ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
Открыть в Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
Больше2 929
Подписчики
+224 часа
+3727 дней
+36730 дней
Архив постов
የመሀመድ ተሰማ ጦር በኢቲዮ-ቴሌኮም የህዝብ መገልገያ ታወር ላይ ያደረሰው ጥፋት!!
=========================
......ነሐሴ 05/2018 ዓ.ም
ሞጣ በሁለት እጁ እነሴ ወረዳ አስቴሪዮ በምትባል ታዳጊ ከተማ ላይ ከሐምሌ 26_ነሐሴ 02/2018 ዓ.ም መሽጎ የቆየው የህዝብ መገልገያ ተቋማትን ካምፕ እና ምሽግ በማድረግ አስቴሪዮ ከተማ ላይ የሚገኘውን የኢትዮ-ቴሌኮም ታወር ካምፕ በማድረግ ለ1ሳምንት መሽጎ በመቆየት ህዝቡ የስልክ አገልግሎት እንዲቋረጥ የሶላር ሲስተም ባትሪወችን እና ፓኔሎችን ሙሉ የኤሌክትሪክ መስመሩን በመቆራረጥ እና ቦክሶችን በመሰባበር ጉዳት ያደረሰ ሲሆን በከተማው ውስጥ የሚገኙ በርካታ የንፁሀን መኖሪያ ቤቶችን ሱቆቹን እና ሆቴሎችን በመዝረፍ ነሐሴ 3 የዘረፋቸውን እቃ በተሽከርካሪ ጭኖ ወጥቷል።
የ54ኛ ክ/ጦር የሁለት እጅ እነሴ ወረዳ ጊዜያዊ መንግስት እና የፀጥታ ዘርፍ ተጠሪወች የኢትዮ -ቴሌኮም ባለሙያወችን በማስመጣት ጥገና ተደርጎለት አገልግሎት እንዲሰጥ ለማድረግ ሁለተኛ ቀን የወሰድ በባለሙያወች የመጠገን ስራ እየተሰራ ይገኛል።
ለሀገር ሰላም እና ደህንነት ነው የወጣው የሚለው የአብይ ዙፋን አስጠባቂ በተግባር ሲገለጥ ይኸው ነው..
የኢቲዮ-ቴሌኮም ባለሙያወች ፈጣን ምላሽ ለመስጠት ላደረጋቹህት ረብርብ በ201ኛ ኮር ስም ምስጋናየን አቀርባለሁ።
የአፋብን ጎጃም ጠቅላይ ግዛት ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
አሜ፣ ከእኔ ጋር ምን የማያምር አለ? ወንድሜ፣ ሺህ ዓመት ኑርልኝ! ፍጹም አማራት፣ ፍጹም ጀግንነት ወንድሜ፤ ሁልጊዜም መኖርህ ያኖረኛል። ለአማራ ሕዝብ ማንኛውንም መስዋዕትነት የማይከፍል የመሬት ታጋይ ፋኖ የለም፤ ኑ አብረን እንሸንፍ ድል ለአማራ ህዝብ! #Dave #Amhara
የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ንቅናቄ ምኒልክ ዕዝ 101ኛ ኮር 35ኛ ክፍለጦረ በአገዛዙ ሰራዊት ላይ ከባድ የደፈጣ ድል ተቀዳጀ!
የ101ኛ ኮር አሃድ የሆነችው 35ኛ ክፍለጦረ 1ኛ ሻለቃ በሰሜን ወሎ ዞን ሀብሩ ወረዳ ከውርጌሳ ወደ መርሳ አቅጣጫ በካሶኒ መኪና ተጭኖ ሲጓዝ በነበር የአገዛዙ ሚኒሻ ላይ ኤላ ከተባለ ቦታ በተወሰደ ደፈጣ ከአምስት (5) በላይ ሚኒሻ ሲደመሰስ ቁጥሩ በውል ያልታወቀ ቁስለኛ በማድረግ የካሶኒው ሾፌር የውረ ድንብሩን ሲያሽከረክር ሁለት (2) የግለሰብ ባጃጆችን በመግጨት ወደ መረሳ ሆስፒታል እንደሄደ የአይን እማኞች ገልፀዋል ሲል የ35ኛ ክፍለጦር ቃል አቀባይ መረጃውን አድርሳል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!!
ነሐሴ 05/2018 ዓ ም
የአደረጃጀት ዜና
ነሐሴ 05/2018 ዓ.ም
አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ፣ 305ኛ ጎቤ መልኬ ኮር፣ 25ኛ ክፍለ ጦር የጎንደር አንድነት በተመሰረተ ማግስት፣ በቀጣይ ክፍለ ጦሩን ይመሩልኛል ያላቸውን አመራሮች መስፈርት አወዳድሮ ለሰራዊቱ ይፋ አደረገ።
ወታደራዊ ክንፉ ከኮር አመራሮች እስከ አባላት ይመራሉ ተብለው የታመነባቸውን በማስገምገም፤ በቀጣይ የአማራን የህልውና ትግል ያስቀጥላሉ ተብለው የሚጠበቁ፣ ያላቸውን ወታደራዊ ብቃት፣ የትግል ቆይታ ጊዜ፣ ለዓላማው ያላቸውን ፅናት፣ የረጅም ጊዜ የመምራት ጥበብና ልምድን ያገናዘበ እንዲሁም በስነ ምግባራቸው የተመሰከረላቸውን አመራሮች መርጧል። ድርጅቱ፣ ዕዙና ኮሩ የሚሰጣቸውን ግዳጅ በአግባቡ መፈፀም የሚችሉና በህዝባችን ዘንድ ጭምር አመኔታ ባላቸው መሪዎች ላይም የኃላፊነት ድልድል ተደርጓል።
በቀን 05/12/2018 ዓ.ም. በቀጠናው የተገኘውን አባልና አመራር በመሰብሰብ በቀጣይ ክፍለ ጦሩን የሚመሩትን በማስገምገም ተሰይመዋል።
የኮሩ ምክትል ወታደራዊ አዛዥ አርበኛ ሸቴ አሸብር፣ የኮሩ ፖለቲካ መምሪያ ኃላፊ አርበኛ መልካሙ ቸኮል እና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በቀጣይ የ25ኛ ክፍለ ጦርን የሚመሩ አመራሮች የተሰጣቸው የሥራ ኃላፊነት ተሰርቶ ይፋ ተደርጓል።
የተመደቡ አመራሮች ዝርዝር፦
1.አርበኛ ደሳለኝ ተቀባ — ዋና አዛዥ
2.አርበኛ አስማማው ነጋ — ም/አዛዥ
3.አርበኛ አምሳሉ ዘሪሁን — አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ
4.አርበኛ መሰንበት አድኖ — ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ
5.አርበኛ ናቃቸው እንያው — ም/ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ
6.አርበኛ አዛናው በየነ — ሎጀስቲክስ መምሪያ ኃላፊ
7.አርበኛ አለምነህ አስማረ — ፋይናንስ መምሪያ ኃላፊ
8.አርበኛ ሀጎስ እጃርገው — ፖለቲካ መምሪያ ኃላፊ
9.አርበኛ ፍታለው አዳነ — ም/ፖለቲካ መምሪያ ኃላፊ
10.አርበኛ ባቡ ከፋለ — ስልጠና መምሪያ ኃላፊ
11.አርበኛ ጌታቸው ዘሪሁን — ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ
12.አርበኛ ወንዴ አለኸኝ — ወታደራዊ ዕቅድና ስትራቴጂ መምሪያ ኃላፊ
13.አርበኛ ባንዴራው ምርኩዝ — ኦዲተር
14.አርበኛ ገበየሁ አዳነ — ህግ ክፍል መምሪያ ኃላፊ
15.አርበኛ ሸት ደሳለኝ — የሰው ሃይል መምሪያ ኃላፊ
16.አርበኛ ሀውልቴ አዳነ — ግዥ መምሪያ ኃላፊ
17.አርበኛ አይሸሽም አበይ — ኦርዲናንስ መምሪያ ኃላፊ
18.መረጃ መምሪያ ኃላፊ — ***
19.አርበኛ ቅንነት አደላዳይ — ትጥቅና ስንቅ መምሪያ ኃላፊ
20.አርበኛ አየልኝ እንዳልክ — መገናኛ መምሪያ ኃላፊ
በመሆን ክፍለ ጦሩን ይመራሉ ተብለው የተመደቡ ሲሆን አመራሮች ሁሉንም በቅንነትና በእኩል ዓይን እንደሚያገለግሉ በአባሉ ፊት ቃል የገቡ ሲሆን፤ በጀግኖች መስዋዕትነት የተገነባው የጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዘለቀ ዕዝ አንድ መሆኑና የአንድነት ዜና መበሰሩ ትልቅ ደስታ የተሰማን መሆኑን እየገለጽን፣ በቀጣይም ድርጅታችን፣ ዕዛችንና ኮራችን የሚሰጡንን ግዴታና ኃላፊነት በአግባቡ ለመወጣት ከጎንደር አንድነቱ ጎን መቆማችንን እናረጋግጣለን ሲል መረጃውን ያደረሰን የኮሩ የህዝብ ግንኙነት ነው ።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
ከእነዋሪ እና ከጅሁር አቅጣጫ የተንቀሳቀሰው የአገዛዙ ጦር በነጎድጓድ ክፍለ ጦር ከባድ ምት አስተናገደ!!
ነሐሴ 0572018 ዓ.ም
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ዓፄ ዘርያዕቆብ ፩ኛ ኮር ነጎድጓድ ክ/ር ከአገዛዙ ጥምር ጦር በኩል የተሰነዘረውን የማፈን ሙከራ በመቀልበስ ከፍተኛ ድል ማስመዝገቡን የኮሩ ሕዝብ ግንኙነት ገለፀ።
የጠላት ኃይል በዛሬው ዕለት ከማለዳው 12:00 ሰዓት ጀምሮ በእነዋሪ ከተማ እና በጅሁር አቅጣጫዎች በመንቀሳቀስ በአፄ ዘርዓያዕቆብ ፩ኛ ኮር ነጎድጓድ ክፍለ ጦር ላይ ከበባ እና ማፈን ለመፈጸም እንቅስቃሴ ያደረገ ሲሆን፤ ነገር ግን የክፍለ ጦሩ ሁለት ሻለቆች በወሰዱት የተቀናጀ ሥልታዊ ማጥቃት ጠላትን ድባቅ መመታቱ ታወቀ።
ለማጥቃትና ለማፈን የመጣው ጠላት፣ በነጎድጓድ ክ/ጦር በመልሶ ማጥቃት የጠላት የሰው ኃይል እና ቁሳቁስ ላይ ከፍተኛ ኪሳራ በማድረስ የጦሩን አቅም የሚመሰክር ወታደራዊ ምት በመሰጠቱ ወደ መጣበት እዲመለስ ተደርጎል ሲል ኮሩ ከግንባር በላከው መረጃ አሳውቋል።
" ክብር ለትግሉ ሠማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
የጽናት፣ የመስዋዕትነት ክንዳችን የአማራ ህዝብ ነፃ እስከሚወጣ ድርስ ይሆናል!!
ተራሮቹ፣ ብርዱ፣ ሸለቆዎቹ... እር ሰንቱ ተነግሮ ያልቃል!
የአማራ ልጅ ፋኖ በየቀኑ የሚያልፍበት የትግል ጎዳና እንዲህ በቀላሉ በቃላት የሚገለጽ ተራ መንገድ አይደለም። በእያንዳንዱ ቁልቁለትና ዳገት ላይ የፅናት ታሪክ ይጻፋል፤ በእያንዳንዱ የሌሊት ቁርና የበረዶ ነፋስ ውስጥ ደግሞ የወገን ፍቅርና የዓላማ ጽናት ይፈተናል።
ዛሬ እኔና ወንድሞቸ ግርም የሚለው ከአራቱም ማዕዘን ከጎጃም ከወሎ ከሽዋ ከጎንደር ተሰባስበን በግዳጅ ቀጠና ላይ ቆመን፣ ያንን መራራ እውነት አብረን እየተጋፈጥነው እንገኛለን።
አካላችን በብርድ ቢቆረቁርም፣ እግራችን በጉዞ ቢዝልም፣ በውስጣችን የሚነደው የሕዝባችን አደራ ግን ከማንኛውም ፈተና በላይ ያሞቀናል። ይህ ጉዞ የምቾት ሳይሆን የህልውና፣ የነጻነት እና የክብር ጉዞ ነው!
እኛ የምንከፍለው እያንዳንዱ መስዋዕትነት ለወደፊቱ ትውልድ የሚተው የነጻነት መንገድ ነው። የትኛውም ዓይነት ዋጋ ቢጠይቅ፣ ምንም ያህል መንገድ ቢረዝም የአማራን ህዝብ ነፃ የማውጣት ታሪካዊ ግዴታችንን በጽናት እስከ መጨረሻው እንወጣታለን! ወንድሜን #አርበኛ #አማረ #አርበኛ #ሀብታም #አርበኛ #ሰይድ ፈጣሪ ይጠብቃችሁ። #Dave Amhara
ሻንበል መሪው እና ሁለት ጋንታ መሪውን ጨምሮ 11አባላት ፋኖን ተቀላቀሉ
➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺
.......ነሐሴ 05/2018 ዓ.ም
የመከላከያ ሻምበል መሪውን ጨምሮ 11 የጠላት ሰራዊት አባላት የ74ኛ ክፍለጦር የአባይ ሸለቆ ፋኖን ተቀላቀሉ።
በአፋብን ቴዎድርስ ዕዝ 201ኛ ኮር 74ኛ ክ/ጦርን 02 ሚሊሻ፣ 02 ፖሊስ፣04 መከላከያ እና 03 የአድማ በትን አባላት ተቀላቅለዋል።
በእነብሴ ሳር ምድር ወረዳ መርጡለ ማርያም ከተማ የሚገኘው የጠላት ካምፕ ሰሞኑን በደረሰበት ከፍተኛ ምት በመደናገጡ በየእለቱ አባላቱ እየከዱት ይገኛል። በዛሬው ዕለትም 11 አባላት ከፋኖ ጋር ተቀላቅለዋል።
1, ዳውድ አብዱ ==ፖሊስ ኮሪያ
2, እያየው ምረት ==ፖሊስ ኮሪያ
3, ይግረም ቸኮል ==ሚሊሻ ጅምስሪ
4, ኤፍሬም ገለቱ ==የመከላከያ ሻምበል መሪ
5, ሀይማኖት ማቲ ==የመከላከያ ጋንታ መሪ
6, መርጋ ፍቅሩ ==የመከላከያ ጋንታ መሪ
7, አሊ ሀሰን ==የመከላከያ አባል
8, ይሁኔ ሞገስ ==የሚሊሻ ብሬን ተኳሽ
9, ደስታው አማረ==አድማ በትን
10, ገብረ ጌታቸው==አድማ በትን
11, ኤርሚያስ ታደለ==አድማ በትን
ከእነ ሙሉ ትጥቃቸው ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 74ኛ ክፍለ ጦርን ተቀላቅለዋል።
አባላቱም እኛ የተለያዩ ተልዕኮዎችን ይዘን ገብተናል በዋናነትም ታጥቆ መውጣት ነበር አላማችን አሳክተነዋል ለመውጣት ስላልተመቸን ለወራት ለጠላት መገልገያ ሆነን ነበር ለዚህም ህዝባችንን እጥፍ አድርገን ለመካስ ዝግጁ ነን በፋኖ በኩል የተደረገልን አቀባበልም አስደስቶናል ብለዋል። ሌሎች አባላትም የግጭት ጠማቂው ጦረኛ ስርዓት ዙፋን ጠባቂ ከመሆን እና ቤተሰቦቹን ከማሳዘን ወደ ፋኖ በመቀላቀል የስርዓቱን እድሜ ማሳጠር እንዳለበት አሳስበዋል።
የአፋብን ጎጃም ጠቅላይ ግዛት ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
ነሐሴ 05/2018 ዓ.ም
የንስሮቹ የጋራ ክንድ እና የጣይመን ከተማው ሽንፈት!
ነሐሴ 04/2018 ዓ.ም አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ዳግማዊ ቴዎድሮስ 5ኛ ኮር ንስር በለሳ ቅጣው እጅጉ ክፍለ ጦር እና የ204ኛ አስቻለው ደሴ ኮር ባደረጉት የተቀናጀ የጦር ዘመቻ፣ በጠላት ኃይል ላይ የማይቀመስ የተባበረ ክንዳቸውን አሳርፈዋል።
ከአርባያ፣ ማክሰኝት፣ ጎሀላ እና ኪንፋዝ በገላ ተውጣጥቶ በ7 ተሽከርካሪዎች ጣይመን ከተማን ለመቆጣጠር አልሞ የነበረው የጠላት ስብስብ፣ በነቃው የንስሮቹ የክትትል መረብ ውስጥ በመግበቱ የታሰበውን ሳያሳካ ክፉኛ ምት አርፎበት እንዲበተን ተደርጓል።
ይህ ስልታዊ አሰራርን የተከተለ የውጊያ ውሎ፣ ንስሮቹ ገዥ ወታደራዊ ጠቀሜታ ያላቸውን ቦታዎች ቀድመው በመያዝ ጠላትን ወደ ወጥመድ በማስገባት የተካሄደ ነው። በተሰነዘረበት ከባድ ምት ክፉኛ የተመታው የጠላት ኃይል ከአቅሙ በላይ ስለሆነበት ከጫዊት አቅጣጫ ተጨማሪ ድጋፍ ቢጠይቅም፣ የጠቅላይ ግዛቱ ዋና ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ ጀኔራል ተሾመ አበባው በወሰደው ፈጣን የውጊያ ውሳኔ የጠላት ተጨማሪ ኃይል እንዳይንቀሳቀስ ተደርጓል። ይህም የወገን ኃይል በከፍተኛ ወታደራዊ መናበብ ጠላትን እንዲመታ ያስቻለ ውጊያ ነበር።
በአምስት አቅጣጫዎች ተግተልትሎ የመጣውና ጣይመን ከተማን ለመያዝ አልሞ የተነሳው የጠላት ስብስብ፣ በንስሮቹ ፈርጣማ ክንድ በተወሰደበት የተቀናጀ እርምጃ ከፍተኛ ሰብአዊና ቁሳዊ ኪሳራ አስተናግዷል። በዚህም 10 ተደምስሰው ከ20 በላይ ቀላልና ከባድ ቁስለኞችን በመሸከም ተስፋ በቆረጠ ሁኔታ ወደ ጎሀላ ለማፈግፈግ ተገዷል። ይህ የጦር ውሎ የፋኖን ከፍተኛ ስልታዊ ዝግጅት፣ የተቀናጀ የአመራር ብቃትና የጠላትን ውጥን ዕቅድ የማክሸፍ፣ ሙሉ ወታደራዊ ብቃትን በግልጽ ያሳየ ድል ነበር።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
+3
✅አፄ ምኒልክ ክፍለ ጦር👏
የአፋብን ሸዋ ጠቅለይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የአፄ አምደ ጽዮን ኮር አካል የሆነው የአፄ ምኒልክ ክፍለ ጦር በዛሬው ዕለት ነሃሴ 04 ቀን 2018ዓ.ም ባተካሔደው መድረክ ላይ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ሲያደርግ፣በመድረኩም በየደረጃው በሚገኙ አመራሮች ለሰራዊቱ የፖለቲካ የግንዛቤ ማስጨበጫ ፕሮግራም ማድረጉን የክፍለ ጦሩ ህዝብ ግንኙነት ክፍል አስታውቋል።
"ክብር ለትግሉ ሠማዕታት!
"ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
ነሃሴ 04/2018 ዓ.ም
የአፄ ምኒልክ ክፍለ ጦር ህዝብ ግንኙነት ክፍል
በምስራቅ ወለጋ እና በሆሩ ጉዱሩ ዞኖች የአንሻ ሰይድ ዕዝ አናብስቶች በጥላት ጥምር ጦር ላይ ድል ተቀዳጁ።
ነሐሴ4ቀን2018ዓም
በምስራቅ ወለጋ ዞን ጊዳ አያና ወረዳ አንገር ጉትን ከተማ መውጫ ላይ ጌጤ ግርማ መብረቅ ክ/ጦር፣አንገር ጉትን ክ/ጦር እና አበጀ ጥበቡ ነበልባል ክ/ጦር በደፈጣ ባንድ በመናበብ የክልሉ ገዳይ ኮማንዶ ላይ አንፀባራቂ ድል ተቀዳጁ።
ትናት አዝረክርኮት የወጣውን አስክሬን ለማሳት በርካታ የክልሉ ጥምር ጦር በመያዝ ዛሬ ረፋድ 4:00ላይ ከአንገር ጉትን ከተማ በመነሳት ከዚያው ከከተማዋ መውጫ በር ኢንጅሮ ላይ ተግተልትሎ ሲመጣ ካስክሬኑም ሳይደርስ የአንሻ ሰይድ አናብስቶች ዶግ አመድ አድርገውታል።በመጨረሻም ወደ መሀል ከተማዋ በመሸሽ በፍርኀት ቤት ዘግተው የጠቀመጡ ንፁኋን አማራዎችን ቤቶችን ገጥሎ በመግባት ህፃናትን፣እናቶችንና አዛውንትን ባደባባይ መስመር ላይ አያወጡ እየረሸኑ ይገኛሉ።
ለክልሉ ህዝብና ለሚመለከታቸው አካላት በሙሉ ንፁሃን ላይ እየተደረገ ያለ የዘር ጭፍጨፋ ባስቸኳይ የማይቆም ከሆነ ግጭቱ ወደ ህዝብ ለህዝብ መግባቱ አይቀሬ ነው።
በሌላኛው በሆሩ ጉዱሩ ዞን አቤደንጎሮ ወረዳ ሎምጫ ቀበሌ ላይ ታፈረ አለሙ ሳተናው ክፍለጦር እና "የሃሳብ ልዩነትን በንግግር ለመፍታት በሂደት ላይ ያለውን ፅናት ክ/ጦር በመናበብ ሎምጫ ቀበሌ የክልሉ ጥምር ጦር ላይ እርምጃ በመውሰድ ከተማዋን መቆጣጠር ተችሏል።የጥላት ጥምር ጦርም የተረፈው ወደ ደንጎሮ ከተማ ፈርጧል።
በአንገር ጉትን ከተማ ሶስቱ ክፍለጦሮች በምርኮ ያገኟቸው ቁሳቁሶች፦
👉ከስልሳ(60)በላይ ይህ ገዳይ
ሃይል የተደመሰሰ
👉አንድ(1)ብሬን
👉አርባሁለት(42) የነፍስ ወከፍ
ክለሽ
👉በርካታ የብሬ እና የክላሺ ተተኳሾች F1በንቦች ከተለያዩ ትጥቆችና ወታደራዊ ሻንጣዎች ገቢ ሲሆኑ ፦
በተጨማሪም በሆሩ ጉዱሩ አቤደንጎሮ ወረዳ ሎምጫ ቀበሌ ላይ በሁለቱ ክፍለጦሮች በምርኮ የተግኙ፦
👉ከ30 በላይ የጥላት ሃይል
ሲደመሰስ
👉14 ክላሾችን መማረክ
ተችሏል።
ግፍ የወለደን:ግፈኞችን የምቀጣ የአንሻ ሰይድ ወድሞች ነን‼️
አፋብን ወለጋ/ቢዛሞ አንሻ ሰይድ ዕዝ ህ/ግንኙነት መምሪያ
ነሐሴ 04/2018 ዓ.ም
አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ 76ኛ ክፍለ ጦር «ያልገባንን እንጠይቃለን፤ አንድነታችንን እናጸናለን» በሚል መሪ ቃል ውይይት አደረገ!
አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ 305ኛ ኮር 76ኛ ክፍለ ጦር፣ ለልዩ ተልዕኮ ለተውጣጡ የ4ቱ ሬጅመንት አባላት በኮር እና በክፍለ ጦር አመራሮች አማካኝነት የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት አድርጓል።
በመድረኩ የክፍለ ጦሩ ዋና አዛዥ አርበኛ ተስፋዬ ማስረሻ፣ የክፍለ ጦሩ ዘመቻ ኃላፊ አርበኛ አጃው አንጋው፣ የክፍለ ጦሩ ወታደራዊ ዕቅድና ስትራቴጂ መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ሙሉቀን ጌትነት እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ሰፊ ውይይት ተካሂዷል።
ለአማራ ሕዝብ ነፃነት ሲሉ በዱር በገደሉ መስዋዕትነት ለከፈሉ ታጋዮች የሕሊና ጸሎት በማድረግ የተጀመረው ይህ መድረክ፤ በጎንደር አንድነት፣ በአሁናዊ ሀገራዊ ሁኔታ እና በተሰጣቸው ልዩ ተልዕኮ ዙሪያ በአመራሮቹ አማካኝነት ለአባላቱ ሰፊ ግንዛቤ ተፈጥሯል።
የሁለቱ ዕዞች ውህደት ትልቅ ደስታ መሆኑን የገለጹት አባላቱ፤ «ያልገባንን እንጠይቃለን፤ አንድነታችንን እናጸናለን» በማለት የገለጹት አባላቱ ከዛ ውጭ ያለ መርህና አሰራር ውጪ በሚንቀሳቀስ ማንኛውም ፀረ-አንድነት ግለሰብም ሆነ አካል ላይ ተቋማዊ እርምጃ እንደሚወስዱ ጭምር ተናግረዋል ሲል መረጃውን ያደረሰን የኮሩ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ነው።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
