ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
Открыть в Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
Больше2 935
Подписчики
-124 часа
+3307 дней
+38330 дней
Архив постов
የፅናትና የክብር ተምሳሌቶች የነፃነት አባት ራስ አርበኛ ዘመነ ካሴ፥በቀኖቹ መከራና በጨለማው ዘመን፣ የአማራ ህዝብ ታሪክና ማንነት አደጋ ላይ ሲወድቅ፣ የቁርጥ ቀን ልጆቹ ዳር ቆመው አልተመለከቱም። እውነተኛው ፋኖ ማለት የጥንታውያኑ አባቶች የአርበኝነት መንፈስና የጀግንነት ደም በውስጡ የሚፈላ፣ ለህዝቡ ነጻነትና ክብር ሲል ነፍሱን በደረት ኪሱ ይዞ የተነሳ የቁርጥ ቀን ጀግና ነው።
እነዚህ ጀግኖች እንደ ዱር አራዊትና እንደ ሆድ አምላኪዎች ለጥቅምና ለስልጣን አይሮጡም፤ መኝታቸውን በበረሃው ድንጋይ፣ ትራሳቸውን በጠመንጃቸው አድርገው፣ በቁርና በሃሩር የሚጋደሉት ለአንድ እና ለአንድ ዓላማ ብቻ ነው የአማራ ህዝብ በገዛ ምድሩ ላይ አንገቱን ቀና አድርጎ፣ በነጻነትና በክብር ይኖር ዘንድ!
የፋኖ ጀግንነት መገለጫዎች የመንፈስ ልዕልና እና ፍርሃት-አልባነት፦ እውነተኛ ፋኖዎች ከፊት ለፊታቸው የሚመጣውን ዘመናዊ የጦር መሣሪያ ሳይሆን ከጀርባታቸው ያለውን የህዝብ ሰቆቃና እንባ የሚያዩ ናቸው። የጠላት ብዛትና የኃይል ሚዛን አያስፈራቸውም፤ በልባቸው ውስጥ ያለው ፍቅርና እምነት ከማንኛውም የብረት ጋሻ ይበልጣል ረቂቅ ነው።
የህዝብ ጋሻና አለኝታነት፦ ፋኖ ለህዝቡ እረኛ፣ ለጠላት ግን መብረቅ ነው። በሄዱበት ምድር ሁሉ የሴቶች ረዳት፣ የህፃናት ዋስትና፣ የአረጋውያን ምርኩዝ በመሆን የሞራል ልዕልናቸውን ያስመሰክራሉ። የእነሱ ጀግንነት የሚለካው በጦር ግንባር በሚያስመዘግቡት ድል ብቻ ሳይሆን፣ ለህዝባቸው በሚያሳዩት ፍፁም ትህትናና ታማኝነት ጭምር ነው።
የታሪክና የማንነት ጠባቂዎች፦ የአማራን ህዝብ ታሪክ ለመበረዝ፣ ባህሉን ለማርከስና ህልውናውን ለማጥፋት ለሚንቀሳቀሱ ኃይሎች ሁሉ የቆሙ የማይናወጡ የዓለት ምሶሶዎች ናቸው። የትናንቱን የአባቶቻቸውን የአርበኝነት ታሪክ ዛሬም በደማቸው እያደሱት ይገኛሉ። የልብ ፅናት "ጀግንነት ማለት ታጥቆ መፎከር ብቻ አይደለም፤ ጀግንነት ማለት ህዝብ በተጨነቀበት ቀን፣ ሁሉም በፈራበትና በከዳበት ሰዓት፣ 'እኔ አለሁልሽ!' ብሎ ለፍትህና ለክብር መሰዋት ነው።
እውነተኛ የአማራ የቁርጥ ቀን ልጆች (ፋኖዎች) በታሪክ መዝገብ ላይ በወርቅ ቀለም የሚጻፉ፣ የትውልድ ኩራትና የነጻነት መብራቶች ናቸው። ስማቸው በጭቃ ሊለሰን፣ ታሪካቸው በከንቱ ፕሮፓጋንዳ ሊጠለሽ አይችልም፤ ምክንያቱም የእነሱ ጀግንነት የተገነባው በሆድና በጥቅም ሳይሆን፣ በማይበገረው የአማራ ህዝብ የልብ ትርታ ላይ ነው! Dave Amhara
+1
201ኛ ክር 74ኛ ክ/ጦር የአባይ ሸለቆ ተርቦች ዲቦ ከተማ የመሸገው ጠላት ላይ ድንቅ ስራ ሰርተዋል።
➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺
...ሐምሌ 05/2018 ዓ/ም
የብልፅግናውን እንክርዳድ ሰራዊትን ሐምሌ 04/2018 ዓ.ም ምሽት 10:00 ሰአት ላይ ከዲቦ ንዑስ ወረዳ ዲቦ ከተማ ተከማችቶ የነበረው ሚሊሻ ከካምፕ ወጥቶ እነብሬ ቀበሌ ተንቀሳቅሶ የነበረውን የሸለቆው አዳኞች ባልጠበቀው መልኩ ድንገተኛ ጥቃት በመፈፀም ሙትና ቁስለኛ አድርገውታል።
በዚህም 05 ሚሊሻና ፖሊስ አድማ በትን ወደ ላይኛው ሲሸኝ ሌላው እግሩ ወደመራው ሲበታተን በርካታው ቆስሎ ሆስፒታል የገባ ሲሆን የብሬን እና የክላሽ ተተኳሾችንም መማረክ ችለዋል።
በእለቱ ከተሸኙት የአብይ አገልጋዮች ውስጥም፦
1ኛ.ተመስገን ይርጋ
2ኛ.ትልቅ አወቀ ብሬን ተኳሹ ጥቂቶቹ ሲሆኑ አብርሃም ወሎየው ፖሊስ በከባድ ከቆሰሉት ውስጥይገኙበታል።
በመጨረሻም አሁንም አልረፈደም ጠብ አጫሪው አብይ አህመድ በሚጠራው የጦርነት ድግስ ውስጥ እየገባችሁ የምትማገዱ የብልፅግና አገልጋዮች ኑ የአማራ ፋኖ ይቅር ባይ ነውና በይቅርታ ወደ ቤተሰባችሁ ተቀላቀሉ በማለት ጥሪያችን እናስተላልፋለን
አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
ካራማራ ክፍለ ጦር ለወራት ሲያሰለጥን የቆየውን እግረኛ ሠራዊት በደማቅ ሁኔታ አስመረቀ
በአፋብን በላይ ዘለቀ ዕዝ መይሳው ካሳ ኮር ሥር የሚንቀሳቀሰው ካራማራ ክፍለ ጦር፡ ለወራት በወታደራዊ እና በፖለቲካዊ ትምህርቶች ሲያሰለጥን የቆየውን ሠራዊት በደማቅ ሥነ-ሥርዓት አስመርቋል።
ካራማራ ክፍለ ጦር በዘንድሮው ዓመት በአገዛዙ ጥምር ሠራዊት ላይ በተደጋጋሚ በማያቋርጥ ኦፕሬሽን ከፍተኛ ድሎችን በማስመዝገብ የበላይነቱን ሲያሳይ የቆየ ታላቅ አደረጃጀት ነው።
ክፍለ ጦሩ ከወታደራዊ ተጋድሎ ጎን ለጎን፣ ወቅቱን የተረዳ፣ ጠንካራ ሥነ-ልቦና እና ጥልቅ የፖለቲካ ግንዛቤ ያለው ሠራዊት በመገንባት ረገድ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ ይገኛል።
አዲስ የተመረቁት ሠራዊት በክፍለ ጦሩ የተሰዉ ጓዶቻቸውን እና እንደ አርበኛ ፈንታሁን ገበየሁ ያሉ ጀግና አመራሮችን በማስታወስ ቃል ኪዳን ገብተዋል።
ሠራዊቱ በትግሉ ሂደት የጀግኖች አባቶቻቸውን አደራ በመቀበል፣ በደምና በአጥንት ዋጋ የሀገሪቱን የዘንዶ ሥርዓት በማስወገድ፣ በምትኩ ፍትሐዊ እና መልካም ሥርዓትን ለትውልድ ለማስረከብ እስከ ድል ድረስ እንደሚታገል በታላቅ ቃል ኪዳን አረጋግጠዋል።
ይህ የሠራዊት ምልመላ እና ስልጠና የፋኖን ድርጅታዊ አቅም በማሳደግ፡ ትግሉን ወደ ላቀ ምዕራፍ የሚያሸጋግር እና የጠላትን ኃይል ሙሉ በሙሉ ለመደምሰስ የሚያስችል ወሳኝ ምዕራፍ ተደርጎ ተወስዷል።
የጀብደኛዉ ምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር 47ኛ ክ/ጦር አትሮንስ ሻለቃ ደፈጣ በመጣል በአገዛዙ ሰራዊት ላይ የማያዳግም እርምጃ ወሰደች!
አፋብን ወሎ ቤተ_አማራ ምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር 47ኛ ክ/ጦር የአትሮንስ_ሻለቃ ተናዳፊ ተርቦች በኦህዴድ/ብልፅግና ወንጀለኛ ቡድን ሥልጣን ጠባቂ ቅጥረኛ ኃይል ላይ ደፈጣ በመጣል የክ/ጦርና የሻለቃ አመራሮችን ሙትና ቁስለኛ በማድረግ ከፍተኛ ሰብዓዊ ኪሳራ አድርሰውበታል።
04/11/2018 ዓ.ም በአምሓራ ሳይንት ሰማይ ስር እፁብ ድንቅ ተብሎ በተመሰገነውና ድንገተኝነትን ባተረፈው የደፈጣ ጥቃት ከደንሳ ከተማ ወደ በለጩማ በ 7 መኪና ሲጓጓዝ የነበረ ወራሪ ኃይል ልዩ ቦታው ወጀድ መገንጠያና ጎዴል በተባሉ ስትራቴጅክ ቦታዎች ላይ የአትሮንስ ሻለቃ ትንታጎች አከርካሪውን በማድቀቅ አሽመድምደውታል።
በዚህ አስደናቂ ጥቃት ክ/ጦር ዘመቻ ኃላፊ ሻለቃ ወልደ ጊዮርጊስና የሻንበል ማዕረግተኛ የሆነው አስራት ከባድ ቁስለኛ ሲሆኑ ሌላኛው ማዕረጉ ለጊዜው ያልታወቀ መስመራዊ መኮነን እስከ አጃቢው ለዘላለም ማሸለቡ ታውቋል።
አመራሮቹን አጅበው በፓትሮልና በካሶኒ ታጭቀው ሲጓዙ ከነበሩት በአልታሰበና ድንገተኛ የቦንብና የጥይት ጥቃት ተጋላጭ በመሆናቸው አያሌ ቁጥር ያላቸው መሠረታዊ ወታደሮች ለኦህዴድ/ብልፅግና ወንጀለኛ ቡድን ሥልጣን ለመጠበቅ ሲባል የመስዋዕት በግ ሆነው ወደከርሰ_መቃብር በመውረድ በአፍንጫቸው አፈር ፈሷል።
የክ/ጦር ዘመቻ ኃላፊው ሻለቃ ወልደ ጊዮርጊስ አጃቢ መሠረታዊ ወታደር ከድር ጀማል ከቀናት በፊት ወደ ፋኖ መኮብለሉ የሚታወቅ ነው። ዛሬ ደግሞ ሻለቃ ወልደ ጊዮርጊስና ሌሎች የክ/ጦርና የሻለቃ አመራሮች በከፍተኛ አጀብ ተከበው ለመንቀሳቀስ ቢሞክሩም እነሆ ከመቅሰፍቶቹ የጥይት ሀሩር ግን ማምለጥ አልቻሉም።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!!!
ህልዉናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ_አማራ ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!
05/11/2018 ዓ.ም
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ጀብደኛዉ ምኒልክ ዕዝ የ303ኛ አሳምነዉ ኮር ከ55 በላይ ጠላትን በመደምሰስ እና ከ40 በላይ ጥቁር ክላሽን በመማረክ ታላቅ ድልን ተጎናጽፈዋል!!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ አሳምነው ኮር አካል የሆነው 21ኛ(ተከዜ) ክፍለ ጦር ፋኖዎች ራሱን 90ኛ ክፍለ ጦር ብሎ የሚጠራው ከኩልመስክ፣ ከ61ኛ ክፍለ ጦር ሁለት ሻለቃዎችን ይዞ ከላሊበላ ከተማ የተንቀሳቀሰውን የብልፅግና ሰራዊትን ስቦ ወደ መግደያ ቦታ በማስገባት አይቀጡ ቅጣት ቀጥተውታል።
ሐምሌ 04 ቀን 2018 ዓ/ም መነሻውን ኩልመስክና ላሊበላ ከተማ አድርጎ ወደ ገነተማርያም የተንቀሳቀሰው የጁላ ሰራዊት በዙ-23 እና በ107 የታገዘ ውጊያ ቢያደርግም መሃል ላይ ስቦ በማስገባት የቆረጣ መሀንዲሶቹ 21ኛ(ተከዜ) ክፍለ ጦር መሀል ከበባ ውስጥ በማስገባት አኩሪ ድል አስመዝግበዋል።
በዚህ አውደ ውጊያ ከ55 በላይ የጠላት ኃይል ሲደመሰስ፣ ከ30 በላይ የቆሰለ፣ 42 ጥቁር ክላሽና አንድ ሬድዮ መገናኛ፣ 27 የደረትና የወገብ ትጥቅ፣ 36 ወታደራዊ ሻንጣ ተማርኳል።
በተያያዘ መረጃ አንድ የመከላከያ ሰራዊት አባል ዛሬ መነሻውን ከላሊበላ ከተማ በማድረግ አንድ ጥቁር ስናይፐርና አንድ ጥቁር ክላሽ በመያዝ 303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር 16ኛ ነብሮ ተወርዋሪ ኮማንዶ ክፍለ ጦርን ተቀላቅሏል ሲል የ303ኛ አሳምነው ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃውን አድርሷል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ!!
ሐምሌ:- 04/ 2018 ዓ/ም
የጠላትን እቅድ በማክሸፍ ፋኖወቻችን ፈጣን የሌሊት ሽምቅ ማጥቃት በመፈፀም ድል ተቀናጅ
^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^
.....ሐምሌ04/2018 ዓ.ም
የአብይ አህመድ ሰራዊት የኦፕሬሽን ቀኑን ከ30 ወደ 10ዝቅ አድርጎ ሞክረው፤ አልተሳካለትም።
ጠላት ከሰኔ10 እስከ ሐምሌ10 ዘመቻ ቢያቅድም አንድም በተኛበት የፋኖ ፈጣን ማጥቃትና ሌላም በእንቅስቃሴ ላይ በተጠና የቆረጣና የሽምቅ ዉጊያ የፋኖን ምት መቋቋም አቅቶታል።
ሐምሌ 03/2018ዓ.ም ጠላት ከድጎፅዮን ወደ ወይንውሃ የሌሊት እንቅስቃሴ ቢያደርጉም የ201ኛ ኮር አካል ነበልባሎቹ የ54ኛ ክ/ጦር ሻለቃ4 ጠላትን በቆረጣ ግርገራድ መገንጠያ ላይ ድባቅ መተውታል።
በዚህ የረጅም ሰዓት የጠላት ጉዞና የፋኖ የደፈጣ ምት በማሳረፉ ጠላት እርስበርሱም እንደተኳኮሱ ማረጋገጥ ተችሏል።
አ(ስከ)ሬን መደበቅ እንደ ጀብድ የሚቆጥረው የአብይ አህመድ ሰራዊት በየጫካው ቀብሮ እንደሄደ ከአካባቢው ነዋሪወች በተጨባጭ 5ጫካ ትቶት የሔደና በርካታ ቁስለኛኞች እንዳሉም ተረጋግጧል። መንገድ መሪ የነበሩ ሚሊሻወችን ጨምሮ ተሸኝተዋል። ከወገን ምንም ጉዳት የሌለበት መሆኑ የበለጠ ልብን ያሞቃል።
በትንሽ የሰው ኃይል ትላልቅ ድሎችን የሚያስመዘግበው ነበልባሏ 54ኛ ክ/ጦር ዛሬም በድል ጎዳና በትግል የአደረጃጀት ቁመና ትገኛለች።
ዘወትር ስለራሳችን እንመክራለን!
ድርጅታችንን እንጠብቃለን!! እናቅዳለን እንፈፅማለን!!
አፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት!!
የራስ አበበ አረጋይ ክፍለ ጦር በደገም ወረዳ በጠላት ላይ የማያዳግም የድል እርምጃ ወሰደ!!
ሐምሌ 04/2018 ዓ.ም
በግራሪያ (ፍቸ ሰላሌ) አውራጃ ነዋሪዎች ላይ ብሔርና ሃይማኖት ሳይለይ የዘረፋ ተግባር ሲፈጽም በነበረው የሸኔ ቡድን ላይ የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ አምደጽዮን ኮር ራስ አበበ አረጋይ ክፍለ ጦር (2ኛ አሊ ሻለቃ) ደገም ወረዳ ውስጥ በሚገኙት ሀሮ እና አቦ ለሊሳ ቡድኑ የሰፈረባቸው ቦታዎች ላይ መብረቃዊና የማያዳግም እርምጃ ወስዷል።
ከንጋቱ 12:00 እስከ ቀኑ 5:00 ድረስ በተደረገው በዚህ ስልታዊና ልዩ ኦፕሬሽን፣ የሻለቃው አናብስቶች የጠላትን ካምፕ በመስበር ከፍተኛ የድል ዜና አብስረዋል። በኦፕሬሽኑ በርካታ የቡድኑ አባላት ተደምስሰዋል።
➡➡በግዳጁ የተገኙ ግብአቶች፦➡
✔.7 የጦር መሣሪያዎችና በርካታ ተተኳሾች ተማርከዋል።
✔.9 የቀንድ ከብቶች እንዲሁም 15 በግና ፍየሎች ከዘራፊው እጅ ለአርሷደሮቹ ተመልሰዋል።
✔.ወታደራዊ ሻንጣዎች፣ ካዝናዎች፣ ልዩ ልዩ ቦምቦችና የወገብ ትጥቆች በቁጥጥር ሥር ውለዋል።
" ክብር ለትግሉ ሠማዕታት!
"ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
ከአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር የተሰጠ ጥብቅ ማስጠንቀቂያ
ሀምሌ 04/2018 ዓ.ም
~~~~~
ለእነማይ ወረዳ እና ሸበል በረንታ ወረዳ ለቤቶች ማህበር የቦታ መሬት ተደራጅተው ለሚጠብቁ ለማህበሩ አባላት በሙሉ፤
የአማራ ሕዝብ በገዛ አገሩና ቀዬው ላይ ተፈናቃይ፣ ተሰዳጅ፣ ታጋች፣ ይባስ ብሎ በደመ ነፍስ እንደሚንቀሳቀሱ ከብትና በሬ እየታረደ ብዙ ጊዜ የመከራ ቀንበር ተጭኖበት ከመንግሥታዊ መዋቅር ተገልሎና ተገፍቶ መቆየቱ ይታወቃል። ይሁን እንጂ ይህ የመከራ ጊዜ ፅዋው ሞልቶ ሲፈስ የአማራ ሕዝብ ከሰላማዊ ትግል፣ ከሰልፍ ወደ ሰይፍ የትጥቅ ትግል ከገባ ወደ 3ኛ ዓመቱን ማስቆጠር ችሏል።
በዚህ የ3 ዓመት የትጥቅ ትግል ቆይታ ለአገራቸውና ለማንነታቸው ሲሉ ብዙዎች ቆስለዋል፣ ደምተዋል፣ አካላቸውን አጥተዋል። ብዙዎች የሕይወት መስዋዕትነትን ከፍለዋል፣ ዛሬም እየከፈሉ ይገኛሉ። ነገር ግን ይህ እየሆነ ባለበት ሁኔታ፣ ከአገራቸው ማንነት ይልቅ ለራሳቸው ክብርና ጥቅም ያስቀደሙ፣ የአማራን የከፍታ ማማ በተራ ጥቅም የቀየሩና ያዋረዱ፤ በእነማይ ወረዳ ቢቸና ከተማ፣ በሸበል በረንታ ወረዳ የዕድውሃ እና መርገጭ ዙሪያ የምትገኙ የቤቶች ማህበር አባላት ቦታ ለማግኘት እየተሳተፋችሁ የምትገኙ መሆኑን አውቀናል።
ስለሆነም 64ኛ ክፍለ ጦር ሠራዊት በትግላችን ብዙ መስዋዕትነት እየከፈለ መሆኑን እያወቃችሁ፣ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ጉዳዮች ጥሶ የተገኘ ግለሰብ፣ ማህበር ወይም ድርጅት ላይ ተቋማዊ እርምጃ የምንወስድ መሆኑን በጥብቅ ማሳሰብ እንወዳለን፦
ከሐምሌ 27/2015 ዓ.ም ጀምሮ በሊዝ ጨረታ የተገዛ挑战፣ የብልፅግና ካቢኔ挑战፣ ሚሊሻ፣ ፖሊስ እና የባንዳ ተንቀሳቃሽም ይሁን ቋሚ ንብረት፤ ከሐምሌ 27/2015 ዓ.ም ጀምሮ የቦታ ምሪት የተመራና የገዛ አካል።
ከዚህ ጋር ተያይዞ በእነማይ እና ሸበል በረንታ ወረዳ ላይ አገዛዙ "በቦታ ካሳ ሰበብ" በሚል የገንዘብ መሰባሰቢያ ዘዴ ዘይዶ የአማራን ሕዝብ የህልውና ትግል ለማኮላሸትና የሕዝባችንን የመከራ ጊዜ ለማርዘም እየሠራ እንደሚገኝ ይታወቃል። የአማራ ሕዝብ በህልውና አደጋ ውስጥ ባለበት ጊዜ ለአገዛዙ የጊዜ ማራዘሚያ የሚሆን የቦታ ካሳ ገንዘብ የሚከፍል አካል ካለ፣ የሕዝባችንን የስቃይና የመከራ ጊዜ ማራዘምና አገዛዙን በፋይናንስ እንደመደገፍ ስለሚቆጠር፣ በዚህ ድርጊት የሚሳተፍ ማንኛውም አካል የካሳ ብር እንዳይከፍልና ከዚህ ድርጊት እንድትቆጠቡ በጥብቅ እያሳሰብን፣ በዚህ ድርጊት በሚሳተፉ የትኞቹም አካላት ላይ አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክፍለ ጦር እርምጃ የሚወስድ መሆኑን እንገልጻለን።
አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክፍለ ጦር!
መረጃ፤
የአዊ ዞን ፖሊስና ሚኒሻ ጭንቅ ጥብብ ብሎታል።
ከሰሞኑ ወደ ግንባር ትዘምታላችሁ መባሉን ተከትሎ በ"ክልሉ" የሚኖሩ የፖሊስና ሚኒሻ አባላት በጠቅላላ ጭንቅ ውስጥ መሆናቸውን በተጨባጭ መረጃ ስንሰማ መቆየታችን ይታወቃል። ይህን ተከትሎም ከየአሃዱ እየጠፋ እየተናደ ይገኛል። ለምሳሌ ያህል በአዊ ዞን ዛሬን ጨምሮ በዚህ ሁለት ሦስት ቀናት ብቻ ከ57 በላይ አባላት ከነሙሉ ትጥቃቸው አሻፈረኝ ብለው አብዛኛዎቹ ፋኖን የተቀላቀሉ ሲሆን ቀሪዎቹ ደግሞ ወደ ቤተሰቦቻቸው በሰላም ተሸኝተዋል። ይህ ወደ ወገን የመሠባሰብና አፈሙዝን የጋራ ወደሆነው ጠላት የማዞር ሂደት በተጨባጭ ቀጣይነት የሚኖረው ይሆናል።
ዛሬ በደረሰን ተጨባጭ መረጃ መሠረት በአዊ ዞን የሚገኙና ወደ ግንባር እንዲዘምቱ እጣ የደረሳቸው(የወጣባቸው) የፖሊስና የሚኒሻ አባላት መዝመት አንፈልግም ማለታቸውን ተከትሎ "አንዘምትም ካላችሁ ብር ክፈሉና ትቀራላችሁ" ተብለው ከፍተኛ ገንዘብ እየከፈሉ ይገኛሉ። ብር የሌላቸው ፖሊስና እና ሚኒሾች ደግሞ ቤታቸውን በማስያዣነት ተጠቅመው ከአብቁተ(ፀደይ ባንክ) ብር እየተበደሩ እየከፈሉ መሆኑን አረጋግጠናል።
እንደ አብነት የአዊ ዞኑን አነሳን እንጂ ቴዎድሮስ ዕዝ 105ኛ ኮር በሚያስተዳድራቸው ሁሉም ቀጠናዎች ይህ የጠላት መጠቀሚያ የሆነ ኃይል እየፈራረሰ ይገኛል።
ምክረ ሀሳብ
÷÷÷÷
በተደጋጋሚ እንደምንለው ትርጉም የሌለው ሞት አትሙቱ። የእስካሁኑ ይበቃችኋል። ለአንድ እብድና ወፈፌ ግለሰብ ስልጣን ብላችሁ አትለቁ። የብአዴን ባለሥልጣንን ጨምሮ ሆቴልና መጋዘን ጠባቂ አለመሆናችሁን በተግባር አሳዩ። ከሕዝባችሁና ከወገናችሁ ጋር ደም አትቃቡ። ሥለሆነም ኑ! እኛ በፍቅር እንቀበላችኋለን። የጋራ ዘረፈጅ ጠላት አለን እሱን እንምታ። ሀገራችንና ሕዝባችን የጋራችን ናቸው። የእኛ ትግል ለእናንተ ነፃነት ጭምር ነው። በእኛ መስዋዕትነት ነፃ የምትወጡት እናንተና ልጆቻችሁ እንዲሁም መላው ቤተሰባችሁ ጭምር ነው። ኑ! በፍቅር እንቀበላችኋለን። በጠላትነት እንድንተያይ እና እርስ በርስ እንድንታኮስ ያደረገን አገዛዙ ነው። እንጅማ ወንድሞቻችን ናችሁ፤ እኛም ወንድሞቻችሁ ነን። ኑ!
ድል ለአማራ ሕዝብ!
ድል ለፋኖ!
አዲስ ትውልድ፤አዲስ አስተሳሰብ፤አዲስ ተስፋ!
ኅልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
ቴዎድሮስ ዕዝ 105ኛ ኮር
ሐምሌ 4/2018 ዓ.ም
+3
🛑 ሰበር ዜና፦
የብልፅግና 102ኛ አየር ወለድ ምክትል አስር አለቃ አና አንድ አባል በመሆን ሙሉ ትጥቃቸዉን በመያዝ ፋኖን ተቀላቀሉ!!
ሐምሌ 04/11 / 2018 ዓ.ም
በኤፍራታ ግድም ወረዳ፣ በርግብይ አካባቢ ህዝቡን በማንገላታት፣ በማሳቀቅና በመድፈር ላይ የሚገኘው የአብይ አህመድ ስርዓትና የፀጥታ መዋቅር በከፍተኛ ሁኔታ እየፈረሰ መሆኑ ተነገረ። ከዚህ መዋቅር ለመውጣት ለብዙ ወራት ሲያቅዱ የቆዩ ሁለት የመከላከያ አባላት፣ የቆዩበትን የአገዛዙን ሰራዊት ጥለው በመውጣት ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሰባት ለሰባ ክፍለ ጦር በሰላም ገብተዋል።
ከተቀላቀሉት የጦር አባላት መካከል የኦሮሚያ ተወላጅ የሆኑ የአብይ አህመድ ወንበር አስጠባቂ 102ኛ ልዩ ዘመቻ አየር ወለድ መከላከያ ክፍለ ጦር ውስጥ የነበረ ምክትል አስር አለቃ እና አንድ አባል ሲሆኑ እነዚህ አባላት ከነሙሉ ትጥቃቸው የፋኖን ትግል ተቀላቅለዋል በሰጡት ቃልም "የቆየንበትን የትግል ዘመን በታሪካችን ህዝብ የበደልንበትና የበዳዮች ተባባሪ የሆንበት በመሆኑ ህዝባችን ይቅር ይበለን" በማለት ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
በአሁኑ ወቅት በርካታ የሰራዊቱ አባላት የሁኔታውን አሳሳቢነት በመረዳትና ህይወታቸውን እያተረፉ ወደ ህዝባዊ ትግሉ እየተቀላቀሉ ይገኛሉ። አማራነት ያሸንፋል!
የአፋብን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የሰባት ለሰባ ክፍለ ጦር
