ru
Feedback
⛪️ማዕደ ኦርቶዶክስ

⛪️ማዕደ ኦርቶዶክስ

Открыть в Telegram

በዚህ ቻናል ፈቃደ እግዚአብሔር ከሆነ አጠቃላይ የቤተክርስቲያን አገልግሎቶች ግጥሞች ዜማዎች ቅኔዎች እንዲሁም የመፅሀፍ ቅዱስ ቃል ይለቀቅበታል።

Больше
782
Подписчики
+224 часа
+107 дней
+1530 день
Архив постов
ጸጥታን እና ዝምታን ቤትህ እና ጓደኛህ አድርጋቸው፤ እንደ መላእክት ያደርጉሃልና፤የመንፈስ ቅዱስም ማደሪያ ትሆናለህ። መጽሐፈ ገነት ዘውእቱ ዜና አበው

2. አርዮስ እና አርዮሳዊነት( Arianism) 🤦‍♂️አርዮስ ከእርሱ በፊት የተነሣው ሰባልዮስ የተባለው መናፍቅ የአካላዊ ቃልን ቀዳማዊና ራሱን የቻለ ህልውና ክዶ አንዱ እግዚአብሔር በሆነ ዘመን የተገለጠበት የመገለጫ መንገድ (Modes of Divine Manifestation ) ብቻ ነው የሚል ክህደት ይዞ ተነሥቶ ብዙ ሞኞችን ሲያስከትልና ግራ ሲያጋባ ነበር። 🗣ይህን የሰባልዮስን ኑፋቄ በመቃወምና አጸፋዊ መልስ ለመስጠት አካላዊ ቃል የራሱ የሆነ ህልውና አለው በማለት የተነሣው አርዮስ ወልድ ዋሕድ ኢየሱስ ክርስቶስን በአብ የተፈጠረ ነው (ሎቱ ክብር ወስብሐት አምልኮ ወስግደት) በማለት ለሰማይ ለምድር የሚቀፍ ክህደት ተናገረ። 🤔 አርዮስ በድፍረት ኢየሱስ ክርስቶስን በባሕርዩ ከአብ ጋር አንድ ያልሆነ ከአብ ያነሰ፣ ያነሰ ብቻ ሳይሆን እግዚአብሔር ሌሎች ፍጥረታትን ለመፍጠር ይጠቀምበት ዘንድ መጀመሪያ የፈጠረው ፍጡር ነው ይል ነበር።
👬 የአርዮስ ተከታዮች እና የእርሱን ኑፋቄ በተለያየ ደረጃ የጠጡት እነ መቅዶንዮስና መሰል መናፍቃን ወልድን እና መንፈስ ቅዱስን ግኖስቲኮች ከአምላክ እየወጡ ይመጣሉ እንደሚሏቸው ኤምኖች (Aems) አድርገው ይመለከቷቸው ነበር::
🧪 በዋናነት የአርዮስ ክህደት አካላዊ ቃል ኢየሱስ ክርስቶስን ከአብ አሳንሶ ማሳየቱ፣ ፍጡር ነው ማለቱ ነው። ይህ ወልድን ከአብ የማሳነስ የመጨረሻ የክህደት ጥልቀት (Subordinationism) አርዮስ ተከሎት የሄደው መርዝ ነበር፡፡ 🙈ይህ ወልድን ከአብ አሳንሶ ማሰብና ማስተማር በተሐድሶዎችም የሚታይ ኢየሱስ ክርስቶስን “ወንድሜ፣ ጓዴ፣..." የሚሉት አስተሳሰቦችና ሌሎችም ለመናገር የሚከብዱ ነገሮቻቸው ከአብ ጋር በባሕርይ አንድ መሆኑንና የባሕርይ አምላክነቱን በግልጽም ባይሆን በስውር ካለማመን የሚመነጩ ሰወር ያሉ አርዮሳዊነት (Latent Arianism) ናቸው፡፡ በቀጣይ ደሞ በአጭሩ ስለ ንስጥሮስ እና አስተምህሮ እንመለከታለን መ.ጽ
ክረምቱን ልክ እንደ አምና ዝም በማለት እንዲው በዋዛ ልታሳልፉት ነው። no no አንድ ወሩ እኮ እንደቀልድ አለቀ😩 2 ወር አለን በዛ ጊዜ ውዳሴ ማርያም እና ቅዳሴ በአጭር ጊዜ ተማሩ🥳። የፈለጋችሁትን የአብነት ወንጌል በግልም ሆነ በቡድን ለመማር DM አናግሩኝ🙏

እንኳን ለመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ልደት በሰላም አደረሳችሁ። በመወለዱ ብዙዎች ደስ ይላቸዋል 😘❤️

በዘመናት የነበሩ ዋና ዋና መናፍቃንና ኑፋቄያቸው በአጭሩ 1. ግኖስቲኮች (Gnosticism) 🐍 በ2ኛውና በ3ኛው መ/ክ/ዘ ቅድስትና ሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያንን ሲያውኳትና ሲፈትኗት የነበሩት መናፍቃን ብዙዎች ነበሩ፡፡ ¤ ከእነዚያ መካከል በተለይም ግኖስቲኮች የተባሉት አካሄዳቸው አደገኛ ነበር፡፡ --> ግኖስቲኮች “ቤተ ክርስቲያን ከክርስቶስ ትምህርት ርቃለች ኢየሱስ ክርስቶስ ካስተማረው ትምህርት ተቃራኒ የሆነ ሌላ እንግዳ ትምህርት ታስተምራለች' እያለ ይቃወሟትና ያብጠልጥሏት ነበር። 🐍 በዚህ ረገድ በግኖስቲኮች ዘንድ የነበሩት ዋና ዋና የስህተት ነጥቦች የሚከተሉት ናቸው:-
ብሉይ ኪዳንን (የሕጉን መጻሕፍት፣ የነቢያትን መጻሕፍት እና ይዘታቸውን) አምርረው መጥላታቸው ፣ ሌሎችን ሐዋርያት የኢየሱስን ትምህርት እንዳበላሹና እንደ ለወጡ አድርጎ ማሰብና ጳውሎስ የተላከው የእነዚያን ስህተት ለማስተካከል ነው ብለው ማሰባቸውና ማስተማራቸው ለዚህም መርቅያን ቅዱስ ጳውሎስን ምስክር አድርጎ (በተለይ የገላትያ መልእክቱን ለማሳየት መሞከሩ) ኢየሱስ ክርስቶስን ከደጉ አምላክ እየወጡ የሚመጡ ነጸብራቆች ወይም ብናኞች (Asons) አለ ይላሉና ከእነዚያ መካከል እንዱ አድርገው መቁጠራቸው ፣ ከቅዱስ ጳውሎስ መልእክታት ትምህርቶች ውስጥ ይደግፉናል የሚሏቸውን አንዳንድ ጥቅሶች ብቻ በማንጠልጠል ያን ቃል ወይም ዐረፍተ ነገር ከተባለበት ዳራና ርእሰ ጉዳይአንጻር መረዳትን ትተው ለራሳቸው አስተሳሰብ ደጋፊ አድርገው ለማቅረብ መታገል ነበሩ።
 በቀጣይ አርዮስ እና አርዮሳዊነት በአጭሩ እናያለን።
ክረምቱን ልክ እንደ አምና ዝም በማለት እንዲው በዋዛ ልታሳልፉት ነው። no no አንድ ወሩ እኮ እንደቀልድ አለቀ😩 2 ወር አለን በዛ ጊዜ ውዳሴ ማርያም እና ቅዳሴ በአጭር ጊዜ ተማሩ🥳። የፈለጋችሁትን የአብነት ወንጌል በግልም ሆነ በቡድን ለመማር DM አናግሩኝ🙏

✝ ሃይማኖት ምንድነው? 👉ሃይማኖት እግዚአብሔር ራሱን ለሰው ልጅ የገለጠው መገለጥ ነው። ሃይማኖት አንድ ጊዜ ከእግዚአብሔር የተሰጠ ነው። ✍የሰው ልጅ ሃይማኖትን ይቀበላል እንጂ ሃይማኖትን ሊሰራ ወይም ሊያሻሽል አይችልም።
የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፣ በሰማያት ያለው አባቴ እንጂ ሥጋና ደም ይህን አልገለጠልህምና ብፁዕ ነህ። ማቴ 16:15-17
👀ኑፋቄ ምንድነው? 🤏ኑፋቄ ማለት እግዚአብሔር የገለጠውን ሃይማኖት እንደ ምእመናን ሙሉ በሙሉ ሳይቀበሉ፣ እንደ ኢአማንያንም ሙሉ በሙሉ ሳይክዱ፣ የተወሰነውን ተቀብሎ ሌላውን ደግሞ አለመቀበል ወይም መጠራጠር ነው፡፡ 👥እንዲህ የሚያደርጉት ሰዎች ደግሞ መናፍቃን (ተጠራጣሪዎች) ይባላሉ፡፡ 👳‍♂ኢ አማንያን የሚባሉት ከመጀመሪያውም የክርስትና ሃይማኖትን ያልተቀበሉ ሲሆኑ መናፍቃን ግን ክርስቲያኖች ነን እያሉ ነገር ግን ከክርስትና አስተምህሮ ውስጥ ለራሳቸው አስተሳሰብና ምኞት የሚመቻቸውን ብቻ ተቀብለው ሌላውን የማይቀበሉና የሚጠራጠሩ፣ በእውነተኛው ትምህርት ፋንታም የራሳቸውን የፈጠራ ትምህርት የሚያስተምሩ ናቸው። በቀጣይ ደሞ በየዘመናቱ የነበሩ ምንፍቅናዎችን እንደዚህ በአጭሩ እናያለን🙏
ክረምቱን ልክ እንደ አምና ዝም በማለት እንዲው በዋዛ ልታሳልፉት ነው። no no አንድ ወሩ እኮ እንደቀልድ አለቀ😩 2 ወር አለን በዛ ጊዜ ውዳሴ ማርያም እና ቅዳሴ በአጭር ጊዜ ተማሩ🥳። የፈለጋችሁትን የትምህርተ ሃይማኖት በግልም ሆነ በቡድን ለመማር @barkchane አናግሩኝ🙏

<<የዝናም ኮቴው ተሰማ፡፡ ዝናም በሚዘንም ጊዜ የተራቡ ይጠግባሉ። የዝናም ኮቴው ተሰማ፡፡ ዝናም በሚዘንም ጊዜ ድሆች ይደሰታሉ፡፡ የዝናም ኮቴው ተሰማ፡፡ አምላካችን ለሰው ልጅ ዕረፍት ሰንበትን ፈጠረ፡፡ የዝናም ኮቴው ተሰማ፡፡ የዝናም ኮቴው ተሰማ፡፡›› ቅዱስ ያሬድ
በቤተክርስቲያናችን አስተምህሮ መሰረት ከ ሰኔ 26 - መስከረም 25 ድረስ ዘመነ ክረምት ይባላል። አከፋፈሉም
1ኛ ከሰኔ 26 እስከ ሐምሌ 18 ቀን ያለው ጊዜ በአተ ክረምት ወይም ዘርዕ፣ ደመና 2ኛ ከሐምሌ 19 እስከ ነሐሴ 9 ቀን ያለው ጊዜ መብረቅ፣ ነጎድጓድ፣ ባሕር፣ አፍላግ፣ ጠል 3ኛ ከነሐሴ 10 – 27 ቀን ዕጕለ ቋዓት፣ ደሰያት፣ ዓይነ ኲሉ 4ኛ ከነሐሴ 28 እስከ ጳጉሜን 5 (6) ቀን ጎህ፣ ነግህ፣ ጽባህ፣ ብርሃን፣ መዓልት 5ኛ ከመስከረም 1 – 4 ቀን ዮሐንስ 6ኛ ከመስከረም 8 – 14 ቀን ፍሬ 7ኛ ከመስከረም 15 - 25 ቀን ፀአተ ክረምት (የክረምት መውጫ) ወይም ዘመነ መስቀል።
ቅዳሴውም ከዕዝል ወደ ግእዝ ገብቷል ከሰኔ 14 እስከ መስከረም 25 ድረስ ግእዝ ነው ቅዳሴው።
አስተውል ስቡህ ተብሎ ማሕሌት ከተቆመ ወይም አመታዊ እና ወርሃዊ ክብረ በዓል 12, 21 እና 29 በሚሆን ቀን ሚቀደሰው ዕዝል ቅዳሴ ነው።
ይህ የክረምት ዘመን ክፉውን አረም ከህይወታችን ነቅለን የሃይማኖትን ዘር ዘርተን ምግባርና ፍቅርን የምናጭድበት ዘመን ያድርግልን።
ታዲያ የተለያዩ የአብነት ትምህርት በ online ልጆችንም እርሶም መማር ከፈለጉ አዋሩኝ። በግልም በቡድንም ውዳሴ ማርያም ዳዊት ቅዳሴ ዜማ ወንጌል ንባባት .... @barkchane

photo content

ሰሞኑን ከአንዳንድ መንፈሳዊ መጽሐፍ roughly አንዳንድ የተመቹኝ ሀሳቦችን ለናንተ ለቤተሰቦቼ እልካለሁ። በመጀመሪያ ዙር ከመድሎተ ጽድቅ መጽሐፍ እንጀምራለን። በመጀመሪያ አጠር ያለ ገለጻ ስለ መጽሐፉ አረግላቹሀለሁ። ከዛ ቦሀላ ስለቅ በምጻረ ቃል ነው ምጠቀመው ለምሳሌ መድሎተ ጽድቅ= መ.ቅ መድሎተ ጽድቅ(የእውነት ሚዛን) ደራሲ፦ ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ ገጽ፦ 519 የመጀመሪያ ዕትም፦ መጋቢት 2007 ይዘት፦ በዋናነት የፕሮቴስታንት "ተሐድሶ" አካላት የሚያነሷቸውን ጥያቄዎችና ክሶች መልስ ለመስጠት ያለመ ነው። እንደ "መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ" (Sola Scriptura) እና "በእምነት ብቻ" (Sola Fide) ያሉ የፕሮቴስታንት መሠረታዊ አስተምህሮችን በመጽሐፍ ቅዱስና በቤተ ክርስቲያን አበው ትምህርት ያጣጥላል። አከፋፈል፦ 6 ክፍሎች እና 10 ምዕራፎች አሉት
ምዕራፍ 1 መኃትው የተሐድሶ መነሻዎች በተለያዩ ዘመናት የነበሩ መናፍቃን እና ኑፋቄ በአጭሩ ክፍል 1 የመዳን ትምህርት ምሥጢራት(ጥምቀት ሜሮን ቁርባን) በእምነት መዳን እና በእምነት ብቻ መዳን ልዩነት ጾም ምጽዋት ቀኖና ክፍል 2 ስለ እመቤታችን ወላዲተ አምላክነት ክፍል 3 ስለ ቅዱሳን አማላጅነት በቅዱሳን ስም ቤተክርስቲያን መሰየም ክፍል 4 ስለ ምንኩስና እና ገዳማዊ ህይወት ክፍል 5 ስለ ፍትሐት ለሞቱ ወገኖች የሚደረግ ጸሎት እና ተዝካርና ዝክር ክፍል 6 ስለ ቅዱሳት መካናትን መሳለም ታሪኩ እና የቅዱሳት በዓላት
የጥንታዊ አባቶችን ብሉይን ሐዲስን ሊቃውንትን በማስረጃ ከሽኖ የተሐድሶን ሆነ የተለያዩ የሐሰት ትምህርቶችን የሚያከሽፍ መጽሐፍ ነው። ገዝታችሁ ማንበብ ምትፈልጉ ካላችሁ ገዝተን እንልካለን። N.B: ማንበብ አዋቂ ያረጋል። ስናውቅ ደሞ የምናመልከውን አምላክ የበለጠ እንወደዋለን።🙏

ሰሞኑን ከአንዳንድ መንፈሳዊ መጽሐፍ roughly አንዳንድ የተመቹኝ ሀሳቦችን ለናንተ ለቤተሰቦቼ እልካለሁ። በመጀመሪያ ዙር ከመድሎተ ጽድቅ

+++ "አንተ ግብዝ አስቀድመህ ከዓይንህ ምሰሶውን አውጣ::" ማቴ.7:5:: ምን ማለት ነው? ➺ በሃይማኖት ሕጸጽ ያለባቸው በበቂ መረጃ አትቃወሙ ማለት ነው? ➜ ቅዱስ አትናቴዎስ ሁሉም ሰው በአርዮስ ምክንያት ፊት ሲነሳው "ዓለም እውነትን ቢቃወምም እኔ ግን ከእውነት ጋር እሞታለሁ::" ነበር ያለው:: ➔ ወንጌል አንድምታ ግን በማቴ.7:5 ያለውን ሲተረጉም፦ ➾ ከጉባዔ ሳትውሉ፥ ምሥጢር ሳታደላድሉ እናስተምራለን አትበሉ:: እናስተምራለን ብትሉ ይፈረድባችኋልና:: ➥ ወንድምህን ላስተምርህ እንደምን ትለዋለህ? አንተ ሳትማር አታስተምር! አንተ ግብዝ ሳትማር?! ➬ አስቀድም አንተ ተማር፥ ዕወቅ ከዚህ በኋላ ወንድምህን ላስተምርህ ትለዋለህ ማለት ነው:: ➲ ታዲያ ኑፋቄን ኑፋቄ ከማለት ጋር ጥቅሱ ምን አገናኘው? ➣ ጥቅሱ የሚገልጸው ሳይማሩ እናስተምር የሚሉት ነው... ➜አንድም አንተ ንስሓ ሳትገባ ወንድምህን እንዴት ንስሓ ግባ ትለዋለህ?! አንተ ግብዝ አንተ አስቀድመህ ንስሐ ሳትገባ?!!

ገሀነመ እሳት ብርሃን የሌለው ጨለማ፣ የማይተኛ ትልና መታሰሪያ ያለበት እጅግ የሚያቃጥል ስፍራ ነው። በዚያም ረዳት የለም፤ ያለማቋረጥ ማልቀስና ጥርስ ማፋጨት ብቻ ነው። ኃጥአን በአንድነት የሚሰቃዩ ቢሆንም፣ በጨለማው ብዛት የተነሳ እርስ በእርስ መተያየት ስለማይችሉ ብቻቸውን የሆኑ ይመስላቸዋል። ስለዚህ ሁልጊዜ ይህንን እያሰቡ ከክፋት መከልከል ይገባል። ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

የማያቋርጥ ጸሎት ማለት በስራህም ሆነ በዕረፍትህ እግዚአብሔርን ማሰብ ነው። ቅዱስ ባስልዮስ አይ ሊቁ👏

አንተ ራስህ ጥረት የማታደርግና ወደ እግዚአብሔር የማትጸልይ ከሆነ እኔም ሆንሁ እግዚአብሔር ምሕረት ልናደርግልህ አንችልም! አባ እንጦንስ

ትዳር የሚደከምለት ነው፣ ፍቅር የሚደከምለት ነው እንጂ ሰጥቶ መቀበል አይደለም፣ ሲወዱን መውደድ አይደለም በክርስትና መቻል እንጂ መቻቻል የሚባል ነገር የለም። ርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን

ሠናይ ለክሙ ሠናይ ኦ አባግዐ መርዔቱ ለክርስቶስ በላዕክሙ ወጸገብክሙ ሰተይክሙ ወረወይክሙ በሰላም እትዉ ውስተ አብያቲክሙ እግዚአብሔር የሀሉ ምስለ ኵልክሙ
#ትርጉም መልካም ይሁንላችሁ(በደህና ሁኑ)የክርስቶስ የመንጋው በጎች በልታችሁ የጠገባችሁ፣ ጠጥታችሁ የረካችሁ በሰላም ወደእየቤታችሁ ግቡ(ተመለሱ)እግዚአብሔር ከሁላችሁ ጋር ይሁን። ቅዳሴ ዮሐንስ አፈወርቅ

ይቺን ቤት አብ አስቀድሞ መሰረታት ይቺን ቤት ወልድ አነጻት ይቺን ቤት መንፈስቅዱስ ጨረሳት ምልጣን ዘቅዱስ ያሬድ
በዓለም ሁሉ ላይ ስለ እመቤታችን ቤተክርስቲያን መታነጽ ምክንያት በዓል በሰላም አደረሳችሁ። ልዑል እግዚአብሔር በህይታችን ያሉ ያልተጀመሩ ነገሮች ለኛ በረከት ያላቸውን ዘወትር ወደሱ ሚያቅረበንን ነገር በሙሉ ያስጀምርልን። የተጀመሩትን በሙሉ በመልካም ባማረ እሱን በምንወድበት መንገድ ያስፈጽመን። መልካም በዓል

"አንደበቱን ከቧልት፣ ከሐሜት፣ ያየውንም ምስጢር ከመናገር የሚከለክል ሰው ልቦናውን ከኀልዮ ኃጢአት ያርቀዋል።" (አረጋዊ መንፈሳዊ)

ቅዱስ ዩሐንስ አፈወርቅ(- John Chrysostom) "አንድ ሰው በአብና በወልድ እንዲሁም በመንፈስ ቅዱስ በትክክል ቢያምን እንኳ ትክክለኛውን ሕይወት ካልመራ እምነቱ ለማዳን ምንም አይጠቅመውም። ኢየሱስ እንዲህ ቢልም፡- “እውነተኛ አምላክ ብቻ የሆንህ አንተን ለማወቅ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት (ዮሐ 17፡3) እኛን ለማዳን ቃሉን መናገሩ ብቻ በቂ እንደሆነ አድርገን አናስብም፤ ሕይወታችንና ምግባራችን ንጹሕ መሆን አለባቸውና። "

photo content

ሰላም ውድ የማዕደ ኦርቶዶክስ ተከታታዮች የሁላችንም ችግር የሆነውን የመጽሐፍ ቅዱስ የማንበብ ችግራችንን እንዲሁ አጫጫር ጣፋጭ ትምርህቶችን ለመስጠት አዲስ የ YouTube ቻናል ለመክፈት ስንጎዳጎድ ነበር። በቅርቡም video ምለቅ ይሆናል። አብረን መጽሐፍ ቅዱስን በአጭር ማብራሪያ እናነባለን። እስከዛ Youtube ላይ ማዕደ ኦርቶዶክስ( Orthodox Banquet ) ብላችሁ search በማረግ subscribe አድርጉ🙏 በአጭሩ ይሄንንም መጻፍ ትችላላችሁ @Ethiopian-canon አልያም በዚ link ቀጥታ ሄዳችሁ ታገኛላችሁ https://youtube.com/@ethiopian-canon?si=iBMa9Sxk0_zj0Kke N.B: በቅርብ ቀን አሐዱ ብዬ ለቅላቹሀለሁ። ለሁሉም ግን ፈቃደ እግዚአብሔር ይሁን።