ru
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

Открыть в Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

Больше
2 931
Подписчики
-124 часа
+1487 дней
+38530 дней
Архив постов
🚨 ሰበር መረጃ 🚨 በትናንትናው እለት የተጀመረውና ዛሬም የቀጠለው ፍልሚያ፤ በሞጣ ቻይና ካምፕ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የቡድንና የነፍስ ወከፍ መሣሪያ ተማረከ!**         ሰኔ 23 ቀን 2018 ዓም         አሻራ ሚዲያ አዲስ አበባ ዛሬ ሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ.ም በምስራቅ ጎጃም ዞን ሞጣ ቻይና ካምፕ አካባቢ በፋኖ ኃይሎች እና በአገዛዙ የጦር ሰራዊት መካከል ከባድ ውጊያ መደረጉ ተሰምቷል። በዚህ በዛሬው እለት በተካሄደው ስልታዊና የተቀናጀ ጥቃት፣ የፋኖ ኃይሎች የአገዛዙን ጦር በበላይነት በመምታት ከፍተኛ ድል ማጠናቀቃቸውን ከአካባቢው የደረሱን መረጃዎች ያመላክታሉ። በዚሁ ኦፕሬሽን በአካባቢው መሽጎ ከነበረው የአገዛዙ ወታደራዊ ካምፕ ውስጥ በርካታ የጦር መሣሪያዎችን በቁጥጥር ሥር ማዋል ተችሏል። እስካሁን በደረሰን ይፋዊ መረጃ መሠረት፣ ከካምፑ የተማረኩትና ወደ ፋኖ የትጥቅ ግምጃ ቤት የገቡት መሣሪያዎች የሚከተሉት ናቸው፦ -ዲሽቃ፦(ከባድ የቡድን መሣሪያ) -ብሬን፦(መካከለኛ የቡድን መሣሪያ) -የስናይፐር ጠመንጃዎች፦** (ለሩቅ ርቀት ኢላማ የሚያገለግሉ) -በርካታ ቁጥር ያላቸው የክላሽንኮቭ (AK-47)ጠመንጃዎች * **በርካታ የቡድንና የነፍስ ወከፍ መሣሪያ ጥይቶችና ወታደራዊ ትጥቆች መማረካቸው ታውቋል ይህ የዛሬው የሞጣ ቻይና ካምፕ ድል በአካባቢው ባለው ወታደራዊ ሚዛን ላይ ከፍተኛ ለውጥ እንዳመጣ እየተነገረ ይገኛል። የፋኖ ኃይሎች አካባቢውን ይበልጥ እያረጋጉና ቁጥጥራቸውን እያጠናከሩ መሆናቸው ታውቋል። የውጊያውን ሙሉ ዝርዝር ሂደት፣ በአገዛዙ ጦር ላይ የደረሰውን ሰብአዊና ቁሳዊ ኪሳራ እንዲሁም የተማረኩትን መሣሪያዎች ትክክለኛ ቁጥር የሚገልጽ ተከታታይ መረጃ ይዘን የምንመለስ ይሆናል። ታማኝና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት አብራችሁን ቆዩ!

⚖#የችሎት_ዉሎ_መረጃ‼️ አማራ ማንነታቸው እንደ ወንጀል ተቆጥሮ በሽብር ወንጀል የተከሰሱ የፖለቲካ እና የሕሊና እስረኞች ፍ/ቤት ቀርበዋል። በእነ ያሬድ/ሰለሞን/ ዋሌ አስረስ መዝገብ ዉስጥ    1. ያሬድ/ሰለሞን/ ዋሌ አስርስ    2. ይፍቱስራ አዳሙ   3. ጋዜጠኛ እና መ/ር ደስታው አለባቸው መንግስት  ሰኔ 19/2018 ዓ.ም ፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት 1ኛ ሰሚ ችሎት የዋስታና ይግባኝ ጠይቀው ችሎት ቀርበዉ ነበር። አንደኛ ተከሳሽ ክሱ ዋስትና የሚያስከለክል በመሆኑ ክርክር አላደረገም። ሁለተኛ ተከሳሽ እና ሶስተኛ ተከሳሽ የተከሰሱበት የፀረ-ሽብር አንቀጽ ህገመንግስታዊ የዋስትና መብትን የማያስከለክል በመሆኑ በእስር ፍርድቤቱ  በፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የሕገ መንግስት እና የፀረ ሽብር ወንጀል ችሎት ቀርበው የዋስትና ክርክር ከአንድ ወር በፊት ማለትም ሚያዚያ 30/2018 ዓ.ም በግፍ ከ3 ወር በላይ ታፍነዉ ከቆዩበት ሜክሲኮ ወንጀል ምርመራ ቢሮ ቀርበዉ ክርክር አድርገው ነበር። ዐቃቤ ሕግ ተከሳሾች ላቀረቡት የዋስትና ክርክር እንደተለመደው፦ 1) ተከሳሾች በዋስትና ቢለቀቁ ቀጠሯቸውን አክብረው አይገኙም እንዲሁም 2) ተከሳሾች በዋስትና ቢለቀቁ ጫካ ሂደው ፋኖን ይቀላቀላሉ ሲል የተቃውሞ አስተያየት ማቅረቡ ታውቋል። ግንቦት 4/2018 ዓ.ም ስር ፍ/ቤቱ በከሳሽ ዐቃቤ ሕግ እና በተከሳሾች መካከል ከዋስትና መብት አንጻር የተደረገውን ክርክር መርምሮ የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ ችሎት የሚከተለውን ብይን ሰጥቶ ነበር። ተከሳሾች በዋስ ለመውጣት ያቀረቡት የጤና ችግር በተመለከተም እንዲሁም የቤተሰብ አስተዳዳሪ ሁኔታ ሲታይ ይህ ችግር እያለባቸው በክስ የተጠቀሰውን ድርጊት ስለፈፀሙ አሁን እንደ ምክንያት ሊቀርብ አይገባም ፤በዋስትና ፍርድቤቱ ቢለቃቸው በድጋሚ እንዲሁ የመንግስትን ስም በማህበራዊ ሚዲያ ያጠፋሉ፤ እንዲህ አይነት ወንጀል ይሰራሉ በማለት ፍርድ ቤቱ የዐቃቤ ህግ ሀሳብን ሙሉ በሙሉ በመቀበል ህገመንግስታዊ የሆነውን የዋስትና መብት በመከልከል በማረሚያ ቤት ሁናችሁ ተከላከሉ በማለት መወሰኑ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።   ይህንን ዉሳኔ ተከትሎ በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ዉስጥ በግፍ እየማቀቁ የሚገኙት እነኚህ ተከሳሾች ሰኔ 7/2018 ዓ.ም የዋስትና መብት በፁሁፍ እና በቃል ክርክር ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት 1ኛ ሰሚ ችሎት የዋስታና ይግባኝ ጠይቀው ችሎት ቀርበዉ ነበር። ችሎቱም በከሳሽ ዐቃቤ ሕግ እና በተከሳሾች መካከል ከዋስትና መብት አንጻር የተደረገውን የፁሁፍ እና ቃል ክርክር መርምሮ ብይን ለመስጠት ከተደጋጋሚ ቀጠሮ በኋላ ለዛሬ ሰኔ 22/2018 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቶ ነበር። የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድቤቱ 1ኛ ሰሚ ችሎት የእስር ፍርድ ቤቱን ዉሳኔ በማፅናት የዋስትና መብትን በመከልከል ህገመንግስታዊ መብታቸውን በመንፈግ በማረሚያ ቤት ሁነው እንዲከታተሉ ወስኖባቸዋል ሲል የደረሰን መረጃ ያመለክታል። ምስሉ ከማህበራዊ ሚዲያ የተገኘ የደስታው አለባቸው መንግስት ሲሆን የሌሎች ምስል እንዳገኘን የምንለጥፈው ይሆናል! #ፍትህ_አማራነት_ወንጀል_ሆኖ_በእስር ለሚሰቃዩ አማራዎች‼️

የጄነራል መሀመድ ተሰማ በብር አዳማ ላይ መታየት እና በሜዳው እውነታ መካከል ያለው ስምጥ!   በታሪክ ማህደር ውስጥ በውሸትና በፕሮፓጋንዳ የቆመ ስርአት በሰይፍ ተመቶ መውደቁ የማይቀር ሀቅ ነው። ዛሬ በኢትዮጵያ ምድር የምናየው የብልፅግና ጄነራሎች እልፍ ውሸት፣ ከታላቁ የውሸት መምህራቸው ኮሎኔል አብይ አህመድ በውርስ ቅብብሎሽ የወሰዱት የባዶ ጩኸት ድስኩር ስልት ነው። ነገር ግን ይህ ድስኩራቸውና በሜካፕ የተለሰነ ጀግንነታቸው፣ በፋኖ ጥይት ሰውነታቸው እንደ በረዶ ከመቅለጥ ውጭ ሊሆን አልቻለም። የብልፅግናው ኮሎኔል አብይ አህመድ በታሪክ አጋጣሚ ስልጣን ከያዘ ጊዜ ጀምሮ እውነታን በልቦለድ የመተካት ስልትን ሲከተል ቆይቷል። ይህ የውሸት ማሳለጫ ባህል ዛሬ ወደ ከፍተኛ የጦር መሪዎች ዘልቋል። ዛሬ በብር አዳማ ተገኘሁ ያለው ጄነራል መሀመድ ተሰማ፣ የዚሁ የስርዓት የባዶ ጩኸት ድስኩር ማሳያ ነው። የጄነራል መሀመድ ተሰማ በብር አዳማ ላይ መታየት፣ በተግባር በጦር ሜዳ እየደረሰ ያለውን ውርደት ለመሸፈን የሚደረግ ሳይኮሎጂካዊ መከላከያ ነው። ሆኖም ታሪክ የሚመዘግበው በብር አዳማ የሚደረጉ ንግግሮችን ሳይሆን፣ በወለጋ(ቢዛሞ) እና በደጋ ዳሞት የፈሰሰውንና የስርዓቱን መቃብር የቆፈረውን የሽንፈት ደም ነው። በአፋብን (ወለጋ)ቢዛሞ አንሻ ሰይድ ዕዝ የደረሰበት ውርደትና በአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ ደጋ ዳሞት ግንባር ህያው ምስክር ነው። የብልፅግና ሰራዊት ድልን በቴሌቪዥን መስኮት ቢሰብክም፣ እውነታው ግን በወለጋ (ቢዛሞ) ጊዳ አያና ዲቾ እና በደጋ ዳሞት ተራሮች ላይ ተቀብሯል። የጦር አዝማች ነን ባዮቹ ጄነራልና ኮሎኔሎች የፋኖን ክንድ መቋቋም አቅቷቸው ወደ አፈርነት ተቀይረዋል። በወለጋ ቢዛሞ ምድር የተንከባለለው የጄኔራል አስናቀ እብሪት፣ በደጋ ዳሞት የረገፈው የኮሎኔል አበራ ትዕቢት፣ ለተቀረው የብልፅግና ስርአት ትልቅ ማስጠንቀቂያ ነው። ዛሬ ጄነራል መሀመድ ተሰማም የቀደሙት ጓዶቹ ናፍቀውት እየተንቀዤቀዤ ይገኛል። አንድ አማራ የሚባል ትልቅ ህዝብን በዘሩ ምክንያት ለይቶ እጨፈጨፈ ያለው ሰራዊት፣ የጥይት ድምፅ ሲሰማ የለበሰው ማዕረግ ሸክም ይሆንበታል። የፋኖ ጀግንነት በአባቶቻችን የአርበኝነት ደም ውስጥ የሰረፀ የታሪክ ውርስ ነው። ይህ ጀግንነት በአድዋ ጦርነት ጣሊያንን ድል ካደረጉት አባቶቻችን የተወረሰ የነፃነት መንፈስ ነው። እንደ ሶማው ነብር ደጃዝማች በላይ ዘለቀ፣ ለሀገሬና ለክብሬ አልሸነፍም ብሎ በጠላቱ ላይ መብረቅ ሆኖ የመውረድ ጥበብ ነው። የበላይ ዘለቀ የጀግንነት ደም ዛሬም በፋኖ ደም ውስጥ ይፈሳል። ፋኖ ማለት ተራ ተዋጊ አይደለም፤ ፋኖ ማለት የታሪክ አደራ ተሸካሚ፣ የፍትህ ናፋቂና የክብር ዘበኛ ነው። ብልፅግና በገንዘብና በስልጣን ጥመኞች የገነባው ሰራዊት፣ ይህንን የመቶ አመታት ታሪክ ያለውን ጽኑ መንፈስ ሊያሸንፈው አይችልም። ጄነራሎቹ ድስኩርን እንደ መከላከያ ይጠቀሙበታል፤ ሆኖም ግን ድስኩር ጥይት አይመልስም፣ ውሸትም ታሪክን አይቀይርም። ፋኖ ግን በእውነት የታጠቀ፣ በህዝብ ትከሻ የተደገፈ በመሆኑ ዘር አጥፊዎችን ወደ መቃብር እየላከ ይገኛል። ©Birhanu Chalie Demelash

ተጠናክሮ በቀጠለው ስቦ ማስከዳት ስምንት የመከላከያ ሰራዊት አባላት ከነሙሉ ትጥቃቸው ፋኖን ተቀላቀሉ! በአፋብን ምኒልክ ዕዝ 303ኛ አሳምነው ኮርን ስምንት የአገዛዙ ብልፅግና ሰራዊት አባላት ሙሉ ትጥቃቸውን ይዘው ተቀላቅለዋል። መነሻቸውን በሰሜን ወሎ አስተዳደር ዞን ላስታ ወረዳ ብልባላ ከተማ 204ኛ ኮር በኮሎኔል አባቡ የምትመራው 38ኛ ክፍለ ጦር ቃኝዎች ስድስት አባላቱ ምቹ ቦታና ጊዜን ይጠብቁ የነበሩት የአማራን ህዝብ ግፍ ቆሞ ማየትና ተባባሪ መሆን የሰለቻቸው ለስለላ በተላኩበት እርስ በርስ በመተማመንና ቆራጥ ውሳኔ በመወሰን ሰኔ 22 ቀን 2018 ዓ/ም ፋኖን ተቀላቅለዋል። በሌላ አቅጣጫ ከ38ኛ ክፍለ ጦር ሁለተኛ ሬጅመንት አንድ መቶ መሪና አንድ ብሬን ተኳሽ ከነ ሙሉ ትጥቃቸው 19ኛ ክፍለ ጦር ወደ ፋኖዎች ቤት ጎራ ያሉ ሲሆን ለመጡት ጥቁር እንግዶችም በአማራነት ባህልና እሴትም በእንክብካቤ ተይዘዋል። አባላቱም አንድ ጥቁር ስናይፐር፣ ሰባት ጥቁር ክላሽ፣ አራት የደረትና የወገብ ትጥቅ፣ 549 የክላሽ ተተኳሽ፣ ስድስት የእጅ ቦምብ በኮሩ ስር ለሚገኙ 19ኛና 30ኛ ክፍለ ጦር ፋኖዎች አበርክተዋል። ምንጭ፦ በአፋብን ምኒልክ ዕዝ ሚዲያ እና ኮሚዩኒኬሽን  መምሪያ!

📌 የዋርካው ጽናት፣ የማይበገሬው ሕዝባዊ መቅረዝ በወታደራዊ ሳይንስ እና በሕዝባዊ አብዮቶች ታሪክ ውስጥ፣ የአንድን ንቅናቄ ዘላቂነት እና ስልታዊ ብስለት የሚወሰነው መሬት ላይ ባለው የጦር መሣሪያ ብዛት ሳይሆን፣ ሰራዊቱን በጥበብ መርቶ አመርቂ ድል የሚያበስር እና በብዙኃኑ ዘንድ ፍጹም ተወዳጅነትና ክብርን ያተረፈ መሪ (Strategic Leadership) ሲኖር ነው። ለአንድ ሕዝብ ነፃነት ደምና አጥንት እየተከሰከሰ፣ በዘመናት የማይተኩ ጀግኖች የሚገበሩበት የሕልውና ትግል፣ በመጨረሻም የጠላትን ስሌት የሚያፈርስ ጽኑ ተቋማዊ መሠረት ይፈጥራል። ዛሬ በአማራ ምድር፣ በተለይም በታሪካዊው የወሎ-ቤተ አማራ ቀጠና፣ ለአምስት ዓመታት በደሙና በአጥንቱ ታሪክ የጻፈውና የሕዝቡ ደማቅ ኩራት የሆነው የአማራ ፋኖ እያስመዘገበ ያለው ወታደራዊ ልዕልና፣ ከዚህ ጥልቅ መሪነትና ሕዝባዊ ደጀንነት የመነጨ ነው። የዚህ ገናና ሕዝባዊ ኃይል ቁልፍ ወታደራዊ አሰባሳቢ ዋርካ፣ አርበኛ ምህረቱ “ምሬ” ወዳጆ—በደጋፊዎቹና በትግል አጋሮቹ ዘንድ “ዋርካው” በሚል የቁልምጫ ስም የሚጠራው ታዋቂ የፋኖ መሪ—የትግል ታሪክና አመጣጥ የዚህን አብዮት Organic Nature ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ ነው። ይህ ዋርካው ዋና ዓላማው ትግል ሲጀምር ለአማራ ሕዝብ ሕልውና ጋሻ ለመሆን ነበር። ዋርካው ትግል ከጀመረበት ጊዜ አንስቶበወሎ ቤተ-አማራ፣ በጎንደር፣ ጎጃምና ሸዋ የፋኖ አደረጃጀቶች ላይም ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከተ ሲሆን፣ በሰሜኑ ጦርነት ወቅትም የምስራቅ አማራ ፋኖን በመምራት በግንባር ቀደምትነት የተሰለፈ የጦር ጠበብት ነው። የአሁኑን የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) እንደ መዋቅራዊ ምሶሶ በመትከል፣ እርሱ እያደረገ ያለው እያንዳንዱ ወታደራዊና ስልታዊ እንቅስቃሴ በብዙኃኑ ሕዝብ ዘንድ እጅግ የሚወደድ፣ የሚከበርና እንደ ትልቅ ተስፋ የሚታይ ሆኗል። የአራት ኪሎው አገዛዝ የክልል ልዩ ኃይሎችን ትጥቅ ለማስፈታትና ሕዝቡን መከላከያ-አልባ ለማድረግ የወሰደውን ዕውር ውሳኔ ተከትሎ፣ ምሬ ወዳጆ እና ኃይሎቹ ወደ በረሃ በመግባት የጀመሩት የትጥቅ ትግል፣ ዛሬ ላይ የአገዛዙን መጠነ-ሰፊ መዋቅር ያሽመደመደበት ታላቅ ማዕበል ሆኗል። ጫማ ሳይኖረው በባዶ እግሩ በመጓዝ፣ የረባ ስንቅ ሳይዝ ደረቅ ቆሎ እየቆረጠመ እና በሽርጡ ብቻ ተሸፋፍኖ የታገለው ይህ ሰራዊት፣ ዛሬ ላይ የአገዛዙን በርካታ ዕዞችና የሪፐብሊካን ጋርድ ልዩ ኮማንዶን በክንዱ ተቋቁሞ ድባቅ የመታበት ምስጢር ይህ የማይበገሬ መዋቅራዊ ጽናትና በሕዝብ ዘንድ ያለው ፍጹም መከበር ነው። ጦርነት አንዴ ከተጀመረ በኋላ በተራ ፕሮፓጋንዳ የማይለሰልስ መራር ጭካኔን የሚተካ ቢሆንም፣ የፋኖ ሰራዊት ግን የሞራል ልዕልናው ምን ያህል ከፍ ያለ መሆኑን በተግባር እያሳየ ይገኛል። አርበኛ ምሬ ወዳጆ በተደጋጋሚ እንደሚያሰምርበት፣ ይህ ትግል የዐማራን ሕዝብ መብትና ጥቅም ለማስጠበቅ፣ ሕልውናውን ለማረጋገጥ የተለኮሰ የአብዮት እሳት ነው። ይህ ግዙፍ ዋርካ ዛፍ ለራሱ የሚተርፍ አንዳችም ነገር ሳያስቀር፤ ጥላውን፣ ፍሬውንና መላ አካሉን ለሰፊው ሕዝብ መጠለያና ህልውና የሰጠ የጀግንነት እና የፍቅር ተምሳሌት ነው። ለዚህ ሁሉን ነገር ለሕዝብ ለሰጠ፣ ስለ ወገኑ ሲል ራሱን ላሳጣ ታላቅ ዋርካ ምንጊዜም የሚላቅ ምስጋና ይገባዋል። የጣለው የራስን ጥቅም የመካድና የመስዋዕትነት መሰረት፣ ለሕዝብ የመኖርን ጥልቅ ሚስጥር ያስተማረን ህያው ተምሳሌታችን ነው። ለከፈለው ወደር የሌለው መስዋዕትነትና ለታላቅ ልግስናው ምስጋናችን የላቀ ነው! ትግላችን ያሸንፋል! ሙሉጌታ አንበርብር

በአንፆኪያ ገምዛ ክላስተር የፋኖ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት የተማሪዎች የዓመቱ የትምህርት ማጠናቀቂያ በደማቅ ሁኔታ ተካሄደ ​       ሰኔ 22 /2018 ዓ.ም ​በሸዋ ጠቅላይ ግዛት በአንፆኪያ ገምዛ ክላስተር ዋሻ ንገት ቀበሌ የሚገኘው የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በትናንትናው ዕለት የዓመቱ የትምህርት ማጠናቀቂያ እና የደረጃ ሽልማት መርሃግብር በደማቅ ሁኔታ ተካሂዷል። ​በዚህ ደማቅ የወላጆች ቀን በዓል ላይ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ወታደራዊ ቃል አቀባይ አርበኛ አበበ ሙላቱ፣ የሸዋ ጠቅላይ ግዛት ከፍተኛ አመራሮች፣ የኮርና የክፍለጦር አመራሮች፣ የሃይማኖት አባቶች እንዲሁም የሀገር ሽማግሌዎች በክብር እንግድነት ተገኝተዋል። በዕለቱ በተከናወነው የበጎ አድራጎትና የማበረታቻ መርሃ-ግብር ላይ በዓመቱ ከፍተኛና የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች በአርበኛ አበበ ሙላቱ እና ጥሪ በተደረገላቸው  እንግዶች አማካኝነት የደረጃ ሽልማትና ልዩ ልዩ ማበረታቻዎች ተበርክቶላቸዋል። ​በመርሀግብሩ ላይ የተገኙት የትምህርት ቤቱ መምህራን ለአርበኛውና ለአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ አባላት ባስተላለፉት መልዕክት፤ በአካባቢው እጅግ አስቸጋሪ እና ስጋት በነበረበት ወቅት ጭምር ፋኖ እውነተኛ ህዝባዊ ደጀንነቱን በተግባር ማሳየቱን ገልፀው፤ የፋኖ ሰራዊት አባላት በከፈሉት ዘርፈ ብዙ መስዋዕትነት እና ባደረጉት ቀጣይነት ያለው ጥበቃ ምክንያት የአካባቢው ሰላም ተጠብቆ፣ የመማር ማስተማር ሂደቱ ሳይቋረጥ ለዚህ የደስታ ቀን መብቃት መቻሉን መምህራኑ በታላቅ አክብሮት አመስግነዋል። የመድረኩን ማጠቃለያ ምክር አዘል መልዕክት ያስተላለፉት የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ንቅናቄ ወታደራዊ ቃል አቀባይ አርበኛ አበበ ሙላቱ፤ የአንፆኪያ ገምዛ ክላስተር ተማሪዎች ነገ ሀገርንና ወገንን የሚረከቡ የነገ ተስፋዎች በመሆናቸው በትምህርታቸው ይበልጥ ሊበረቱና ሊተጉ እንደሚገባ አሳስበዋል። ​ቃል አቀባዩ የድርጅቱን ፅኑ አቋምና ቁርጠኝነት ሲያረጋግጡም፦"በእኛ በኩል ትምህርት አይቋረጥም፤ ወደፊትም የተማሪዎቻችን የትምህርት ጉዞ ሳይስተጓጎል በሰላም እንዲቀጥል በድርጅታችን በአማራ ፋኖ ብሄራዊ ንቅናቄ ስም  በታላቅ እምነትና ቁርጠኝነት ገልፀዋል። ክብር ለትግሉ ሰማዕታት ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ

Baye Desta Per የ206ኛ ኮር አዳኝ ቡድን በደብረ ማርቆስ ከተማ ከሌሊቱ 6:35 በፈፀመው የቦምብ ጥቃት 4 የፌዴራል ፖሊሶች ህይወታቸውን አጠዋል። ሰኔ 22/2018 ዓ.ም ============
Baye Desta Per የ206ኛ ኮር አዳኝ ቡድን በደብረ ማርቆስ ከተማ ከሌሊቱ 6:35 በፈፀመው የቦምብ ጥቃት 4 የፌዴራል ፖሊሶች ህይወታቸውን አጠዋል። ሰኔ 22/2018 ዓ.ም ========================= የጀብደኛው 206ኛ ኮር አዳኝ ቡድን ከሌሊቱ 6:35 በደብረ ማርቆስ ከተማ የፌዴራል ፖሊስ አጃቢዎችን ጭና ስትንቀሳቀስ በነበረች ፓትሮል ላይ ኢላማውን የጠበቀ የቦምብ ጥቃት በማድረግ በ9 የአመራር ጠባቂዎች ላይ ጉዳት መድረሱ ታውቋል። ከመስከረም ሆቴል በቅርብ እርቀት በተፈፀመው የቦምብ ጥቃት 4 የፌዴራል ፖሊሶች ሲደመሰሱ 3 ከባድ ቁስለኛ 2 ቀላል ቁስለኛ መሆናቸው ተረጋግጧል። አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳሰብ ! አዲስ ተስፋ ! አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት

አየር መቃዎሚያው ተመታ!/ተኳሾቹ ተገደሉ! በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ወሎ ቤተ ዐምሐራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር 71ኛ ክ/ጦር ስር የሚገኙት የ1ኛ ሙሐመድ ዳውድ ሬጅመንት አርበኞች ትናንት ሰኔ 21/2018 ዓ.ም በከላላ ግንባር በታላቅ የጦር ብቃት የጠላትን ኃይል በማፍረክረክ አንፀባራቂ ድል አስመዝግበዋል። በአየር መቃዎሚያና በሌሎች የሜካናይዝድ መሣሪያዎች ታጅቦ መነሻውን ከጊምባ ያደረገው የጠላት ኃይል፡ ንፁኋንን ለመጨፍጨፍ፣ ሃብት-ንብረት ለማውደምና ወረራ ለመፈፀም ወደ ሻፊ እና ባከት አከባቢዎች ለመንቀሳቀስ ሙከራ አድርጎ የነበረ ቢሆንም፡ በአርበኞቹ ልዩ የውጊያ ጥበብ ሁለትና ሦስት ቦታዎች ላይ ተቆርጦ አይቀጡ ቅጣት ተቀጥቷል። ትናንት አመሻሽ ድረስ በወሎ ቤተአማራ ቀጠና ከላላ ግንባር ሻፊና በባከት አከባቢዎች ላይ በተደረገው ተጋድሎ፡ የፋኖ አስደማሚ የፀረ ማጥቃትና የመልሶ ማጥቃት ጥበብ ሲታየ፡ በአንፃሩ የጠላት ብልፅግና ኃይሎች ከወደ ፋኖ የተወሰደባቸውን እርምጃ የሚመክቱበት ፋታ አጥተው ተሽመድምደው የዋሉበት አውደ ውጊያ ተካሂዷል። አርበኞቹ ጠላትን በሁለት አቅጣጫ ማለትም በሻፊ እና በባከት በኩል ቆርጠው ቀጠናውን በመቆለፍ ከባድ እርምጃ ወስደውበታል። በአከባቢው በተለይ ጎራዳ ተብሎ በሚጠራው ቦታ፡ ጠላት በአየር መቃዎሚያ መሣሪያ ታግዞ ከወደ ፋኖ የተከፈተበትን የፀረ ማጥቃት እርምጃን ለመቋቋም ሙከራ ቢያደርግም፡ ነገር ግን ከጥቃቱ መክበድና ከአጥቂዎቹ ፍጥነት ጋር ተዳምሮ ጠላት ሙትና ቁስለኛውን አዝረክርኮ ለመሸሽ ተገድዷል። በዚህ ተጋድሎ ሙትና ቁስለኛ ከተደረጉ የጠላት እግረኛ ወታደሮች በተጨማሪ የአየር መቃዎሚያው አፈሙዝ በፋኖ ዲሽቃ ተመቶ በእሳት ሲጋይ፡ የአየር መቃዎሚያ ተኳሹና ረዳቶቹ ፋኖ ባካሄደው የዲሽቃና የብሬን ስብጥር ተኩስ ተገድለዋል። የ71ኛ አባናደው ክፍለጦር አርበኞች ከወሰዱት ከባድ የሆነ የፀረ ማጥቃትና የመልሶ ማጥቃት ስልትን ከአንዳች አማራዊ ጀግንነትና ወኔ ጋር ያዋሃደ እርምጃ አንፃር የጠላት ከባባድ መሣሪያዎችና የሰው ኃይሉ ትርጉም ባጣበት በዚህ ተጋድሎ፡ 23 የአገዛዙ ወታደሮች ተደምስሰዋል፡ በርካታ ልዩ ልዩ  የጦር መሣሪያዎችና ሌሎች ወታደራዊ ቁሣቁሶች በፋኖ ቁጥጥር ስር ውለዋል። አርበኞቹ ከሚያደርጉት የመደበኛ ውጊያ በተጨማሪ፡ የጠላት ኃይልን ስቦ ከመምታት ጀምሮ፡ በከባባድ የጦር መሣሪያዎች ሽፋን ታግዞ በሚንቀሳቀሰው የጠላት ኃይል ላይ የፀረ ማጥቃት እርምጃ በመውሰድ እንዲሁም የቆረጣና የደፈጣ ጥቃት በመፈፀም የብልፅግናውን አገዛዝ አሽመድምደው በድል ጎዳና እየገሰገሱ ይገኛሉ። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!! በአፋብን ወሎ ቤተ- አማራ ምኒልክ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! ሰኔ 22/ 2018 ዓ/ም

በአንፆኪያ ገምዛ ክላስተር የፋኖ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት የተማሪዎች የዓመቱ የትምህርት ማጠናቀቂያ በደማቅ ሁኔታ ተካሄደ ​ ሰኔ 22 /2018 ዓ.ም ​በሸዋ ጠቅላይ ግዛት በአንፆኪያ ገምዛ ክላስተር ዋሻ ንገት ቀበሌ የሚገኘው የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በትናንትናው ዕለት የዓመቱ የትምህርት ማጠናቀቂያ እና የደረጃ ሽልማት መርሃግብር በደማቅ ሁኔታ ተካሂዷል። ​በዚህ ደማቅ የወላጆች ቀን በዓል ላይ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ወታደራዊ ቃል አቀባይ አርበኛ አበበ ሙላቱ፣ የሸዋ ጠቅላይ ግዛት ከፍተኛ አመራሮች፣ የኮርና የክፍለጦር አመራሮች፣ የሃይማኖት አባቶች እንዲሁም የሀገር ሽማግሌዎች በክብር እንግድነት ተገኝተዋል። በዕለቱ በተከናወነው የበጎ አድራጎትና የማበረታቻ መርሃ-ግብር ላይ በዓመቱ ከፍተኛና የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች በአርበኛ አበበ ሙላቱ እና ጥሪ በተደረገላቸው እንግዶች አማካኝነት የደረጃ ሽልማትና ልዩ ልዩ ማበረታቻዎች ተበርክቶላቸዋል። ​በመርሀግብሩ ላይ የተገኙት የትምህርት ቤቱ መምህራን ለአርበኛውና ለአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ አባላት ባስተላለፉት መልዕክት፤ በአካባቢው እጅግ አስቸጋሪ እና ስጋት በነበረበት ወቅት ጭምር ፋኖ እውነተኛ ህዝባዊ ደጀንነቱን በተግባር ማሳየቱን ገልፀው፤ የፋኖ ሰራዊት አባላት በከፈሉት ዘርፈ ብዙ መስዋዕትነት እና ባደረጉት ቀጣይነት ያለው ጥበቃ ምክንያት የአካባቢው ሰላም ተጠብቆ፣ የመማር ማስተማር ሂደቱ ሳይቋረጥ ለዚህ የደስታ ቀን መብቃት መቻሉን መምህራኑ በታላቅ አክብሮት አመስግነዋል። የመድረኩን ማጠቃለያ ምክር አዘል መልዕክት ያስተላለፉት የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ንቅናቄ ወታደራዊ ቃል አቀባይ አርበኛ አበበ ሙላቱ፤ የአንፆኪያ ገምዛ ክላስተር ተማሪዎች ነገ ሀገርንና ወገንን የሚረከቡ የነገ ተስፋዎች በመሆናቸው በትምህርታቸው ይበልጥ ሊበረቱና ሊተጉ እንደሚገባ አሳስበዋል። ​ቃል አቀባዩ የድርጅቱን ፅኑ አቋምና ቁርጠኝነት ሲያረጋግጡም፦"በእኛ በኩል ትምህርት አይቋረጥም፤ ወደፊትም የተማሪዎቻችን የትምህርት ጉዞ ሳይስተጓጎል በሰላም እንዲቀጥል በድርጅታችን በአማራ ፋኖ ብሄራዊ ንቅናቄ ስም በታላቅ እምነትና ቁርጠኝነት ገልፀዋል። ክብር ለትግሉ ሰማዕታት ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ

አገዛዙ በአርበኛ ኢንጂነር ዘበነ በላይነህ ቤተሰቦች ላይ እስራትና ከባድ ድብደባ መፈጸሙ ተገለጠ ​ሰኔ 22/2018 ዓ.ም በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ተጉለትና ቡልጋ አውራጃ፣ ከአንኮበር ወረዳ የአፋብን ዕቅድና ስትራቴጅ መምሪያ ኃላፊ የሆኑት የአርበኛ ኢንጂነር ዘበነ በላይነህ ቤተሰቦች በአገዛዙ ታስረው ማሰቃዬት እየተፈጸመባቸው መሆኑ ተረጋግጧል። ​የፋኖን ወታደራዊ ክንድ መቋቋም ያቃተው የብልፅግና አገዛዝ ከዚህ ቀደም የጀግናውን አርበኛ ቤተሰቦች ንብረት ያወደመ ሲሆን፣ ዛሬ ደግሞ ንፁሃን እናቱንና መላው ቤተሰቡን በማሰርና በማንገላታት ላይ ይገኛል። ይህ የእስራትና የማንገላታት እርምጃ የአገዛዙን ተሸናፊነት የሚያሳይ እንጂ ትግሉ ላይ የሚያመጣው ምንም ዓይነት የውጤት ለውጥ እንደሌለ ይታወቃል። ​ጀግናው አርበኛ ኢንጂነር ዘበነ በላይነህ በአገዛዙ እየተፈጸመ ባለው በዚህ እኩይ ተግባር ምክንያት ይበልጥ የሚጠነክር እንጂ የሚዝል ክንድ እንደሌለውና ትግሉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል። ​በዚህ ግፍና በደል ሰለባ የሆኑትና በአሁኑ ወቅት በቁጥጥር ስር ውለው የሚገኙት የቤተሰቡ አባላት ዝርዝር የሚከተለው ነው፦ ▸እናት፦ ወይዘሮ ይማልዱ ሸዋን ታምሬ ▸ ​ወንድም፦ ምንዳ በላይነህ ▸ ​ወንድም፦ ሽመልስ በላይነህ ▸ ​አጎት፦ አቶ ሙላቱ በቀለ ​በአገዛዙ አማካኝነት በንፁሃን ዜጎችና በቤተሰብ አባላት ላይ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት በተለያዩ አካባቢዎች የሚፈፀም ይህ ዓይነቱ ግፍና ማንገላታት፣ በሕዝብ ዘንድ ከፍተኛ ቁጣን ከመቀስቀሱም በላይ የትግል ወኔን ይበልጥ እያጠናከረው እንደሚገኝ ከአካባቢው የተገኘው መረጃ ያመላክታል።       ክብር ለትግሉ ሰማዕታት       ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ

አለቃ ከነ ልጁ 👥 ጀግና እና ደግ መሪ አለን:: እንደ እሱ ያለ መሪ ማግኘት መታደል ነው:: እድለኞች ነን:: ትዕግስቱ፣ አስተውሎቱ፣ ጥበቡ፣ ድፍረቱ፣ ደግነቱ እና ለሞት ያለው ንቀት እሱን ለየት
+1
አለቃ ከነ ልጁ 👥 ጀግና እና ደግ መሪ አለን:: እንደ እሱ ያለ መሪ ማግኘት መታደል ነው:: እድለኞች ነን:: ትዕግስቱ፣ አስተውሎቱ፣ ጥበቡ፣ ድፍረቱ፣ ደግነቱ እና ለሞት ያለው ንቀት እሱን ለየት ያደርገዋል:: ልጁ ንጉሥ ምሬም ልክ እንደ አባቱ ነው:: ለወራት የስፔሻል ኮማንዶ ስልጠና ወስዶ ተመርቋል:: በዚያ ጀግንነት ላይ ወታደራዊ እውቀትና ጥበብ ሲጨመርበት አስቡት:)

#በመጨረሻም አንዷን ቀለሃ ወደ ራሱ ተኩሶ የአፄ ቴዎድሮስን ክብር ተቀናጀ፦ "አርበኛ ቅዱሴ ዘውዱ ከአርበኛ ቀኝአዝማች ጨለፍ ተስፋው ጋር ለሁለት ወራቶች ብቻ በእድሜ ተበላልጠወ ተጠራርተው ወደቁ። ከሁለት ወር በኋላ የቀኝአዝማች ጨለፍ ተስፋውን ናፍቆት አልቻለው አለና ቅዱሴም ወደ ጨለፍ ገሰገሰ! "አርበኛ ቅዱሴ ከኔ በላይ ጀግና ነው። የቅዱሴ ጀግንነት ወደር አልባ ነው።" ብሎ ቀኝአዝማች ጨለፍ የመሰከረለት ሰልካካ ውብና ወንዳ ወንዱ አርበኛ ቅዱሴ ዘውዱ መቄት ምድር ካፈራቻቸው ጉምቱ ጀግና መካከል አንዱና ኮከቡ እርሱ ነው። "ሰኔ 20/2018 ዓ/ም በመቄት ወረዳ ቁርአምበሳ ከተባለ ቦታ ላይ ጠላት በመድፍና ፔምፒ ታግዞ ሙሉ መካናይዝድ ሆኖ 22ኛ ክፍለጦርን ለመክበብ በተቀሳቀሰበት ቅስፈት አርበኛ ቅዱሴ ዘውዱ የጠላትን ሰራዊትን እያራገበ ከበባ ውስጥ የገባን ሰራዊቱን ከጠላት ቀጠና ሙሉ በሙሉ ማውጣት ቻለ።ቅዱሴ በቀኝና ግራ ደረት ትጥቁ አራት ካዝና አምስተኛ ከነፍጡ የተገጠመ ካዝናውን በጥላት ሰራዊት ቅንድብና ግንባር ላይ ከተኮሰ በኋላ በመጨረሻም ሰላሳ አንደኛዋን ቀለሃ ወደ ራሱ ተኮሳት። "አርበኛው እጁን ለጠላት ሊሰጥ ፈፅሞ አልፈቀደም! እርሱ የአፄ ቴወድሮስ፣የንጉስ ሚካኤል፣ የእምዬ ምኒልክ፣ የራስ አበበ አረጋዊና የጀነራል አሳምነው ፅጌ የአብራክ ልጅ ነውና፣ በደም አጥንቱ፣ በእስትንፋስ በሞራሉ የአማራዊ የሞራል ልህቀት ባለቤት ነውና አንዷን ጥይት ወደ ራሱ ተኮሳታ! እሳት እጁን የሚጨብጣት የለምና የጨለፍ ተስፋው ወንድም በፀጋውና ክብሩ ታላቅ ጀብድን በጥላት ላይ በመፈፀም ለአማራ ህዝብ በክብር ተሰዋ!!! "በደረቱ ያነገባቸውን አራት ካዝናዎችና አንድ ከነፍጡ የተገጠመ ካዝናውን ከጥላት ሰራዊት ላይ አርከፈከፈው። ከአገዛዙ ሰራዊት መሀል ዘሎ ገብቶ በቀኝ እጁ ክላሹን ከጥላት ደረት ላይ ተኮሰው፤ በግራ እጁ ቦምቡን እየመነጨ የጥላትን ምሽግና ከለላ እያፈራረሰ ወደ ፊት እሳት ለብሶ እሳት ጎርሶ ተጓዘ። የጥላት ሰራዊትም በርካቶች ወደ ምድር እየተዝለፈለፉ ወደቁ። አርበኛ ቅዱሴ ዘውዱ በቀኝአዝማች ጨለፍ ተስፉ እየማለ ወራሪውን ሀይል ዶግ አመድ አደረገው። በፂም የተከለለ ስንጥቅ መልኩን በጥላቶች ፊት ላይ እያበራ ለልዕልና የሚመኙትን ሸበላነቱን እያፀባረቀ ወንድነቱን እያስመሰከረ የጥላትን የጥፋት ሰንሰለት እየቆራረጠ በመቄት ምድር ከመድፍና ፔምፒ ላቃ ጋር ተናነቀ። "አርበኛው ለሀገር ዋርካ ለቀልብ እፎይታን የተቸረው ወንዳወንድ ሲሆን ከቀኝአዝማች ጨለፍ ተስፋው ጋር የትግል ጅማሮውን የጀመረ ሲሆን ከዛ ማዶ ወዶ ገቦች ጭንቅና ፈተናን ሸሽተው ኮምቦልቻ በተወሸቁበትና አማራነታቸውን ክደው ለኦህዴድ ባጎበደዱበት ዕለት እርሱ ግን ህቅታውን ለአማራ ትውልድ ያለ ስስት ከጠላት ጋር በመተናነቅ ታላቅና ህያው ታሪክን ሰርቶ የነ በላይ ዘለቀን ስምና ዝናን ተቀናጅቷል። ጀግኖችን ፀንሶ የመውለድ ችግር የማይነካካት የመቄት ምድር ያፈራችው አርበኛ ቅዱሴ ዘውዱ ሰኔ 20/2018 ዓ/ም በክብር ለአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተሰዋ። "ጀግና የነፃነት አለምን ፈጥሮ ያልፋል! ትውልድ ሁሉ ለዘላለም ይዘክረዋል!!! ©አርበኛ ፋኖ Eshetu Abate