተቻላቸውን ያክል ጠላትን አጋድመው ልክ እንደ አባታቸው የራሳቸውን ጥይት ጠጥተው የተሰው ጀግኖች የቴወድሮስ ልጆች የፈለቁባት ልክ እንደ ታማኙ ገብርየ ለዚህ ትግል እስከመጨረሻው የታመኑና ከፊት የሚዋጉ ጀግና የጦር ሰራዊት እና አመራር ያሉባት በመስዋዕትነት የተገነባች ጀብደኛ ጦር ናቸው።
አንፆኪያ ገምዛ፥ ግሸ ራቤልና የዳዋ ጨፋ ወረዳ ውስን ቀበሌ የሚያስተዳድር ሲሆን በፍትህ አሰጣጡና በሲቪል አስተዳደር የህዝብ ቅቡልነቱ የሚለይና ደጀን የሆነ ህዝብ ያለው ለህዝብ የሚኖር ክፍለ ጦር ህዝቡም ለክፍለ ጦሩ ታማኝና የጀርባ አጥንት መሆኑን ያስመሰከረ ነው።
ምንጭ-መሀመድ ቢሆነኝ ኮር ህ/ግንኙነት ክፍል
"ክብር ለትግሉ ሰማዕታት "
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
ሰኔ 20/2018 ዓ/ም
#ሰበር የአውደ ውጊያ ዜና!
▭▭▭▭▭▭▭▭▭
#ስም_ከጠየቋችሁ_መብረቅ_ክፍለ-ጦር በሏቸው✊
#በትናትናው ዕለት 19/10/2018 ዓ/ም የዳግማዊ ቴዎድሮስ 5ኛ ኮር መብረቅ ክፍለ-ጦር በሊቦ ከምከም ወረዳ ሚካኤል ደብር ቀበሌ ባደረገችው ተጋድሎ
ከጠላት በምርኮ የተገኙ፦
➣19 ክላሽ ኮፍ የነፍስወከፍ መሳሪያ ✅
➣1 ብሬን እስከ ሸንሸኑ✅
➣1ጥቁር ስናይፐር ✅
➣2 መገናኛ ሬዲዮ✅
➣17 የሞተ
➣ 37 ቁስለኛ
#ክብር ምስጋና ለትጉሉ ሰማዕታት 🙏
#ድል ለህዝባችን💪
የመብረቅ ክፍለ-ጦር ህ/ግንኙነት ክፍል
ፋኖ አላዓዛር ዳግማዊ ቴድሮስ
አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ 106ኛ ኮር 34ኛ ክፍለጦር ታላቅ ተጋድሎ አደረጉ!
የአገዛዙ ሰራዊት በጋዞ ወረዳ እና በአንጎት ወረዳ አይነኬዎቹን የምድር ድሮን 34ኛ ( ደጀን) ክፍለጦርን ለማፈን በገፍ ያስገበውን ሰራዊት ሙት እና ቁስለኛ በማድረግ ወደመጣበት መልሰውታል። በቀን 18/2018 ዓ.ም የወገን ሰራዊት ከግዳጅ መልስ በደጋው አካባቢ በሰፈረበት ወቅት ቆላማውን ከሰራዊት ነፃ የሆነውን ቦታ ጋዞ ወረዳ 02 ቀበሌ ቢጦይ ከኩልመስክ ተነስቶ በመግባት የገበሬን አዝመራ እና ገንዘብ ዘርፏል።
የዘረፈው የንፁሀን የቤት ውስጥ ንብረት ዝርዝር:-
=> ስንዴ = 10 ኩንታ
=> የመስኖ ማዳበሪያ = 2ኩንታል
=> ብር /ገንዘብ/ = 185ሺ ብር (ገበሬው የሽጠው የበሬ ብር )
=> ማር = 10ኪግ
=> ሶላር = 3 ( የአንዱ ዋጋ 10ሺ ብር)
=> ፍራሽ = 2 ፍሬ
=> አካፋ = 4
=> ዶማ = 5
=> የታሰሩ ንፁሀን አርሶ አደሮች =10
=> ተደብድበው የተኙ ንፁህ አርሶ አደሮች 3
ይህን ዘርፎ የወሰደ ሲሆን የተፈጨ ዱቂት እንዲሁም የጠላ እህልን በማደባለቅ እና በማውደም ለማህበረሰቡ የጥላቻ ጥጉን አሳይቷል። አናብስቶቹ የ34ኛ ክ/ጦር 1ኛ ሻለቃ እና የክፍለጦሯ ቃኝ በሌሊት ከሻሪያገነት ቢጦይ በመግባት አስፈርጥተውታል፤ ለማህበረሰቡም ደርሰውለታል ። 2ኛ እና 3ኛ ሻለቃዎች በእስታይሽ(ደረቅ ወንዝ፣ በርበሬ ዛፍ፣አላላች ፣) በአንጎት(አድስኬ ፣ዋይደፈር ) የመጠውን የጠላት ሀይል ሙት እና ቁስለኛ በማድረግ ወደመጣበት መልሰውታል። በጋዞ ወረዳ እስተይሽ ከተማ ዙ23 በመተኮስ የማህበረሰቡን ንብረት አውዱሟል። ገበየ የሚገበያየውን ማህበረሰብ በማንበራገግ ንብረቱ እንድጠፋና እንድዘረፍ እንድሁም በሰላም እንደይገበያይ አድርጓል።
ህልናውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ 106ኛ ኮር 34ኛ ክ/ጦር ህዝብ ግንኙነት
ሰኔ 20/2018ዓ.ም
+4
ታሪክን አገላብጠህ ጠይቅ... 'ኢትዮጵያ' የምትለዋን ቃል ስትጠራ፣ ከጀርባዋ ማንን ታገኛለህ? ሀገር ስትደፈር የደረት ጋሻ፣ ድንበር ሲጣስ የነጻነት ምሰሶ የሆነው ማነው?"
"ለዚህ ነው ዛሬ ላይ... 'አማራ ማለት ለዚህች ውድ ሀገር የአማራ ፋኖ' የአሳምነው ግልገል የሚለው ቃል ተራ መፈክር ያልሆነው። እርሱ የደም ቃል ነው! ፋኖነት ትናንት በአድዋ በረሃዎች የጠላት መደናገጫ የነበረ ህዝባዊ ማዕበል ነው። ዛሬም ያው ታሪካዊ መንፈስ በልጆቹ ደም ውስጥ ይጮኻል!
"አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ... ፋኖ ማለት የጦርነት ናፋቂ አይደለም። ፋኖ ማለት የአማራ ህዝብ የህልውና ዋስትና፣ የማንነቱ ጥበቃ፣ እና የነጻነቱ የመጨረሻ ምሽግ ነው። የደረሱበትን በደሎች ለመመከት፣ ክብርና ፍትህ በምድሪቱ ላይ ለማንገስ የተነሳ የህዝብ አለኝታ!"
አዎ ! አማራ ማለት ፋኖ ነው... ለሀገር ፍቅር የሚሰዋ፣ ለነጻነቱ የማይደራደር፣ እና ፍትህ እስኪረጋገጥ ድረስ ወደኋላ የማይመለስ ፅኑ አለት! ታሪክ አይዋሽም... ትናንትም፣ ዛሬም፣ ነገም!"
አማራ ማለት ፋኖ!#Dawit #Amhara
+2
በሜካናይዝድ የታገዘ ውጊያ የከፈተው የአረመኔው ሰራዊት በ206ኛ ኮር 34ኛ ክ/ጦር በአዋባል ድባቅ ተመቷል።
ሰኔ 20/2018 ዓ.ም
~~~~~~
በሜካናይዝድ ድጋፍ ተማምኖ መነሻውን የትኖራ በማድረግ በአዋባል ወረዳ ጥቃት ለማድረስ የተንቀሳቀሰው የአረመኔው ሰራዊት በ206ኛ ኮር 34ኛ ክ/ጦር በመብረቁ ሻለቃ ድባቅ ተመቷል።
ከወጀል እስከ ፅድ ማርያም ሉማሜን አካሎ በተደረገው እልህ አስጨራሽ ውጊያ ከጠዋቱ 1:00 ሰዓት እስከ ምሽት 1:00 የመብረቁ ሻለቃ ጠላትን ተፋልመዋለች።
ከጦር መኮንኖች ጀምሮ በርካታ የሚኒሻ አባላት በተደመሰሱበት ግንባር ድባቅ የተመታው ጠላት የሉማሜ ጤና ጣቢያ በቁስለኞች አጥለቅልቆታል።
አነጋጉን ውጊያ ከፍቶ የጀመረው የአረመኔው ሰራዊት በመብረቁ ሻለቃ ግንባር ግንባሩን ተመቶ ጨለማን ተገን በማድረግ ወደ መጣበት የተመለሰ ሲሆን መድፍ፣ ዘ-23፣ ሞርተር፣ ዲሽቃ እንደ ዝናብ በወረደበት ከባድ ትንቅንቅ መብረቁ ሻለቃ የጠላትን እግረኛ ሰራዊት በማናጠል ከአፈር ሲቀላቅለው ውሏል።
አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳሰብ ! አዲስ ተስፋ
የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
በስምህ እየማሉ አላማህን የሚያስፈፅሙ ሺ ጀግኖችን አፍርተሀል በመላዉ የአማራ ህዝብ ልብ ዉስጥ ለዘላለም በክብር ትኖራለህ 💚💛❤
ጾታዊ ጥቃት የአማራውን ሞራልና ሥነ-ልቦና ለመስበር የሚተገበር የብልፅግና የእርኩሰት ተግባር!
የአብይ አህመዱ የብልፅግና ስርዓት ከመደበኛ ውጊያው ባለፈ ስልታዊ በሆነ መንገድ አሁንም ንፁህና አቅመ ደካማ እንዲሁም ኢላማ ያደረገ መዋቅራዊ ጥቃት እያካሄደ ነው። የብልፅግና ወንበር ጠባቂው መከላከያ ሠራዊት ከፍተኛ አመራሮች በሴቶች ላይ ሚፈጽሙት ወሲባዊ ጥቃት፣ ግድያ እና የሰብአዊ መብት ጥሰት ይገኙበታል። በዚህ ሁኔታ ውስጥ አፋብን የሚወስደው እርምጃ ከመደበኛ የህልውና የትጥቅ ትግል ባለፈ፣ የአማራን ህዝብ ደህንነት የመጠበቅና ፍትሕን በራስ የማስከበር ትግል ነው።
የብልፅግናው መከላከያ ህግና ስርዓት ያውቃል ባይባልም ዓለም አቀፍ የወንጀል ሕግ በጦርነት ወቅት የሚፈጸሙ ጾታዊ ጥቃቶችን እንደ ጦርነት ወንጀል ይፈርጃቸዋል። በአሁኑ ወቅት የሚታየው እውነታ ግን ይህ ድርጊት በግለሰብ ወታደሮች የሚፈጸም አጋጣሚ ሳይሆን፣ የአማራን ህዝብ አለፍ ሲልም የአማራ ፋኖን ሞራልና ሥነ-ልቦና ለመስበርና የሚተገበር ስልታዊ መሣሪያ መሆኑን ያሳያል። በከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖች (ለምሳሌ እንደ ኮሎኔል አበራ አይነትና መሰል አመራሮች) የሚፈጸሙ እንደ አስገድዶ መድፈርና ወሲባዊ ባርነት ያሉ ድርጊቶች፣ በሠራዊቱ ውስጥ ያለውን የተቋማዊ ዲሲፕሊን ውድቀትና የሞራል ዝቅጠት በግልጽ ያሳያሉ። ሴቶች ጥበቃ ሊደረግላቸው ሲገባ በጠላት የብልፅግናው ስርዓት ፆታዊ ጥቃቱን እንደ አንድ የጦርነት ግንባር አድርጎ የአማራውን ስነ ልቦና ማዳከሚያ መንገድ አድርጎ ይዞታል።
የአብይ አህመድ ዙፉን ጠባቂ መከላከያ ሠራዊት በአሁኑ ወቅት ለሕዝብ ሉዓላዊነት፣ ለህግና ስርዓት ከመገዛት ይልቅ የአንድ የዘመናችን እብድ ስብስብ የፖለቲካ ቡድን ፍላጎት ለማስፈጸም በገዛ ወገኖቹ ላይ የኃይል እርምጃ የሚወስድ የሥርዓት አስከባሪ ሆኗል። አሁን ላይ የአፋብን ትግል በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ዘንድ የሕዝብ መከላከያ ጋሻ ሁኖ እየታየ ይገኛል። ወንጀለኛው ብልፅግና ስርዓት ራሱ ሕግ አስከባሪ በሆነበት ሁኔታ፣ ፋኖ ግፈኞችን በመደምሰስ የሚወስደው እርምጃ በሕዝብ ዘንድ ከፈጣሪ እንደተሰጠ ፍትሕ ይቆጠራል። በአማራ ህዝብ ላይ የሚታየው ግፍ የሰው ልጅ ክብር መረገጥን የሚያሳይ የታሪክ ጥቁር ነጥብ ነው። የፋኖ ትግል ይህንን ጥቁር ታሪክ ለመቀየርና ለአማራ ህዝብ ሰብአዊ መብት፣ ክብር ዋስትና ለመሆን የሚደረግ የሞት ሽረት ትግል ነው።
©Birhanu Chalie Demelash
+5
በእነማይ ወረዳ የሚገኙ ቀበሌዎች ህዝባው ውይይቶች እንደቀጠሉ ነው!!
64ኛ ክ/ጦር ሰኔ 20/2018 ዓ.ም
~~~~~~~~
ሰኔ 19/2018 ዓ.ም የ64ኛ ክ/ጦር፣ የእነማይ ወረዳ ጊ/መንግስት እና የ4ኛ ሻለቃ አመራሮች በተገኙበት በእነማይ ወረዳ ቀሸምሽ ቀበሌ ህዝባዊ ውይይት ተካሂዶል።
በህዝባዊ ውይይት መድርኩ ለተገኙት የማህበረሰብ ክፍል የአማራ ህዝብ የህልውና ትግል ያለበት ወቅታዊ ሁኔታ ሰፊ ግንዛቤ በመስጠት በቀበሌ ጊ/መንግስት አመራሮች የፍትህ አሰጣጥ፣ የቀበሌ መልካም አስተዳደር ፀጥታ፣ ህገወጥ የኦል መሬት ማስከበር፣ የፋይናስ እና ሎጀስቲክ አሰባሰብ በተመለከተ ውይይት በማድረግ በመገምገም ለቀበሌ ጊ/መንግስት አመራሮች አቅጣጫ ተሰጥቷል።
በውይይት መድረኩ የተገኙት የማህበረሰብ ክፍል እንደተናገሩት በአማራ ህዝብ ላይ ከፍተኛ የሆነ በደል እና ጭቆና የሚፈፅም የአብይ አህመድ አምባ ገነን አገዛዝ ለመገርሰስ ህዝባችን ከፋኖ ጎን መሆኑን በሰፊው አስረድተዋል።
አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳሰብ! ?አዲስ ተስፋ!!
ሰኔ 20/2018 ዓ.ም
አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት
አስቸኳይ የጥንቃቄ መልዕክት⚠️
እንዴት አደራቹህ ጓዶች ጠላት በሁሉም ቀጠና አመራሮችን ለይቶ ለመምታት ሰርጎ ገቦችን በከፍተኛ ገንዘብ ገዝቶ ስምሪት በመስጠቱ ከፍተኛ ጥንቃቄ ይደረግ።
👉መረጃዉ እስከ ታችኛዉ የአመራር መዋቅር ተደራሽ ይደረግ❗️
(መረጃው: የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የህዝብ ግንኙነት መምሪያ ነው)✅
አስቸኳይ የጥንቃቄ መልዕክት⚠️
እንዴት አደራቹህ ጓዶች ጠላት በሁሉም ቀጠና አመራሮችን ለይቶ ለመምታት ሰርጎ ገቦችን በከፍተኛ ገንዘብ ገዝቶ ስምሪት በመስጠቱ ከፍተኛ ጥንቃቄ ይደረግ።
👉መረጃዉ እስከ ታችኛዉ የአመራር መዋቅር ተደራሽ ይደረግ❗️
(መረጃው: የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የህዝብ ግንኙነት መምሪያ ነው)✅
+1
የፓዊ ወረዳ ጊዜያዊ መንግስት ግምገማ አካሄደ !!!
ሰኔ 19/2018 ዓ.ም የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ቴዎድሮስ ዕዝ 105ኛ ኮር 66ኛ ክ/ጦር የፓዊ ወረዳ ጊዜያዊ መንግስት የ105ኛ ኮር አመራሮች እና የ66ኛ ክ/ጦር አመራሮች በተገኙበት የወረዳ አመራሩ ጥቅል ግምገማ በማድረግ ጠንካራ እና ደካማ ጎኖችን በመለየት እንዲሁም የአመራር ሽግሽግ በማድረግ የቀጣይ ጊዜያት የስራ አቅጣጫ በማስቀመጥ ከዚህ በበለጠ ጠንክሮ መስራት እንደሚገባ በኮር አመራሮች እና ክ/ጦር አመራሮች ተገልጿል።
አዲስ ትዉልድ፣አዲስ አስተሳሰብ፣አዲስ ተስፋ !!!
ሰበር ዜና
#ሁለቱ የደጋ መብረቆች ፈረስ ቤት ላይ ታሪክ ሰርተዋል።
ደጋ ዳሞት ፈረስ ቤት ላይ እንደተለመደው እጅን በአፍ የሚያስጭን ታሪክ ተሰርቷል።
ደጋ ዳሞት ሐሙስ ገበያ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ጀግናው የደጋ ዳሞት ሻለቃ፣ የደጋ ዳሞት አባት አርበኞች ጦርና ተርቦች የስናን አባጅሜ ሻለቃ ተዋርዋሪ ኃይል በጋራ ባካሄዱት ከፍተኛ ውጊያ፣ የአገዛዙን 76ኛና 79ኛ ክፍለጦር ሰራዊትና አመራሮችን በመደምሰስ በርካታ የቡድንና የነፍስ ወከፍ መሳሪያ ማርከዋል።
የ76ኛ ክ/ጦር መሪ የነበረው ኮለኔል አበራና የ79ኛ ክ/ጦር ሻለቃ መሪ ሌ/ኮለኔል አለሙ በውጊያው ከተደመሰሱ የአገዛዙ ዙፋን ጠባቂዎች መካከል ናቸው። ከእነዚህ አመራሮች በተጨማሪ በርካታ የሻለቃ፣ የሻምበልና የመቶ መሪዎች በውጊያው ተደምስሰዋል።
ፈረስ ቤት ከተማ ለመግባት ላለፉት 7 ተከታታይ ቀናት ሲዋጋ የነበረው የአገዛዙ ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት ሐሙስ ገበያና አበርት ላይ በደረሰበት ከፍተኛ ምት ለአሞራ ቀለብ ሆኖ ቀርቷል።
የ24ክ/ጦር አንድ አካል የሆነው የስናን አባጅሜ ተወርዋሪ ሻለቃ፣
ድል የማይለያቸው ጀግኖች፣ አካባቢ የማይገድባቸው በየሄዱበት ምርኮ የማይለያቸው፣ ሞት አይፈሪዎች ዛሬም ከደጋ ዳሞት ወንድሞቻቸው ጋር በመሆን እንደተለመደው ሞትን ተረማምደው ታምር ሰርተዋል።
የቡድንና የነፍስ ወከፍ መሳሪያ በመማረክ ታሪካቸውን ዛሬም በደማቁ ከተበዋል።
የአብይ አህመድ ኮሎኔሎች በአማራ ህዝብ ላይ የሚፈፅሙት ሁለንተናዊ ጦርነት ነው። በጅምላ ጨራሽ መሳሪያ ከሚጨፈጭፉት ጎን ለጎን እናቶችን እና ልጃገረዶችን አስገድደው በመድፈር እየፈፀሙት ያለው የጦር ወንጀል በብዙ መልኩ ያልተነገረ ነው።
ዛሬ ደጋ ዳሞት ላይ የተሸኘው ኮሎኔል አበራ ከእጅ ስልኩ ከተገኘው ምስል ማረጋገጥ እንደሚቻለው በዚህ መልኩ ንፁሃንን ያዋርዳሉ። እነኝህን አለመታገል እንዴት ይቻላል።
በዚህ ውጊያ አንድ የክፍለ ጦር አዛዥ፣ አንድ የኮሎኔል ማዕረግ ያለው የስታፍ አባል እና ሁለት ሻለቃ መሪዎች ይገኙበታል።
