fa
Feedback
⛪️ማዕደ ኦርቶዶክስ

⛪️ማዕደ ኦርቶዶክስ

رفتن به کانال در Telegram

በዚህ ቻናል ፈቃደ እግዚአብሔር ከሆነ አጠቃላይ የቤተክርስቲያን አገልግሎቶች ግጥሞች ዜማዎች ቅኔዎች እንዲሁም የመፅሀፍ ቅዱስ ቃል ይለቀቅበታል።

نمایش بیشتر
780
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-17 روز
+230 روز
آرشیو پست ها
ኢዮብ 22:27
ኢዮብ 22:27

ነገረ ድኅነት 🌴 የእምነት ምልክት የነበረችውን ዛፍ ቆርጦ በመብላት ከሐልዮ ወደ ገቢር በማሳደግ በተግባር ባረጋገጠ ጊዜ በዚያው ቅጽበት ከዚያ በፊት በባሕርዩ አብሮት ያልነበረ(ያልተፈጠረበት)፣ ነገር ግን በኃጢአቱ ምክንያት የሕይወት ምንጭ ከሆነው ከእግዚአብሔር የመለየቱ ውጤት የሆነ ብዙ ተደራራቢ ነገሮች ደረሱበት። እነዚህም
1. ሞት፣ ሟችነት 2. የባሕርይ መጎስቆል ደረሰበት 3. ስደተኛ ሆነ 4. ሰላም አጣ፣ ተጨነቀ 5. መንፈሳዊ እድገቱ ተቋረጠ፣ መቋረጥ ብቻም ሳይሆን ጉዞው በተቃራኒ አቅጣጫ ሆነ። 6. በአጠቃላይ እግዚአብሔር ሲፈጥረው ያዘጋጀለትን ጸጋና ክብር በሙሉ አጣ።

8. ማርቲን ሉተር 📆  በ16ኛው መቶ ዓመት በምድረ አውሮፓ የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያንን በመቃወምና በመገንጠል የፕሮቴስታንቲዝምን እንቅስቃሴ ያስከተለውን የማርቲን ሉተርን አስተምህሯዊ፣ ታሪካዊ እና ፖለቲካዊ ዳራዎችና ምንነቶች እዚህ ላይ በዝርዝርና በጥልቀት ባንመለከተቻውም መሠረታዊ የሆኑትን ጉዳዮች ብቻ በአጭሩ አንሥተናቸው እናልፋለን፡፡ 🙄ይህም ሉተርና እንቅስቃሴው ከራሱ ግለሰ ሰብእና ባሻገር በነበረበት ዘመን የነበሩት ሃይማኖታዊ፣ ፖለቲካዊ እና ማኅበረሰባዊ ነባራዊ ሁኔታዎች ዳራ የተፈጠሩ በመሆናቸው ነው፡፡ ሰብእናውም ከእነዚህ ነገሮች ተለይቶ ሊታይ አይቻልም፡፡ 📕ከአስተምህሮቶቹ መሀልም
የቅድመ ምርጫ ውሳኔ ጥንተ አብሶ መጽሐፍ ቅዱስን በራስ መተርጎም መዳን በእምነት ብቻ  ምንኩስና አያስፈልግም ወዘተ
መድሎተ ጽድቅ

የዕለቱ ወንጌል (ምንባብ ዘወንጌል) እናንብብ ሐምሌ ፳፫ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን የዮሐንስ ወንጌል ፲፱፥፴፩-፴፰ (ዮሐ 19፥31-38) አይሁድም የማዘጋጀት ቀን ስለ ሆነ ያ ሰንበት ትልቅ ነበረና ሥጋቸው በሰንበት በመስቀል ላይ እንዳይኖር፥ ጭናቸውን ሰብረው እንዲያወርዱአቸው ጲላጦስን ለመኑት። ጭፍሮችም መጥተው የፊተኛውን ጭን ከእርሱም ጋር የተሰቀለውን የሌላውን ጭን ሰበሩ፤ ወደ ኢየሱስ በመጡ ጊዜ ግን እርሱ ፈጽሞ እንደ ሞተ አይተው ጭኑን አልሰበሩም፤ ነገር ግን ከጭፍሮች አንዱ ጎኑን በጦር ወጋው፤ ወዲያውም ደምና ውኃ ወጣ። ያየውም መስክሮአል፤ ምስክሩም እውነት ነው፤ እናንተም ደግሞ ታምኑ ዘንድ እርሱ እውነት እንዲናገር ያውቃል። ይህ የሆነ፦ ከእርሱ አጥንት አይሰበርም የሚል የመጽሐፉ ቃል እንዲፈጸም ነው። ደግሞም ሌላው መጽሐፍ፦ የወጉትን ያዩታል ይላል። ከዚህም በኋላ አይሁድን ስለ ፈራ በስውር የኢየሱስ ደቀ መዝሙር የነበረ የአርማትያስ ዮሴፍ የኢየሱስን ሥጋ ሊወስድ ጲላጦስን ለመነ፤ ጲላጦስም ፈቀደለት። ስለዚህም መጥቶ የኢየሱስን ሥጋ ወሰደ። "በወልድ ያመነ የዘለዓለም ሕይወት አለው" መልካም ዕለተ ሐሙስ!! ፮ ኪሎ ግቢ ጉባኤ

1•  ምስጢረ ሥላሴ (Mystery of the Holy Trinity) የመጽሐፍ ቅዱስ መሰረት፡- “በአብ፣በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው አህዛብን ሁሉ አስተምሩ፡፡ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ አስተምሯቸው፡፡” ማቴ 28፡19 ➢ 2• ምስጢረ ሥጋዌ (Mystery of Incarnation) የመጽሐፍ ቅዱስ መሰረት፡- “ቃል ሥጋ ሆነ፤ በእኛም አደረ፤ ለአባቱ አንድ እንደ ሆነ ልጅ ክብር ያለ ክብሩን አየን፤ ጸጋንና እውነትን የተመላ ነው፡፡” ዮሐ 1፡14 ➢ 3• ምስጢረ ጥምቀት (Mystery of Baptism) የመጽሐፍ ቅዱስ መሰረት፡- “ያመነ የተጠመቀም ይድናል፤ ያላመነ ግን ይፈረድበታል፡፡” ማር 16፡16 ➢ 4• ምስጢረ ቁርባን (Mystery of the Holy Communion) የመጽሐፍ ቅዱስ መሰረት፡- “ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ የዘለዓለም ሕይወት አለው፡፡” ዮሐ 6፡54 ➢ 5• ምስጢረ ትንሳኤ ሙታን (Mystery of the Resurrection of the Dead) የመጽሐፍ ቅዱስ መሰረት፡- "ትንሳኤና ሕይወት እኔ ነኝ፡፡ የሚያምንብኝም ቢሞትም ይነሣል፡፡” ዮሐ 11:25

ስንክሳር ዘወርኀ ነሐሴ ፳፩ አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ነሐሴ ሃያ አንድ በዚች ቀን አምላክን በሥጋ የወለደች የእመቤታችን ድንግል ማርያም የበዓሏ መታሰቢያ ነው። እርሷ ስለእኛ ሁልጊዜ ትማልዳለችና። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን የሕይወትና የድኅነት ወደብ ትሆነን ዘንድ እርሷን እናቱን ስለሰጠን በረከቷም በሁላችን የክርስቲያን ወገኖች ላይ ይደር ለዘላለሙ አሜን።
ሰላም ለኪ ለዘእምኔኪ ወጽአ። ዘያድኅን እግዚእ እንስሳ ወሰብአ። በቍስለ ኃጢአት ሥጋየ አመ በኊበጐ ወጽአ። ኢረከብኩ ማርያም እንበሌኪ አሐደ ባቍዐ። እመ ኢገበርኪ ሊተ ሐዲሰ መልክዐ።

ማንም ሰው የሚናገር ቢሆን፥ እንደ እግዚአብሔር ቃል ይናገር፤ የሚያገለግልም ቢሆን፥ እግዚአብሔር በሚሰጠኝ ኃይል ነው ብሎ ያገልግል፤ ክብርና ሥልጣን እስከ ዘላለም ድረስ ለእርሱ በሚሆነው በኢየሱስ ክ
ማንም ሰው የሚናገር ቢሆን፥ እንደ እግዚአብሔር ቃል ይናገር፤ የሚያገለግልም ቢሆን፥ እግዚአብሔር በሚሰጠኝ ኃይል ነው ብሎ ያገልግል፤ ክብርና ሥልጣን እስከ ዘላለም ድረስ ለእርሱ በሚሆነው በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን። 1ኛ ጴጥሮስ 4:11

ወንድሜ፣ የሚከዱህ ሰዎች ከሕይወትህ ሲርቁ አትዘን፤ ፈጣሪ ወደ ተሻለ ቦታ ሲወስድህ አላስፈላጊ ሰዎችን ከመንገድህ ያስወግዳል። ከሚከዳህ ጓደኛ ይልቅ ብቸኝነት ይሻላል።

ኢየሱስም ገብርኤልም ያደናሉ ኢየሱስ በስልጣኑ ገብርኤል በኢየሱስ። ተምታቶባቹ አታምታቱብን
የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ፡ ይሰፍራል፥ ያድናቸውማል። መዝ 34:7
እንኳን አደረሳችሁ🙏

“ወዳጄ ሆይ፦ #የትዕቢት_መርዝ_ተጠራቅሞ_አብጦብሃልን? እንኪያስ ወደ ቅዱስ ሥጋዉና ክቡር ደሙ ቅረብ፤ ስለ ወዳጆቹ ሲል አርአያ ገብርን የነሣ ትሑቱ ጌታም ትሕትናን ያስተምርሃል፡፡ #የስግብግብነት_ትኩሳት_አስቸግሮሃልን? ወደ ቅዱስ ሥጋዉና ክቡር ደሙ ቅረብ፤ ደግነትንም ትማራለህ፡፡ #የምቀኝነት_ብርድ_አስቸግሮሃልን? እንኪያስ ወደ ሰማያዊው መዓድ ቅረብ፤ ምህረት ማድረግንም ገንዘብ ታደርጋለህ፡፡ #ትዕግሥትን_የማጣት_እከክ_ይዞሃልን? እንኪያስ ወደ ቅዱስ ሥጋዉና ክቡር ደሙ ቅረብ፤ ራስን መግዛትንም ገንዘብ ታደርጋለህ፡፡ በመንፈሳዊ ሕይወትህ ልል ዘሊል ብትሆን ይህን መንፈሳዊ መዓድ ተመገብና ብርቱ ትሆናለህ፡፡ #ቆሽሸሃልን? እንኪያስ ወደዚሁ መብልና መጠጥ ቅረብ ብዬ እመክርሃለሁ፤ ንጽሕናንም ገንዘብ ታደርጋለህ፡፡” ቅዱስ ቄርሎስ ዘእስክንድርያ

ተሰብሮ ይወጋይ የማይባል ምርኩዝ ተንዶ ያዳልጣል የማይባል የጸና ግንብ ከማዕበል ወጥተን የምናርፍበት ወደብ ኢየሱስ ክርስቶስ!

የአዳም የመጀመሪያውና ዋናው ኃጢአቱ (በደሉ) ቅጠል ቆርጦ መብላቱና አለመታዘዙ ሳይሆን እግዚአብሔርን አለማመኑ ነበር። አለመታዘዙ የመጣው ካለማመኑ ነበር፤ ማለትም አዳምን የፈጣሪውን ትእዛዝ ወደ መጣ
የአዳም የመጀመሪያውና ዋናው ኃጢአቱ (በደሉ) ቅጠል ቆርጦ መብላቱና አለመታዘዙ ሳይሆን እግዚአብሔርን አለማመኑ ነበር። አለመታዘዙ የመጣው ካለማመኑ ነበር፤ ማለትም አዳምን የፈጣሪውን ትእዛዝ ወደ መጣስና ሕጉን ወደ ማፍረስ የወሰደው በእግዚአብሔር ላይ የነበረው እምነት በዲያብሎስ ስብከት ከተለወጠ በኋላ ነበር:: መ.ጽ

ሚያስጨንቁህን አጋንንት ትተህ ሊረዱ ሚፋጠኑ መላእክት አስብ።

7. አርዮስ ዘሴባስቴ (Arius of Sebaste) 🤦‍♂️ ይህ አርዮስ ሌላ አርዮስ ሲሆን በፖንተስ ኤዎስጣቴዎስ ከተባለው የሴባስቴ ጳጳስ ጋር የነበረ ካህን ነበር፡፡ 🧩 መጀመሪያ ላይ በ360ዎቹ ዓ. ም. ገደማ የኤዎስጣቴዎስ ዘሴባስቴ የብሕትውና እንቅስቃሴ አካል ነበር፣ እርሱ ራሱም ተሐራሚ ባሕታዊ ነበር፡፡ 🧑‍🍳ሆኖም ወደ ኋላ ላይ ጾምን እና በዓመቱ ውስጥ ክርስቲያኖች ሁሉ በአንድነት የሚጸሙበት የታወቀ የጾም ጊዜ መኖሩን ይቃወም ነበር፡፡
በሰሙነ ሕማማት መጾምን ይቃወሙ ነበር፡፡ በሰንበተ ክርስቲያን በፈቃዳቸው ይጸሙ ነበር፡፡ የአይሁዳውያን ተረፍ ነው በማለት የትንሣኤን በዓል ማክበርን ይቃወም ነበር፡፡ እንዲሁም ለሙታን ጸሎት ማድረግንም ይቃወም ነበር፡፡
🤔 ቅዱስ ኤጲፋንዮስ ደግሞ አርዮሳዊም ነበር ይለዋል፡፡

ጥያቄ፩ኛ ተሰ.፭፥፲፮ ላይ "ሁል ጊዜ ደስ ይበላችሁ" ይላል። እንዴት ነው ዅል ጊዜ ደስ ሊለን የሚችለው? መልስ፦ ሁልጊዜ ደስ ሊለን የሚችለው ብንኖርም ለእግዚአብሔር የምንኖር፣ ብንሞትም ለእግዚአብሔር የምንሞት ከሆነ ነው። ሁሉ ለበጎ እንደሚደረግ ካወቅን ሁልጊዜም ደስተኛ እንሆናለን።

"ሰው ሆይ፦ እያንዳንዷን ድርጊትኽን የሚመለከት የሰማይ የምድር ንጉሥ እንዳለ ፈጽመኽ አትርሳ።" [ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ]

"የማርን ጥፍጥና ማርን ቀምሶ ለማያውቅ ሰው በመቅመስ እንጂ በቃላት ማስተማር እንደማይቻል ሁሉ የእግዚአብሔርን መልካምነት በቃላት በጠራ መልኩ ማስተማር አይቻልም። ራሣችን ወደ እግዚአብሔር መልካምነት ዘልቀን መግባት ይኖርብናል እንጂ።" ቅዱስ ባስልዮስ ታላቁ

ኃጢአት የለብንም ብንል ራሳችንን እናስታለን፥ እውነትም በእኛ ውስጥ የለም። በኃጢአታችን ብንናዘዝ ኃጢአታችንን ይቅር ሊለን ከዓመፃም ሁሉ ሊያነጻን የታመነና ጻድቅ ነው። ኃጢአትን አላደረግንም ብንል ሐሰተኛ እናደርገዋለን ቃሉም በእኛ ውስጥ የለም። 1ኛ ዮሐንስ 1:8

6. ቪጂላንቲየስ (Vigilantius) 🌓 ቪጂላንቲየስ በ4ኛው መቶ ዓመት ማብቂያና በ5ኛው መጀመሪያ ላይ የነበረ ቄስ ሲሆን ዋና ተቃውሞውም በሌሊት በቤተ ክርስቲያን የሚደረጉ የሊጦን፣ የማኅሌት እና የመሳሰሉትን ጸሎታት (Vigilis) ማድረግን አጥብቆ ይቃወም ነበር፡፡ 😴 አባ ሄሮኒመስ ቪጂላንቲየስን ግብሩ እንደ ስመ ሳይሆን በተቃራኒው ስለሆነ “ቪጂላንቲየስ - Vigilantius - ትጉሁ" መባሉ ቀርቶ "ዶርሚቲያኖስ -Dormitsamus - እንቅልፋም" ቢባል ይሻላል ያለው ለዚህ ነበር፡፡ ⛰ ከዚህም ጋር ለዐጽመ ቅዱሳን ክብር መስጠትን ይቃወም ነበር፡፡ ክርስቲያኖችን “ዐጽም አምላኪዎች"መተተኞች" እንዲሁም “ጣዖት አምላኪዎች" እያለ ይሰድባቸው ነበር፡፡ 🧑‍🍳 ቪጂላንቲያስ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ
የማታና የሌሊት ጸሎት ማድረግን አምርሮ ይነቅፍ ነበር:: ከዚህም ጋር ጾምን፣ ራስን መግዛትን፣ ድንግልናን፣ ንጽሕናን ሁሉ ይነቅፍና ይዘልፍ ነበር፡፡  ቅዱሳን የጸሟቸውን አጽዋማት ይቃወም ነበር፡፡
📕 መዝሙረ ዳዊት መጸለይ (መደገም) ያለበትም የተድላና የደስታ ቀናት በሆኑ በዓላት ቀን ብቻ መሆን አለበት ይል ነበር፡፡ በቀጣይ አርዮስ ዘሴባስቴ (Arius of Sebaste) እናያለን መ.ጽ