ሳሌም የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሚዲያ/ SALEM GURAGE DIOCESE MEDIA
Открыть в Telegram
ይህ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሳሌም የጉራጌ ሀገረ ስብከት የቴሌግራም ቻናል ነው።
Больше1 952
Подписчики
Нет данных24 часа
+67 дней
+1730 день
Загрузка данных...
Похожие каналы
Облако тегов
Нет данных
Возникли проблемы? Пожалуйста, обновите страницу или обратитесь к нашему support-менеджеру .
Входящие и исходящие упоминания
---
---
---
---
---
---
Привлечение подписчиков
июль '26
июль '26
+5
в 0 каналах
июнь '26
+63
в 0 каналах
Get PRO
май '26
+90
в 0 каналах
Get PRO
апрель '26
+93
в 0 каналах
Get PRO
март '26
+108
в 0 каналах
Get PRO
февраль '26
+82
в 0 каналах
Get PRO
январь '26
+81
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '25
+80
в 0 каналах
Get PRO
ноябрь '25
+61
в 0 каналах
Get PRO
октябрь '25
+44
в 0 каналах
Get PRO
сентябрь '25
+73
в 2 каналах
Get PRO
август '25
+187
в 0 каналах
Get PRO
июль '25
+38
в 1 каналах
Get PRO
июнь '25
+63
в 0 каналах
Get PRO
май '25
+27
в 0 каналах
Get PRO
апрель '25
+65
в 0 каналах
Get PRO
март '25
+111
в 0 каналах
Get PRO
февраль '25
+72
в 1 каналах
Get PRO
январь '25
+75
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '24
+57
в 0 каналах
Get PRO
ноябрь '24
+76
в 0 каналах
Get PRO
октябрь '24
+62
в 0 каналах
Get PRO
сентябрь '24
+43
в 0 каналах
Get PRO
август '24
+82
в 1 каналах
Get PRO
июль '24
+24
в 0 каналах
Get PRO
июнь '24
+28
в 0 каналах
Get PRO
май '24
+36
в 0 каналах
Get PRO
апрель '24
+18
в 0 каналах
Get PRO
март '24
+62
в 0 каналах
Get PRO
февраль '24
+79
в 0 каналах
Get PRO
январь '24
+159
в 2 каналах
Get PRO
декабрь '23
+45
в 0 каналах
Get PRO
ноябрь '23
+42
в 0 каналах
Get PRO
октябрь '23
+7
в 0 каналах
Get PRO
сентябрь '23
+17
в 0 каналах
Get PRO
август '23
+24
в 0 каналах
Get PRO
июль '23
+6
в 0 каналах
Get PRO
июнь '23
+29
в 0 каналах
Get PRO
май '23
+54
в 0 каналах
Get PRO
апрель '23
+69
в 0 каналах
Get PRO
март '23
+307
в 0 каналах
| Дата | Привлечение подписчиков | Упоминания | Каналы | |
| 04 июля | 0 | |||
| 03 июля | +1 | |||
| 02 июля | +3 | |||
| 01 июля | +1 |
Посты канала
+9
በጉራጌ ሀገረ ስብከት አዲስ ለተመረጡ የሰበካ ጉባኤ አባላት የአቅም መገንቢያ ሥልጠና ተሰጠ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የጉራጌ ሀገረ ስብከት፣ አዲስ ለተመረጡ የሰበካ ጉባኤ አባላት የሥራ አቅጣጫን የሚያመላክትና ግንዛቤን የሚያስጨብጥ ሰፊ የሥልጠና መድረክ አዘጋጀ። ሥልጠናው የተዘጋጀው አባላቱ በይፋ ወደ ተግባራዊ አገልግሎት ከመሰማራታቸው በፊት፣ ኃላፊነታቸውን በተገቢው መንገድ እንዲወጡና የአስተዳደር ሥራቸውን በዕውቀት እንዲመሩ ለማገዝ ታስቦ መሆኑ ተገልጿል።
በዚሁ መድረክ ላይ ከሀገረ ስብከቱ ሥር ከሚገኙ ልዩ ልዩ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት የተውጣጡ ከ300 በላይ አዲስ ተመራጭ የሰበካ ጉባኤ አባላት ተሳትፈዋል።
የሥልጠናው ይዘትም የቤተክርስቲያንን ሁለንተናዊ መዋቅርና ሌሎች አሠራር ያካተተ ሥልጠና መሆኑ ተገልጧል።
ይህ የአቅም ግንባታ መድረክ፣ አዲስ ወደ ኃላፊነት ለመጡት የአገልግሎት መሪዎች ትልቅ መነቃቃትን የፈጠረ ከመሆኑም በላይ፣ መጪውን የሥራ ዘመን በውጤታማነት ለመጀመርና ጠንካራ መሠረት ለመጣል ከፍተኛ ግንዛቤ ያስጨበጠ መሆኑ ታውቋል።
ሥልጠናው በብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ መመሪያ መሠረት በየ ጊዜ ለሚመረጡ የሰበካ ጉባኤ አባላት የሚሰጥ ሲሆን የዛሬው ለ5ኛ ጊዜ የተሰጠ ሥልጠና ነው።
| 2 | የሥራ ማስታወቂያ | 686 |
| 3 | Нет текста... | 732 |
| 4 | የምሁር ኢየሱስ ገዳም ብርሃን አፀደ ሕፃናት የዩኬጂ (UKG) ተማሪዎችን አስመረቀ።
ሰኔ 23/2018 ዓ.ም (ምሁር አክሊል)
በጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ የሚገኘው የምሁር ኢየሱስ ገዳም ብርሃን አፀደ ሕፃናት ትምህርት ቤት፣ ላለፉት ሦስት ዓመታት በቅድመ መደበኛ የትምህርት ዘርፍ ሲያስተምራቸው የነበሩ 61 የዩኬጂ (UKG) ተማሪዎቹን ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በተገኙበት አስመርቋል።
ተቋሙ በሕፃናት ዝግጅት ወቅት በዘንድሮው የትምህርት ዘመን በሁሉም ዘርፎች 181 ተማሪዎችን ተቀብሎ ሲያስተምር እንደነበር የተገለጠ ሲሆን በምረቃው ሥነ-ሥርዓት ላይ የተገኙት ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ዜና ማርቆስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ሓላፊ ሕፃናት በእውቀት፣ በሥነ-ምግባርና በመንፈሳዊ እሴቶች ታንጸው እንዲያድጉ የቤተሰብና የትምህርት ቤት የጋራ ጥረት ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው አስገንዝበዋል።
ብፁዕነታቸው ትምህርት ቤቱ ልጆችን በጥራት እያስተማረና በመልካም ሥነ-ምግባር እያሳደገ በመሆኑ የአስተዳደሩንና የመምህራኑን ትጋት አመስግነው፣ ለተማሪዎቹም በቀጣይ የትምህርት ጉዟቸው የላቀ ውጤት እንዲያስመዘግቡ መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።
የገዳሙ አብምኔት አባ ዘኢየሱስና በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የምሁር አክሊል ወረዳ ትምህርት ጽሕፈት ቤት ሓላፊ አቶ ሰብስብ ብርሃኑ፣ በብፁዕነታቸው መመሪያ ንግግር አድርገዋል።
በዕለቱ በተካሄደው የምረቃ መርሐ-ግብር ላይ በተማሪዎች የተዘጋጁ የግጥም፣ የዝማሬና የጥበባዊ ትዕይንቶች አቅርበው በብፁዕነታቸው፣ በወላጆች፣ በገዳሙ አባቶችና ጥሪ በተደረገላቸው እንግዶች ዘንድ ከፍተኛ አድናቆትን አትርፈዋል። በመርሃ-ግብሩ ተመራቂ ሕፃናት የምረቃ ምስክር ወረቀታቸውን ከብፁዕነታቸው እጅ ተባርከው ተቀብለዋል። | 731 |
| 5 | https://youtu.be/zFWgbFnO3lg?si=XHhh0udk4nGAIz_3 | 749 |
| 6 | Нет текста... | 968 |
| 7 | Нет текста... | 960 |
| 8 | ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በእምድብረ ከተማ ሁለት የልማት መሠረተ ድንጋይ አኖሩ።
ሰኔ ፳፩ ቀን ፳፻፲፰ ዓም
ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤ የቅዱስ ዜና ማርቆስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ሓላፊ በእምድብር ከተማ የወረዳው ቤተ ክህነት ባለ ሁለት ፎቅ ጽ/ቤትና የደብረ ፀሐይ አቡነ ተክለ ሀይማኖት ቤተ ክርስቲያ ባለ አራት ፎቅ ሁለገብ የገበያ ማዕከል የመሠረት ድንጋ አኖሩ።
ብፁዕነታቸው በሥነ-ሥርዓቱ ላይ በሰጡት ቃለ ምዕዳን፤ አካባቢው በርካታ ምሁራንን ያፈራ ጥንታዊ ቢሆንም፣ የወረዳው ቤተክህነት እስካሁን በኪራይ ቤት ውስጥ መቆየቱና ከሌሎች አካባቢዎች ወደኋላ መቅረቱ የሚቆጭ እንደሆነ ገልጸዋል። አያይዘውም «ቤተክርስቲያን መቅደስና መዝሙር ብቻ ሳይሆን ማስተማርና ማስተዳደርም ጭምር ስላለባት፣ እንደማንኛውም ተቋም በዘመናዊ መሣሪያዎችና የተሟላ ጽሕፈት ቤት ሊኖራት ይገባል» ብለዋል።
ይህንን ታላቅ ግንባታ በተሳካ ሁኔታ ለማጠናቀቅ የወረዳ ቤተ ክህነቱ፣ የማኅበረ ትንሣኤ አብያተ ክርስቲያናት ዘቸሃ፣ የአጥቢያ አድባራት ሁሉም የሚጠበቅባቸውን ሓላፊነት እንዲወጡ አሳስበዋል። ብፁዕነታቸው ሲቀጥሉ የወረዳው መንግሥት እስካሁን ላደረገው ትብብር ምስጋና አቅርበው፤ መንግሥት ለሁሉም የሃይማኖት ተቋማት እኩልና ቀልጣፋ አስተዳደራዊ አገልግሎት በመስጠት፣ ከቢሮክራሲና ውጣ ውረድ በጸዳ መልኩ አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግ ተጠይቋል።
በመጨረሻም፣ የደብረ ጸሐይ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ሁለገብ የገበያ ማዕከልን አስመልክተው በሰጡት ቃለ በረከት ቤተክርስቲያን በመለመን ሳይሆን በራሷ ይዞታ ላይ በማምረትና ሕንፃዎችን በመሥራት የገቢ ምንጯን ማሳደግ እንዳለባት ተገልጿል። ከዚህ ከሚገኘው ገቢም ለአገልጋዮች የሚመጥን ደሞዝ ለመክፈል፣ ዘመናዊና የአብነት ትምህርት ቤቶችን ለመገንባት እንዲሁም ለዘላቂ ልማት ማዋል እንደሚገባ ገልጸዋል።
ይህ ባለ 4 ፎቅ ሕንፃ ሲጠናቀቅ ለቤተክርስቲያኗ የገቢ ምንጭ ከመሆኑም በላይ ለከተማዋ ዕድገትና ገጽታ ግንባታ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል። | 836 |
| 9 | Нет текста... | 955 |
| 10 | Нет текста... | 856 |
| 11 | Нет текста... | 710 |
| 12 | የወልቂጤ ቅዱስ ዜና ማርቆስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የሁለተኛውን ዙር የነገረ መለኮት ደቀ መዛሙርት በታላቅ ድምቀት አስመረቀ።
ሰኔ ፳ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም ወልቂጤ
በብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ ሣልሳይ የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የተመሠረተው የወልቂጤ ቅዱስ ዜና ማርቆስ መንፈሳዊ ኮሌጅ፣ ለሦስት ተከታታይ ዓመታት በነገረ መለኮት ትምህርት ዘርፍ ሲያስተምራቸው የነበሩ የሁለተኛ ዙር ደቀ መዛሙርት በዛሬው ዕለት በታላቅ ድምቀት አስመርቋል። የሀገርና የቅድስት ቤተክርስቲያን ተተኪ አገልጋዮችንና ምሁራንን በማፍራት ላይ የሚገኘው የዚህ ኮሌጅ ታሪካዊ የምረቃ ሥነ-ሥርዓት በከፍተኛ መንፈሳዊ ድምቀትና ሥርዓት የተከናወነ ሲሆን፤ በበዓሉ ላይ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ ሣልሳይ (የኮሌጁ መሥራችና የበላይ ኃላፊ ሊቀ ጳጳስ)፣ ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ (የሲዳማ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የታቦር ፍኖተ ጥበብ መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ኃላፊ) እና ብፁዕ አቡነ መቃሪዎስ (የምዕራብ ካናዳ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ) ተገኝተዋል። በተጨማሪም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ከፍተኛ ልዑካን እና የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ አመራር አካላት፣ ጥሪ የተደረገላቸው የመንግስት አካላት በክብር እንግድነት በመገኘት የሥነ-ሥርዓቱ ተካፋይ ሆነዋል።
በዛሬው የምረቃ መርሐ ግብር ላይ መደበኛ የነገረ መለኮት ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ 19 ደቀ መዛሙርት እንዲሁም ለአንድ ወር ተከታታይ የአጭር ጊዜ የአቅም ማጠናከሪያ ሥልጠና ሲከታተሉ የነበሩ 30 ካህናትና አገልጋዮች በብፁዓን አበው እጅ የዲፕሎማና የሰርተፍኬት የምስክር ወረቀት ተቀብለዋል። ይህ የምረቃ በዓል ኮሌጁ በቤተ ክርስቲያን ትምህርት ዘርፍ እያበረከተ ያለውን ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያሳይ ሲሆን፤ ተመራቂዎቹም ላለፉት ሦስት ዓመታት የቀሰሙትን ዕውቀት መሠረት በማድረግ ኦርቶዶክሳዊነትን ለማስፋፋትና ቅድስት ቤተክርስቲያንን በዕውቀት ለማገልገል የሚሰማሩበት ልዩ ምዕራፍ መሆኑ ተገልጿል። ኮሌጁ በቤተ ክርስቲያን ትምህርት ዘርፍ እያበረከተ ያለው ይህ ከፍተኛ አስተዋጽኦ፣ በሀገረ ስብከቱም ሆነ በቤተክርስቲያኗ ውስጥ የሚታየውን የአገልጋይ እጥረት ለመቅረፍ ትልቅ ተስፋ የሰነቀ መሆኑም በዕለቱ ተነግሯል።
በምረቃው ሥነ-ሥርዓት ላይ ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ ሰፋ ያለና ጥልቅ ትምህርተ ወንጌል ሰጥተዋል።
ለአጠቃላዩ ተመራቂዎች መንፈሳዊ መመሪያና አባታዊ መልዕክት ያስተላለፉት ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ ሣልሳይ፤ መነሻቸውን "ለክርስቶስ ወንጌል እንደሚገባ ኑሩ" (ፊል 1፥27) በሚለው የቅዱስ መጽሐፍ ቃል ላይ በማድረግ ይህ ዕለት የትምህርታቸው ማብቂያ ሳይሆን የአገልግሎታቸው ጅማሬ መሆኑን ተመራቂዎቹ አውቀው ሊያስቡበት እንደሚገባ አሳስበዋል። በጉባኤው ውስጥ የተማሩት የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ምዕመናንን የሚጠብቁበት ክንድ በመሆኑ፣ የተቀሰመው ዕውቀት ከአገልግሎት የተለየ እንዳይሆንና በትምህርት ደረጃ ብቻ ሳይቀረጽ በተግባር ላይ ሊውል እንደሚገባም መመሪያ ሰጥተዋል። ተመራቂዎቹ ለምዕመናን ምሳሌ በመሆን መንፈሳዊ አገልግሎታቸውን በሓላፊነት ስሜትና በትጋት ሊወጡ እንደሚገባ የገለጹት ብፁዕነታቸው፣ የክህነት አገልግሎት ልዩ ክብር ያለው ቢሆንም ከሁሉ በላይ የመስዋዕትነትና የኃላፊነት ዋጋ መሆኑን፣ ያላችሁበት ዘመንም በብዙ ፈተናዎች የተከበበ መሆኑን በተለየ ሁኔታ መገንዘብና ማወቅ እንደሚገባ በጥብቅ አሳስበዋል። ታሪካዊው የምረቃ ሥነ-ሥርዓት በብፁዕ አቡነ መቃርዮስ ቃለ ምዕዳንና አባታዊ ቡራኬ ተጠናቋል። | 669 |
| 13 | https://www.youtube.com/live/O2eNtVQmL24?si=1Px_T4KDgsn_wg2S | 681 |
| 14 | https://www.youtube.com/live/O2eNtVQmL24?si=8jYmgQL_W_vH4zar | 762 |
| 15 | Нет текста... | 740 |
| 16 | https://youtu.be/srP92z4nNU0?si=5QUEVIWmhEc-bQb4 | 879 |
| 17 | የብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ አባታዊ መልእክት ለአበሽጌ ወረዳ ካህናትና ምእመናን!
" ለአንድ ሳምንት ምሕላ ያዙ"
➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺
የተከበራችሁ የአበሽጌ ወረዳ ቤተክህነት ጽ/ቤት ሠራተኞች እና የአብያተ ክርስቲያናቱ ካህናት እንዲሁም ምዕመናን የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን:- በያዝነው ወርኃ ክረምት በወረዳው ወቅታዊው ዝናብ በማነሱ ምክንያት የተዘራው የበቆሎ ዘር በታለመው ሁኔታ ባለመሳካቱ መሬቱ እንደገና ተገልብጦ ለሌላ ሰብል እየተዘጋጀ መሆኑ ስንሰማ የሕዝባችን ድካም አሳዝኖናል።
ይሁን እንጂ ተፈጥሮን የሚያዘው የፍጥረቱ ባለቤት ሁሉን ቻይ ልዑለ ባህርይ እግዚአብሔር ስለሆነ ተስፋ ባለመቁረጥ ለበጎ ነው ብሎ የሆነውን በእምነት በመቀበል፤ የቀጣዩን የሕዝባችን ድካም እንዲባርክ፣ ዝናሙንም፣ እንዲሰጥ ሁሉን ለሚችለው አምላክ አሁንም በእምነት ጽናት በጸሎት ማሳሰብ ይገባል።
ጸሎቱም እንዲሰምር ንፁህ ልብ ያስፈልጋልና ንስሐ በመግባት በእግዚአብሔር ፊት በንፁህ ልብ ልንጸልይ ይገባል። ስለሆነም በዚህ መንፈስ ባሳሰብናችሁ መሰረት የአንድ ሳምንት ምህላን ያዙ::
"በተስፋ ደስ ይበላችሁ; በጸሎት ጽኑ..." መልእክተ ጳውሎስ ዘሮሜ ምዕራፍ 12
እግዚአብሔር ሕዝባችንን ይባርክ ጸሎቱንም ይስማ አሜን::
አባ መልከጼዴቅ
የጉራጌ ሀ/ስብከት
ሊቀጳጳስ | 1 274 |
| 18 | Нет текста... | 819 |
| 19 | ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ፣ የቅዱስ ዜና ማርቆስ መንፈሳዊ ኮሌጅ መሥራችና የበላይ ሓላፊ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ሰብሳቢ የአድባራትን የእርሻ ልማት እንቅስቃሴ ጎበኙ። ብፁዕነታቸው በጉብኝታቸው አድባራት እያከናወኑአቸው ያሉ ተስፋ ሰጪ የግብርና ሥራዎች በመመልከት በቀጣይ ሊሠሩ የሚገባቸውን ሥራዎች አቅጣጫ አመላክተዋል።
ዝርዝሩን እንመለስበታለን።
ለፈጣን መረጃ ሳሌም የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሚዲያ። ቤተሰብ ይሁኑ። የማኅበራዊ ሚዲያዎቻችን።
Facebook; https://www.fb.com/GurageDiocese
Telegram; https://t.me/GurageDiocese
Tiktok; tiktok.com/@guragediocese
Instagram; instagram.com/gurage_diocese
YouTube; https://youtube.com/@guragediocese | 878 |
| 20 | https://youtu.be/VTGJIiGbp8I?si=RNDOIzdrSvFGJtNI | 827 |
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
