ru
Feedback
Abdulkarim 🇵🇸

Abdulkarim 🇵🇸

Открыть в Telegram

فاصل الايمان مشروط باصل الحب وكمال الايمان مشروط بكمالالحب "እውነተኛ እምነት በእውነተኛ ፍቅር ይጀምራል፤ ፍጹም እምነት ደግሞ በፍጹም ፍቅር ላይ የተመሰረተ ነው። ይህም የነቢዩ (ﷺ) ፍቅር ነው፡፡''

Больше
471
Подписчики
-224 часа
-47 дноК
-630 день
Архив постов
የምቶዱን ነገር እንደምቶዱት ንገሩት ይላል ሃዲሱ ታሪኩን ከወዳዳችሁት ላይክ አድርጉት እንጂ😐

. ሚያዝያ ላይ ለአስራአምስት ቀን እረፍት ተሰጥቶን ወደየቤታችን ተበተንን። አምሪን እስካገኛት በጣም ቸኩያለሁ። ገና ወደ ቤት እንደገባሁ በየክፍሉ ፈለግኳት። የለችም። አስራአንድ ሰዓት አካባቢ ስለነበር ሰፈር መስጂድ ልትማር ሄዳ እንደሚሆን ጠረጠርኩ። ትንሽ እንደቆየሁ አምሪ ኪታቧን ይዛ ከሰፈር መስጂድ ተመለሰች። ኪታብ ማለት መፅሀፍ ማለት ነዉ።  በአግባቡ ሰላም ብዬ ናፍቆቴን መወጣት ይኑርብኝ ወይ ስ መቆጣት ግራ ገባኝ። ረጋ ብሎ ምክንያቷን መስማቱ እንደሚሻል ስለተሰማኝ ሰላም ከተባባልን በኋላ "አምሪ በሰላም ነዉ መርከዝ መጥተሽ ሰላም ሳትይኝ የምትሄጂዉ?" አልኳት። "ሀቢቤ ይቅርታ ትንሽ በስራ ቢዚ ነበርኩ።" አለችኝ። እልህ እየተናነቀኝ "እኔን አስርደቂቃ አግኝቶ ሰላም ከማለት ያገደሽ ምንአይነት ስራ ነዉ ባክሽ?" አልኳት። እያቀረቀረች "ባክህ ባል እየፈለግኩ ነበር!" አለችኝ። ከሁኔታዋ ሁሉም ነገር ገባኝ። ለካ "ለትዳር የጠየቀህ የለም ወይ?" ስትለኝ "አሉ ትምህርቴን ስጨርስ ሰብስቤ አገባቸዋለሁ!" ስላልኳት ነበር ያኮረፈችኝ! አምሪ ትወደኛለች ማለት ነዉ። እሷ የጠየቀችኝ አንቺን ነዉ የማገባዉ እንድላት ነበር። ምን አይነት ደነዝ ነኝ በአላህ? እንዴት ይሄን መረዳት ከበደኝ? በርግጥ የዛኔ እየቀለድኩ ስለነበር አምሪን እንዲህ ያስመርራታል ብዬ አላሰብኩም ነበር። እየሳቅኩ "እና ባል አገኘሽ?" አልኳት። አምሪ እንደተረዳኋት ገባት መሰለኝ እየተሽኮረመመች "ከአንድ ሰዉ ጋር እያወዳደርኳቸዉ ሁሉም ወደቁ!" አለችኝ። አሁንም እየሳቅኩ "በደንብ ፈተናዉን ቀጥይ!" አልኳት። እየተሽኮረመመች "አመዳም!" አለችኝ። ሁሉ ነገሯ ደስ የምትል ፍጥረት! . ቤት ተቀምጠን እነሀጂም መጥተዉ እየተጨዋወትን ከጎረቤት ጭቅጭቅ መስማት ጀመርን። አምሪ "አዪ በአላህ ዛሬም ሊደበድባት ነዉ?" አለች። ስልችት ያላት ትመስላለች። "የት ነዉ?" አልኳት። "ባክህ እነሰሚራ ጋር ነዉ። ሰዉየዉ ሰሞኑን ልጅቷን ምን ሁኚ እንደሚላት እኔንጃ!" አለችኝ። ጭቅጭቁ ሲያይል ሰሚራ ስትጮህ ሰማን። ሀጂናእኔ እየሮጥን ወደነሰሚራ ቤት ሄድን። የዉጪዉ በር ክፍት ነበር። ወደ ዉስጥ ስንገባ ባሏ ሰሚራን እየመታት ነበር። ሀጂ ጎትተዉ አላቀቁት። ሰዉየዉ ግን በጣም የተበሳጨ ይመስላል። ሀጂ ሲያስጥሉት "ድሮም ቆሻሻ ነሽ። የትም ቀሚስሽን ስትገልቢ የኖርሽ ባለጌ!" አለ። ለሰሚራ እኔ ስቅጥጥ አለኝ። ሰሚራ በተጣላን ቁጥር ያነሳዋል ያለችዉን ዉርደቷን ይኸዉ ዛሬ ከአፉ ሰማሁት። በለዉ በለዉ አለኝ። ደሞ ማን ነኝ ብዬ እመታዋለሁ? እንዲህ ሰሚራን ከሰዉ በታች ያደረጋት እኮ ክብሯን በኔዉ መነጠቋ ነዉ። ሀጂ ባሏ እስኪረጋጋ ሰሚራን እኛ ቤት ይዣት እንድገባ አዘዙኝ። ሰሚራን ወደኛ ቤት ይዣት ሄድኩ። ሀጂ ሰዉየዉን አስቀምጠዉ ይመክሩት ጀመሩ። ከሰሚራ ጋር እኛ ቤት ስንገባ ሰሚራ እያለቀሰች ነበር። የሞት ሞቴን "አይዞሽ ሰሙ!" አልኳት። በሂጃቧ ጫፍ እንባዋን እየጠረገች ዝም ብላኝ ወደ ሳሎን ገባች። አምሪና ወ/ሮ ለይላ ተቀብለዉ ማባበል ጀመሩ። የትኛዉ ቀን ነዉ ከሰሚራ ጋር አንሶላ ያጋፈፈኝ? ምን አይነት ህሊና ቢስ ነበርኩ በአላህ? ትናንት የሰራሁት ርካሽ ስራ ዛሬ የስንቱን ህይወት በጠበጠ? ሰሚራን የመሰለች ሚስኪን ህይወቷ ብልሽትሽት አለ! ጌታዬ ይቅር ይበለኝ! የኔስ በጣም በዛ! በጣም! ሀጂ ሰዉየዉን ካረጋጉት በኋላ ወደኛ ቤት መጥቶ ይቅርታ ጠይቆ ይዟት ሄደ። ከወደዳት ምናባቱ አፉን ይከፍትባታል!? ለነገሩ ያልተነካ ግልግል ያዉቃል አይደል የሚባለዉ? እሱ የሚስቱን ክብርም ሳያገኝ ልጅም ተከልክሎ ባይበሳጭ ነዉ የሚገርመዉ! ወይ ሰሚራ! መች ነዉ ያወቅኩሽ?! ምናለ በቀረሽብኝ እና ህይወትሽ ባልተበጠበጠ! ወደ ኋላ መመለስ ቢቻል ሁሉንም አስተካክለዉ ነበር! ችግሩ አይቻልም! . ይቀጥላል... .

የማይፋቅ ስህተት ክፍል አስራአራት (ፉአድ ሙና) . የረመዳንን የመጀመሪያ ቀን ፆም የገደፍነዉ ሰሚራ በሰራችዉ ምግብ እነሰሚራ ቤት ነበር።  ከልቤ ፈጣሪ ልጅ እንዲሰጣቸዉ ለመንኩ። አምሪ ሰሚራ "ምን ልጨምርልህ?" እያለች ስታስተናግደኝ ስታይ የሌለ ሳቀች። ምን ያስቅሻል እንዳይሏት በጣም ፈርቼ ነበር። ደግነቱ ብዙም ትኩረት አልሰጧትም። ሰሚራ በደንብ ነበር ያስተናገደችን። ምግቡም በጣም ይጣፍጥ ነበር። በወጉ ተስተናግደን ከነሰሚራ ቤት ወጣን። የሰሚራ ባል ስንወጣ ያዝ አድርጎኝ "አላህ ያንተን ይሰማሀል አደራ ለምንልኝ! ልጅ በጣም እወዳለሁ።" አለኝ። "አላህ የማንን እንደሚቀበል አናዉቅም አንተም አድርግልኝ። አብሽር!" አልኩት። እንደዚህ አክብሮ የሚያወራኝ ሰዉ የሚስቱን ክብር የገፈፍኩት እኔ እንደሆንኩ ቢያዉቅ ምን ይል ይሆን? የብዙዎቻችን ጉድ አደባባይ ቢወጣ አንዳችንም ቀና ብለን መሄድ የምንችል አይመስለኝም። ፈጣሪ እያመፅነዉ እንኳ ወንጀላችንን መሸሸጉ እንድንመለስ እድል እየሰጠን እንደሆነ እና ምን ያህል ለባሮቹ አዛኝ መሆኑን የሚያሳይ ይመስለኛል። . የረመዳን ፆም ገብቶ የተወሰኑ ቀናት አለፉ። እኔም እንደተለመደዉ ማሰገዴን ቀጥያለሁ። የረመዳንን አስራአምስተኛ ለሊት ስግደት ጨርሼ ከመስጂዱ ስወጣ ፌቨንን ከመስጂዱ አቅራቢያ ቆማ ተመለከትኳት። ከነሀጂ ጋር ስለነበርኩ ባላየ ወደ ሀጂ መኪና ገባሁ። መኪናዉ በአጠገቧ ሲያልፍ ትኩር ብዬ አየኋት። በደንብ ዘንጣለች። ረዘም ያለ ሱሪ እና ሌዘር ጃኬት ለብሳለች።እጇ ላይ ሲጃራ አለ። ሱስ የሚባል የቀራት አይመስለኝም። ለሁሉም ተጠያቂዉ እኔ ነኝ። ሚስኪኗን የቤት ልጅ አበላሸኋት። ቆይ ግን እንዴት መስጂድ በር ላይ መጥታ ቆመች? ልደዉልላት ፈለግኩ። ደሞ ለሌላ ነገር የፈለግኳት ይመስላታል ብዬ ተዉኩት። ከዚህ ቀን በኋላ ፌቪ ሁሌ ማታ ማታ መስጂድ በር ላይ ትቆምና ትሄዳለች። ሀያኛዉ ለሊት ላይ ሰግጄ ስወጣ ከመስጂዱ ትንሽ ራቅ ብላ ቆማለች። ዛሬ ሀጂ የሉም። ከወ/ሮ ለይላ እና ከአምሪ ጋር ነዉ የመጣሁት! እነሱ ከሴቶች መስጂድ እስኪወጡ ስጠብቃቸዉ ፌቪ እየተራመደች ወደኔ መጣች። አለባበሷ ሙስሊም ሴት አስመስሏታል።ቀሚስ ነዉ የለበሰችዉ። ፀጉሯ ላይ ሻሽ ጠምጥማለች። እኔ ደግሞ  ጀለቢያ እንደለበስኩ ጥምጣሜንም እንደጠመጠምኩ ነኝ። ሰዉ እየመጣ ሰላም እያለኝ ያልፋል።ፌቪ አጠገቤ ስትደርስ አቀረቀርኩ። "ሀቢቤ ሰላም ነህ?" አለችኝ። መልስ ሳልሰጣት "እዚህ ምን ትሰሪያለሽ?" አልኳት። "ያዉ ድምፅህ ናፍቆኝ ነበርና እዚህ ይፀልያል ሲባል ሰምቼ መጣሁ! ባይዘዌይ  ድምፅህ በጣም ያምራል!" አለችኝ። "ፌቪ ለሁሉም ይቅርታ! ከዚህ በኋላ ግን ያንቺ መሆን አልችልም! እኔን ለመርሳት ሞክሪ!" አልኳት። ፌቪ ድምጿ በሳግ እየታፈነ "አዉቃለሁ! ጌታ መልካሙን ይስጥህ! ግን ሁሌም አፈቅርሀለሁ። ከዚህ በኋላ ሰዉ መሆን አልችልም። እስከምሞትም ሰዉ አልሆንም! ያዉ ባስጀመርከኝ የሴሰኝነት መንገድ እጓዛለሁ። አንተ እራስህን አፅዳ ግድ የለም! ቀለል አድርገህ እርሺኝ በል! ግድ የለም!" ብላ እንባዋን መጠራረግ ጀመረች። ቀና ስል እነአምሪያ ወደኛ ሲመጡ አየኋቸዉ። ፈጠን ብዬ "ፌቪ አሁን ሂጂ! ለኔ ጥሩ አይደለም!" አልኳት። "ላንተ ጥሩ አይደለም!? አንተን ካወቅኩ በኋላ እኮ ለኔ ምንም ጥሩ ሆኖ አያዉቅም!" አለችኝ። አምሪያ እየተጠጋችን "አሰላሙአለይኩም ሀቢቤ!" አለች። በጣም ጨነቀኝ። አምሪ ፊቷን ካየቻት ታዉቃታለች። አምሪ ስትጠጋን ፌቪ ድምጿን ከፍ አድርጋ "አመሰግናለሁ ኡስታዝ! አላ ይስጥልኝ።" ብላ ወደ አምሪያ ሳትዞር ሄደች። አምሪ ፌቪ መጨረሻ ላይ ያለችዉን ስለሰማች አልጠረጠረችም። እያደነቀችኝ መስሏትም ይሆናል። አምሪ እየሳቀች"ሀቢቤ እየፈረምክላት ነዉ? አድናቂህ በዛ አይደል?" አለችኝ። ወ/ሮ ለይላ እየሳቁ "አይ አምሪያዬ እስኪ ተይዉ መወደድ የአላህ ፀጋ ነዉ!" አሉ። አምሪ አሁንም እየሳቀች "ኧረ እኔ እኛን እንዳይረሳን ብዬ ነዉ!" አለች። እኔ ዉስጤ ላይ መረጋጋት የለም። ፌቪን ያደረግኳት ነገር ፀፀቱ ሰላም ነሳኝ። ያበላሸሁት ማንነት ሊስተካከል የሚችል አይነት አይደለም። ምናለ ባላወቅኳት! . የረመዳን ፆም ከተጠናቀቀ እና የኢድ አል ፈጥር በዓል ተከብሮ አስራአምስት ቀናት ካለፉ በኋላ ወደ መርከዝ ተመለስኩ። ወደ ዉዱ የሀይማኖት ትምህርት ቤት! ቁርዓንን ሸምድጄ ስለጨረስኩ በተለየ መልኩ ሙሉ ሰዓቴን ሌሎች የእምነቱ ዘርፍ ትምህርቶችን በመማር አሳልፋለሁ። ከአንድ ኡስታዛችን ጋር በጋራ ሆነን ደግሞ ትምህርቶችን በድምፅ እየቀረፅን ኢንተርኔት ላይ እንለቃለን። እኔም አዲስ የፌስቡክ አካዉንት ከፍቼ ሀይማኖታዊ ፅሁፎችን መልቀቅ ጀምሬያለሁ። ከቀን ወደ ቀን አንባቢዎቼም እየበዙ እየሄዱ ነዉ። ኢንተርኔት የምንጠቀመዉ ቢሮ ባሉት ኮምፒዩተሮች ነዉ። በርግጥ ሰዓት እንዳይሻማብኝ እኔ አልጠቀምም። በወረቀት ፅፌ ለነኡስታዝ ሰጥቼያቸዉ እነሱ ናቸዉ በኮምፒዩተር ፅፈዉ ፌስቡኬ ላይ የሚለጥፉት። እኔ በሳምንት እሁድ ባየዉ ነዉ። ህይወት በመማር እና በማስተማር ታጥራ ነጎደች። መርከዝ ከገባሁ አመት ከአራት ወር አለፈ። አምሪ በየሳምንቱ ከራቀም በአስራአምስት ቀን እየመጣች ትጠይቀኛለች። ዛሬ ወደ መርከዝ መጥታ ትንሽ ከተጨዋወትን በኋላ "ሀቢቤ አሁን ታዋቂም እየሆንክ ነዉ! አሪፍ ሚስት ታገኛለህ! እስከአሁን አግባኝ ያለችህ የለችም?" አለችኝ። እየሳቅኩ "ኧረ በሽ ናቸዉ ትንሽ በትምህርቱ ልግፋ ብዬ ነዉ እንጂ ስጨርስ ሰብሰብ አድርጌ አገባቸዋለሁ!" አልኳት።  አምሪ ወዲያዉ ኮስተር እንደማለት አለችና "ለምን ዛሬ ሰብስበህ አታገባቸዉም ከፈለግክ!?" ብላ እየተበሳጨች ትታኝ ሄደች። የሚያስከፋ ነገር የተናገርኳት አይመስለኝም። ለምን ተናደደች? ግራ ተጋባሁ። አምሪ ከዚህ ቀን በኋላ በሳምንቱም ወደ መርከዝ አልመጣችም። በአስራአምስተኛዉ ቀን በጣም ናፍቃኝ ብጠብቅም ሳታስጠራኝ ቀረች። በሶስተኛዉ ሳምንት ሳትመጣ ስትቀር ሀጂን "አምሪ ሰላም ናት?" ብዬ ጠየቅኳቸዉ። እየተገረሙ "እሁድ ልትማር ስትመጣ አትዘይርህም እንዴ?" አሉኝ። "ድሮ ሰላም ሳትለኝ አትሄድም ነበር። ይሄን ሶስት ሳምንት ግን ጠፍታለች።" አልኳቸዉ። ሀጂ "ያዉ ህክምና ስለምትማር ምናልባት ፈተና በዝቶባት ይሆናል።" አሉኝ። ትንሽ ተናደድኩ። እኔን አስር ደቂቃ ለማናገር እንዴት ጊዜ ታጣለች? እኔ የሚያስከፋ ነገር አልተናገርኳትም። ካስከፋኋትም ቢያንስ ጥፋቴን ነግራ ልታርመኝ ትችል ነበር። በቀጣዩ ሳምንት ንዴት እና ናፍቆት ተቀላቅሎብኝ ብጠብቃትም ቀረች። የኡስታዝን ስልክ ተዉሼ ደወልኩላት። ስልኩን ባታዉቀዉም አነሳችዉ። "ሄሎ አምሪ!" አልኩ። ምንም ምላሽ የለም። ስልኩን ዘጋችዉ። አምሪን ያስኮረፋት ምን እንደሆነ መገመት ጀመርኩ። ሰሚራ ፍቅረኛዬ እያለች አብረን እንደተኛን ነግራት ይሆን? ሰሚራ ለራሷም ክብር አይጠቅማትም አትነግራትም! ፌቨን ተበሳጭታብኝ ነግራት ይሆን እንዴ? ፌቪ ህይወቴን መበጥበጥ ብትፈልግ ኖሮ ለረመዳን በአካል የተገናኙ ጊዜ ልትነግራት ትችል ነበር! እሷም አትሆንም! ታዲያ ማነዉ? በጣም ጨነቀኝ።

“እና በረንዳ ላይ ሆነሽ ነው ምታወሪኝ” “አዋ” “ለምን አትገቢም” “ሳወራህ ይሰሙኛላ ቤት” “እና በኃላ ብርድ ቢመታሽስ” “እሱን ተወውና ዛሬ ጨረቃ ግማሽ ነች እኮ” “ቀሪዋ ግማሽ በረንዳ ላይ ቆማ ነዋ”

photo content

🧡በምንም ሁኔታም ሆነ በማንም ሰው ምክንያት መራራ በመሆን አታባክኗት! የቀኑ መልካም ጎን ላይ በማተኮር አጣጥሟት!      #ፏ_ያለ ቀን 💚

😘እሷ ~ በአመት 365 ቀናት እና ሌሊቶች  ስላንተ ያላሰብኩበት ጊዜ የለም ፍቅር ነው አይደል ውዴ?? 🥴እሱ ~ አረ ይሄማ ካላንደር ነው

#👨‍🦳 አባት : 1+1 ስንት ነው? # 👶ልጅ: 11   አባትየው "መልሱ ሁለት ነው " ብሎ ቢያስረዳው ልጁ ገገመ። በዚህ ሰአት የተናደደው አባት " ሂድና 2 ብስኩት ገዝተህ ና " አለና ሱቅ ላከው ።ልጁ ከሱቅ ሲመለስ #👨‍🦳 እባት: በል አሁን አንዱን ብስኩት ለኔ          አንዱን ደሞ ለእህትህ ስጣት #👶 ልጅ: እንዴ ለኔስ??? # 👨‍🦳አባት: ዘጠኙን ብስኩት ብላ  😜 ♡ ㅤ     ❍ㅤ       ⎙ㅤ     ⌲             ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ    ˢᵃᵛᵉ       ˢʰᵃʳ

አንገቴን ደፍቼ "ሰሙ ዛሬ እንደትናንት አይደለሁም። ትናንት ባለማወቅ ህይወትሽን አመሰቃቅያለሁ። በአላህ ይሁንብሽ ይቅር በይኝ!" አልኳት። ሰሚራ ዝም ካለች በኋላ እያለቀሰች "ሀቢብ ትናንት የገፈፍከዉ ክብሬ ሊመለስ የሚችል አይደለም። ባሌ ድንግል አለመሆኔን ካወቀ ጀምሮ በትንሽ ነገር በተጣላን ቁጥር እያነሳ ያሸማቅቀኛል። ሁሌም በሀፍረት ነዉ ኑሮዬ! በሰዉ ዘንድ እንዲህ ካሸማቀቀኝ አላህ ዘንድ እኔንጃ!" አለች። እንባዋ ፊቷን ሸፍኖታል። በራሴ ተሸማቀቅኩ። ሳግ ድምፄን እያነቀዉ "ሰሚራ ለሁሉም ነገር ጥፋተኛዉ እኔ ነኝ።ህይወትሽን አበላሸሁ። ፀፅቶኛል። ሰላም እያጣሁ ነዉ። ቢያንስ ይቅር በይኝ።" አልኳት። "አላህ ይቅር ይበለን።" አለችና እንባዋን እየጠረገች  "እኔም ከፈጣሪዬ ምህረትን ፈላጊ ነኝ። ይቅር ብዬሀለሁ።" አለችና ባለሁበት ትታኝ ሮጥ እንደማለት እያለች ወደ ቤቷ ሄደች። ዉስጤ በሰራሁት ወንጀል ሲደማ ተሰማኝ። ምን አይነት ጨለማ ዉስጥ ነበርኩ? . የተሰጠን እረፍት ሲያልቅ ወደ መርከዝ ተመለስኩ። መርከዝ ሀይማኖታዊ ትምህርት የምንማርበት ተቋም ነዉ። ወደ መርከዝ ስመለስ ዉስጤ ላይ ትልቅ አላማ ተፈጠረ። በመሀይምነቴ ያበላሸኋቸዉን ህይወቶች መጠገን ባልችልም በደንብ ተምሬ ንፁሀን እንዳይበላሹ መንገዱን ማሳየት! አዎን በጣም ማወቅ አለብኝ ፤ አዉቄም ህዝቡን ማሳወቅ! የኔ አይነቱ እንዳያጠፋቸዉ ሚስጥሩን ማዉጣት! ከተሳካልኝ ደግሞ አምሪን ማግባት! . ወደ መርከዝ ከተመለስኩ በኋላ ህይወቴ ሁሉ ትምህርቴ ሆነ። ከትምህርት ሰዓታት ዉጪ ሳይቀር ኡስታዞቹን እያስቸገርኩ ተጨማሪ ሰዓት የተለያዩ ትምህርቶችን እማራለሁ። የሁለተኛዉ መንፈቀ አመት ትምህርት ተጀምሮ ሁለት ወራት አለፉ። እሁድ ነዉ። በጠዋቱ የትምህርት ቤቱ ግቢ ዉስጥ ከተማሪዎች ጋር ሆነን የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እየሰራን ነዉ። ነስሩ ፑሽአፕ እየሰራ ያስቆጥረኛል። ከኔ እኩል ለመስራት እየተፍጨረጨረ ነዉ። እላዩ ላይ እጄን ጭኜ መሬት ላይ ጣልኩትና እየሳቅኩ ወደ መኝታ ክፍል ሄድኩ። ወደ መኝታ ክፍል እየሄድኩ መተላለፊያ ላይ ስደርስ አዳራሽ ከምንለዉ ክፍል በጣም በሚያምር ድምፅ ቁርዓን ሲነበብ ሰማሁ። አህመድ ነበር። ገና አስራስድስት አመቱ ነዉ። ቁርዓን ሲያነብ በጣም ያለቅሳል። አሁንም እያለቀሰ ነዉ። የአዳራሹን በር ከፍቼ ገባሁ። አህመድ እየተንሰቀሰቀ ነዉ። ጀርባዉን ስለሰጠ አያየኝም። አህመድ "አለም የዕኒለዚነ አመኑ አንተኽሸዓ ቁሉቡሁም ሊዚክሪላህ?" የሚለዉን የቁርዓን አንቀፅ እየደጋገመ እያነበበ ያለቅሳል። ሰዉነቴ ተንዘፈዘፈ ፣ አይኔን እንባ ሸፈነዉ። በእንባዬ ዉስጥ ብዥታ ይታየኛል። አህመድ ያነበበዉ የቁርዓን አንቀፅ ተቀራራቢ ትርጉሙ "እነዚያ በአላህ ያመኑ ሰዎች ለጌታቸዉ ግሳፄ ልባቸዉ የሚፈራበት ጊዜ አልደረሰምን?" የሚል ወቀሳ አዘል ተግሳፅ ነዉ። ሰዉነቴ እየተንዘፈዘፈ "ደርሷል ጌታዬ!" አልኩ። ትናንት ሳልፈራ የተዳፈርኳቸዉ ወንጀሎች ሁሉ ፊቴ ተደቀኑ። አህመድ መንሰቅሰቁን ትቶ ዞሮ አየኝ። ሰዉነቴ ከብዶኝ እንሰቀሰቃለሁ።  ከተቀመጠበት ተነስቶ መጣና አቅፎኝ መንሰቅሰቅ ጀመረ። ተላቅሰን ስንጨርስ ልብሴን ለመቀየር ወደ መኝታ ክፍል ሄድኩ። ላይመለሱ ያጠፋኋቸዉ የሰዉ ህይወቶች መረጋጋት ነሱኝ። ሰላም ፣ ሰሚራ እና ፌቨን! ህይወታቸዉን የቀማኋቸዉ ሚስኪን እንስቶች! . ይቀጥላል... .

Fuad Muna (Fuya): የማይፋቅ ስህተት ክፍል አስራሁለት (ፉአድ ሙና) . ከኦፊስ ቀጥታ ወደ መስጂድ ሄጄ ሰገድኩና ጌታዬን ተንሰቅስቄ ምህረቱን ለመንኩት። አምስቱን ወር በሙሉ የወንጀልን ምንነት ጠንቅቄ ብማርም አንድም ቀን የራሴ ወንጀል ታይቶኝ አያዉቅም ነበር። በህይወቴ ያበላሸኋቸዉ ህይወቶች ሰላም ነሱኝ! ከስንቱ ጋር አንሶላ እንደተጋፈፍኩ ሳስበዉ ሰቀጠጠኝ። ወንጀሌ ምንም ቢገዝፍ የፈጣሪዬን ይቅርታ አይሸፍነዉም ብዬ ተንሰቀሰቅኩ። ከመስጂድ እንደወጣሁ በቀጥታ ወደ ቤት ሄድኩ። ገና ስገባ አምሪ በታብሌት የሆነ ስዕል ያለበት ነገር እያነበበች "እሺ የኔ ማፍያ ትተኸኝ ሄድክ አይደል?" አለች። ታብሌቱን እየተቀበልኳት "ምን እያነበብሽ ነዉ?" አልኳት። "ባክህ 'ስላይድ' ነዉ። ግቢ የምንማርበት ነዉ።" አለችኝ። ዘግቼ መለስኩላትና "ኡሚ አትጋብዘንም እንዴ?" አልኳት። ከተቀመጠችበት እየተነሳች "አንተ እስከምትመጣ እየጠበቅንህ ነበር። መጥታለች። መኝታ ቤት ናት!" አለችኝና በደንብ እያየችኝ "ደሞ ጀለቢያህን አዉልቀህ በሱሪ የት ሄደህ ነዉ?" አለችኝ። "እነሚኪ ጋር ሄጄ ነዉ!" አልኳት። አምሪ እንደመሳቅ እያለች "ሀቢቤ ከዚህ በፊት የሰራኸዉ ወንጀል ከፀፀተህ ወንጀል ወደሰራህበት ቦታ መመላለስ አታብዛ! ድጋሚ ወንጀል ላይ ይጥልሀል!" አለችኝ። አምሪ ትሰልለኝ ይሆን እንዴ ብዬ መጠርጠር ጀምሬያለሁ። ወንጀል ወደሰራሁበት ቦታ እንደሄድኩ እንዴት አወቀች? ከነሚኪ ጋር ስላልኳት ይሆን? እኔንጃ! . አምሪ በግድ ሱሪዬን አስወልቃ ጀለቢያ አስለበሰችኝ። ሴት ያዘዘዉ ሆኖብኝ ጀለቢያ ለብሼ ከወ/ሮ ለይላ እና ከአምሪ ጋር ሰፈራችን ወዳለ ታዋቂ ሬስቶራንት ሄድን። አዝዘን እንደተቀመጥን አንድ ወንድና አንድ ሴት ወደ ሬስቶራንቱ ገብተዉ ወደኛ ጠረጴዛ መጡ። ሲቀርቡ ወንዱን አወቅኩት የኛን ቤት የተከራየዉ ሰዉዬ ነዉ። ሴቷ ሚስቱ መሰለችኝ። መጥቶ እኔን ጨበጠኝ። ልጅቷ ደግሞ እነአምሪን እያቀፈች ሰላም አለቻቸዉ። ልጅቷን ትክ ብዬ ሳያት ድንጋጤ መላ ሰዉነቴን ወረረዉ። አቀረቀርኩ። ሰሚራ ነበረች። የድሮ ፍቅረኛዬ! አንሶላ የተጋፈፍኳት! አግብታለች! ሲገርም! እንዴት ባልጠፋ ቤት የኛን ቤት ተከራዩ!? ከአምሪ እና ከወ/ሮ ለይላ ጋር አዉርተዉ እስኪጨርሱ ቀና አላልኩም። ሲሄዱ ቀና ብዬ አምሪያን አየኋት! እየሳቀች ነዉ። ከዚህ በፊት "የናንተን ቤት የተከራዩትን ሰዎች ታዉቃቸዋለህ ወይ?" ብላኝ ነበር። እማዬን ስናስታምም አምሪ የሰሚራን ፎቶ ከቁምሳጥኔ ዉስጥ አግኝታ አይታዉ ነበር። የሰሚራ ባል ይገባዉ የነበረዉን የሰሚራን ክብር እኔ እንደገፈፍኩት ቢያዉቅ ምን ይል ይሆን? ድንግል እንዳልሆነች ሲያዉቅ ምን ብሏት ይሆን? በራሴ ተሸማቀቅኩ። . በልተን እንደጨረስን ወደ ቤት ተመለስን። አምሪ ወ/ሮ ለይላ ክፍላቸዉ ሲገቡ ጠበቀችና "ሀቢቤ ልጅቷን አስታወስካት?" አለችኝ። በአዎንታ ጭንቅላቴን ነቀነቅኩላት። "እኔ እኮ ያየኀት መስሎኝ ነበር። ዛሬ ገና ነዉ እንዴ ያየኀት?" አለችኝ። ከሰሚራ ጋር ያደረግነዉ ሁሉ አይኔ ላይ ድቅን እያለብኝ "ኧረ ዛሬ ነዉ ያየኋት።" አልኩ። "ምክንያቱን ባላዉቅም ብዙ ጊዜ ከባሏ ጋር ይጣላሉ።" አለችኝ። እኔ ግን ምክንያቱን መገመት አልከበደኝም። ምንም በደሌ ጣራ ቢነካም ሰሚራን ይቅርታ ለመጠየቅ አሰብኩ። አምሪ ፍቅረኛዬ እንደነበረች ልትገምት እንደምትችል ግልፅ ነዉ። ከሷ ጋር ከእንስሳ በታች ሆኜ እንደማዉቅ አምሪ ብታዉቅ ምን ትለኝ ይሆን? . በነጋታዉ ከፌቪ ጋር ተቀጣጥረን ነበር። ግን አምሪ ወንጀል የሰራሁበት ቦታ መመላለሴ ወንጀል ላይ ሊጥለኝ እንደሚችል የነገረችኝ ሀቅ ስለሆነ ላላገኛት አሰብኩ። ደሞ ያመሰቃቀልኩትን ህይወቷን ለማስተካከል መሞከር አለብኝ። ለጥቂት ደቂቃ አግኝቼያት ለመመለስ አሰብኩና ጠዋት ወደ አራት ሰዓት አካባቢ ወደ ኦፊስ ሄድኩ። ሀሳቤ ኦፊስ ሆኜ ልደውልላት ነዉ። ስገባ ፌቪ ፣ አብነት ፣ ከሪም ፣ ሚኪና አንድ የማላዉቃት ልጅ ክፍሉ ዉስጥ ተዘርረዋል። ሚኪና ያላወቅኳት ልጅ ተቃቅፈዉ ተኝተዋል። የሚኪም የሷም ሱሪ ወልቋል። ከሪም የአብነት ደረት ላይ ተመቻችቶ ተኝቷል። ፌቪ ሸሚዟ ቁልፉ ተከፋፍቶ ፀጉሯ ተንጨባሮ ተዘርራለች። ክፍሉ ዉስጥ የቢራ ጠርሙሶች ወዳድቀዋል። በፌቪ በኩል ትዉከት ትራሱን አጨማልቆታል። ክፍሉ በጣም በሚቀፍ ጠረን ታምቋል። እኔን ከነሱ ዉስጥ እንደዚህ ከመዝቀጥ ያተረፈኝን ጌታዬን አመሰገንኩት። ከክፍሉ ልወጣ ስል አብነት አይኑን እያሸ "እንዴ ሀቢቤ! ግቢ! ግቢ!" አለና ከሪምን ከደረቱ ገፍትሮ ቀሰቀሰዉ። ሁሉም ተነሱ። ፌቪ ተነስታ ሸሚዟን ቆላልፋ ወደኔ መጣች። ልትስመኝ ስትሞክር ከለከልኳት። "ኤጭ ሙድህ አይነፋም!" ብላ አልጋዉ ላይ ተቀመጠች። ሚኪና ልጅቷ ተነስተዉ ሱሪያቸዉን ለባበሱ። ሚኪ አይኑን እየጠራረገ "ሀቢቤ ተዋወቃት! አዲሷ ህይወቴ ናት!" አለኝ። ህይወቷን ሊቀማት ህይወቴ ሲላት አሳቀኝ። ልጅቷ ፍልቅልቅ እያለች  "ኤልዳና እባላለሁ" አለችና እጇን ዘረጋችልኝ። እጇን እያየሁ "ይቅርታ ይለፈኝ!" አልኳት። ሚኪ እየሳቀ "ሀቢቤ ግን አክራሪ ሆነሻል!" አለ። ፌቪ "ዉጡ ዛሬ ኦፊሱ የኔና የሀቢቤ ነዉ!" አለች። ከሪምና አብነት የፈጣሪ ትዕዛዝ ይመስል ወዲያዉ ብድግ አሉ። ብሽቅ እያልኩ "ተቀመጡ! ምነዉ ለደህና ነገር እንዲህ በሮጣችሁ!" አልኳቸዉና ወደ ፌቨን ዞሬ "ክለብ አትዉጪ! አትጠጪ! አላልኩሽም ለምን ጠጣሽ?" አልኳት። ፌቪ ፈገግ እንደማለት አለችና "ሀቢቤ ማስተካከል የማበላሸትን ያህል ቀላል አይደለም እኮ! በአንዴ እኔን ሁኑ ትላለህ እንዴ! ዛሬ አብረኸኝ ከተኛህ ልስተካከል! ትተኛለህ?" አለችኝ። ንዴቴ እየተቀጣጠለ "አልተኛም!" አልኳት። ፌቪ ከመቀመጫዋ ተፈናጥራ ተነሳችና "ገና ከመጀመሪያዉ ገብቶኛል! አታፈቅረኝም! አታስመስል! ያበላሸኸዉ እኔነቴ አሳዝኖህ ከሆነ ተወኝ! መመለስ የማልችላቸዉ ብዙ ነገሮቼን አሳጥተኸኛል! ሲፈልግህ የፈጣሪ በግ ሲሻህ የሰይጣን ፈረስ አድርገህ የምትጠፈጥፈኝ ጭቃ አይደለሁም!" አለችኝ። "ምናለ የፈጣሪ በግ ሳደርግሽ ከምትነቂ የሰይጣን ፈረስ ሳደርግሽ በነቃሽ" አልኩ በልቤ። ፌቪ ተነስታ መጥታ "ደስ ሲልህ ልትተወኝ አትችልም!" አለችና ልትስመኝ ታገለች። ገፍትሬ አልጋዉ ላይ ወረወርኳት። እልህ እየተናነቃት ተንደርድራ ልትስመኝ ተመልሳ መጣች። በጥፊ አልጋዉ ላይ ዘረርኳት። እነሚኪ መሀል ገብተዉ ያዙን። ፌቪ እያለቀሰች "ሀቢቤ አትተወኝ እንደ ድሮዉ ሁንልኝ!" አለች። ላስተካክላት ብል እራሴን ወደ ዝቅጠት ልመልስ ማለቴ እንደሚሆን ስለገባኝ ቤቱን ለቅቄ ወጣሁ። . ወደ ቤት እየተመለስኩ በማይመለስ መልኩ ያበላሸኋቸዉን ህይወቶች አሰብኩ። ፌቪ ምንም የማታዉቅ የቤት ልጅ ነበረች። ዛሬ እኔ በለኮስኩት እሳት ክብሯን ተነጥቃ መጠጥ የሚሉት እርኩሰት ላይ ወደቀች። ትምህርቷን አቋረጠች።  አሁን እኔ ማነኝ? ብዙዎችን ያቆሸሽኩ ንፁህ? አላዉቅም። ወደ ሰፈር ስደርስ ሰሚራ ከሱቅ እቃ ገዝታ ስትመለስ ተገጣጠምን። ባላየ ልታልፈኝ ስትል "ሰሙ አንዴ ላናግርሽ!" አልኳት። ቆመች። ተጠጋኋት።

oQgwpOGTeIqGoilDIUIAWuGXLxeAEC7ACIdkAe.mp37.13 KB

ህመም....
ቀይስ የለይላን መታጨት በሰማበት ጊዜ የተሰማው ስሜት እሱ ነው ህመም ማለት!💔  

🏪#የስራ ቅጥር #ማስታወቂያ 🏦 👱‍♀ የስራ አይነት - ፀሀፊ       ፆታ - ሴት       እድሜ -  20-28      ልምድ -  0 አመት      የስራ ሰአት - በቀን 5 ሰአት      ደሞዝ - 8000ብር 👨‍💼ፆታ - ወንድ     እድሜ -  20-25     ልምድ -  20 አመት    የስራ ሰአት - በቀን 14 ሰአት እንስሳትን ማውራት የሚችል, በ1ኛው እና በ2ኛው የአለም ጦርነት የተሳተፈ እና ቢያንስ 5ሰው የገደለ, 2ጎል በአለም ዋንጫ ላይ ያስቆጠረ, በአክሱም እና በላሊበላ ግንባታ ላይ የተሳተፈ 🤝          - ከሂትለር ጋ ሰልፊ ፎቶ ያለው ✊         - ዳይኖሰር የጋለበ💪         - የማቱሳላ ጎረቤት የነበረ🦾         -ደሞዝ - 4000 ብር

አቧራን የጠገበ ምንጣፍ የምትመታው አቧራውን ለማራገፍ  እንጂ ምንጣፉን ለመግዷት አደለም ... የሰውን ድክመት  የምትነግረው  ስህተትን እንዲያርም እንጂ በስህተቱ ተስፋ እንዲቆርጥ  አይደለም👌

ቁርአን 🌷
መልካም አዳር 🫀

መኪና እየነዳህ ሰው ሰላም ካልክ ጉረኝነት ነው ዝም ብለክ ካለፍክም #ጉረኝነት ነው አልሃምዱሊላህ መኪና የለኝም😁

#እሷ:- ሚስትና ልጆች እንዳሉህ ለምን አልነገርከኝም #እሱ:- አይናፋር ነኝ ማሬ😔😔😔

እኔ በአደኩበት ቦታ ፍቅር በአፍ አደለም ሚነገረው ይታያል ነው እኔን የሚወደኝ እናቴ አባቴም ጓደኞቼም አይነግሩኝም ምን ያህል እንደሚወዱኝ እንደሚጨነቁልኝ በአይናቸው ነው ሚያስታውቀው ለኔ በሚሆኑት ነገር

ፍቅር ማለት❤

አሰላሙአለይኩም ቤተሰብ
ጁምዓ ተሰገደ ወይ?